TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ዕለታዊ : የዶላር ምንዛሬ ዋጋ ላይ ጭማሪ ታይቷል።

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአሜሪካ ዶላር ዋጋ ጭማሪ አሳይቷል። የሌሎችም ምንዛሬ ዋጋ ላይ መጠነኛ ጨማሪ ታይቷል።

(ንግድ ባንክ)

💵 አንድ የአሜሪካ ዶላር መግዣ 104.0934 ፤ መሸጫ 115.3244

💷 ስተርሊግ መግዣው 128.1856፤ መሸጫው 142.6853

💶 ዩሮ መግዣ 114.4293 ፤ መሸጫ 126. 7877

🇰🇼 የኩዌት ዲናር መግዣው 324.8780 መግዣ ፤ መሸጫው 361.6181

🇦🇪 የUAE ድርሃ መግዣ 28.3398 ፤ መሸጫው 31.4004

በግል ባንኮች ደግሞ የአንዱ የአሜሪካ ዶላር መግዣ ከ103 ብር አንስቶ እስከ 119 ብር ድረስ መሸጫ ተቆርጦለታል።

(ዕለታዊ የባንክ ምዛሬ ከላይ ተያይዟል)

(ነሐሴ 11/2016 ዓ/ም

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ጉምሩክ ➡️ “ ከፍተኛ የወደብ ኪራይ የኮንቴነር ዲመሬጅ በየቀኑ እየጨመረብን ነው ” - አስመጪዎች ➡️ “ ከዚህ ሳምንት አያልፍም ” - ጉምሩክ ኮሚሽን አስመጪዎች ፣ ተግባራዊ የተደረገውን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ተከትሎ የጉምሩክ ኮሚሽን አዋጅን የሚተካ ' አዲስ መመሪያ ' በማውረድ እስከዛሬ ሲከፍሉት ከነበረው ቀረጥ ከእጥፍ በላይ ካልከፈሉ እቃቸውን መውሰድ እንዳይችሉ እያደረጋቸው መሆኑን ለቲክቫህ…
#Update

“ ሞጆ ቅርንጫፍ እየተጉላላን ነው። ትላንት የተላከውን ደብዳቤ ስራ አስኪያጅ ‘አልመራበትም’ ተብሎ ” - አስመጪዎች

“ ደብዳቤው ትላንትና ከመሸ ነው እኛ ጋ የደረሰው ከዋና መስሪያ ቤት፡፡ ተመርቶ ለሚመለከተው ክፍል ሰጥጠናል ” - ሥራ አስኪያጅ ክፍሉ

አስመጪዎች የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ በጉምሩክ እያጋጠማቸው ስላለው ሁኔታ ፤ ክፈሉ ስለተባሉትም ከፍተኛ ቀረጥ በተመለከተ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቤት ማለታቸው ይታወሳል፡፡

በወቅቱ ምላሽ የጠየቅነው የኮሚሽኑ የኮሚዩኒኬሽን ክፍል፣ ኮሚሽኑ አስመጪዎቹ የሚያነሱትን ጉዳይ እንደተረዳና በሰርኩላሩ ዙሪያም ውይይት እንደሚያደርግ አስረድቶ ነበር፡፡

ይህ በእንዲህ እያለ አስመጪዎቹ፣ ኮሚሽኑ ውይይት ማድረጉ መልካም ሆኖ እያለ ውሳኔው በዘገዬ ቁጥር ክፍያ እየጨመረባቸው በመሆኑ አፋጣኝ ውሳኔ እንዲሰጥ በድጋሚ ማሳሰባቸው ይታወቃል።

ለዚሁ ቅሬታ ምላሽ የጠየቅነው የኮሚሽኑ ኮሚዩኒኬሽን ክፍልም፣ በጉዳዩ ውይይት እየተደረገ መሆኑን ግልጾ፣ “ ከዚህ ሳምንት አያልፍም ” የሚል ምላሽ ሰጥቶ ነበር፡፡

ጉዳዩ ከምን ደረሰ? አስመጪዎችስ ምን አሉ ?

አስመጪዎችን ቅር ያሰኘው ሰርኩላር ላይ ኮሚሽኑ ማስተካከያ እንዳደረገበትና፣ በማስተካከያው መሠረት ደንበኞች እንዲስተናገዱ ማዘዙን ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው ማስተካከያ የተደረገበት ሰርኩላር ያስረዳል፡፡

ማስተካከያውን ተከትሎም አስመጪዎች ዛሬ (ቅዳሜ ነሐሴ 11 ቀን 2016 ዓ/ም) ወደ ጉምሩክ ኮሚሽን ሞጆ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት እቃቸውን ለማውጣት እንደሄዱ፣ ነገር ግን የሚያስተናግዳቸው ባለመኖሩ እየተጉላሉ መሆኑን ዛሬም ለቲክቫህ አቤት ብለዋል፡፡

“ ሞጆ ቅርንጫፍ እየተጉላላን ነው። ትላንት የተላከውን ደብዳቤ ስራ አስኪያጅ ‘አልመራበትም’ ብሎ ” ነው ያሉት፡፡

“ ትላንት የእቃ መልቀቂያ ደብዳቤ ወጥቶልን ነበር፡፡ ሞጆ ቅርንጫፍ ግን ጭራሽ እያስተናገዱን አይደለም፡፡ እንዳለ ሠራተኞች ቁጭ ብለዋል፡፡ የሚጭን መኪና ቆሟል፡፡ ከትላንትና ከሰዓት ጅምሮ ግን ምንም ሥራ እየተሰራ አይደለም ” ሲሉ አማረዋል፡፡

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ አስመጪዎቹ እየተጉላላን ነው የሚል ቅሬታ አላቸው ለምን አታስተናግዷቸውም ? ሲል የኮሚሽኑን ሞጆ ቅርንጫፍ የደንበኞች አገልግሎት ክፍልን ጠይቋል፡፡

የደንበኞች አገልግሎት ክፍል በሰጠው ምላሽ፣ “ ጉዳዩን እናጣራው እኛ ሙያተኞች ነን፡፡ አመራሮች ጋ ጉዳዩን እናጣራ፡፡ ወደ አመራር ሂደው ጉዳያቸው እንዲፈታ ነው የምናደርገው እንጅ ዝም ብለን የምናጉላላበት ጉዳይ የለም ” ብሏል፡፡

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በተጨማሪም፣ አስመጪዎች “ ሥራ አስኪያጅ ደብዳቤ አልተመራም ” በሚል እያጉላላቸው መሆኑን ቅሬታ አቅርበዋል፤ ደብዳቤው አልደረሳችሁም ? ሲል የኮሚሽኑም ሞጆ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ሥራ አስኪያጅ ክፍል ጠይቋል፡፡

የሥራ አስኪያጅ ክፍሉ ፀሐፊ አመራሮቹ ስብሰባ እንደገቡ ገልጸው፣ “ ደብዳቤው ትላንትና ከመሸ ነው እኛ ጋ የደረሰው ከዋና መስሪያ ቤት፡፡ እሱን ተመርቶ ለሚመለከተው ክፍል ሰጥጠናል ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

(ኮሚሽኑ ማስተካከያ ያደረገበት ደብዳቤ ከላይ የተያያዘ ሲሆን፤ ጉዳዩ ከምን እንደሚደርስ የምንከታተለው ይሆናል)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Gamo : ሰሞኑን ለሶስት ተከታታይ ቀናት በጣለ ከባድ ዝናብ በተፈጠረ የመሬት መንሸራተት በጋሞ ዞን በገረሴ ዙሪያ ወረዳ ካምአለ ባርኤ ኦሮ ቀበሌ የ4 ሰዎች ሕይወት አልፏል። መረጃው  የገረሴ ዙሪያ ወረዳ ኮሙዩኒኬሽን ጉ/ጽ/ቤት ነው። @tikvahethiopia
#Update

" አራቱ ሟቾች የአንድ ቤተሰብ አባል ናቸው " - በጋሞ ዞን የገረሴ ወረዳ አስተዳዳሪ

በጋሞ ዞን፣ ገረሴ ዙሪያ ወረዳ ካማአለ ባርኤ ኦሮ ቀበሌ በደረሰ የናዳ አደጋ የ4 ሰዎች ህይወት ማለፉ ይወቃል።

ከዚህ ባለፈ ደግሞ ከሰላሳ ሰባት በላይ የቤት እንስሳት ላይ ጉዳት ደርሷል ፤ 15 ቤቶችም መፍረሳቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተረድቷል።

የገረሴ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ካሳሁን ካማ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፥ " የሟቾችን ቀብር ከአካባቢዉ ማህበረሰብ ጋር በመሆን በክብር አስፈጽመናል " ብለዋል።

በአካባቢዉ ችግር ይከሰታል የሚል ቅድመ ትንበያም ይሁን ግምት ፈጽሞ እንዳልነበር ይልቁኑ በቀርከሀ የተሞላ ደን እያለ አደጋዉ መከሰቱ ሁኔታዉን አስደንጋጭ አድርጎታል ሲሉ ገልጸዋል።

አራቱ ሟቾች የአንድ ቤተሰብ አባል መሆናቸዉን የገለጹት አስተዳዳሪው በአንድ ቤት ዉስጥ ከነበሩት ሰባት ሰዎች ውስጥ በጓዳ የነበሩት አራቱ ሞተው ሶስቱ ከጓዳ ወጭ የነበሩት መትረፋቸውን ነግረውናል።

የሟቾች ስርዓተ ቀብር ከተፈፀመ በኃላ ወደ ቀጣይ ተግባር ተገብቷል ሲሉም ገልጸዋል።

አሁን ላይ የዝናቡ መጠን ከፍ እንደሚል መረጃ ማግኘታቸውን ተከትሎ ሌላ አደጋ እንዳይከሰት እንቅስቃሴ መጀመሩንና የአካባቢውን ሰው በማሸሽ በአጎራባች ቀበሌዎች ውስጥ ባሉ ትምህርት ቤቶች የጤና ኬላዎችና የእምነት ቦታዎች ማሳረፍ መጀመሩን አመልክተዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray " ሁሉንም የፓለቲካ ሃይሎች ያቀፈ መንግስት በአስቸኳይ መመስረት ያስፈጋል " - ሦስት የፓለቲካ ፓርቲዎች በትግራይ የሚንቀሳቀሱት ባይቶና፣ ሳወት፣ ናፅነት የፓለቲካ ፓርቲዎች በጋራ በሰጡት መግለጫ ፤ " ሳምንቱን በስርዓቱ ባለቤቶች መካከል በመካሄድ ያለው ህገ-ወጥ እንቃስቃሴና ፍጥጫ ተው መባል ይገባዋል " ብለዋል። በህወሓት አመራሮች የተፈጠረው ፍጥጫ ተከትሎ በህዝቡ የሚታየው መረበሽ…
#TPLF

" በህወሓት (ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ) ስም ማንኛውም ፓለቲካዊ እንቅስቃሴ ማድረግ አይቻልም " - እነ ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመሩት ጉባኤ ውሳኔ

በአመራሮች መካከል ክፍፍል የፈጠረው የህወሓት ጉባኤ ባወጣው መግለጫ ፥ " የተለየ ሃሳብ አለኝ " የሚል በጉባኤ ያልተገኘ አካል ወደ ጉባኤው ቀርቦ ሃሳቡ በነፃነት እንዲገልፅ ፣ በዴሞክራሲያዊ ምጉት ለሚተላለፉት ውሳኔዎች ተገዢ እንዲሆን ነሃሴ 8/2016 ዓ.ም ጥሪ ማቅረቡ አስታውሰዋል።

" የድርጅቱ ጉባኤ ከተሰየመበትና ከተጀመረበት ነሀሴ 7/2016 ዓ.ም ቀን በኋላ ተራ አባል እንጂ የማእከላዊ ኮሚቴ የሚባል ሃላፊነት የላቸውም " ብሏል የእነ አቶ ጌታቸው ረዳ አቋም በመደገፍ ጉባኤውን ላወገዙ የቀድሞ ጉምቱ አመራሮቹ።

" ስለሆነም ከህግና ተቋማዊ የደርጅታችን አሰራር ውጪ በአሁኑ ወቅት በህወሓት ስም ማንኛውም የፓለቲካ ስራ ለመፈፀም ሃላፊነት ያለው የማእከላዊ ኮሚቴና የማዕከላዊ የቁጥጥር ኮሚሽን ሆነ ሌላ አካል የለም " በማለት አብራርቷል።

" ስለዚህ ህዝባችንና መላ አባላችን ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት የጉባኤውን ውሳኔ በመረዳት እንዲተገብሩና እንዲተገበር  እንዲሰሩ ጥሪ እናቀርባለን " በማለት አክለዋል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ፤ ቀደም ብሎ ለዚህ ጉባኤና በጉባኤው ለሚተላለፉ ማናቸውም ውሳኔዎች ምንም እውቅና እንደማይሰጥ ማሳወቁ ይታወሳል።

በምርጫ ቦርድ ውሳኔ መሰረት አሰራሩን ያልተከተለ ጉባኤ null and void / ምንም እውቅናና ህጋዊ መሰረት የሌለው ነው።

በሌላ በኩል ፥ በአሁን ሰዓት የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት እና የህወሓት ም/ሊቀመንበር አቶ ጌታቸው ረዳ መግለጫ እየሰጡ ናቸው፤ ያነሷቸውን ሀሳቦች እናደርሳችኋለን።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia            
TIKVAH-ETHIOPIA
#TPLF " በህወሓት (ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ) ስም ማንኛውም ፓለቲካዊ እንቅስቃሴ ማድረግ አይቻልም " - እነ ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመሩት ጉባኤ ውሳኔ በአመራሮች መካከል ክፍፍል የፈጠረው የህወሓት ጉባኤ ባወጣው መግለጫ ፥ " የተለየ ሃሳብ አለኝ " የሚል በጉባኤ ያልተገኘ አካል ወደ ጉባኤው ቀርቦ ሃሳቡ በነፃነት እንዲገልፅ ፣ በዴሞክራሲያዊ ምጉት ለሚተላለፉት ውሳኔዎች ተገዢ እንዲሆን…
#Tigray🚨

" የጊዚያዊ አስተዳደሩን ስልጣን ለመንጠቅ የመሞከር እንቅስቃሴ ያደርጋሉ ብለን እንጠብቃለን " - አቶ ጌታቸው ረዳ

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንትና የህወሓት ምክትል ሊቀ-መንበር ጌታቸው ረዳ በክልሉ ወቅታዊ ሁኔታ ዛሬ ነሀሴ 11/2016 ዓ.ም መገለጫ ሰጥተዋል።

በጋዜጣዊ መግለጫቸው ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች ምንድናቸው ?

- የህወሓትና ሌሎች ህገ-ደንቦች ያላሟለና ተጨባጭ የትግራይ ሁኔታ ግምት ውስጥ ያላስገባ ጉባኤ በመካሄድ ላይ ነው።

- የጉባኤው መነሻ የጥቂት የማእከላዊና ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ፍላጎት ነው።

- ትግራይ ወደ ከባድ አደጋ እንድትወድቅ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደረገ ከፍተኛ አመራር ተመልሶ ስልጣን ላይ ለመውጣት ያደረገው እንቅስቃሴ ነው።

- ጉባኤው መላው የህወሓት አባላት የሚወክል አይደለም።

- ውጤት እንደሌለው ስለምናውቅ ወደ አላስፈላጊ መሳሳብ ላለመግባት በማሰብ ጉባኤ እንዳያካሂዱ አልከለከልንም።

- ማንነቱ ያልታወቀና ደጀን ይሆነናል የሚሉት ሃይል ተማምነው እያካሄዱት ያለው ጉባኤ ወደ አልተፈለገ ችግር ሊያስገባን የሚችል ነው።

- ድርጊታቸው የመንግስት ስራ መስራት የሚገባቸው አካላት ከስራ ውጪ የሚያደርግ ነው።

- የጊዚያው አስተዳደሩ ስልጣን ለመንጠቅ የመሞከር እንቅስቃሴ ያደርጋሉ ብለን እንጠብቃለን።

- የትግራይ የፀጥታ ሃይሎች የስልጣን ፈላጊ አካላት መሳሪያ መሆን የለባቸውም።

- ህወሓት መዳን አለባት የምትድነው ግን በያዙት መንገድ አይደለም።

ትላንት የህወሓት ጉባኤ ቃለ-አቀባይ አቶ ኣማኑኤል ኣሰፋ መግለጫ ሰጥተው የነበረ ሲሆን ፤ ጉባኤው እንዲራዘም የሚጠይቅ ጥያቄ ቢነሳም በጉባኤተኞቹ ወድቅ መደረጉን ተናግረዋል።

ድርጅቱ " አጋጠሞኛል " የሚለው የስትራቴጂክ አመራር ውድቀት ለመፍታት አልሞ ጉባኤውን በማካሄድ ላይ እንደሚገኝ ነው " ቃለ-አቀባዩ ጨምረው የገለጹት።

ፎቶ፦ #TigraiTelevision

#TikvahEthiopiaMekelle
@tikvahethiopia
We are looking for HER! Women have an incredible potential to lead and drive change. If you embody these qualities, and want to join an entrepreneurship program, we want to hear from you. Join us and be part of the 7th cohort of the talent investor program.

Apply today! : https://bit.ly/3A8rxtV

Join our telegram channel for more information: @Jasiri4africa
#Safaricom

በ5 ብር ከ M-PESA 150 ሜ.ባ. ስንገዛ፤ በ100 ሜ.ባ. ጉርሻ ፏ እንላለን !
በ12 ብር ከ M-PESA 400 ሜ.ባ. ስንገዛ ደግሞ 200 ሜ.ባ. ጉርሻ የራሳችን ነው !
በ25 ብር ከ M-PESA 1 ጂ.ቢ. ስንገዛ፤ 500 ሜ.ባ. ጉርሻ ይለቀቅብናል!
በሽ በሽ በM-PESA !

የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያን በዚህ ሊንክ እናውርድ ፡ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

የቴሌግራም ቻናላችንን እዚህ እንቀላቀል 👉https://t.iss.one/Safaricom_Ethiopia_PLC

ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ  በቴሌግራም   ቻናላችን https://t.iss.one/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!
🔈#የባለሙያዎቹድምጽ

“ የክረምት ስልጠና ሁሌም እኛን ያገለለ በመሆኑ ከፍተኛ ቅሬታ ፈጥሮብናል ” - የሳይኮሎጅና የልዩ ፍላጎት ባለሙያዎች

በተያዘው ክረምት ለመምህራን የክረምት ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል፡፡

የትምህርት ቤት ሳይኮሎጅስቶች እና የልዩ ፍላጎት ባለሙያዎች በዬጊዜው ከእንዲህ አይነት ስልጠና መገለላቸው ከፍተኛ ቅሬታ እንዳሳደረባቸው በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ቅሬታ አቅርበዋል።

ይህንን ስልጠና የሚሰጡ የዩኒቨርሲቲ መምህራንን በበኩላቸው፣ ይሄው ቅሬታ በስፋት እየተነሳ መሆኑን ገልጸዋል።

“ የአቅም ግንባታ ተብሎ በክረምት የሚሰጠው ስልጠና በተለመደው መልኩ ነው የሆነው፡፡ ማለት የሚሰጠው ለሱፐርናይዘሮች፣ ለዕርሳነ መምህራንና ለመምህራን ብቻ ነው ” የሚል ቃል ሰጥተዋል።

“ትምህርት ቤት ውስጥ ያለው Stakeholder የትምህርት ቤት Guidanace and counciling Professors, Psychologists, Special need ባሙያዎችን አላሳተፈም” ብለዋል።

አንድ የዩኒቨርሲቲ መምህር በበኩላቸው፣ “ከዚህ በፊት ያስተማርናቸው ባለሙያዎች 'ድምጽ ሁኑን እኛስ ሰዎች አይደለንምን? ስልጠናው እኛን ያገለለ ነው' የሚል ጥያቄ አላቸው እኛም ጥያቄ ፈጥሮብናል" ሲሉ ለቲክቫህ ተናግረዋል።

"በደርግ፣ በኢህአዴግ፣ በብልጽግና ጊዜም እነዚህ ባለሙያዎች የትምህርቱ አጋዥ እንዳይሆኑ ለምን እንደተፈለገ አልገባንም” ነው ያሉት።

“ግን ትምህርት ቤት ለስሙም ቢሆን አለ ‘Guidance and counciling officer’ ተብሎ፡፡ ይህም የመማር ማስተማሩን ሂደት ማገዝ በሚገባው መልኩ እንዲታገዝ ይገባል" ብለዋል።

"ክረምት ፕሮግራም ት/ቤት ላይ ሚሰሩ ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠናው የሚያስፈልጋቸው ሆኖ እያለ እንዳይሳተፉ ማድረጋቸው ከፍተኛ ቅሬታ ፈጥሮባቸዋል፡፡ እኛም እንደባለሙያ ቅሬታ ፈጥሮብናል” ሲሉ አክለዋል።

“እኔ አሁን እያሰለጠንኩ ነው፡፡ ማተሪያሉን ስናይ የሳይኮሎጅ ነው፡፡ ስናወያያቸው ለውይይት የሚቀርበው ‘የእነዚህ ባለሙያዎች አክቲቨሊ ትምህርት ቤቶቻችን ላይ አለመሳተፋቸው በመማር ማስተማር ላይ ክፍተት ፈጥሯል’” የሚል ቅሬታ እንደሚያቀርቡ ገልጸዋል።

ቅሬታ አቅራቢዎቹ፣ “ለወደፊት ምን ታስቧል? የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ለምንድን ነው የማይዘጋጅልን?” ሲሉ ጠይቀዋል፡፡

ከትምህርት ሚኒስቴር ስለጉዳዩ ምላሽ የጠየቅናቸው አንድ  አካል እሳቸው የሚሰሩት ዩኒቨርሲቲዎችን የተመለከተውን እንደሆነ፣ አሁን የቀረበው ቅሬታ ግን የሚመለከተው ሌሎችን እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

ሆኖም ወደ ሌሎች አካላት ቲክቫህ ያደረገው ሙከራ ለጊዜው ያልተሳካ ሲሆን፣ ጉዳዩ እስከመጨረሻ በመከታተል የትምህርት ሚኒስቴርን ምላሽ በቀጣይ የምናቀርብ ይሆናል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM