TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.9K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
27 ሚሊዮን ብር የሚገመት አደንዛዥ ዕፅ ወደ አገር ውስጥ ሊገባ ሲል ተያዘ!

የገቢዎች ሚኒስቴርና የጉምሩክ ኮሚሽን በቦሌ አለም አቀፍ አየርመንገድ በኩል ወደ አገር ሊገባ የነበረ 27 ሚሊዮን ብር የሚገመት 10.8 ኪ.ግ የሚመዝን አደንዛዥ ዕፅ በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታውቋል።

የጉምሩክ ተቆጣጣሪዎች ባደረጉት ክትትል በቁጥጥር ስር ያዋሉት #ሄሮይን እና #ኮኬን የተባሉ አደንዛዥ እፆችን ነው፡፡ አደንዛዥ እፆቹን አንድ ናይጄሪያዊ ዜጋ በያዘው ቀላል ሻንጣ ውስጥ ደብቆ ለማለፍ ሲሞክር በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተደረገበት እንደሚገኝ የቦሌ ኤርፖርት ጉምሩክ ቅ/ፅ/ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ ተገኔ ደረሰ ለኢቢሲ ገልፀዋል፡፡

Via #EBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከእስር ያመለጠው ግለሰብ ከ28 ዓመታት በኃላ ተላልፎ ተሰጠ።

#ፓናማ ከእስር ካመለጠ 28 ዓመታት ያለፈውን #የእስራኤል እስረኛ አሳልፋ ሰጥታለች።

ፓናማ የእስራኤል እስረኛ የሆነውን ዮሲ ቤን-ኤሪን አሳልፋ መስጠቷን KAN ሪፖርት አድርጓል።

ቤን-ኤሪ የተባለው ግለሰብ 5 ኪሎግራም የሚጠጋ #ሄሮይን ከኔዘርላንድ ወደ እስራኤል በማስገባቱ ጥፋተኛ ተብሎ 12 ዓመት እንዲታሰር ተፈርዶበት ነበር።

ይህ ግለሰብ ከ28 ዓመት በፊት ነበር ከእስር ያመለጠው ፤ እንሆ ከ28 ዓመት በኃላ ፓናማ እስረኛውን አሳልፋ ለእስራኤል ሰጥታለች።

በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ጉዳዩን የሰሙ ሰዎች ማንም ግለሰብ ጥፋተኛ ከሆነ የፈጀውን ጊዜ ይፈጃል እንጂ ከህግ እንደማያመልጥ ማሳያነው ሲሉ ገልፀውታል።

@tikvahethiopia