#NationalExam
" ምዝገባውን ያላደረገ ተማሪ የመልቀቂያ ፈተናውን አይፈተንም " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች ምዝገባ ከመጋቢት 20 እስከ ሚያዚያ 15/2015 ዓ.ም እንደሚከናወን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።
የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ምዝገባ በበይነ መረብ አማካይነት እንደሚከናወን ነው የተገለፀው።
የፈተና ሂደት ላይ ችግር እንዳይፈጠር ተማሪዎች መረጃዎቻቸውን በወቅቱ ማስመዝገብ እንዳለቸው ማሳሰቢያ ተላልፏል።
የመደበኛ እና የማታው ክፍለ ጊዜ ተማሪዎች ምዝገባ በትምህርት ቤቶች እንደሚካሄድ የተጠቀሰ ሲሆን ተማሪዎች የምዝገባ ሂደቱን ለማካሄድ በአካል መገኘት ይኖርባቸዋል፡፡
የድጋሚ ተፈታኞች እና የርቀት ተማሪዎች ምዝገባ ደግሞ በተመረጡ የወረዳ ትምህርት ጽ/ቤቶች ይካሄዳል።
የምዝገባ ሂደቱ በተጠቀሱት ቀናት ተከታታይ የሥራ ቀናት የሚከናወን ሲሆን ምዝገባውን ያላደረገ ተማሪ የመልቀቂያ ፈተናውን እንደማይፈተን አገልግሎቱ አሳውቋል።
የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የመልቀቂያ ፈተና በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ይሰጣል።
ለምዝገባ ምን ያስፈልጋል / ተማሪዎች ምን ማሟላት አለባቸው ?
- መደበኛ ተመዝጋቢዎች ከ9 - 12ኛ ክፍል በተከታታይ ሲማሩ የነበሩ እና በ2015 ዓ.ም በመማር ላይ መሆን ይጠበቅባቸዋል።
- የማታ እና የርቀት ተማሪዎች የ11ኛ ክፍል ሶስት ሴሚስተር እንዲሁም ለ12ኛ ክፍል የሁለት ሴሚስተር የትምህርት ማስረጃ ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።
- ድጋሜ ተፈታኞች ከዚህ ቀደም የተፈተኑበትን የትምህርት ማስረጃ በመያዝ መመዝገብ አለባቸው።
- ተማሪዎች ለምዝገባ ሲመጡ ማንነታቸውን የሚገልፅ መታወቂያ በመያዝ በአካል ተገኝተው በበይነ መረብ መመዝገብ ይጠበቅባቸዋል።
ፈተናው መቼ እና የት ይሰጣል ?
ፈተናው የሚሰጥበት ቀንን በተመለከተም ፈተናው በዩኒቨርስቲ ውስጥ እንደሚሰጥና ቀኑ ወደ ፊት የሚገለፅ መሆኑን ዋና ዳይሬክተሩ ገልፀዋል።
Credit : #MoE
@tikvahuniversity @tikvahethiopia
" ምዝገባውን ያላደረገ ተማሪ የመልቀቂያ ፈተናውን አይፈተንም " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች ምዝገባ ከመጋቢት 20 እስከ ሚያዚያ 15/2015 ዓ.ም እንደሚከናወን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።
የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ምዝገባ በበይነ መረብ አማካይነት እንደሚከናወን ነው የተገለፀው።
የፈተና ሂደት ላይ ችግር እንዳይፈጠር ተማሪዎች መረጃዎቻቸውን በወቅቱ ማስመዝገብ እንዳለቸው ማሳሰቢያ ተላልፏል።
የመደበኛ እና የማታው ክፍለ ጊዜ ተማሪዎች ምዝገባ በትምህርት ቤቶች እንደሚካሄድ የተጠቀሰ ሲሆን ተማሪዎች የምዝገባ ሂደቱን ለማካሄድ በአካል መገኘት ይኖርባቸዋል፡፡
የድጋሚ ተፈታኞች እና የርቀት ተማሪዎች ምዝገባ ደግሞ በተመረጡ የወረዳ ትምህርት ጽ/ቤቶች ይካሄዳል።
የምዝገባ ሂደቱ በተጠቀሱት ቀናት ተከታታይ የሥራ ቀናት የሚከናወን ሲሆን ምዝገባውን ያላደረገ ተማሪ የመልቀቂያ ፈተናውን እንደማይፈተን አገልግሎቱ አሳውቋል።
የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የመልቀቂያ ፈተና በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ይሰጣል።
ለምዝገባ ምን ያስፈልጋል / ተማሪዎች ምን ማሟላት አለባቸው ?
- መደበኛ ተመዝጋቢዎች ከ9 - 12ኛ ክፍል በተከታታይ ሲማሩ የነበሩ እና በ2015 ዓ.ም በመማር ላይ መሆን ይጠበቅባቸዋል።
- የማታ እና የርቀት ተማሪዎች የ11ኛ ክፍል ሶስት ሴሚስተር እንዲሁም ለ12ኛ ክፍል የሁለት ሴሚስተር የትምህርት ማስረጃ ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።
- ድጋሜ ተፈታኞች ከዚህ ቀደም የተፈተኑበትን የትምህርት ማስረጃ በመያዝ መመዝገብ አለባቸው።
- ተማሪዎች ለምዝገባ ሲመጡ ማንነታቸውን የሚገልፅ መታወቂያ በመያዝ በአካል ተገኝተው በበይነ መረብ መመዝገብ ይጠበቅባቸዋል።
ፈተናው መቼ እና የት ይሰጣል ?
ፈተናው የሚሰጥበት ቀንን በተመለከተም ፈተናው በዩኒቨርስቲ ውስጥ እንደሚሰጥና ቀኑ ወደ ፊት የሚገለፅ መሆኑን ዋና ዳይሬክተሩ ገልፀዋል።
Credit : #MoE
@tikvahuniversity @tikvahethiopia
#AwashBank
ታታሪዎቹ !
የስራ ፈጠራ ውድድር በቅርብ ቀን በOBN እና ፋና ቴሌቪዥን ይጠብቁን !!
#Tatariwoch #EmpoweringTheVisionaries
(አዋሽ ባንክ)
ታታሪዎቹ !
የስራ ፈጠራ ውድድር በቅርብ ቀን በOBN እና ፋና ቴሌቪዥን ይጠብቁን !!
#Tatariwoch #EmpoweringTheVisionaries
(አዋሽ ባንክ)
የነጻ ትምህርት ዕድል !
በሰዎች ለሰዎች ድርጅት ወይንም Menschen für Menschen Foundation ስር የሚተዳደረው የሐረር ቴክኖሎጂ ኮሌጅ በ2015 የትምህርት ዘመን ብቁ የሆኑ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎችን በመጀመሪያ ዲግሪ መርሐግብር ሙሉ ወጪያቸውን ሸፍኖ ማስተማር ይፈልጋል፡፡
የዚህ ዕድል ተጠቃሚ መሆን የምትፈልጉ ተማሪዎች ከመጋቢተ 18 - 30 ቀን 2015 ዓ.ም. ባሉት የስራ ቀናት በአካል ቀርባችሁ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናስታውቃለን።
የመመዝገቢያ መስፈርቶች ፦ ትምህርት ሚኒስቴር በ2014 ዓ.ም. ያወጣውን የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ መስፈርት የሚያሟሉ ወይንም በአገር አቀፍ ፈተና 50% እና ከዚያ በላይ ያመጡ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች፡፡
የምዝገባ ቦታዎች በአዲስ አበባ ቦሌ ቡልቡላ በሚገኘው የሰዎች ለሰዎች ድርጅት ዋና መ/ቤት፤ ሐረር በኮሌጁ ቅጥር ግቢ፤ የድርጅቱ ፕሮጄክት ጽ/ቤቶች በሚገኙባችው በተጨማሪም በድረ-ገጻችን https://www.mfmattc.edu.et ላይም መመዝገብ ትችላላችሁ፡፡
ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 0256663738/1139 ወይም 0114714579 ደውሎ ማንጋገር ይቻላል፡፡
(ሰዎች ለሰዎች ድርጅት Menschen für Menschen Foundation)
በሰዎች ለሰዎች ድርጅት ወይንም Menschen für Menschen Foundation ስር የሚተዳደረው የሐረር ቴክኖሎጂ ኮሌጅ በ2015 የትምህርት ዘመን ብቁ የሆኑ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎችን በመጀመሪያ ዲግሪ መርሐግብር ሙሉ ወጪያቸውን ሸፍኖ ማስተማር ይፈልጋል፡፡
የዚህ ዕድል ተጠቃሚ መሆን የምትፈልጉ ተማሪዎች ከመጋቢተ 18 - 30 ቀን 2015 ዓ.ም. ባሉት የስራ ቀናት በአካል ቀርባችሁ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናስታውቃለን።
የመመዝገቢያ መስፈርቶች ፦ ትምህርት ሚኒስቴር በ2014 ዓ.ም. ያወጣውን የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ መስፈርት የሚያሟሉ ወይንም በአገር አቀፍ ፈተና 50% እና ከዚያ በላይ ያመጡ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች፡፡
የምዝገባ ቦታዎች በአዲስ አበባ ቦሌ ቡልቡላ በሚገኘው የሰዎች ለሰዎች ድርጅት ዋና መ/ቤት፤ ሐረር በኮሌጁ ቅጥር ግቢ፤ የድርጅቱ ፕሮጄክት ጽ/ቤቶች በሚገኙባችው በተጨማሪም በድረ-ገጻችን https://www.mfmattc.edu.et ላይም መመዝገብ ትችላላችሁ፡፡
ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 0256663738/1139 ወይም 0114714579 ደውሎ ማንጋገር ይቻላል፡፡
(ሰዎች ለሰዎች ድርጅት Menschen für Menschen Foundation)
#አሁን
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ስብሰባው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እያካሄደ ነው።
የም/ ቤቱ አባላት ጥያቄዎችን እየቀረቡ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለቀረቡላቸው ጠያቄዎች ምላሽ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
እስካሁን ፦
- ከኦነግ ሸኔ፣
- ከአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ፣
- ከሰሜኑ የሰላም ስምምነት፣
- ከዜጎች መፈናቀልና ግድያ፣
- ወደ አዲስ አበባ እንዳይገቡ ስለተከለከሉ ዜጎች፣
- አርሶ አደሩ ምርቱን ለመሸጥ ከመቸገሩ ጋር በተያያዘ፣
- ወደ አዲስ አበባ ምርት እንዳይገባ ከመከልከሉ ጋር፣
- ከክልሎች የርስ በርስ መናበብ አለመቻል፣
- የሱዳን ወታደሮች ወረው የያዙትን የኢትዮጵያ መሬትና ያወደሟቸውን ንብረቶች የተመለከቱ ጥያቄዎች ቀርበዋል።
አሁንም የምክር ቤቱ አባላት ጥያቄዎችን በማቅረብ ላይ ናቸው።
#ኢፕድ
@tikvahethiopia
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ስብሰባው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እያካሄደ ነው።
የም/ ቤቱ አባላት ጥያቄዎችን እየቀረቡ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለቀረቡላቸው ጠያቄዎች ምላሽ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
እስካሁን ፦
- ከኦነግ ሸኔ፣
- ከአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ፣
- ከሰሜኑ የሰላም ስምምነት፣
- ከዜጎች መፈናቀልና ግድያ፣
- ወደ አዲስ አበባ እንዳይገቡ ስለተከለከሉ ዜጎች፣
- አርሶ አደሩ ምርቱን ለመሸጥ ከመቸገሩ ጋር በተያያዘ፣
- ወደ አዲስ አበባ ምርት እንዳይገባ ከመከልከሉ ጋር፣
- ከክልሎች የርስ በርስ መናበብ አለመቻል፣
- የሱዳን ወታደሮች ወረው የያዙትን የኢትዮጵያ መሬትና ያወደሟቸውን ንብረቶች የተመለከቱ ጥያቄዎች ቀርበዋል።
አሁንም የምክር ቤቱ አባላት ጥያቄዎችን በማቅረብ ላይ ናቸው።
#ኢፕድ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#አሁን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ስብሰባው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እያካሄደ ነው። የም/ ቤቱ አባላት ጥያቄዎችን እየቀረቡ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለቀረቡላቸው ጠያቄዎች ምላሽ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። እስካሁን ፦ - ከኦነግ ሸኔ፣ - ከአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ፣ - ከሰሜኑ የሰላም ስምምነት፣ - ከዜጎች መፈናቀልና ግድያ፣ - ወደ አዲስ…
#ፓርላማ
" እርስዎስ ስልጣንዎን በመልቀቅ የመፍትሄው አካል ለመሆን አላሰቡም ወይ ? በሰብዓዊነት ላይ በተፈፀሙ እንዲሁም በማንነት ተኮር የዘር ማጥፋት ፣ የዘር ማፅዳት እና የማንነት ማሳሳት ወንጀሎች ተጠያቂ ለመሆን ምን ያህል ዝግጁ ኖት ?
#አቶ_ክርስቲያን_ታደለ (የህ/ተ/ም/ቤት አባል) ጠቅላይ ሚኒስትሩን ምን ጠየቁ ?
" የጥያቄዬ መንደርደሪያ የሚሆን ማስታወሻ ብዬ ወደ ጥያቄዬ አመራለሁ።
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር በዚህ ምክር ቤት እና በተለያዩ መድረኮች ስለ እርሶ እና ስለሚመሩት የአስፈፃሚ መንግስት ተጠየቅ ሲቀርብቦት ለተጠየቁ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ጠያቂዎችን የሚያጥላላ አስተያየት ሲያራምዱ አለፍ ሲል ተጠየቅ የቀረበቦት የወጡበትን ብሄር በመጥላት እንደሆነ አድርገው ምላሽ ሲሰጡ የቅርብ ትዝታችን ነው።
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ጥያቄ የማቀርብልዎ እኔ በብሄሬ አይደለም፤ ይህን ጥያቄ ሳቀርብልዎ እርሶ የሚወክሉትን ብሄር በመጥላት አይደለም ምላሽ እና ማብራሪያ ሲሰጡም ለጥያቄዬ ብሄርዎን እና ምናልባት የመንግስት ግልበጣ ሴራ ነው ከሚል ምላሽ እና ማብራሪያ እንዳይሰጡ ከወዲሁ አደራ ማለት እፈልጋለሁ።
ወደ ጥያቄዬ አመራለሁ ...
የዜጎችን ደህንነት እና የሀገርን ሉዓላዊነት መጠበቅ ዝቅተኛው የመንግስት ኃላፊነት ሆኖ ሳለ ዜጎች በማንነታቸው ምክንያት በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች ይገደላሉ፤ ይፈናቀላሉ፣ ቤታቸው ይፈርሳል፣ ንብረታቸው ይወድማል የሀገር ሉዓላዊነትን በሚዳፈር መልኩ የጎረቤት ሀገራት ሰራዊቶች በኢትዮጵያ ሰሜን ምዕራብ፣ እና ደቡብ ምዕራብ ወሰኖች በርከታ ኪሎ ሜትሮችን ዘልቀው በመግባት ወረራ ፈፅመዋል።
... የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በሪፖርቱ ደጋግሞ በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች ስለሚገደሉ ዜጎች፣ ስለሚፈፀሙ የሰብዓዊ መብት ወንጀሎች ፣ መፈናቀሎች፣ ግድያዎች ፣ ቤት መፍረሶች በሪፖርቱ ያቀረበው ነው።
አሁን ላይ ባለው ተጨባጭ ሁኔታ የዜጎች ደህንነት እና የሀገር ልዑላዊነት ዋና ስጋት ምንጭ ሆኖ የምናየው እርሶ የሚመሩት መንግስትን ነው።
እርሶ በአፍዎ ኢትዮጵያ አትፈርስም ቢሉንም በተግባር ግን ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊነት በመንግስትዎ እየተናዱ ነው።
የበርካታ ሀገራት መሪዎች መሰል ኃላፊነትን በወጉ አለመወጣት ጉድለት ሲያሳዩ ህዝብን ይቅርታ ጠይቀው ስልጣናቸውን ሲለቁ ይታያል፤ በሀገራችንም የቀድሞ ጠ/ሚ ክቡር ኃይለማርያም ደሳለኝ ተመሳሳይ ህዝባዊ ተጠየቅነት ሲቀርብባቸው ስልጣን መልቀቃቸውን እናስታውሳለን እርስዎም ወደ ስልጣን የመጡት በዚሁ ተጠየቅ ምክንያት ነው፤ እርስዎስ ስልጣንዎን በመልቀቅ የመፍትሄው አካል ለመሆን አላሰቡም ወይ ? በሰብዓዊነት ላይ በተፈፀሙ እንዲሁም በማንነት ተኮር የዘር ማጥፋት ፣ የዘር ማፅዳት እና የማንነት ማሳሳት ወንጀሎች ተጠያቂ ለመሆን ምን ያህል ዝግጁ ኖት ? አመሰግናለሁ !! "
@tikvahethiopia
" እርስዎስ ስልጣንዎን በመልቀቅ የመፍትሄው አካል ለመሆን አላሰቡም ወይ ? በሰብዓዊነት ላይ በተፈፀሙ እንዲሁም በማንነት ተኮር የዘር ማጥፋት ፣ የዘር ማፅዳት እና የማንነት ማሳሳት ወንጀሎች ተጠያቂ ለመሆን ምን ያህል ዝግጁ ኖት ?
#አቶ_ክርስቲያን_ታደለ (የህ/ተ/ም/ቤት አባል) ጠቅላይ ሚኒስትሩን ምን ጠየቁ ?
" የጥያቄዬ መንደርደሪያ የሚሆን ማስታወሻ ብዬ ወደ ጥያቄዬ አመራለሁ።
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር በዚህ ምክር ቤት እና በተለያዩ መድረኮች ስለ እርሶ እና ስለሚመሩት የአስፈፃሚ መንግስት ተጠየቅ ሲቀርብቦት ለተጠየቁ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ጠያቂዎችን የሚያጥላላ አስተያየት ሲያራምዱ አለፍ ሲል ተጠየቅ የቀረበቦት የወጡበትን ብሄር በመጥላት እንደሆነ አድርገው ምላሽ ሲሰጡ የቅርብ ትዝታችን ነው።
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ጥያቄ የማቀርብልዎ እኔ በብሄሬ አይደለም፤ ይህን ጥያቄ ሳቀርብልዎ እርሶ የሚወክሉትን ብሄር በመጥላት አይደለም ምላሽ እና ማብራሪያ ሲሰጡም ለጥያቄዬ ብሄርዎን እና ምናልባት የመንግስት ግልበጣ ሴራ ነው ከሚል ምላሽ እና ማብራሪያ እንዳይሰጡ ከወዲሁ አደራ ማለት እፈልጋለሁ።
ወደ ጥያቄዬ አመራለሁ ...
የዜጎችን ደህንነት እና የሀገርን ሉዓላዊነት መጠበቅ ዝቅተኛው የመንግስት ኃላፊነት ሆኖ ሳለ ዜጎች በማንነታቸው ምክንያት በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች ይገደላሉ፤ ይፈናቀላሉ፣ ቤታቸው ይፈርሳል፣ ንብረታቸው ይወድማል የሀገር ሉዓላዊነትን በሚዳፈር መልኩ የጎረቤት ሀገራት ሰራዊቶች በኢትዮጵያ ሰሜን ምዕራብ፣ እና ደቡብ ምዕራብ ወሰኖች በርከታ ኪሎ ሜትሮችን ዘልቀው በመግባት ወረራ ፈፅመዋል።
... የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በሪፖርቱ ደጋግሞ በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች ስለሚገደሉ ዜጎች፣ ስለሚፈፀሙ የሰብዓዊ መብት ወንጀሎች ፣ መፈናቀሎች፣ ግድያዎች ፣ ቤት መፍረሶች በሪፖርቱ ያቀረበው ነው።
አሁን ላይ ባለው ተጨባጭ ሁኔታ የዜጎች ደህንነት እና የሀገር ልዑላዊነት ዋና ስጋት ምንጭ ሆኖ የምናየው እርሶ የሚመሩት መንግስትን ነው።
እርሶ በአፍዎ ኢትዮጵያ አትፈርስም ቢሉንም በተግባር ግን ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊነት በመንግስትዎ እየተናዱ ነው።
የበርካታ ሀገራት መሪዎች መሰል ኃላፊነትን በወጉ አለመወጣት ጉድለት ሲያሳዩ ህዝብን ይቅርታ ጠይቀው ስልጣናቸውን ሲለቁ ይታያል፤ በሀገራችንም የቀድሞ ጠ/ሚ ክቡር ኃይለማርያም ደሳለኝ ተመሳሳይ ህዝባዊ ተጠየቅነት ሲቀርብባቸው ስልጣን መልቀቃቸውን እናስታውሳለን እርስዎም ወደ ስልጣን የመጡት በዚሁ ተጠየቅ ምክንያት ነው፤ እርስዎስ ስልጣንዎን በመልቀቅ የመፍትሄው አካል ለመሆን አላሰቡም ወይ ? በሰብዓዊነት ላይ በተፈፀሙ እንዲሁም በማንነት ተኮር የዘር ማጥፋት ፣ የዘር ማፅዳት እና የማንነት ማሳሳት ወንጀሎች ተጠያቂ ለመሆን ምን ያህል ዝግጁ ኖት ? አመሰግናለሁ !! "
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#አሁን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ስብሰባው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እያካሄደ ነው። የም/ ቤቱ አባላት ጥያቄዎችን እየቀረቡ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለቀረቡላቸው ጠያቄዎች ምላሽ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። እስካሁን ፦ - ከኦነግ ሸኔ፣ - ከአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ፣ - ከሰሜኑ የሰላም ስምምነት፣ - ከዜጎች መፈናቀልና ግድያ፣ - ወደ አዲስ…
#ፓርላማ
" እነኚህ ሰዎች ሰላም ቢኖር ምን ያጣሉ ? #ከህወሓት ጋር ሰላም ወረደ ሰላም አገኘን ምን አጡ ? #ከኦነግ_ሸኔ ጋር ሰላም ቢወርድ ምን ያጣሉ ? "
ዶክተር ከፈና ኢፋ (የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል) ጠቅላይ ሚኒስትሩን ምን ጠየቁ ?
" .... በኦሮሚያ ክልል ጦርነት በኢኮኖሚ ላይ በፖለቲካ ላይ ፣ በማህበራዊ ህይወት ላይ ያስከተለውን መጠነ ሰፊ ጥፋት እና ጉዳት ዘርዝሬ መጨረስ አልችልም፤ ህዝብ ያወቀው ፀሀይ የሞቀው ጉዳይ ነው።
ህዝባችም በጣም እየተንገላታ ነው፤ በቅርቡ የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በኦሮሚያ ክልል ታጥቆ ለሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች የሰላም ጥሪ አቅርቦላቸዋል፤ ይሄ የሰላም ጥሪ ምን ላይ ደርሷል ? ጅምሩ ምን ይመስላል ? ህዝባችን በአሁን ጊዜ በጉጉት አይደለም እየጠበቀ ያለው ይሄን የሰላም ድርድር በፀሎት ጭምር ነው በፆም በፀሎት ጭምር የዚህን ድርድር መጀመር እየጠበቅን ያለንበት ሁኔታ ነው ያለው።
ስለዚህ #ሰላም ለተጠማው ህዝባችን ሰላም ለማውረድ በዚህ ረገድ መሬት ላይ ምን እየተሰራ ነው ?
ከኦነግ ሸኔም ጋር ይሁን ከህወሓት ጋር ለተደረገው የተሳካ ስምምነት ኢትዮጵያውያን ሆነው የሚቃወሙ ሰዎች አሉ፤ ይሄን የሚያደርጉት ከውሥጥም ከውጭም ነው።
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ፤ ሰላም ከምንም በላይ ብሄራዊ ጥቅማችን ነው ፤ ኢትዮጵያውያን ሆነው ከራሳቸው ብሄራዊ ጥቅም በተፃራሪነት መቆም ትርጉሙ ምንድነው ? ምን ለማግኘት ነው ? ምን ለማጣት ነው ?
እነኚህ ሰዎች ምን ያጣሉ ሰላም ቢኖር ? ከህወሓት ጋር ሰላም ወረደ ሰላም አገኘን ምን አጡ ? ከኦነግ ሸኔ ጋር ሰላም ቢወርድ ምን ያጣሉ ? መፈናቀል ነው የሚቀረው ፣ ተጨማሪ የሰው ስቃይ ነው የሚቀረው ፣ የንብረት መውደም ነው የሚቀረው፣ የመሰረተ ልማት መውደም ነው የሚቀረው ይሄን የሚቃወም ኢትዮጵያዊ ምን አይነት ኢትዮጵያዊ ነው ? ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ፤ አመሰግናለሁ !! "
@tikvahethiopia
" እነኚህ ሰዎች ሰላም ቢኖር ምን ያጣሉ ? #ከህወሓት ጋር ሰላም ወረደ ሰላም አገኘን ምን አጡ ? #ከኦነግ_ሸኔ ጋር ሰላም ቢወርድ ምን ያጣሉ ? "
ዶክተር ከፈና ኢፋ (የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል) ጠቅላይ ሚኒስትሩን ምን ጠየቁ ?
" .... በኦሮሚያ ክልል ጦርነት በኢኮኖሚ ላይ በፖለቲካ ላይ ፣ በማህበራዊ ህይወት ላይ ያስከተለውን መጠነ ሰፊ ጥፋት እና ጉዳት ዘርዝሬ መጨረስ አልችልም፤ ህዝብ ያወቀው ፀሀይ የሞቀው ጉዳይ ነው።
ህዝባችም በጣም እየተንገላታ ነው፤ በቅርቡ የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በኦሮሚያ ክልል ታጥቆ ለሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች የሰላም ጥሪ አቅርቦላቸዋል፤ ይሄ የሰላም ጥሪ ምን ላይ ደርሷል ? ጅምሩ ምን ይመስላል ? ህዝባችን በአሁን ጊዜ በጉጉት አይደለም እየጠበቀ ያለው ይሄን የሰላም ድርድር በፀሎት ጭምር ነው በፆም በፀሎት ጭምር የዚህን ድርድር መጀመር እየጠበቅን ያለንበት ሁኔታ ነው ያለው።
ስለዚህ #ሰላም ለተጠማው ህዝባችን ሰላም ለማውረድ በዚህ ረገድ መሬት ላይ ምን እየተሰራ ነው ?
ከኦነግ ሸኔም ጋር ይሁን ከህወሓት ጋር ለተደረገው የተሳካ ስምምነት ኢትዮጵያውያን ሆነው የሚቃወሙ ሰዎች አሉ፤ ይሄን የሚያደርጉት ከውሥጥም ከውጭም ነው።
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ፤ ሰላም ከምንም በላይ ብሄራዊ ጥቅማችን ነው ፤ ኢትዮጵያውያን ሆነው ከራሳቸው ብሄራዊ ጥቅም በተፃራሪነት መቆም ትርጉሙ ምንድነው ? ምን ለማግኘት ነው ? ምን ለማጣት ነው ?
እነኚህ ሰዎች ምን ያጣሉ ሰላም ቢኖር ? ከህወሓት ጋር ሰላም ወረደ ሰላም አገኘን ምን አጡ ? ከኦነግ ሸኔ ጋር ሰላም ቢወርድ ምን ያጣሉ ? መፈናቀል ነው የሚቀረው ፣ ተጨማሪ የሰው ስቃይ ነው የሚቀረው ፣ የንብረት መውደም ነው የሚቀረው፣ የመሰረተ ልማት መውደም ነው የሚቀረው ይሄን የሚቃወም ኢትዮጵያዊ ምን አይነት ኢትዮጵያዊ ነው ? ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ፤ አመሰግናለሁ !! "
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ፓርላማ " እርስዎስ ስልጣንዎን በመልቀቅ የመፍትሄው አካል ለመሆን አላሰቡም ወይ ? በሰብዓዊነት ላይ በተፈፀሙ እንዲሁም በማንነት ተኮር የዘር ማጥፋት ፣ የዘር ማፅዳት እና የማንነት ማሳሳት ወንጀሎች ተጠያቂ ለመሆን ምን ያህል ዝግጁ ኖት ? #አቶ_ክርስቲያን_ታደለ (የህ/ተ/ም/ቤት አባል) ጠቅላይ ሚኒስትሩን ምን ጠየቁ ? " የጥያቄዬ መንደርደሪያ የሚሆን ማስታወሻ ብዬ ወደ ጥያቄዬ አመራለሁ። ክቡር…
#ፓርላማ
ጠቅላይ ሚኒስትሩ " ስልጣን በመልቀቅ የመፍትሄው አካል አይሆኑም ወይ ? ለሚለው ጥያቄ ምን መለሱ ?
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፦
" ስልጣን ብትለቅ የተባለው በጣም ጥሩ ጥያቄ ነው ፤ ግን ጥሩ የሚሆነው ስልጣን ብንለቅ ነበረ ምክንያቱም መንግስት ማለት አስፈፃሚ ብቻ ማለት አይደለም።
ህግ አውጪ መንግስት ነው፣ ህግ ተርጓሚ መንግስት ነው ፣ አስፈፃሚ መንግስት ነው እኛ እዚህ ያለን ሰዎች የመንግስት ባለስልጣኖች ነን።
ይልቁኑንም የተከበሩ አቶ ክርስቲያን ደግሞ የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ናቸው የአንድ ሚኒስትር አለቃ ናቸው እና በጋራ ብንለቅ ቢሆን ምክንያቱም እርሶም እንደሚገነዘቡት የሁሉ ችግር ምንጭ እና ባለቤት እኔ ብቻ ልሆን አልችልም።
ኃላፊነት ከወሰድንም በጋራ ቢሆን ጥሩ ይሆናል ብዬ አስባለሁ።
ነገር ግን ይሄን ጥያቄ እሳቸው ቢያነሱትም እሳቸው ላይም ይነሳ ነበር በውጭ ያሉ እንደሳቸው ፓርላማ አሸንፈው መግባት ያልቻሉ ሰዎች ለምንድነው እኚህ ሰውዬ የቋሚ ኮሚቴ ኃላፊነት ላይ የተቀመጡት አይለቁም እንዴ ? እያሉ ከዚህ ቀደም በሚዲያ እንደምትሰሙት ብዙ ይተቻሉ፤ እርሶ ምርጫ አሸንፈው ነው የገቡት እዚህ ተቀምጠው የህዝቡን ጥያቄ ማንሳትዎ ተገቢ ነው ብዬ ማስበው መቆጣጠሩም የሚያደርጉት ጥረትም።
ግን ከስልጣን ጋር ተያይዞ ያለውን ጉዳይ በአንድ ቀላል ምላሴ ለማስረዳት በደቡብ ህንድ ጦጣን የማጥመድ ቴክኒክ አለ ጦጣን እንደምታውቁት ቁንጥንጥ ናት፣ ቅብዝብዝ ናት ለአደን አትመችም እና በደቡብ ህንድ ያሉ አዳኞች ጦጣን ለማጥመድ የኮኮናት ፍሬ በጦጣ እጅ ልክ በቀጭኑ ይቀዱና ከውሥጥ ሩዝ ያስቀምጣሉ ሲቀዱት የጦጣ እጅ ቀጭን ስለሆነ በዚያ ልክ ይቀዱትና ውስጥ ግን ሰፋ አድርገው ሩዝ ያስቀምጣሉ፤ሊይዟት ስለማይችሉ ጦጣ ሩዝ አየሁ ብላ እጇን ሰዳ ካፈሰች በኃላ ልውጣ ስትል የተሰራው ለቀጭኑ ስለሆነ ከጨበጠች በኃላ አይለቃትም።
ይቺ ጦጣ የሰው ሩዝ ነው የያዝኩት የማይገባኝን ሩዝ ነው የያዝኩት ይዤው ከቆየሁ ልያዝ እችላለሁ በትኜው ልሂድ አትልም እንደጨበጠች ትታገላለች በዚህ ጊዜ ያን የኮከናት ፍሬ መውሰድ ስለማትችል አዳኙ መጥቶ ይይዛታል። ጦጣዋን ያደናት የያዛት ምንድነው ያላችሁ እንደሆነ ሃሳቧ ነው እንጂ ወጥመዱ አይደለም፤ እዛው በትና በትለቅ ትወጣለች በሀሳብ ግን ሩዝ አፍሼ ካልወጣሁ ስላለች ሀሳቧ አጥምዶ ያስቀራታል እዛው።
ዶሮ ብታልም ጥሬዋን እንደሚባለው ቁጭ ብለው የሚያልሙ ሰዎች አሉ ሁል ጊዜ በዚያ መንገድ ጥሩ አይሆንም።
ሁለተኛ ቢጨበጥ ጥሩ የሚሆነው ስልጣንን በሚመለከት በእኔ እና በተከበሩ አቶ ብናልፍ መካከል የሚደረግ ድርድር የለም።
የስልጣን ባለቤት ህዝብ ነው፤ስልጣን ሰጪም ነፋጊም ህዝብ ነው፤እኔ ና አቶ ብናልፍ ማድረግ ያለብን የተሻለ ሃሳብ ይዘን ህዝባችን ጋር መቅረብ እና የኔን ሃሳብ ምረጥልኝ ብለን በሰጪው ነው የምንመረጠው እንጂ በምክር ቤት ውስጥ ስጠኝ ልቀቅልኝ በሚል አይሆንም።
ሰጪው ጋር ሃሳብ የተሻለ ይዞ መቅረብ ታስፈልጋል፤ ስለዚህ ስልጣን በኮሮጆ እንጂ በመናጀ አይያዝም እና ሶስት ዓመት ይቅራል ለምርጫ በውጭም አሉ ይሄ የኦሮሞ መንግሥት ይሄ የኦሮሞ መንግስት እያሉ የሚዘፍኑ ዘፋኞች አሉ እነሱን ጨምሮ ሰብሰብ ብሎ ሃሳብ አጠናክሮ ለኢትዮጵያ ህዝብ ማቅረብ ነው እኛ ለኢትዮጵያ ህዝብ እንደተባለድ የተገባውን ቃል ካልመለስን የኢትዮጵያ ህዝብ በእኛ አስተዳደር ካልረካ በምርጫ ከጣለን በተደጋጋሚ እንዳልነው በደስታ እናስረክባለን።
ፓርቲዎች መዘጋጀት ያለባቸው ሃሳብ ይዘው መምጣት ነው፤ አሁን ሃሳብ የለም፤ ሰብሰብ ብሎ ሃሳብ ይዞ ያን ወደ ህዝብ አቅርቦ ለመመረጥ እና ለማሸነፍ የሚደረግ ጥረት ለሁላችን የሚጠቅመን ይሆናል "
@tikvahethiopia
ጠቅላይ ሚኒስትሩ " ስልጣን በመልቀቅ የመፍትሄው አካል አይሆኑም ወይ ? ለሚለው ጥያቄ ምን መለሱ ?
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፦
" ስልጣን ብትለቅ የተባለው በጣም ጥሩ ጥያቄ ነው ፤ ግን ጥሩ የሚሆነው ስልጣን ብንለቅ ነበረ ምክንያቱም መንግስት ማለት አስፈፃሚ ብቻ ማለት አይደለም።
ህግ አውጪ መንግስት ነው፣ ህግ ተርጓሚ መንግስት ነው ፣ አስፈፃሚ መንግስት ነው እኛ እዚህ ያለን ሰዎች የመንግስት ባለስልጣኖች ነን።
ይልቁኑንም የተከበሩ አቶ ክርስቲያን ደግሞ የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ናቸው የአንድ ሚኒስትር አለቃ ናቸው እና በጋራ ብንለቅ ቢሆን ምክንያቱም እርሶም እንደሚገነዘቡት የሁሉ ችግር ምንጭ እና ባለቤት እኔ ብቻ ልሆን አልችልም።
ኃላፊነት ከወሰድንም በጋራ ቢሆን ጥሩ ይሆናል ብዬ አስባለሁ።
ነገር ግን ይሄን ጥያቄ እሳቸው ቢያነሱትም እሳቸው ላይም ይነሳ ነበር በውጭ ያሉ እንደሳቸው ፓርላማ አሸንፈው መግባት ያልቻሉ ሰዎች ለምንድነው እኚህ ሰውዬ የቋሚ ኮሚቴ ኃላፊነት ላይ የተቀመጡት አይለቁም እንዴ ? እያሉ ከዚህ ቀደም በሚዲያ እንደምትሰሙት ብዙ ይተቻሉ፤ እርሶ ምርጫ አሸንፈው ነው የገቡት እዚህ ተቀምጠው የህዝቡን ጥያቄ ማንሳትዎ ተገቢ ነው ብዬ ማስበው መቆጣጠሩም የሚያደርጉት ጥረትም።
ግን ከስልጣን ጋር ተያይዞ ያለውን ጉዳይ በአንድ ቀላል ምላሴ ለማስረዳት በደቡብ ህንድ ጦጣን የማጥመድ ቴክኒክ አለ ጦጣን እንደምታውቁት ቁንጥንጥ ናት፣ ቅብዝብዝ ናት ለአደን አትመችም እና በደቡብ ህንድ ያሉ አዳኞች ጦጣን ለማጥመድ የኮኮናት ፍሬ በጦጣ እጅ ልክ በቀጭኑ ይቀዱና ከውሥጥ ሩዝ ያስቀምጣሉ ሲቀዱት የጦጣ እጅ ቀጭን ስለሆነ በዚያ ልክ ይቀዱትና ውስጥ ግን ሰፋ አድርገው ሩዝ ያስቀምጣሉ፤ሊይዟት ስለማይችሉ ጦጣ ሩዝ አየሁ ብላ እጇን ሰዳ ካፈሰች በኃላ ልውጣ ስትል የተሰራው ለቀጭኑ ስለሆነ ከጨበጠች በኃላ አይለቃትም።
ይቺ ጦጣ የሰው ሩዝ ነው የያዝኩት የማይገባኝን ሩዝ ነው የያዝኩት ይዤው ከቆየሁ ልያዝ እችላለሁ በትኜው ልሂድ አትልም እንደጨበጠች ትታገላለች በዚህ ጊዜ ያን የኮከናት ፍሬ መውሰድ ስለማትችል አዳኙ መጥቶ ይይዛታል። ጦጣዋን ያደናት የያዛት ምንድነው ያላችሁ እንደሆነ ሃሳቧ ነው እንጂ ወጥመዱ አይደለም፤ እዛው በትና በትለቅ ትወጣለች በሀሳብ ግን ሩዝ አፍሼ ካልወጣሁ ስላለች ሀሳቧ አጥምዶ ያስቀራታል እዛው።
ዶሮ ብታልም ጥሬዋን እንደሚባለው ቁጭ ብለው የሚያልሙ ሰዎች አሉ ሁል ጊዜ በዚያ መንገድ ጥሩ አይሆንም።
ሁለተኛ ቢጨበጥ ጥሩ የሚሆነው ስልጣንን በሚመለከት በእኔ እና በተከበሩ አቶ ብናልፍ መካከል የሚደረግ ድርድር የለም።
የስልጣን ባለቤት ህዝብ ነው፤ስልጣን ሰጪም ነፋጊም ህዝብ ነው፤እኔ ና አቶ ብናልፍ ማድረግ ያለብን የተሻለ ሃሳብ ይዘን ህዝባችን ጋር መቅረብ እና የኔን ሃሳብ ምረጥልኝ ብለን በሰጪው ነው የምንመረጠው እንጂ በምክር ቤት ውስጥ ስጠኝ ልቀቅልኝ በሚል አይሆንም።
ሰጪው ጋር ሃሳብ የተሻለ ይዞ መቅረብ ታስፈልጋል፤ ስለዚህ ስልጣን በኮሮጆ እንጂ በመናጀ አይያዝም እና ሶስት ዓመት ይቅራል ለምርጫ በውጭም አሉ ይሄ የኦሮሞ መንግሥት ይሄ የኦሮሞ መንግስት እያሉ የሚዘፍኑ ዘፋኞች አሉ እነሱን ጨምሮ ሰብሰብ ብሎ ሃሳብ አጠናክሮ ለኢትዮጵያ ህዝብ ማቅረብ ነው እኛ ለኢትዮጵያ ህዝብ እንደተባለድ የተገባውን ቃል ካልመለስን የኢትዮጵያ ህዝብ በእኛ አስተዳደር ካልረካ በምርጫ ከጣለን በተደጋጋሚ እንዳልነው በደስታ እናስረክባለን።
ፓርቲዎች መዘጋጀት ያለባቸው ሃሳብ ይዘው መምጣት ነው፤ አሁን ሃሳብ የለም፤ ሰብሰብ ብሎ ሃሳብ ይዞ ያን ወደ ህዝብ አቅርቦ ለመመረጥ እና ለማሸነፍ የሚደረግ ጥረት ለሁላችን የሚጠቅመን ይሆናል "
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ፓርላማ " እነኚህ ሰዎች ሰላም ቢኖር ምን ያጣሉ ? #ከህወሓት ጋር ሰላም ወረደ ሰላም አገኘን ምን አጡ ? #ከኦነግ_ሸኔ ጋር ሰላም ቢወርድ ምን ያጣሉ ? " ዶክተር ከፈና ኢፋ (የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል) ጠቅላይ ሚኒስትሩን ምን ጠየቁ ? " .... በኦሮሚያ ክልል ጦርነት በኢኮኖሚ ላይ በፖለቲካ ላይ ፣ በማህበራዊ ህይወት ላይ ያስከተለውን መጠነ ሰፊ ጥፋት እና ጉዳት ዘርዝሬ መጨረስ አልችልም፤…
#ፓርላማ
መንግሥት ከ " ኦነግ ሸኔ " ጋር የሚደረግን የሰላም ድርድር የሚመራ ኮሚቴ አቋቁሞ እየሰራ እንደሚገኝ ዛሬ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ለፓርላማ ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለ " ኦነግ ሸኔ " ምን አሉ ?
ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፦
" ሸኔን በሚመለከት ለተነሳው ጥያቄ ... ላለፉት አራት ፣ አምስት ዓመታት ወለጋ አካባቢ ልማት እንዳይሰራ ሰዎች እንዲፈናቀሉ እንዲገደሉ ብዙ መጎሳቀል ግጭት ነው።
ይሄ ግጭት በሰላም እንዲፈታ መንግሥት ከፍተኛ ፍላጎት አለው። ከፍተኛ ፍላጎት አለው ብቻ ሳይሆን በባለፈው በማዕከላዊ ኮሚቴ ተወያይቶ በፓርቲያችን ምክትል ፕሬዜዳንት የሚመራ ኮሚቴ አቋቁሟል። የሰላም ድርድሩን የሚመራ።
ከቤኒሻንጉል ጋር የተሻለ ውጤት ተገኝቷል፣ ከጋምቤላ ጋር የተሻለ ውጤት ተገኝቷል፣ ከቅማንት ጋርም እንዲሁ የተሻለ ውጤት ተገኝቷል የሚቀሩ ጉዳዮች ቢኖሩም ሸኔን በሚመለከት ባለፉት አንድ / ሁለት ወር ገደማ ከ10 በላይ ሙከራዎች ተደርገዋል ያስቸገረው ነገር አንድ የተሰባሰበ ኃይል ባለመሆኑ ምንነጋገርባቸው ኃይሎች የተለያየ ሃሳብ እና አቋም ይዘው ስለሚመጡ ነው።
የሆነው ሆኖ በእኛ በኩል የኦሮሚያ መንግስት ያቀረበው የሰላም ጥሪ የሚባለው የኦሮሚያ መንግስት ያቀረበው ሳይሆን እንደ ፓርቲ ተወያይተን ወስነን በምክትል ፕሬዜዳንት የሚመራ ኮሚቴ አቋቁመን የዛን ተቀጥያ ነው የኦሮሚያ መንግሥት የገለፀው/ ያብራራው።
ሰላሙን የሚጠላው ሰው ይኖራል ብዬ አላስብም ኢትዮጵያዊና ጤነኛ ሰው ከሆነ ምክንያቱም ብዙ ሰው እየተጎዳ እየተፈናቀለ ስለሆነ ሰላሙን ሁሉም ይፈልገዋል የሚል ተስፋ አድርጋለሁ በእኛ በኩል ጉዳዩ በሰላም እንዲፈታ አበክረን እንሰራለን። ጉዳዩ በሰላም እንዲፈታ አበክረን እየሰራን ተጨማሪ ደግሞ ማፈናቀል እና መግደል እንዳይፈጠር / እንዳይቻልም ኃይሎቻችን በስፋት እዛ አካባቢ ጠንከር ያለ ስራ እየሰሩ ይገኛሉ።
ለሰላሙ ግን ጥርጣሬ መኖር የሌለበት ለአገው ሸንጎም፣ ለቅማንትም፣ ለTPLFም ፣ ለኦነግም ለሁሉም የታጠቁ ኃይሎች የኢትዮጵያ መንግስት የሚፈልገው ጉዳዩን በንግግር ፣ በምክክር ፣ በውይይት መፍታ ነው። መገዳደል አይጠቅምም የሚል የፀና አቋም አለን የሚያዋጣንም መንገድ እሱ ይመስለኛል።
በዚህ አግባብ ቢታይ የሸኔ ጉዳይ እየተመራ እንደሆነ ኮሚቴዎች ተቋቁመው እየተነጋገሩ እንደሆነ ውጤቱን ደግሞ በጋራ የምናይ ይሆናል ። "
@tikvahethiopia
መንግሥት ከ " ኦነግ ሸኔ " ጋር የሚደረግን የሰላም ድርድር የሚመራ ኮሚቴ አቋቁሞ እየሰራ እንደሚገኝ ዛሬ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ለፓርላማ ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለ " ኦነግ ሸኔ " ምን አሉ ?
ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፦
" ሸኔን በሚመለከት ለተነሳው ጥያቄ ... ላለፉት አራት ፣ አምስት ዓመታት ወለጋ አካባቢ ልማት እንዳይሰራ ሰዎች እንዲፈናቀሉ እንዲገደሉ ብዙ መጎሳቀል ግጭት ነው።
ይሄ ግጭት በሰላም እንዲፈታ መንግሥት ከፍተኛ ፍላጎት አለው። ከፍተኛ ፍላጎት አለው ብቻ ሳይሆን በባለፈው በማዕከላዊ ኮሚቴ ተወያይቶ በፓርቲያችን ምክትል ፕሬዜዳንት የሚመራ ኮሚቴ አቋቁሟል። የሰላም ድርድሩን የሚመራ።
ከቤኒሻንጉል ጋር የተሻለ ውጤት ተገኝቷል፣ ከጋምቤላ ጋር የተሻለ ውጤት ተገኝቷል፣ ከቅማንት ጋርም እንዲሁ የተሻለ ውጤት ተገኝቷል የሚቀሩ ጉዳዮች ቢኖሩም ሸኔን በሚመለከት ባለፉት አንድ / ሁለት ወር ገደማ ከ10 በላይ ሙከራዎች ተደርገዋል ያስቸገረው ነገር አንድ የተሰባሰበ ኃይል ባለመሆኑ ምንነጋገርባቸው ኃይሎች የተለያየ ሃሳብ እና አቋም ይዘው ስለሚመጡ ነው።
የሆነው ሆኖ በእኛ በኩል የኦሮሚያ መንግስት ያቀረበው የሰላም ጥሪ የሚባለው የኦሮሚያ መንግስት ያቀረበው ሳይሆን እንደ ፓርቲ ተወያይተን ወስነን በምክትል ፕሬዜዳንት የሚመራ ኮሚቴ አቋቁመን የዛን ተቀጥያ ነው የኦሮሚያ መንግሥት የገለፀው/ ያብራራው።
ሰላሙን የሚጠላው ሰው ይኖራል ብዬ አላስብም ኢትዮጵያዊና ጤነኛ ሰው ከሆነ ምክንያቱም ብዙ ሰው እየተጎዳ እየተፈናቀለ ስለሆነ ሰላሙን ሁሉም ይፈልገዋል የሚል ተስፋ አድርጋለሁ በእኛ በኩል ጉዳዩ በሰላም እንዲፈታ አበክረን እንሰራለን። ጉዳዩ በሰላም እንዲፈታ አበክረን እየሰራን ተጨማሪ ደግሞ ማፈናቀል እና መግደል እንዳይፈጠር / እንዳይቻልም ኃይሎቻችን በስፋት እዛ አካባቢ ጠንከር ያለ ስራ እየሰሩ ይገኛሉ።
ለሰላሙ ግን ጥርጣሬ መኖር የሌለበት ለአገው ሸንጎም፣ ለቅማንትም፣ ለTPLFም ፣ ለኦነግም ለሁሉም የታጠቁ ኃይሎች የኢትዮጵያ መንግስት የሚፈልገው ጉዳዩን በንግግር ፣ በምክክር ፣ በውይይት መፍታ ነው። መገዳደል አይጠቅምም የሚል የፀና አቋም አለን የሚያዋጣንም መንገድ እሱ ይመስለኛል።
በዚህ አግባብ ቢታይ የሸኔ ጉዳይ እየተመራ እንደሆነ ኮሚቴዎች ተቋቁመው እየተነጋገሩ እንደሆነ ውጤቱን ደግሞ በጋራ የምናይ ይሆናል ። "
@tikvahethiopia
#ቴሌብር #ኢትዮቴሌኮም
ገና በአጭር እድሜው 30 ሚሊየን ተጠቃሚ ያፈራ ፤ 370 ቢሊየን ብር በገበያ ያዘዋወረ ፤ ከ18 ባንኮች ጋር የተጣመረ ፡ እነሆ ቴሌብር ሱፐርአፕን አበሰረ!!!
ከእንግዲህ ለተለያዩ አገልግሎቶች በርካታ መተግበሪያዎችን አይጭኑም፦
በቴሌብር ሱፐርአፕ ሁሉም ስለተጣመሩ
ጊዜና ጉልበት ሳይባክኑ እልፍ ጉዳይዎን እዛው ይከውናሉ።
የትራንስፖርት፣ የመዝናኛ፣ ኢ-ኮሜርስ፣ የመሠረታዊ አገልግሎቶች፣ የምግብ እና ዴሊቨሪ አገልግሎት ሰጪዎች ኧረ ማን የቀረ አለ በቴሌብር ሱፐርአፕ ሁሉም በአንድ ተሰብስበዋል።
የስራ ውጥረት ሲበዛ የክፍያዎች ቀን ይረሳል ፤ ሱፐርአፕ አያንቀላፋም ቀደም ብሎ ያስታውሳል።
የደህንነት አጥሩ አስተማማኝ እና ጠንካራ ፤ ከይለፍ ቃል በተጨማሪ በፊት ገፅና በአሻራ
እልፍ ጉዳይ በአንድ መተግበሪያ
ከ onelink.to/75zfa5 አውርደው ይሞክሩት
(ኢትዮ ቴሌኮም)
ገና በአጭር እድሜው 30 ሚሊየን ተጠቃሚ ያፈራ ፤ 370 ቢሊየን ብር በገበያ ያዘዋወረ ፤ ከ18 ባንኮች ጋር የተጣመረ ፡ እነሆ ቴሌብር ሱፐርአፕን አበሰረ!!!
ከእንግዲህ ለተለያዩ አገልግሎቶች በርካታ መተግበሪያዎችን አይጭኑም፦
በቴሌብር ሱፐርአፕ ሁሉም ስለተጣመሩ
ጊዜና ጉልበት ሳይባክኑ እልፍ ጉዳይዎን እዛው ይከውናሉ።
የትራንስፖርት፣ የመዝናኛ፣ ኢ-ኮሜርስ፣ የመሠረታዊ አገልግሎቶች፣ የምግብ እና ዴሊቨሪ አገልግሎት ሰጪዎች ኧረ ማን የቀረ አለ በቴሌብር ሱፐርአፕ ሁሉም በአንድ ተሰብስበዋል።
የስራ ውጥረት ሲበዛ የክፍያዎች ቀን ይረሳል ፤ ሱፐርአፕ አያንቀላፋም ቀደም ብሎ ያስታውሳል።
የደህንነት አጥሩ አስተማማኝ እና ጠንካራ ፤ ከይለፍ ቃል በተጨማሪ በፊት ገፅና በአሻራ
እልፍ ጉዳይ በአንድ መተግበሪያ
ከ onelink.to/75zfa5 አውርደው ይሞክሩት
(ኢትዮ ቴሌኮም)
#አቢሲንያ_ባንክ
ጊዜ ገና ብዙ ያሳየናል!
አፖሎን ይበልጥ ተመራጭ የሚያደርገው የጣት አሻራዎን በመጠቀም የባንክ ሒሳብዎን ደህንነት አስተማማኝ ማድረግ ማስቻሉ ነው።
መተግበሪያውን ለማውረድ ሊንኩን ይጠቀሙ።
https://apollo.bankofabyssinia.com/download-apollo
#Apollodigitalproduct #AbyssiniaDigital #Abyssiniabank #poweredbybankofabyssinia #BankofAbyssinia #የሁሉም_ምርጫ #The_Choice_For_all
የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ Telegram: https://t.iss.one/apollodigitalproduct
ጊዜ ገና ብዙ ያሳየናል!
አፖሎን ይበልጥ ተመራጭ የሚያደርገው የጣት አሻራዎን በመጠቀም የባንክ ሒሳብዎን ደህንነት አስተማማኝ ማድረግ ማስቻሉ ነው።
መተግበሪያውን ለማውረድ ሊንኩን ይጠቀሙ።
https://apollo.bankofabyssinia.com/download-apollo
#Apollodigitalproduct #AbyssiniaDigital #Abyssiniabank #poweredbybankofabyssinia #BankofAbyssinia #የሁሉም_ምርጫ #The_Choice_For_all
የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ Telegram: https://t.iss.one/apollodigitalproduct
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#NewsAlert
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በውግዘት የተለዩ 17 "የቀድሞ" አባቶች ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በተገኙበት በተደረሰው ስምምነት መሰረት 10ሩን የስምምነት ነጥቦች መቀበልላቸውን የሚገልጽ ደብዳቤ ለቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ለብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) አስገብተዋል ሲል የቤተክርስቲያኒቱ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ አስታውቋል።
ደብዳቤውን ያስገቡት 17 ሲሆኑ አንዱ ወደ ጸበል መሄዳቸውን ገልጸው ደብዳቤአቸውን በተወካይ አስገብተዋል።
በጥቅሉ ደብዳቤ ያስገቡት18 ሲሆኑ ቀሪዎቹ 6 የቀድሞ አባቶች በህመም ምክንያት እንዳልተገኙ በዛሬው ዕለት የተገኙት የቀድሞ አባቶች ገልጸው በቅርብ ጊዜ ቀሪዎቹ ግለሰቦች ማመልከቻቸውን ይዘው እንደሚመጡ አስረድተዋል ነው ያለው።
መምሪያው ፥ " በቪዲዮ የይቅርታ መልዕክት እንዲያስተላልፉ እድል እንዲሰጣቸው የተደረገ ቢሆንም ግለሰቦቹ አልተቀበሉትም " ሲል ገልጿል።
@tikvahethiopia
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በውግዘት የተለዩ 17 "የቀድሞ" አባቶች ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በተገኙበት በተደረሰው ስምምነት መሰረት 10ሩን የስምምነት ነጥቦች መቀበልላቸውን የሚገልጽ ደብዳቤ ለቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ለብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) አስገብተዋል ሲል የቤተክርስቲያኒቱ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ አስታውቋል።
ደብዳቤውን ያስገቡት 17 ሲሆኑ አንዱ ወደ ጸበል መሄዳቸውን ገልጸው ደብዳቤአቸውን በተወካይ አስገብተዋል።
በጥቅሉ ደብዳቤ ያስገቡት18 ሲሆኑ ቀሪዎቹ 6 የቀድሞ አባቶች በህመም ምክንያት እንዳልተገኙ በዛሬው ዕለት የተገኙት የቀድሞ አባቶች ገልጸው በቅርብ ጊዜ ቀሪዎቹ ግለሰቦች ማመልከቻቸውን ይዘው እንደሚመጡ አስረድተዋል ነው ያለው።
መምሪያው ፥ " በቪዲዮ የይቅርታ መልዕክት እንዲያስተላልፉ እድል እንዲሰጣቸው የተደረገ ቢሆንም ግለሰቦቹ አልተቀበሉትም " ሲል ገልጿል።
@tikvahethiopia
#እንድታውቁት
" #አስቸኳይ የፓስፖርት አገልግሎት ለጊዜው ተቋርጧል " - የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት
በኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ዋና መሥሪያ ቤት እንዲሁም በ11ዱ የክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቶች ሲሰጥ የነበረው “ አስቸኳይ ” የፓስፖርት አገልግሎት ለጊዜው መቋረጡን የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት አሳውቋል።
አገልግሎቱ ለምን ተቋረጠ ?
አገልግሎቱ የተቋረጠው #ከአቅም_በላይ የባለ ጉዳይ ፍሰት ከመፈጠሩ ጋር ተያይዞ መጠነ ሰፊ #የሠነድ_ማጭበርበሮች በመስተዋላቸው ነው።
ከዚህም በተጨማሪ ተገልጋዮች ሊገለገሉ ሌሊት ላይ በሚመጡበት ወቅት በተለያዩ ህገ-ወጥ ግለሰቦች የሚደርስባቸው እንግልትና ጉዳት በአገልግሎት አሰጣጥና በተገልጋዩ ላይ ተግዳሮት በመፍጠሩ ነው።
ስለሆነም የማስተናገድ አቅም እና ሌሎች ክፍተቶች እስከሚስተካከሉ ድረስ ይሰጥ የነበረው የ “ አስቸኳይ ” ፓስፖርት አገልግሎት ለጊዜው ተቋርጧል።
አስቸኳይ ጉዞ ያላቸው በምን ይስተናገዳሉ ?
ቀድሞ ይሰራበት በነበረው አሰራር መሰረት #አስቸኳይ_ጉዞ ያላቸው አገልግሎት ጠያቂዎች ማስረጃዎቻቸውን አቅርበው #በዋና_መስሪያ ቤት ብቻ ከመጋቢት 20 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ይስተናገዳሉ።
ማሳሰቢያ ፦ ተገልጋዮች ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ከህገወጥ ደላሎች እንዲጠነቀቁ ማሳሰቢያ ተላልፏል።
የመደበኛ ፓስፖርትን በተመለከተስ ?
የመደበኛ ፓስፖርት ተገልጋዮች ቀድሞ በነበረው ሂደት መስተናገድ #ይቀጥላሉ።
ምንጭ፦ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት
@tikvahethiopia
" #አስቸኳይ የፓስፖርት አገልግሎት ለጊዜው ተቋርጧል " - የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት
በኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ዋና መሥሪያ ቤት እንዲሁም በ11ዱ የክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቶች ሲሰጥ የነበረው “ አስቸኳይ ” የፓስፖርት አገልግሎት ለጊዜው መቋረጡን የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት አሳውቋል።
አገልግሎቱ ለምን ተቋረጠ ?
አገልግሎቱ የተቋረጠው #ከአቅም_በላይ የባለ ጉዳይ ፍሰት ከመፈጠሩ ጋር ተያይዞ መጠነ ሰፊ #የሠነድ_ማጭበርበሮች በመስተዋላቸው ነው።
ከዚህም በተጨማሪ ተገልጋዮች ሊገለገሉ ሌሊት ላይ በሚመጡበት ወቅት በተለያዩ ህገ-ወጥ ግለሰቦች የሚደርስባቸው እንግልትና ጉዳት በአገልግሎት አሰጣጥና በተገልጋዩ ላይ ተግዳሮት በመፍጠሩ ነው።
ስለሆነም የማስተናገድ አቅም እና ሌሎች ክፍተቶች እስከሚስተካከሉ ድረስ ይሰጥ የነበረው የ “ አስቸኳይ ” ፓስፖርት አገልግሎት ለጊዜው ተቋርጧል።
አስቸኳይ ጉዞ ያላቸው በምን ይስተናገዳሉ ?
ቀድሞ ይሰራበት በነበረው አሰራር መሰረት #አስቸኳይ_ጉዞ ያላቸው አገልግሎት ጠያቂዎች ማስረጃዎቻቸውን አቅርበው #በዋና_መስሪያ ቤት ብቻ ከመጋቢት 20 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ይስተናገዳሉ።
ማሳሰቢያ ፦ ተገልጋዮች ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ከህገወጥ ደላሎች እንዲጠነቀቁ ማሳሰቢያ ተላልፏል።
የመደበኛ ፓስፖርትን በተመለከተስ ?
የመደበኛ ፓስፖርት ተገልጋዮች ቀድሞ በነበረው ሂደት መስተናገድ #ይቀጥላሉ።
ምንጭ፦ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት
@tikvahethiopia