የኢትዮ. አየር መንገድ ከግጭት ተረፈ⬇️
ዘ ኢስት አፍሪካን እንደዘገበው ባለፈው #ረቡዕ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነ ኢት 858፣ ቦይንግ 737-800 ከጣሊያኑ የሌዢር ኤርላይን ኒዮስ ቦይንግ 767-306 R የበረራ ቁጥር NOS 252 ጋር በኬንያ ሰማይ ላይ #ለመጋጨት ሲቃረብ #በአንድ ደቂቃ ልዩነት ተርፏል።
አደጋ ተፈጥሮ ቢሆን ኖሮ በአለም አሰቃቂው የአውሮፕላን አደጋ ተብሎ ይመዘገብ እንደነበር ጋዜጣው ዘግቧል። ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ ከተማ ተነስቶ ወደ አዲስ አበባ በ37 ሺ ጫማ ከፍታ ላይ በመብረር ላይ የነበረ ሲሆን፣ በተመሳሳይ ቀን ምሽት 12 ሰዓት ላይ የጣሊያን አውሮፕላን ከቪሮና ተነስቶ ወደ ዛንዚባር በማምራት ላይ ነበር። እኩለ ሌሊት ላይ ሁለቱም አውሮፕላኖች ወደ ኬንያ አየር ክልል የገቡ ሲሆን፣ ሁለቱም ለግጭት በሚያደርሳቸው ሁኔታ ፊት ለፊት እየተጓዙ እንደነበር ጋዜጣው ዘግቧል።
የግጭት መቆጣጠሪያ መሳሪያው ለኢትዮጵያ አየር መንገድ የማስጠንቀቂያ መልዕክት እንዳስተላለፈ ፣ ፓይለቱ በአንድ ደቂቃ ውስጥ ወደ 38 ሺ ጫማ ከፍ በማድረግ እና ለ5 ደቂቃ በዚሁ ከፍታ ላይ በመቆየት አደጋ እንዳይፈጠር ለማድረግ ችሎአል። የኬንያ አየር ተቆጣጣሪዎች የኢትዮጵያን የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ተጠያቂ አድርገዋል።
የኢትዮጵያ የአየር ታረፊክ ተቆጣጣሪዎች
እንደገለጹት የጣሊያን አየር መንገድ አስቀድሞ በምን ያክል ከፍታ እንደሚበር ሲገልጽ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግን ይህን ባለማድረጉ አደጋው ሊደርስ እንደነበር ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች አደጋው ከመድረሱ አራት ቀናት በፊት የስራ ማቆም አድማ አድርገው ነበር።
ይህንን ተከትሎ የኬንያ አየር መንገድ ከ አዲስ አበባ የሚነሱና ወደ አዲስ አበባ የሚደረጉ በረራዎች ደህንነታቸው አስተማማኝ አለመሆኑን አስቀድሞ #ማስጠንቀቂያ ልኮ እንደነበር ጋዜጣው አክሎ ዘግቧል።
የኢትዮጵያ ሲቪል አቬሽን ባለስልጣን በኬንያ በኩል የቀረበውን ክስ ውድቅ አድርጎታል። የኬንያ አየር ተቆጣጣሪ ያወጣው መግለጫ ሃሰትና መሰረተ ቢስ ነው ያለው የሲቪል አቬሽን ባለስልጣን፣ እንዲህ አይነት አደጋ ይከሰታል የሚል መረጃ ለኢትዮጵያአየር ተቆጣጣሪዎች አለመነገሩን ገልጿል።
📌የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎችን ለአድማ አነሳስተዋል የተባሉ 9 አመራሮችና ሰራተኞች #መታሰራቸው ይታወቃል።
©ESAT
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዘ ኢስት አፍሪካን እንደዘገበው ባለፈው #ረቡዕ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነ ኢት 858፣ ቦይንግ 737-800 ከጣሊያኑ የሌዢር ኤርላይን ኒዮስ ቦይንግ 767-306 R የበረራ ቁጥር NOS 252 ጋር በኬንያ ሰማይ ላይ #ለመጋጨት ሲቃረብ #በአንድ ደቂቃ ልዩነት ተርፏል።
አደጋ ተፈጥሮ ቢሆን ኖሮ በአለም አሰቃቂው የአውሮፕላን አደጋ ተብሎ ይመዘገብ እንደነበር ጋዜጣው ዘግቧል። ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ ከተማ ተነስቶ ወደ አዲስ አበባ በ37 ሺ ጫማ ከፍታ ላይ በመብረር ላይ የነበረ ሲሆን፣ በተመሳሳይ ቀን ምሽት 12 ሰዓት ላይ የጣሊያን አውሮፕላን ከቪሮና ተነስቶ ወደ ዛንዚባር በማምራት ላይ ነበር። እኩለ ሌሊት ላይ ሁለቱም አውሮፕላኖች ወደ ኬንያ አየር ክልል የገቡ ሲሆን፣ ሁለቱም ለግጭት በሚያደርሳቸው ሁኔታ ፊት ለፊት እየተጓዙ እንደነበር ጋዜጣው ዘግቧል።
የግጭት መቆጣጠሪያ መሳሪያው ለኢትዮጵያ አየር መንገድ የማስጠንቀቂያ መልዕክት እንዳስተላለፈ ፣ ፓይለቱ በአንድ ደቂቃ ውስጥ ወደ 38 ሺ ጫማ ከፍ በማድረግ እና ለ5 ደቂቃ በዚሁ ከፍታ ላይ በመቆየት አደጋ እንዳይፈጠር ለማድረግ ችሎአል። የኬንያ አየር ተቆጣጣሪዎች የኢትዮጵያን የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ተጠያቂ አድርገዋል።
የኢትዮጵያ የአየር ታረፊክ ተቆጣጣሪዎች
እንደገለጹት የጣሊያን አየር መንገድ አስቀድሞ በምን ያክል ከፍታ እንደሚበር ሲገልጽ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግን ይህን ባለማድረጉ አደጋው ሊደርስ እንደነበር ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች አደጋው ከመድረሱ አራት ቀናት በፊት የስራ ማቆም አድማ አድርገው ነበር።
ይህንን ተከትሎ የኬንያ አየር መንገድ ከ አዲስ አበባ የሚነሱና ወደ አዲስ አበባ የሚደረጉ በረራዎች ደህንነታቸው አስተማማኝ አለመሆኑን አስቀድሞ #ማስጠንቀቂያ ልኮ እንደነበር ጋዜጣው አክሎ ዘግቧል።
የኢትዮጵያ ሲቪል አቬሽን ባለስልጣን በኬንያ በኩል የቀረበውን ክስ ውድቅ አድርጎታል። የኬንያ አየር ተቆጣጣሪ ያወጣው መግለጫ ሃሰትና መሰረተ ቢስ ነው ያለው የሲቪል አቬሽን ባለስልጣን፣ እንዲህ አይነት አደጋ ይከሰታል የሚል መረጃ ለኢትዮጵያአየር ተቆጣጣሪዎች አለመነገሩን ገልጿል።
📌የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎችን ለአድማ አነሳስተዋል የተባሉ 9 አመራሮችና ሰራተኞች #መታሰራቸው ይታወቃል።
©ESAT
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ብርጋዴር ጀኔራል #አሳምነው_ጽጌ፦
"በቅማንት ስም የሚንቀሳቀሱ ታጣቂ ኃይሎች በሰነዘሩት ጥቃት #በአንድ መንደር 200 ቤቶች ተቃጥለዋል፤ 2 ሺ ዜጎች ተፈናቅለዋል፤ 55 ሰዎች ሞተዋል፡፡"
.
.
"ከሌላ አካባቢ መጥተው #በግጭት ሲሳተፉ የነበሩና የሞቱ ሶስት ሰዎች መኖራቸውን መታወቂያቸውን በመመልከት #አረጋግጠናል፡፡"
.
.
"ጥፋት #ለመፈጸም የተደራጀው ኃይል ለጊዜው #ተገቷል፤ የታጠቁ ኃይሎች በመሸጉበት ስፍራ ተደምስሰዋል፡፡ በአማራ ክልል በኦሮሚያ ልዩ ዞን ባቲ አካባቢና በጎረቤት ክልልም ሕገወጥ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ጣቢያዎች በቅርብ ርቀት አሉ። የእኛን እርምጃ ወስደናል፡፡ የቀረውንም ከሚመለከታቸው ጋር #መፍትሄ ለመስጠት በቅንጅት እየሰራን ነው፡፡"
©አዲስ ዘመን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"በቅማንት ስም የሚንቀሳቀሱ ታጣቂ ኃይሎች በሰነዘሩት ጥቃት #በአንድ መንደር 200 ቤቶች ተቃጥለዋል፤ 2 ሺ ዜጎች ተፈናቅለዋል፤ 55 ሰዎች ሞተዋል፡፡"
.
.
"ከሌላ አካባቢ መጥተው #በግጭት ሲሳተፉ የነበሩና የሞቱ ሶስት ሰዎች መኖራቸውን መታወቂያቸውን በመመልከት #አረጋግጠናል፡፡"
.
.
"ጥፋት #ለመፈጸም የተደራጀው ኃይል ለጊዜው #ተገቷል፤ የታጠቁ ኃይሎች በመሸጉበት ስፍራ ተደምስሰዋል፡፡ በአማራ ክልል በኦሮሚያ ልዩ ዞን ባቲ አካባቢና በጎረቤት ክልልም ሕገወጥ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ጣቢያዎች በቅርብ ርቀት አሉ። የእኛን እርምጃ ወስደናል፡፡ የቀረውንም ከሚመለከታቸው ጋር #መፍትሄ ለመስጠት በቅንጅት እየሰራን ነው፡፡"
©አዲስ ዘመን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#FDREDefenseForce
የመከላከያ መሃንዲስ ዋና መምሪያ ከግልገል በለስ እስከ አባይ ግድብ የሚደርሠውን መንገድ ስራ ማጠናቀቁ ተገልጿል።
ዋና መምሪያው 210 ኪ.ሜ ርዝማኔ ያለውን ሶስተኛ ደረጃ የጠጠር መንገድ ወደ ከፍተኛ ደረጃ የጠጠር መንገድ በማሳደግ ነው ስራውን ሰርቶ ያጠናቀቀው።
ለታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ የሚውሉ የተለያዩ ግብዓቶች ሲጓጓዙ በመንገድ ላይ እስከ ሁለት ሳምንት ይቆዩ የነበረ ሲሆን በተከናወነው መንገድ የማሻሻል ጥገና ስራ የግድቡ የግንባታ ግብዓቶች #በአንድ_ቀን ለመድረስ ይችላሉ ተብሏል።
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ ሰራዊት
@tikvahethiopia
የመከላከያ መሃንዲስ ዋና መምሪያ ከግልገል በለስ እስከ አባይ ግድብ የሚደርሠውን መንገድ ስራ ማጠናቀቁ ተገልጿል።
ዋና መምሪያው 210 ኪ.ሜ ርዝማኔ ያለውን ሶስተኛ ደረጃ የጠጠር መንገድ ወደ ከፍተኛ ደረጃ የጠጠር መንገድ በማሳደግ ነው ስራውን ሰርቶ ያጠናቀቀው።
ለታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ የሚውሉ የተለያዩ ግብዓቶች ሲጓጓዙ በመንገድ ላይ እስከ ሁለት ሳምንት ይቆዩ የነበረ ሲሆን በተከናወነው መንገድ የማሻሻል ጥገና ስራ የግድቡ የግንባታ ግብዓቶች #በአንድ_ቀን ለመድረስ ይችላሉ ተብሏል።
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ ሰራዊት
@tikvahethiopia
#ETHIOPIA #GERD
" አሁን ላይ በተገኘው አንፃራዊ ሰላም የኮንቮይ ጉዞ ያለምንም ችግር #በአንድ_ቀን መድረስ ችሏል " - ኢ/ር በላቸው ካሳ
የኢትዮጵያ ታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ እየተካሄደ በሚገኝበት ቀጠና በተገኘው ሰላም የግድቡ ግንባታ እየተፋጠነ መሆኑ ተገልጿል።
የግድቡ ምክትል ስራ አስኪያጅ የሆኑት ኢንጂነር በላቸው ካሳ ፤ " በቀጠናው የተገኘው አስተማማኝ ሰላም የግድቡን የግንባታ ሂደት #እያፋጠነው ይገኛል " ሲሉ አሳውቀዋል።
" የፀጥታው ጉዳይ ለግድቡ ግንባታ መሠረታዊ ፍላጎት መሆኑን በመገንዘብ #የሀገር_መከላከያ_ሰራዊት ከሌሎች የፀጥታ ሃይሎች ጋር ተቀናጅቶ ተልዕኮውን በጀግንነት በመፈፀም በቀጠናው የከፈለው መስዋዕትነት የኢትዮጵያን ህዝብና መንግስት ያኮራ በታሪክ የሚኖር ነው " ብለዋል።
ኢ/ር በላቸው፤ በቀጠናው በነበረው የሰላም ችግር ምክንያት ወደ ግድቡ የሚመላለሱ ተሽከርካሪዎች ከሁለትና ከሶስት ቀን በላይ በመቆም መስተጓጎል ይፈጥር እንደነበር አስታውሰው አሁን ላይ የኮንቮይ ጉዞ በተገኘው አንፃራዊ ሰላም ያለምንም ችግር #በአንድ_ቀን መድረስ መቻሉን አስረድተዋል።
የግድቡን ግንባታ ዳር ለማድረስ ሌት ተቀን ሃያ አራት ሰዓት ያለ ዕረፍት የሚተጉ የግንባታዉ ሰራተኞች የአካባቢውን የሙቀት ሁኔታ ተቋቁመው ታሪካዊ ሃላፊነታቸውን በደማቅ ሞራል እየተወጡ እንደሚገኙ አረጋግጠዋል።
በስፍራው ከሚገኙ የሀገር መከላከያ አባላት የቀጠናውን ዘላቂ ሰላም በአስተማማኝ የዝግጁነት ደረጃ በማረጋገጥ ሰራዊቱ የተሰጠውን ግዳጅ በሞራል እየተወጣ እነደሆነ ተናግረዋል።
ሰራዊቱ የሀገሪቱን ሰላም የማይፈልጉ ፀረሠላም የሆኑ ኃይሎችን ፍላጎት በማምከን የግድቡን የፍፃሜ ትንሳኤ ለማብሰር ደከመኝ ሳይል ሀገራዊ ተልዕኮዉን እየተወጣ ነው ብለዋል።
#FDREDefenseForce
@tikvahethiopia
" አሁን ላይ በተገኘው አንፃራዊ ሰላም የኮንቮይ ጉዞ ያለምንም ችግር #በአንድ_ቀን መድረስ ችሏል " - ኢ/ር በላቸው ካሳ
የኢትዮጵያ ታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ እየተካሄደ በሚገኝበት ቀጠና በተገኘው ሰላም የግድቡ ግንባታ እየተፋጠነ መሆኑ ተገልጿል።
የግድቡ ምክትል ስራ አስኪያጅ የሆኑት ኢንጂነር በላቸው ካሳ ፤ " በቀጠናው የተገኘው አስተማማኝ ሰላም የግድቡን የግንባታ ሂደት #እያፋጠነው ይገኛል " ሲሉ አሳውቀዋል።
" የፀጥታው ጉዳይ ለግድቡ ግንባታ መሠረታዊ ፍላጎት መሆኑን በመገንዘብ #የሀገር_መከላከያ_ሰራዊት ከሌሎች የፀጥታ ሃይሎች ጋር ተቀናጅቶ ተልዕኮውን በጀግንነት በመፈፀም በቀጠናው የከፈለው መስዋዕትነት የኢትዮጵያን ህዝብና መንግስት ያኮራ በታሪክ የሚኖር ነው " ብለዋል።
ኢ/ር በላቸው፤ በቀጠናው በነበረው የሰላም ችግር ምክንያት ወደ ግድቡ የሚመላለሱ ተሽከርካሪዎች ከሁለትና ከሶስት ቀን በላይ በመቆም መስተጓጎል ይፈጥር እንደነበር አስታውሰው አሁን ላይ የኮንቮይ ጉዞ በተገኘው አንፃራዊ ሰላም ያለምንም ችግር #በአንድ_ቀን መድረስ መቻሉን አስረድተዋል።
የግድቡን ግንባታ ዳር ለማድረስ ሌት ተቀን ሃያ አራት ሰዓት ያለ ዕረፍት የሚተጉ የግንባታዉ ሰራተኞች የአካባቢውን የሙቀት ሁኔታ ተቋቁመው ታሪካዊ ሃላፊነታቸውን በደማቅ ሞራል እየተወጡ እንደሚገኙ አረጋግጠዋል።
በስፍራው ከሚገኙ የሀገር መከላከያ አባላት የቀጠናውን ዘላቂ ሰላም በአስተማማኝ የዝግጁነት ደረጃ በማረጋገጥ ሰራዊቱ የተሰጠውን ግዳጅ በሞራል እየተወጣ እነደሆነ ተናግረዋል።
ሰራዊቱ የሀገሪቱን ሰላም የማይፈልጉ ፀረሠላም የሆኑ ኃይሎችን ፍላጎት በማምከን የግድቡን የፍፃሜ ትንሳኤ ለማብሰር ደከመኝ ሳይል ሀገራዊ ተልዕኮዉን እየተወጣ ነው ብለዋል።
#FDREDefenseForce
@tikvahethiopia