#አሁን
በትግራይ ስለተፈፀሙ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች እና የሽግግር ፍትህ በማረጋገጥ ሂደት ዙርያ ያለመ የውይይት መድረክ በመቐለ እየተካሄደ ይገኛል።
ውይይቱ ፤ የፍትህ ሚኒስትሩን ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ እና የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለን ያካተተ የፌደራል ልኡካን ቡድን እንዲሁም የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር የመንግስት ከፍተኛ ኃላፊዎች በተገኙበት እየተካሄደ እንደሚገኝ ድምፂ ወያነ ዘግቧል።
ፎቶ፦ ትግራይ ቴሌቪዥን
@tikvahethiopia
በትግራይ ስለተፈፀሙ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች እና የሽግግር ፍትህ በማረጋገጥ ሂደት ዙርያ ያለመ የውይይት መድረክ በመቐለ እየተካሄደ ይገኛል።
ውይይቱ ፤ የፍትህ ሚኒስትሩን ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ እና የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለን ያካተተ የፌደራል ልኡካን ቡድን እንዲሁም የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር የመንግስት ከፍተኛ ኃላፊዎች በተገኙበት እየተካሄደ እንደሚገኝ ድምፂ ወያነ ዘግቧል።
ፎቶ፦ ትግራይ ቴሌቪዥን
@tikvahethiopia
#ቁሳቁስ
በአሉን በበለጠ ድምቀት እንዲያሳልፉ ለልጆችዎ ለፋሲካ እና ለኢድ የሚሆኑ ምርጥ ምርጥ አልባሳት እና ጫማዎች እንደተለመደው አስገብተናል።
በሁሉም እድሜ ክልል ላሉ ልጆች ካሉን ሰፊ አማራጮች የወደዱትን ለመሸመት ለቡ ቫርኔሮ፣ ለቡ ኮሜርሻል ህንፃ (ጋራ ማርት) 3ኛ ፎቅ የሚገኘውን Qusaqus Kids Store ይጎብኙ ዋጋቸውን ለማየት https://t.iss.one/Qusaqus ይቀላቀሉ ስልክ +251944032449
+251987308753
+251941993049
በአሉን በበለጠ ድምቀት እንዲያሳልፉ ለልጆችዎ ለፋሲካ እና ለኢድ የሚሆኑ ምርጥ ምርጥ አልባሳት እና ጫማዎች እንደተለመደው አስገብተናል።
በሁሉም እድሜ ክልል ላሉ ልጆች ካሉን ሰፊ አማራጮች የወደዱትን ለመሸመት ለቡ ቫርኔሮ፣ ለቡ ኮሜርሻል ህንፃ (ጋራ ማርት) 3ኛ ፎቅ የሚገኘውን Qusaqus Kids Store ይጎብኙ ዋጋቸውን ለማየት https://t.iss.one/Qusaqus ይቀላቀሉ ስልክ +251944032449
+251987308753
+251941993049
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ስለ ሐሰተኛ መረጃ ዓይነቶች ምን ያህል ያውቃሉ?
1. ምፀት/ስላቅ (Satire or parody)
2. የውሸት ግንኙነት (False Connection)
3. አሳሳች ይዘት (Misleading Content)
4. የውሸት ዐውድ (False Context)
6. የተዛባ ይዘት (Manipulated Content)
7. የተፈበረከ ይዘት (Fabricated Content)
Source: www.firstdraftnews.org
💬 ሙሉ ይዘቱን ከቪዲዮው ላይ ይመልከቱ
#ግራቀኝ
1. ምፀት/ስላቅ (Satire or parody)
2. የውሸት ግንኙነት (False Connection)
3. አሳሳች ይዘት (Misleading Content)
4. የውሸት ዐውድ (False Context)
6. የተዛባ ይዘት (Manipulated Content)
7. የተፈበረከ ይዘት (Fabricated Content)
Source: www.firstdraftnews.org
#ግራቀኝ
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
የኢትዮጵያ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት በወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ መግለጫ ልኮልናል።
ምክር ቤቱ ከሰሞኑን የክልሎችን ልዩ ሀይልን መልሶ ለማደራጀት ከተደረሰው ውሳኔ ጋር ተያይዞ እየተፈጠሩ ያሉ ሁኔታዎችን በአንክሮ ሲከታተል መቆየቱን አመልክቷል።
በተለይ በአማራ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች በተከሰተው ግጭት በሰዎች ላይ የአካል ጉዳት እና የህይወት መጥፋት መድረሱን ገልጿል።
ህይወታችው ካለፉ ሰዎች መካከል የካቶሊክ ሪሊፍ ሰርቪስ ግብረ ሰናይ ድርጅት ሁለት ሰራተኞች እንደሚገኙበት እንዲሁም በስራ ላይ በነበሩ የቀይ መስቀል ሰራተኞች ላይም ጉዳት የደረሰ መሆኑን ለማወቅ እንደቻለ ገልጿል።
ይህ በሰብአዊ ድጋፍ ስራ ላይ በተሰማሩ ሰራተኞች እየደረሰ ያለው ተደጋጋሚ ጥቃት እና ህልፈተ ህይወት በእጀጉ ያሳዘነው መሆኑን የገለፀው ምክር ቤቱ መሰል ጥቃቶች በሰብአዊ እርዳታ ስራ ላይ የተሰማሩ ድርጅቶች የሚያከናውኑትን የሰብአዊ ድጋፍ ስራን በማስተጓጐል፣ የዕለት እርዳታ የሚፈልጉ ዜጎች ተገቢው ድጋፍ በወቅቱ እንዳይደርሳቸው የሚያደርግ በመሆኑ በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚያሳስበው አመልክቷል።
የኢትዮጲያ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት በዜጎች እንዲሁም በሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት እና ሰራተኞች ላይ እየደረሰ ያለው ጉዳት እንዲቆም፤ ተገቢው ጥበቃም እንዲደረግ ጥሪ አቅርቧል።
ምክር ቤቱ በሀገራችን ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን፤ የሚፈጠሩ ግጭቶች እና አለመግባባቶች ሁሉ በሰላማዊ መንገድ መፍትሄ እንዲያገኙ የጀመረውን ሁለንተናዊ ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጧል።
@tikvahethiopia
ምክር ቤቱ ከሰሞኑን የክልሎችን ልዩ ሀይልን መልሶ ለማደራጀት ከተደረሰው ውሳኔ ጋር ተያይዞ እየተፈጠሩ ያሉ ሁኔታዎችን በአንክሮ ሲከታተል መቆየቱን አመልክቷል።
በተለይ በአማራ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች በተከሰተው ግጭት በሰዎች ላይ የአካል ጉዳት እና የህይወት መጥፋት መድረሱን ገልጿል።
ህይወታችው ካለፉ ሰዎች መካከል የካቶሊክ ሪሊፍ ሰርቪስ ግብረ ሰናይ ድርጅት ሁለት ሰራተኞች እንደሚገኙበት እንዲሁም በስራ ላይ በነበሩ የቀይ መስቀል ሰራተኞች ላይም ጉዳት የደረሰ መሆኑን ለማወቅ እንደቻለ ገልጿል።
ይህ በሰብአዊ ድጋፍ ስራ ላይ በተሰማሩ ሰራተኞች እየደረሰ ያለው ተደጋጋሚ ጥቃት እና ህልፈተ ህይወት በእጀጉ ያሳዘነው መሆኑን የገለፀው ምክር ቤቱ መሰል ጥቃቶች በሰብአዊ እርዳታ ስራ ላይ የተሰማሩ ድርጅቶች የሚያከናውኑትን የሰብአዊ ድጋፍ ስራን በማስተጓጐል፣ የዕለት እርዳታ የሚፈልጉ ዜጎች ተገቢው ድጋፍ በወቅቱ እንዳይደርሳቸው የሚያደርግ በመሆኑ በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚያሳስበው አመልክቷል።
የኢትዮጲያ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት በዜጎች እንዲሁም በሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት እና ሰራተኞች ላይ እየደረሰ ያለው ጉዳት እንዲቆም፤ ተገቢው ጥበቃም እንዲደረግ ጥሪ አቅርቧል።
ምክር ቤቱ በሀገራችን ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን፤ የሚፈጠሩ ግጭቶች እና አለመግባባቶች ሁሉ በሰላማዊ መንገድ መፍትሄ እንዲያገኙ የጀመረውን ሁለንተናዊ ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጧል።
@tikvahethiopia
" የሰላም ስምምነት ቢፈረምም ከ2.3 ሚሊዮን በላይ ሕጻናት ወደ ትምህርት ገበታቸው አልተመለሱም " - የህፃናት አድን ድርጅት
በሰሜን ኢትዮጵያ የተከሰተውን ግጭት ለማስቆም የሰላም ስምምነት ቢፈረምም ከ2.3 ሚሊዮን በላይ ሕጻናት ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዳልተመለሱ የሕፃናት አድን ድርጅት አሳውቋል።
ድርጅቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መግለጫ በሰሜን ኢትዮጵያ የተከሰተውን ግጭት ለማስቆም በያዝነው ዓመት ሕዳር ወር የሰላም ስምምነት ቢፈረምም ከ2.3 ሚሊዮን በላይ ሕጻናት ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዳልተመለሱ አመልክቶ ፤ የመማር ማስተማር ሂደቱን ለማስጀመር ተጨማሪ የገንዘብ እርዳታ ያስፈልጋል ብሏል።
በአሁኑ ወቅት በመላው ኢትዮጵያ ከ3.5 ሚሊዮን ሕፃናት በላይ ከትምህርት ገበታቸው የተፈናቀሉ ሲሆን ይህም እድሜያቸው ለትምህርት ከደረሰ ፣16 ኢትዮጵያውያን ሕፃናት መሃከል አንዱ ከትምህርት ገበታ መገለሉን ሲያሳይ ይሄ አሃዝ ኢትዮጵያን ከትምህርት ጋር በተያያዘ ከፍተኛ ቀውስ ካስተናገዱ ሃገራት አንዷ ያደርጋታል ብሏል።
በሰሜን ኢትዮጵያ በትግራይ፣ በአማራ እና በአፋር ክልል ግጭት በተከሰተባቸው አካባቢዎች በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን በትምህርት ሚኒስቴር፣ በሴቭ ዘችልድረን እና ዩኒሴፍ የሚመራው የትምሀርት ክላስተር ያወጣው የቅርብ ጊዜ መረጃ ያሳያል።
በተለይ በትግራይ 85 በመቶ ትምሀርት ቤቶች ከባድ ወይም ከፊል ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን ሁሉም የህዝብ ትምህርት ቤቶች እንደተዘጉ ናቸው። ይህም በክልሉ 2.3 ሚሊዮን የሚJቱ ህጻናት በኮቪድ ወረርሽን ጀምሮ የሁለት አመቱ ጦርነት ሲታከልበት ለሶሰት አመታት ከትምህርት እንዲገለሉ ያደረገ ሲሆን 22,500 መምህራን ያለ ደሞዝ ከሁለት አመት በላይ ቆይተዋል።
ለረጅም ጊዜ ከትምህርት ቤት የራቁ ሕፃናት ለበርካታ የመብት ጥሰት እና ብዝበዛ እንዲሁም ጥቃት የመጋለጥ እድላቸው ይጨምራል ሲል ድርጅቱ ገልጻል።
የህፃናት አድን ድርጅት (ሴቭ ዘ ችልድረን) በጦርነት ሳቢያ ከቀያቸው ለተፈናቀሉ ህጻናት ባሉበት ስፍራ ደህንነቱ የተጠበቀ የመጫወቻ እና መማሪያ ስፍራዎችን በማሰናዳት፣ ስሜታቸውን ጤናማ በሆነ መልኩ እንዲገልጹ እና የስነልቦና ድጋፍ እንዲያገኙ ሰራዎችን እያከናወነ እንደሆነ አሳውቆናል።
ድርጅቱ ህጻናት ወደ ትምህርት ቤት እንዲመለሱ ለማገዝ መጽሃፍትን እና ሌሎች የመማሪያ ቁሳቁሶችን እያቀረበ ቢሆንም ትምህርትን ጨምሮ ሌሎች ፍላጎታቸውን ለማሟላት ከዚህ የበለጠ ስራ እና መዋእለ- ነዋይ ይጠይቃል ብሏል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኢትዮጵያን የዚህ አመት ሰብአዊ እርዳታ ጥያቄ ለማሟላት ያስፈልጋል ብሎ ከጠየቀው የገንዘብ መጠን 18.4% ብቻ የሚያሟላ የገንዘብ ድጋፍ የተሰበሰበ ሲሆን እቅዱን ሙሉ በሙሉ ለመደገፍ ተጨማሪ 3.26 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋል ሲል አሳውቋል።
(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
በሰሜን ኢትዮጵያ የተከሰተውን ግጭት ለማስቆም የሰላም ስምምነት ቢፈረምም ከ2.3 ሚሊዮን በላይ ሕጻናት ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዳልተመለሱ የሕፃናት አድን ድርጅት አሳውቋል።
ድርጅቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መግለጫ በሰሜን ኢትዮጵያ የተከሰተውን ግጭት ለማስቆም በያዝነው ዓመት ሕዳር ወር የሰላም ስምምነት ቢፈረምም ከ2.3 ሚሊዮን በላይ ሕጻናት ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዳልተመለሱ አመልክቶ ፤ የመማር ማስተማር ሂደቱን ለማስጀመር ተጨማሪ የገንዘብ እርዳታ ያስፈልጋል ብሏል።
በአሁኑ ወቅት በመላው ኢትዮጵያ ከ3.5 ሚሊዮን ሕፃናት በላይ ከትምህርት ገበታቸው የተፈናቀሉ ሲሆን ይህም እድሜያቸው ለትምህርት ከደረሰ ፣16 ኢትዮጵያውያን ሕፃናት መሃከል አንዱ ከትምህርት ገበታ መገለሉን ሲያሳይ ይሄ አሃዝ ኢትዮጵያን ከትምህርት ጋር በተያያዘ ከፍተኛ ቀውስ ካስተናገዱ ሃገራት አንዷ ያደርጋታል ብሏል።
በሰሜን ኢትዮጵያ በትግራይ፣ በአማራ እና በአፋር ክልል ግጭት በተከሰተባቸው አካባቢዎች በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን በትምህርት ሚኒስቴር፣ በሴቭ ዘችልድረን እና ዩኒሴፍ የሚመራው የትምሀርት ክላስተር ያወጣው የቅርብ ጊዜ መረጃ ያሳያል።
በተለይ በትግራይ 85 በመቶ ትምሀርት ቤቶች ከባድ ወይም ከፊል ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን ሁሉም የህዝብ ትምህርት ቤቶች እንደተዘጉ ናቸው። ይህም በክልሉ 2.3 ሚሊዮን የሚJቱ ህጻናት በኮቪድ ወረርሽን ጀምሮ የሁለት አመቱ ጦርነት ሲታከልበት ለሶሰት አመታት ከትምህርት እንዲገለሉ ያደረገ ሲሆን 22,500 መምህራን ያለ ደሞዝ ከሁለት አመት በላይ ቆይተዋል።
ለረጅም ጊዜ ከትምህርት ቤት የራቁ ሕፃናት ለበርካታ የመብት ጥሰት እና ብዝበዛ እንዲሁም ጥቃት የመጋለጥ እድላቸው ይጨምራል ሲል ድርጅቱ ገልጻል።
የህፃናት አድን ድርጅት (ሴቭ ዘ ችልድረን) በጦርነት ሳቢያ ከቀያቸው ለተፈናቀሉ ህጻናት ባሉበት ስፍራ ደህንነቱ የተጠበቀ የመጫወቻ እና መማሪያ ስፍራዎችን በማሰናዳት፣ ስሜታቸውን ጤናማ በሆነ መልኩ እንዲገልጹ እና የስነልቦና ድጋፍ እንዲያገኙ ሰራዎችን እያከናወነ እንደሆነ አሳውቆናል።
ድርጅቱ ህጻናት ወደ ትምህርት ቤት እንዲመለሱ ለማገዝ መጽሃፍትን እና ሌሎች የመማሪያ ቁሳቁሶችን እያቀረበ ቢሆንም ትምህርትን ጨምሮ ሌሎች ፍላጎታቸውን ለማሟላት ከዚህ የበለጠ ስራ እና መዋእለ- ነዋይ ይጠይቃል ብሏል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኢትዮጵያን የዚህ አመት ሰብአዊ እርዳታ ጥያቄ ለማሟላት ያስፈልጋል ብሎ ከጠየቀው የገንዘብ መጠን 18.4% ብቻ የሚያሟላ የገንዘብ ድጋፍ የተሰበሰበ ሲሆን እቅዱን ሙሉ በሙሉ ለመደገፍ ተጨማሪ 3.26 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋል ሲል አሳውቋል።
(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
" ድርቱን የፈፀመው ግለሰብ በፖሊስ እየተፈገለ ነው "
ሆን ብሎ፥ የታመመ ከብት በድብቅ አርዶና ደግሶ ባበላ ግለሰብ ምክንያት የአንድ ሰው ህይወት አለፈ።
በምስራቅ ሀረርጌዞን ባቢሌ ወረዳ አንድ ግለሰብ የታመመ ከብት በድብቅ አርዶ የአካባቢውን ሕብረተሰብ በማብላቱ ምክንያት የአንድ ሰው ህይወት ያለፈ ሲሆን 46 ሰዎች ለጤና ችግር መጋለጣቸው ተገልፃል፡፡
የባቢሌ ወረዳ ኤረር አባድር ቀበሌ ነዋሪ የሆነ ግለሰብ መጋቢት 25/2015 የታመመ በሬ በድብቅ በእርሻ ውስጥ በማረድ ድግስ በመደገስ የአካባቢው ነዋሪዎች እንዲመገቡት አድርጓል ነው የተባለው፡፡
ግለሰቡ ድግሱን በደገሰበት ወቅት እርሱ እና ቤተሰቡ ስጋውን ያልተመገቡ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን ድርጊቱ ሆን ብሎ በሰዎች ላይ ጉዳት ማድረስ መሆኑን ፖሊስ አስረድቷል፡፡
በኤረር አባድር ቀበሌ የእንስሳት ጤና ባለሞያ የሆኑት አቶ አብዱልፈታሕ መሀመድ እንስሳቶች ታመው መድሃኒት ከተሰጣቸው እስከ 28 ቀን ስጋቸው እና ወተታቸው ለምግብነት ሊውል አይገባም ብለዋል፡፡
ይህ ግለሰብ ግን የታመመ በሬውን ያለ ባለሙያ እገዛ በራሱ ከከተማ መድሃኒት እየገዛ በመርፌ ሲሰጠው ቆይቶ ከበሽታው መዳን ሳይችል ሲቀር በድብቅ አርዶ ሰዎችን መመገቡ ጭካኔ የተሞላበት ወንጀል ነው ብለዋል፡፡
ድርቱን የፈፀመው ግለሰብ ባሁን ግዜ ከአካባቢው የሸሸ መሆኑን እና በፖሊስ እየተፈገለ መሆኑ ተገልፃል፡፡
የቢሲዲሞ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር አይመን ሙሳ መጋቢት 27 እና 28 የተመረዘ ስጋ የተመገቡ 47 ሰዎች ለህክምና ወደ ሆስፒታሉ የገቡ መሆኑን ገልፀው የአንድ ሰው ሕይወት ሲያልፍ ለ4 ሰዎች ህክምና መደረጉን ተናግረዋል፡፡
ዘገባው የምስራቅ ሀረርጌ ፖሊስ ጽ/ቤት ነው።
More : @tikvahethmagazine
ሆን ብሎ፥ የታመመ ከብት በድብቅ አርዶና ደግሶ ባበላ ግለሰብ ምክንያት የአንድ ሰው ህይወት አለፈ።
በምስራቅ ሀረርጌዞን ባቢሌ ወረዳ አንድ ግለሰብ የታመመ ከብት በድብቅ አርዶ የአካባቢውን ሕብረተሰብ በማብላቱ ምክንያት የአንድ ሰው ህይወት ያለፈ ሲሆን 46 ሰዎች ለጤና ችግር መጋለጣቸው ተገልፃል፡፡
የባቢሌ ወረዳ ኤረር አባድር ቀበሌ ነዋሪ የሆነ ግለሰብ መጋቢት 25/2015 የታመመ በሬ በድብቅ በእርሻ ውስጥ በማረድ ድግስ በመደገስ የአካባቢው ነዋሪዎች እንዲመገቡት አድርጓል ነው የተባለው፡፡
ግለሰቡ ድግሱን በደገሰበት ወቅት እርሱ እና ቤተሰቡ ስጋውን ያልተመገቡ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን ድርጊቱ ሆን ብሎ በሰዎች ላይ ጉዳት ማድረስ መሆኑን ፖሊስ አስረድቷል፡፡
በኤረር አባድር ቀበሌ የእንስሳት ጤና ባለሞያ የሆኑት አቶ አብዱልፈታሕ መሀመድ እንስሳቶች ታመው መድሃኒት ከተሰጣቸው እስከ 28 ቀን ስጋቸው እና ወተታቸው ለምግብነት ሊውል አይገባም ብለዋል፡፡
ይህ ግለሰብ ግን የታመመ በሬውን ያለ ባለሙያ እገዛ በራሱ ከከተማ መድሃኒት እየገዛ በመርፌ ሲሰጠው ቆይቶ ከበሽታው መዳን ሳይችል ሲቀር በድብቅ አርዶ ሰዎችን መመገቡ ጭካኔ የተሞላበት ወንጀል ነው ብለዋል፡፡
ድርቱን የፈፀመው ግለሰብ ባሁን ግዜ ከአካባቢው የሸሸ መሆኑን እና በፖሊስ እየተፈገለ መሆኑ ተገልፃል፡፡
የቢሲዲሞ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር አይመን ሙሳ መጋቢት 27 እና 28 የተመረዘ ስጋ የተመገቡ 47 ሰዎች ለህክምና ወደ ሆስፒታሉ የገቡ መሆኑን ገልፀው የአንድ ሰው ሕይወት ሲያልፍ ለ4 ሰዎች ህክምና መደረጉን ተናግረዋል፡፡
ዘገባው የምስራቅ ሀረርጌ ፖሊስ ጽ/ቤት ነው።
More : @tikvahethmagazine
" መንግሥት የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎችን እስር እና እንግልት ያቁም " - የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማሕበር
የኢትዮጵየ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማህበር ባወጣው መግለጫ ፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ ባለሙያዎች የሚሰሩበት አውድ እየጠበበ ጋዜጠኞች ስራቸውን በነፃነት እንዳይሰሩ በመንግስት የፀጥታ አካላት #እየተሸማቀቁ እና #እንግልት እየደረሰባቸው እንደሆነ መታዘቡን ገልጿል።
ከሰሞኑን ፤ የማህበሩ መስራችና የስራ አስፈፃሚ አባል እንዲሁም የማህበሩ የህዝብ ግንኙነት ክፍል ኃላፊ ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻውን ጨምሮ ፦
👉 ጋዜጠኛ አራጋው ሲሳይ ፣
👉 ጋዜጠኛ ገነት አስማማው ፣
👉 ጋዜጠኛ ጌትነት አሻግሬ ፣
👉 ጋዜጠኛ በየነ ወልዴ፣
👉 ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ አስፋው በመንግስት ሀይሎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አሳውቋል።
አንዳንዶቹ ያሉበት ቦታ እና ምን ሁኔታ ላይ እንዳሉ እንኳን ቤተሰቦቻቸውም በቂ መረጃ ሳይኖራቸው በእስር ላይ ይገኛሉ ብሏል።
ማህበሩ ፤ ጋዜጠኞች ያለ ፍርድ ቤት ማዘዣ እየታሰሩ፣ እየታፈኑና ቤታቸውና ቢሯቸው እየተበረበረ መሆኑ ባለሞያዎች ስራቸውን በነፃነት እንዳይሰሩ፤ የፕረስ ምህዳሩ የበለጠ እንዲጠብ እያደረገ ነው ሲል ገልጿል።
ማህበሩ የተቋቋመው እንደዚህ አይነት ሙያውን የሚያቀጭጩ ጫናዎችን ለመታገል መሆኑን በመግለፅ የመንግሥት እርምጃዎችን በፅኑ አውግዟል።
ጋዜጠኞች በወንጀል ሲጠረጠሩ ጉዳያቸውን እስር ቤት ሳይቆዩ መከታተል እንደሚችሉ ከሁለት ዓመት በፊት በወጣው በመገናኛ ብዙኃን አዋጅ ቢደነገግም ይህ ግን #ተግባራዊ_አለመደረጉ ማህበሩ እንደሚያሳስበው ገልጿል።
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማሕበር መንግስት፦
- የፕረስ ነፃነት እንዲረጋገጥ
- ያጸደቃቸውን ህገ-መንግስታዊና ዓለም አቀፋዊ ህጎች እንዲያከብርና ውስጡን እንዲፈትሽ
- ያለምንም የህግ አግባብ ያሰራቸውን የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች በአስቸኳይ እንዲፈታ
- ባለሙያዎች ላይ የሚያደርሰውን ማሸማቀቅ እንዲያቆም ጠይቋል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵየ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማህበር ባወጣው መግለጫ ፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ ባለሙያዎች የሚሰሩበት አውድ እየጠበበ ጋዜጠኞች ስራቸውን በነፃነት እንዳይሰሩ በመንግስት የፀጥታ አካላት #እየተሸማቀቁ እና #እንግልት እየደረሰባቸው እንደሆነ መታዘቡን ገልጿል።
ከሰሞኑን ፤ የማህበሩ መስራችና የስራ አስፈፃሚ አባል እንዲሁም የማህበሩ የህዝብ ግንኙነት ክፍል ኃላፊ ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻውን ጨምሮ ፦
👉 ጋዜጠኛ አራጋው ሲሳይ ፣
👉 ጋዜጠኛ ገነት አስማማው ፣
👉 ጋዜጠኛ ጌትነት አሻግሬ ፣
👉 ጋዜጠኛ በየነ ወልዴ፣
👉 ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ አስፋው በመንግስት ሀይሎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አሳውቋል።
አንዳንዶቹ ያሉበት ቦታ እና ምን ሁኔታ ላይ እንዳሉ እንኳን ቤተሰቦቻቸውም በቂ መረጃ ሳይኖራቸው በእስር ላይ ይገኛሉ ብሏል።
ማህበሩ ፤ ጋዜጠኞች ያለ ፍርድ ቤት ማዘዣ እየታሰሩ፣ እየታፈኑና ቤታቸውና ቢሯቸው እየተበረበረ መሆኑ ባለሞያዎች ስራቸውን በነፃነት እንዳይሰሩ፤ የፕረስ ምህዳሩ የበለጠ እንዲጠብ እያደረገ ነው ሲል ገልጿል።
ማህበሩ የተቋቋመው እንደዚህ አይነት ሙያውን የሚያቀጭጩ ጫናዎችን ለመታገል መሆኑን በመግለፅ የመንግሥት እርምጃዎችን በፅኑ አውግዟል።
ጋዜጠኞች በወንጀል ሲጠረጠሩ ጉዳያቸውን እስር ቤት ሳይቆዩ መከታተል እንደሚችሉ ከሁለት ዓመት በፊት በወጣው በመገናኛ ብዙኃን አዋጅ ቢደነገግም ይህ ግን #ተግባራዊ_አለመደረጉ ማህበሩ እንደሚያሳስበው ገልጿል።
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማሕበር መንግስት፦
- የፕረስ ነፃነት እንዲረጋገጥ
- ያጸደቃቸውን ህገ-መንግስታዊና ዓለም አቀፋዊ ህጎች እንዲያከብርና ውስጡን እንዲፈትሽ
- ያለምንም የህግ አግባብ ያሰራቸውን የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች በአስቸኳይ እንዲፈታ
- ባለሙያዎች ላይ የሚያደርሰውን ማሸማቀቅ እንዲያቆም ጠይቋል።
@tikvahethiopia
#Tigray #DDR
የትግራይ ክልል ግዚያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት አቶ ጌታቸው ረዳ ከብሄራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ተሾመ ቶጋ ጋር ተወያዩ።
በውይይቱ በትግራይ ውስጥ ያሉ ታጣቂዎችን ትጥቅ የማስፈታቱ ሂደት የተገመገመበት እንደሆነ ተገልጿል።
ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው እስካሁን የተሰሩ ስራዎች መገምገማቸውን እና በቀጣይም ስለሚሰሩ ስራዎች ውይይት መደረጉን ከዚህ በተጨማሪ ታጣቂዎችን ትጥቅ የማስፈታቱ እና መልሶ የማቋቋም ስራዎች ላይ ከኮሚሽኑ ጋር በቅርበት ለመስራት መስማማታቸውን አመልክተዋል።
@tikvahethiopia
የትግራይ ክልል ግዚያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት አቶ ጌታቸው ረዳ ከብሄራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ተሾመ ቶጋ ጋር ተወያዩ።
በውይይቱ በትግራይ ውስጥ ያሉ ታጣቂዎችን ትጥቅ የማስፈታቱ ሂደት የተገመገመበት እንደሆነ ተገልጿል።
ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው እስካሁን የተሰሩ ስራዎች መገምገማቸውን እና በቀጣይም ስለሚሰሩ ስራዎች ውይይት መደረጉን ከዚህ በተጨማሪ ታጣቂዎችን ትጥቅ የማስፈታቱ እና መልሶ የማቋቋም ስራዎች ላይ ከኮሚሽኑ ጋር በቅርበት ለመስራት መስማማታቸውን አመልክተዋል።
@tikvahethiopia
" ስቅለት "
በክርስትና አስተምሮ ይህ ዕለት የአይሁድ ካህናት ያለ በደል ያለ ጥፋት ንጹሕ እና ጻድቅ የኾነውን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰቀሉበት ዕለት ነው።
ዕለቱ በእምነቱ ተከታዮች ዘንድ ኢየሱስ ክርስቶስ የዓለም ዂሉ መድኀኒት ለአዳምና ለልጆቹ ሲል በመልዕልተ መስቀል በቀራንዮ አደባባይ ተሰቅሎ መዋሉን የሚታሰብበት ታላቅ ቀን ነው።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እና ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን #በስግደት እና #በጾም የሚታሰብ ሲሆን በወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረትም በተለያዩ ስነ-ስርዓቶች ታስቦ ይውላል፡፡
በተለይ ደግሞ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከንጋታው ጀምሮ እስከ ማምሻው በዕለቱ የተፈጸሙትን ክስተቶች በሰዓት ከፍላ በልዩ መንፈሳዊ ሥርዓትና በስግደት ታከብረዋለች ፦
✝ ዓርብ ጠዋት
ዓርብ ጠዋት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በጲላጦስ ፊት በፍርድ አደባባይ መቆሙ ይታሰባል። የካህናት አለቆችና ሕዝቡ ሽማግሎች ሁሉ ሊገድሉት በኢየሱስ ላይ ተማከሩ፤ አስረውም ወሰዱት ፥ ለገዢው ለጰንጤናዊው ጲላጦስም አሳልፈው ሰጡት።
✝ በ3 ሰዓት
ጲላጦስ በወቅቱ በነበረው ሕዝብ ግፊት መሠረት ወንጀለኛውን በርባንን ከእስር አስፈትቶ በምትኩ ኢየሱስን አሳልፎ የሰጠበት፤ አካሉ እስኪያልቅም 6,666 የገረፉት ከሊቶስጥራ - ቀራኒዮ እርጥብ መስቀል አሸክመው የወሰዱበት ነው።
✝ በ6 ሰዓት
ኢየሱስ ክርስቶስን እጆቹን እና እግሮቹን ቸንክረው በቀራንዮ ጎልጎታ ተራራ በ2 ወንበዴዎች መካከል የተሰቀለበት ነው።
✝ በ9 ሰዓት
በእምነቱ አስተምሮ ይህ ሰዓት ኢየሱስ ክርስቶስ ነፍሱን ከሥጋው በባሕርይ ሥልጣኑ የለየበት ወደ ሲዖል ወርዶም የታሠሩትን ሁሉ ያስፈታበት ነው።
✝ 11 ሰዓት
ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ከታላቅ ክብር እና ሐዘን ጋር በአዲስ መቃብር የቀበሩበት ነው።
#Repost
@tikvahethiopia
በክርስትና አስተምሮ ይህ ዕለት የአይሁድ ካህናት ያለ በደል ያለ ጥፋት ንጹሕ እና ጻድቅ የኾነውን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰቀሉበት ዕለት ነው።
ዕለቱ በእምነቱ ተከታዮች ዘንድ ኢየሱስ ክርስቶስ የዓለም ዂሉ መድኀኒት ለአዳምና ለልጆቹ ሲል በመልዕልተ መስቀል በቀራንዮ አደባባይ ተሰቅሎ መዋሉን የሚታሰብበት ታላቅ ቀን ነው።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እና ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን #በስግደት እና #በጾም የሚታሰብ ሲሆን በወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረትም በተለያዩ ስነ-ስርዓቶች ታስቦ ይውላል፡፡
በተለይ ደግሞ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከንጋታው ጀምሮ እስከ ማምሻው በዕለቱ የተፈጸሙትን ክስተቶች በሰዓት ከፍላ በልዩ መንፈሳዊ ሥርዓትና በስግደት ታከብረዋለች ፦
✝ ዓርብ ጠዋት
ዓርብ ጠዋት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በጲላጦስ ፊት በፍርድ አደባባይ መቆሙ ይታሰባል። የካህናት አለቆችና ሕዝቡ ሽማግሎች ሁሉ ሊገድሉት በኢየሱስ ላይ ተማከሩ፤ አስረውም ወሰዱት ፥ ለገዢው ለጰንጤናዊው ጲላጦስም አሳልፈው ሰጡት።
✝ በ3 ሰዓት
ጲላጦስ በወቅቱ በነበረው ሕዝብ ግፊት መሠረት ወንጀለኛውን በርባንን ከእስር አስፈትቶ በምትኩ ኢየሱስን አሳልፎ የሰጠበት፤ አካሉ እስኪያልቅም 6,666 የገረፉት ከሊቶስጥራ - ቀራኒዮ እርጥብ መስቀል አሸክመው የወሰዱበት ነው።
✝ በ6 ሰዓት
ኢየሱስ ክርስቶስን እጆቹን እና እግሮቹን ቸንክረው በቀራንዮ ጎልጎታ ተራራ በ2 ወንበዴዎች መካከል የተሰቀለበት ነው።
✝ በ9 ሰዓት
በእምነቱ አስተምሮ ይህ ሰዓት ኢየሱስ ክርስቶስ ነፍሱን ከሥጋው በባሕርይ ሥልጣኑ የለየበት ወደ ሲዖል ወርዶም የታሠሩትን ሁሉ ያስፈታበት ነው።
✝ 11 ሰዓት
ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ከታላቅ ክብር እና ሐዘን ጋር በአዲስ መቃብር የቀበሩበት ነው።
#Repost
@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ
ለመጪው የፋሲካ በዓል ወደ ሃገር ቤት ገንዘብ ለመላክ አስበዋል ?
በካሽጎ መተግበሪያ ቪዛ ወይም ማስተር ካርድዎን ተጠቅመው ገንዘብ በነፃ ወደ ኢትዮጵያ ይላኩ፡፡
የሞባይል መተግበሪያውን ከ Play Store ወይም App Store በማውረድ ይጠቀሙ።
ለአንድሮይድ ስልኮች 👇
https://play.google.com/store/apps/details?id=com.bankofabyssinia.cashgo&hl=en&gl=US
ለአፕል ስልኮች 👇
https://apps.apple.com/us/app/cashgo/id1559346306
#CashGo #visa #mastercard #የሁሉም_ምርጫ
ለመጪው የፋሲካ በዓል ወደ ሃገር ቤት ገንዘብ ለመላክ አስበዋል ?
በካሽጎ መተግበሪያ ቪዛ ወይም ማስተር ካርድዎን ተጠቅመው ገንዘብ በነፃ ወደ ኢትዮጵያ ይላኩ፡፡
የሞባይል መተግበሪያውን ከ Play Store ወይም App Store በማውረድ ይጠቀሙ።
ለአንድሮይድ ስልኮች 👇
https://play.google.com/store/apps/details?id=com.bankofabyssinia.cashgo&hl=en&gl=US
ለአፕል ስልኮች 👇
https://apps.apple.com/us/app/cashgo/id1559346306
#CashGo #visa #mastercard #የሁሉም_ምርጫ