TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ይፈለጋል‼️

የአሜሪካ መንግሥት የቀድሞ የአል ቃኢዳ መሪ የኦሳማ ቢላደን ልጅ #ሀምዛ_ቢላደን ያለበትን ለሚጠቁማት 1 ሚሊየን ዶላር ሽልማት አዘጋጀች፡፡

ቢቢሲ እንደዘገበው ሀምዛ ቢን ላደን #የአል_ቃኢዳ ታጣቂ ቡድን መሪ ለመሆን በመዘጋጀት ላይ እንደሆነም ተነግሯል።

የኦሳማ ቢን ላደን ልጅ በአሁኑ ሰዓት በአፍጋኒስታንና በፓኪስታን ድንበር አቅራቢያ ሊኖር ይችላል የሚል ግምት መኖሩን የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል።

አሜሪካ እድሜው 30 ዓመት እንደሆነ የሚገመተውን ሀምዛ ቢን ላደን ከሁለት ዓመት በፊት በዓለም አቀፋዊ አሸባሪነት ፈርጃዋለች።

ከጥቂት ዓመታት በፊት በድምፅና በምስል በለቀቀው መልዕክት አሜሪካና ምዕራባዊ አጋሮቿ ላይ ጥቃት በመፈጸም የአባቱን ሞት እንዲበቀሉ ለተካታዮቹ ጥሪ አስተላልፏል።

በፈረንጆቹ 2011 የአሜሪካ ልዩ ኃይሎች ፓኪስታን አቦታባድ በሚገኘው የራሱ ግቢ ኦሳማ ቢን ላደንን መግደላቸው ይታወሳል።

ምንጭ፦ BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopua
1,000,000$ ሽልማት‼️

የቀድሞውን የአል ቃኢዳ መሪ የኦሳማ ቢላደን ልጅ #ሀምዛ_ቢላደን ያለበትን ለሚጠቁም 1 ሚሊየን ዶላር ሽልማት አሜሪካ አዘጋጅታለች። የኦሳማ ቢን ላደን ልጅ በአሁኑ ሰዓት #በአፍጋኒስታንና #በፓኪስታን ድንበር አቅራቢያ ሊኖር ይችላል የሚል ግምት መኖሩን የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
1
#BREAKING የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ የ9/11 ጥቃት /ማስተር ማይንድ/ እና የአልቃይዳ መሪ የነበረው ኦሳማ ቢላደን ልጅ #ሀምዛ_ቢላደን መገደሉን አረጋገጡ።
@tsegabwolde @tikvahethiopia