ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ለሶስት ሰዎች የክብር ዶክትሬት ሰጠ!
ዶክተር ሰገነት ቀለሙ፣ ፕሮፌሰር ሃንስ ማትሰን እና ማርክ ጌልፋንድ ናቸው በባህርዳር የኒቨርሲቲ በዛሬው ዕለት የክብር ዶክትሬታቸውን አግኝተዋል፡፡
ዶክተር ሰገነት ቀለሙ በልዩ መሪነትና ተመራማሪነት ዘርፍ የተመረጡ ሲሆን ናይሮቢ የሚገኘው ዓለማቀፉ የነፍሳት ግብረ አካል እና ሥነ-ምኅዳር የመጀመሪያዋ ሴት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ናቸው፡፡ ከ25 ዓመታት በላይ በሰሜን አሜሪካና በላቲን አሜሪካ በርካታ ምርምሮችን ሠርተዋል፡፡ በዓለማቀፍ ደረጃ ዕፅዋትን በሚያጠፉ በሽታዎች ላይ ሳይንሳዊ ምርምር በማድረግ ቀዳሚ ሴት ተመራማሪ በመሆናቸውም በርካታ ሽልማቶችን አሸንፈዋል፡፡
#ስዊድናዊው ፕሮፌሰር #ሃንስ_ማትሰን በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲና በምሥራቅ አፍሪካ የመሬት አስተዳደር ዘርፍ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተዋል፡፡
አሜሪካዊው ማርክ ጌልፋንድ በበኩላቸው በኢትዮጵያና በሌሎች ታዳጊ ሀገራት የሳይንስ፣ የቴክኖሎጂ፣ የምሕንድስና እና የሒሳብ ትምህርቶች ልዩ ትኩረት እንዲሰጣቸው ድጋፍ ያደረጉ ምሁር ናቸው፡፡ በባሕር ዳር፣ በጎንደር፣ በአዲስ አበባና በሌሎችም 12 ዩኒቨርሲቲዎችና አካባቢዎች የስቲም ማዕከላት እንዲከፈቱ ድጋፍ አድርገዋል፡፡
Via #fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዶክተር ሰገነት ቀለሙ፣ ፕሮፌሰር ሃንስ ማትሰን እና ማርክ ጌልፋንድ ናቸው በባህርዳር የኒቨርሲቲ በዛሬው ዕለት የክብር ዶክትሬታቸውን አግኝተዋል፡፡
ዶክተር ሰገነት ቀለሙ በልዩ መሪነትና ተመራማሪነት ዘርፍ የተመረጡ ሲሆን ናይሮቢ የሚገኘው ዓለማቀፉ የነፍሳት ግብረ አካል እና ሥነ-ምኅዳር የመጀመሪያዋ ሴት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ናቸው፡፡ ከ25 ዓመታት በላይ በሰሜን አሜሪካና በላቲን አሜሪካ በርካታ ምርምሮችን ሠርተዋል፡፡ በዓለማቀፍ ደረጃ ዕፅዋትን በሚያጠፉ በሽታዎች ላይ ሳይንሳዊ ምርምር በማድረግ ቀዳሚ ሴት ተመራማሪ በመሆናቸውም በርካታ ሽልማቶችን አሸንፈዋል፡፡
#ስዊድናዊው ፕሮፌሰር #ሃንስ_ማትሰን በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲና በምሥራቅ አፍሪካ የመሬት አስተዳደር ዘርፍ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተዋል፡፡
አሜሪካዊው ማርክ ጌልፋንድ በበኩላቸው በኢትዮጵያና በሌሎች ታዳጊ ሀገራት የሳይንስ፣ የቴክኖሎጂ፣ የምሕንድስና እና የሒሳብ ትምህርቶች ልዩ ትኩረት እንዲሰጣቸው ድጋፍ ያደረጉ ምሁር ናቸው፡፡ በባሕር ዳር፣ በጎንደር፣ በአዲስ አበባና በሌሎችም 12 ዩኒቨርሲቲዎችና አካባቢዎች የስቲም ማዕከላት እንዲከፈቱ ድጋፍ አድርገዋል፡፡
Via #fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia