ኦነግ 600 የሚሆኑ አባላቶቹ በመንግስት እንደታሰሩበት አስታወቀ!
የኦሮሞ ነፃነት ግንባር በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ እየሰጠ ይገኛል፤ ኦነግ በመግለጫው 600 የሚሆኑ አባላቶቹ በመንግስት መታሰራቸውን አስታውቋል።
ኦነግ በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ብንወስንም የድርጅታችን አመራሮች እና አባላትን ማሰር እና ማጠልሸት እየተሰራ ነው ብሏል።
በኦነግ እና በሕወሓት መካከል አለ እየተባለ የሚወራው ግንኙነት ፍፁም ሀሰትና የሁለቱ ድርጅቶች ግንኙነት የጦርነት ግንኙነት ነው ሲልም ገልጿል።
ከዚህ በተጨማሪ ኦነግ በርካታ አባላት ስላሉን 100 በመቶ ሰላማዊ ትግሉን ተቀብለው ይንቀሳቀሳሉ የሚል ሙሉ እምነት የለንም ሲል መናገሩን አዲስ ማለዳ ዘግቧል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የኦሮሞ ነፃነት ግንባር በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ እየሰጠ ይገኛል፤ ኦነግ በመግለጫው 600 የሚሆኑ አባላቶቹ በመንግስት መታሰራቸውን አስታውቋል።
ኦነግ በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ብንወስንም የድርጅታችን አመራሮች እና አባላትን ማሰር እና ማጠልሸት እየተሰራ ነው ብሏል።
በኦነግ እና በሕወሓት መካከል አለ እየተባለ የሚወራው ግንኙነት ፍፁም ሀሰትና የሁለቱ ድርጅቶች ግንኙነት የጦርነት ግንኙነት ነው ሲልም ገልጿል።
ከዚህ በተጨማሪ ኦነግ በርካታ አባላት ስላሉን 100 በመቶ ሰላማዊ ትግሉን ተቀብለው ይንቀሳቀሳሉ የሚል ሙሉ እምነት የለንም ሲል መናገሩን አዲስ ማለዳ ዘግቧል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ዛሬ ከአዲስ ዘመን ወደ ጎንደር በሚወስደውና ቋላ ዮሐንስ ከሚባለው ዳገታማ ሥፍራ ላይ በናዳ ምክንያት መንገዱ ተዘግቶ ነበር፤ ይህ መንገድ በአሁን ሰዓት ለተሽከርካሪ ክፍት መደረጉን ከአማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት የተገኘው መረጃ ያሳያል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#UPDATE
በወላይታ ዞን በተለይም በተከሰተው ሁከት በትንሹ የ8 ሰዎች ህይወት ማለፉን አል ዐይን ዘግቧል።
ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ አንድ የዞኑ ባለስልጣን እንዳረጋገጡት በሶዶ ከተማ ትናንት ለተቃውሞ አደባባይ በወጡ ሰልፈኞ ላይ በፀጥታ ሀይሎች በተወሰደ እርምጃ የ4 ሰዎች ህይወት አልፏል።
በተመሳሳይ በቦዲቲ ከተማ 4 ሰዎች መገደላቸውን ተናግረዋል።
ከሞቱት በተጨማሪ በርካታ ሰዎች ጉዳት ደርሶባቸው ሆስፒታል መግባታቸውንም ገልፀዋል።
በደቡብ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ በተሰጠ መግለጫ በተፈጠረው ሁከት አንድ ሰው ብቻ እንደተገደለ ነው የተገለፀው #AlAin
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በወላይታ ዞን በተለይም በተከሰተው ሁከት በትንሹ የ8 ሰዎች ህይወት ማለፉን አል ዐይን ዘግቧል።
ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ አንድ የዞኑ ባለስልጣን እንዳረጋገጡት በሶዶ ከተማ ትናንት ለተቃውሞ አደባባይ በወጡ ሰልፈኞ ላይ በፀጥታ ሀይሎች በተወሰደ እርምጃ የ4 ሰዎች ህይወት አልፏል።
በተመሳሳይ በቦዲቲ ከተማ 4 ሰዎች መገደላቸውን ተናግረዋል።
ከሞቱት በተጨማሪ በርካታ ሰዎች ጉዳት ደርሶባቸው ሆስፒታል መግባታቸውንም ገልፀዋል።
በደቡብ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ በተሰጠ መግለጫ በተፈጠረው ሁከት አንድ ሰው ብቻ እንደተገደለ ነው የተገለፀው #AlAin
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በወላይታ ሶዶ የዳታ ኢንተርኔት ተቋረጠ!
በወላይታ ሶዶ ከተማ የዳታ ኢንተርኔት አገልግሎት መቋረጡን የቲክቫህ ኢትዮጵያ ወላይታ ሶዶ አባላት አሳውቀዋል። እንደ አባላቶታችን መልዕክት ከሆነ አገልግሎቱ ከሰዓት ጀምሮ ነው የተቋረጠው።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በወላይታ ሶዶ ከተማ የዳታ ኢንተርኔት አገልግሎት መቋረጡን የቲክቫህ ኢትዮጵያ ወላይታ ሶዶ አባላት አሳውቀዋል። እንደ አባላቶታችን መልዕክት ከሆነ አገልግሎቱ ከሰዓት ጀምሮ ነው የተቋረጠው።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የትግራይ ምርጫ ከመስከረም 5-10 ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል!
በትግራይ ክልል የሚደረገው 6ኛው ክልላዊ ምርጫ እስካሁን የመጨረሻው የምርጫ ቀን ባይቆረጥለትም የትግራይ ምርጫ ኮሚሽን ምርጫው በመስከረም ወር (ከመስከረም 5 - መስከረም 10) ባሉት ቀናት ለማድረግ #እንደታሰበ ለኤስ ቢኤስ ሬድዮ አስታውቋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በትግራይ ክልል የሚደረገው 6ኛው ክልላዊ ምርጫ እስካሁን የመጨረሻው የምርጫ ቀን ባይቆረጥለትም የትግራይ ምርጫ ኮሚሽን ምርጫው በመስከረም ወር (ከመስከረም 5 - መስከረም 10) ባሉት ቀናት ለማድረግ #እንደታሰበ ለኤስ ቢኤስ ሬድዮ አስታውቋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#DrLiaTadesse
'ቲክ ቶክ' በኢትዮጵያ ለኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ምርመራ የሚያገለግሉ 100 ሺህ የምርመራ ኪቶችን ድጋፍ ማድረጉን የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ በይፋዊ የትዊተር ገፃቸው አሳውቀዋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
'ቲክ ቶክ' በኢትዮጵያ ለኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ምርመራ የሚያገለግሉ 100 ሺህ የምርመራ ኪቶችን ድጋፍ ማድረጉን የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ በይፋዊ የትዊተር ገፃቸው አሳውቀዋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በኢትዮጵያ ተጨማሪ 773 ሰዎች በኮቪድ-19 ተያዙ!
ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 11,039 የላብራቶሪ ምርመራ 773 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ሲረጋገጥ የ13 ሰዎች ህይወት አልፏል። በተጨማሪ በትላንትናው ዕለት 205 ሰዎች አገግመዋል።
በአጠቃላይ በሀገራችን በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች 23,591 የደረሱ ሲሆን የሟቾች ቁጥር 420 ደርሷል ፤ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች 10,411 ናቸው።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 11,039 የላብራቶሪ ምርመራ 773 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ሲረጋገጥ የ13 ሰዎች ህይወት አልፏል። በተጨማሪ በትላንትናው ዕለት 205 ሰዎች አገግመዋል።
በአጠቃላይ በሀገራችን በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች 23,591 የደረሱ ሲሆን የሟቾች ቁጥር 420 ደርሷል ፤ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች 10,411 ናቸው።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ነሃሴ 4/2012 ዓ/ም አጫጭር መረጃዎች፦
ባለፉት 24 ሰዓት በኦሮሚያ ክልል ከተደረገው 1,387 የላብራቶሪ ምርመራ 64 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። የአንድ ሰው ህይወት አልፏል።
ከ64ቱ መካከል ፦
- 13 ከሰበታ
- 12 ከቢሾፍቱ
- 7 ከባቱ
- 6 ከገላን
- 6 ከሞጆ
- 4 ከአዳማ
- 4 ከነቀምቴ ይገኙበተል።
#Afar
በአፋር ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 423 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 63 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። አጠቃላይ በክልል በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 380 ደርሰዋል።
#TIGRAY
በትግራይ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 472 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 51 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል፤ የ1 ሰው ህይወት አልፏል፤ ትላንት 33 ሰዎች አገግመዋል።
አጠቃላይ በትግራይ ፦
- 1,137 በቫይረሱ የተያዙ
- 6 ሞት
- 636 ያገገሙ
#BenishangulGumuz
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ከተደረገው 235 የላብራቶሪ ምርመራ 27 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያቸው ተረጋግጧል።
- 13 ከዛይ ወረዳ
- 5 ከካማሽ ከተማ
- 1 ከዳምቤ ወረዳ
- 6 ከአሶሳ ከተማ
- 1 ከመንጌ ወረዳ
#HARARI
በሐረሪ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት የ2 ሰው ህይወት አልፏል ፤ ከ208 የላብራቶሪ ምርመራ ደግሞ 28 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።
አጠቃላይ በሐረሪ ክልል፦
- 346 በቫይረሱ የተያዙ
- 11 ሞት
- 78 ያገገሙ
#DireDwa
በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ባለፉት 24 ሰዓት 182 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 27 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። 19 ከጅቡቲ ተመላሾች በለይቶ ማቆያ ያሉ፤ 8 ከማህበረሰቡ በተወሰደ ናሙና የተገኙ ናቸው።
#AddisAbaba
በአዲስ አበባ ባለፉት 24 ሰዓት 446 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል፤ የ10 ሰዎች ህይወት አልፏል (5 ሰዎች ከአስክሬን ምርመራ እና 5 ሰዎች ከጤና ተቋም)
* እስካሁን በአዲስ አበባ የተመዘገበው አጠቃላይ የኮሮና ቫይረስ ኬዝ 15,834 ደርሷል።
#AMHARA
ባለፉት 24 ሰዓት በአማራ ክልል ከተደረገው 3,314 የላብራቶሪ ምርመራ 45 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል
በቫይረሱ ከተያዙት መካከል ፦
- 17 ከባህር ዳር
- 3 ከሰ/ወሎ ዞን
- 8 ከምስ/ጎጃም ዞን
- 6 ከኦሮሞ ብ/ሰብ ዞን
- 5 ከሰ/ሸዋ ዞን ይገኙበታል።
#SNNPRS
- በደቡብ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 622 የላብራቶሪ ምርመራ ሁለት ሰዎች (1 ከጋሞና 1 ከኮንሶ ዞኖች) በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።
#SIDAMA
ባለፉት 24 ሰዓት 547 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 18 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል፤ እንዲሁም የአንድ ሰው ህይወት አልፏል።
አጠቃላይ በሲዳማ ፦
- 448 አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ
- 7 ህይወታቸው ያለፈ
- 109 ያገገሙ
ተጨማሪ : telegra.ph/TikvahEthiopia-08-10
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ባለፉት 24 ሰዓት በኦሮሚያ ክልል ከተደረገው 1,387 የላብራቶሪ ምርመራ 64 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። የአንድ ሰው ህይወት አልፏል።
ከ64ቱ መካከል ፦
- 13 ከሰበታ
- 12 ከቢሾፍቱ
- 7 ከባቱ
- 6 ከገላን
- 6 ከሞጆ
- 4 ከአዳማ
- 4 ከነቀምቴ ይገኙበተል።
#Afar
በአፋር ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 423 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 63 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። አጠቃላይ በክልል በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 380 ደርሰዋል።
#TIGRAY
በትግራይ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 472 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 51 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል፤ የ1 ሰው ህይወት አልፏል፤ ትላንት 33 ሰዎች አገግመዋል።
አጠቃላይ በትግራይ ፦
- 1,137 በቫይረሱ የተያዙ
- 6 ሞት
- 636 ያገገሙ
#BenishangulGumuz
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ከተደረገው 235 የላብራቶሪ ምርመራ 27 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያቸው ተረጋግጧል።
- 13 ከዛይ ወረዳ
- 5 ከካማሽ ከተማ
- 1 ከዳምቤ ወረዳ
- 6 ከአሶሳ ከተማ
- 1 ከመንጌ ወረዳ
#HARARI
በሐረሪ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት የ2 ሰው ህይወት አልፏል ፤ ከ208 የላብራቶሪ ምርመራ ደግሞ 28 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።
አጠቃላይ በሐረሪ ክልል፦
- 346 በቫይረሱ የተያዙ
- 11 ሞት
- 78 ያገገሙ
#DireDwa
በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ባለፉት 24 ሰዓት 182 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 27 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። 19 ከጅቡቲ ተመላሾች በለይቶ ማቆያ ያሉ፤ 8 ከማህበረሰቡ በተወሰደ ናሙና የተገኙ ናቸው።
#AddisAbaba
በአዲስ አበባ ባለፉት 24 ሰዓት 446 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል፤ የ10 ሰዎች ህይወት አልፏል (5 ሰዎች ከአስክሬን ምርመራ እና 5 ሰዎች ከጤና ተቋም)
* እስካሁን በአዲስ አበባ የተመዘገበው አጠቃላይ የኮሮና ቫይረስ ኬዝ 15,834 ደርሷል።
#AMHARA
ባለፉት 24 ሰዓት በአማራ ክልል ከተደረገው 3,314 የላብራቶሪ ምርመራ 45 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል
በቫይረሱ ከተያዙት መካከል ፦
- 17 ከባህር ዳር
- 3 ከሰ/ወሎ ዞን
- 8 ከምስ/ጎጃም ዞን
- 6 ከኦሮሞ ብ/ሰብ ዞን
- 5 ከሰ/ሸዋ ዞን ይገኙበታል።
#SNNPRS
- በደቡብ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 622 የላብራቶሪ ምርመራ ሁለት ሰዎች (1 ከጋሞና 1 ከኮንሶ ዞኖች) በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።
#SIDAMA
ባለፉት 24 ሰዓት 547 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 18 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል፤ እንዲሁም የአንድ ሰው ህይወት አልፏል።
አጠቃላይ በሲዳማ ፦
- 448 አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ
- 7 ህይወታቸው ያለፈ
- 109 ያገገሙ
ተጨማሪ : telegra.ph/TikvahEthiopia-08-10
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ኦነግ 600 የሚሆኑ አባላቶቹ በመንግስት እንደታሰሩበት አስታወቀ! የኦሮሞ ነፃነት ግንባር በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ እየሰጠ ይገኛል፤ ኦነግ በመግለጫው 600 የሚሆኑ አባላቶቹ በመንግስት መታሰራቸውን አስታውቋል። ኦነግ በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ብንወስንም የድርጅታችን አመራሮች እና አባላትን ማሰር እና ማጠልሸት እየተሰራ ነው ብሏል። በኦነግ እና በሕወሓት መካከል አለ እየተባለ የሚወራው ግንኙነት…
#UPDATE
የኦነግ ሊቀመንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ ዛሬ የተሰጠው መግለጫ የፓርቲያቸው እውቅና እንደሌለውና እርሳቸውም ስለ መግለጫው መረጃ እንደሌላቸው #ለቢቢሲ ተናግረዋል።
አቶ ዳውድ ፥ ስለዚህ መግለጫ ምንም የማውቀው ነገር የለም ፤ አንጀንዳውም ሆነ አላማው ምን እንደሆነ አይገባኝም፤ ምክትሌም ስለ መግለጫው አላውቅም ብሎ ዛሬ ግን በመግለጫው ላይ ተገኝቷል፤ በአጠቃላይ የማምታት ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል።
የኦነግ ሊቀ መንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ በቅርቡ ከመኖሪያ ቤታቸው እንዳይወጡ በተደረጉበት ሰዓት በምክትላቸው አቶ አራርሶ ቢቂላ የተመራው ስብሰባ ብዙ የተምታታ ነገር አለበት ብለዋል፤ ጉዳዩን የፓርቲው የህግና ቁጥጥር ኮሚቴ እያጣራ እንደሆነም ተናግረዋል።
አቶ ዳውድ በፓርቲያቸው ውስጥ እየተፈጠረ ላለው ልዩነት ኦነግ በመንግስት ኢላማ ተደርጓል በሚል መንግስትን ተጠያቂ አድርገዋል ሲል ቢቢሲ በዛሬ ምሽት ስርጭቱ ዘግቧል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የኦነግ ሊቀመንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ ዛሬ የተሰጠው መግለጫ የፓርቲያቸው እውቅና እንደሌለውና እርሳቸውም ስለ መግለጫው መረጃ እንደሌላቸው #ለቢቢሲ ተናግረዋል።
አቶ ዳውድ ፥ ስለዚህ መግለጫ ምንም የማውቀው ነገር የለም ፤ አንጀንዳውም ሆነ አላማው ምን እንደሆነ አይገባኝም፤ ምክትሌም ስለ መግለጫው አላውቅም ብሎ ዛሬ ግን በመግለጫው ላይ ተገኝቷል፤ በአጠቃላይ የማምታት ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል።
የኦነግ ሊቀ መንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ በቅርቡ ከመኖሪያ ቤታቸው እንዳይወጡ በተደረጉበት ሰዓት በምክትላቸው አቶ አራርሶ ቢቂላ የተመራው ስብሰባ ብዙ የተምታታ ነገር አለበት ብለዋል፤ ጉዳዩን የፓርቲው የህግና ቁጥጥር ኮሚቴ እያጣራ እንደሆነም ተናግረዋል።
አቶ ዳውድ በፓርቲያቸው ውስጥ እየተፈጠረ ላለው ልዩነት ኦነግ በመንግስት ኢላማ ተደርጓል በሚል መንግስትን ተጠያቂ አድርገዋል ሲል ቢቢሲ በዛሬ ምሽት ስርጭቱ ዘግቧል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በኢትዮጵያና ጎረቤት ሀገራት የኮቪድ-19 ስርጭት!
በኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ ሱማሊያ፣ ጅቡቲ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን እና ኤርትራ በአጠቃላይ 73,801 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ተይዘዋል።
ከኤርትራ ውጭ በ6ቱ ሀገራት ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተገናኘ የ1,823 ሰዎች ህይወት ማለፉ ተረጋግጧል ፤ በአጠቃላይ 38,426 ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል።
በኢትዮጵያና በጎረቤት ሀገራት ያለውን የኮቪድ-19 ወቅታዊ መረጃ ከ CARD ጋር በመተባበር ባዘጋጀነው ምስል ከላይ መመልከት ትችላላችሁ።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ ሱማሊያ፣ ጅቡቲ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን እና ኤርትራ በአጠቃላይ 73,801 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ተይዘዋል።
ከኤርትራ ውጭ በ6ቱ ሀገራት ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተገናኘ የ1,823 ሰዎች ህይወት ማለፉ ተረጋግጧል ፤ በአጠቃላይ 38,426 ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል።
በኢትዮጵያና በጎረቤት ሀገራት ያለውን የኮቪድ-19 ወቅታዊ መረጃ ከ CARD ጋር በመተባበር ባዘጋጀነው ምስል ከላይ መመልከት ትችላላችሁ።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#NewsAlert
ሩሲያ በዓለማችን የመጀመሪያውን የኮሮና ቫይረስ ክትባት አዘጋጅታ መጨረሷን በፕሬዘዳንቷ ቭላድሚር ፑቲን በኩል ይፋ አድርጋለች።
ፕሬዘዳንት ፑቲን በክትባት ዝግጅት ላይ መታለፍ ያለባቸው ደረጃዎች ተፈትኖ ያለፈና ውጤታማ እንደሆነ ተናግረዋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ሩሲያ በዓለማችን የመጀመሪያውን የኮሮና ቫይረስ ክትባት አዘጋጅታ መጨረሷን በፕሬዘዳንቷ ቭላድሚር ፑቲን በኩል ይፋ አድርጋለች።
ፕሬዘዳንት ፑቲን በክትባት ዝግጅት ላይ መታለፍ ያለባቸው ደረጃዎች ተፈትኖ ያለፈና ውጤታማ እንደሆነ ተናግረዋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#UPDATE
ሩሲያ አዘጋጅታ የጨረሰችው ክትባት በሞስኮ ጋመሌያ ኢንስቲቱዩት የተዘጋጀ ነው። ይኸው ክትባት ዛሬ ከሀገሪቱ ጤና ሚኒስቴር ማረጋገጫን አግኝቷል።
የሩሲያው ፕሬዘዳንት ሀገራቸው በቅርብ ጊዜያት የኮቪድ-19 ክትባቱን በብዛት ማምረት እንደምትጀምር አሳውቀዋል።
ፑቲን የመጀመሪያውን የኮሮና ቫይረስ ክትባት ልጃቸው መውሰዷን መናገራቸውን የኢንደፔንዳት እና አርቲ ዘገባ ያመለክታል።
ልጃቸው ክትባቱን ከወሰደች በኋላ መጠነኛ ሙቀን እንደነበራት የገለፁቱት ፕሬዚዳንቱ ከቆይታ በኋላ ግን መጠናኛ ሙቀቱ መጥፋቱን ተናግረዋል - #ኤፍቢሲ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ሩሲያ አዘጋጅታ የጨረሰችው ክትባት በሞስኮ ጋመሌያ ኢንስቲቱዩት የተዘጋጀ ነው። ይኸው ክትባት ዛሬ ከሀገሪቱ ጤና ሚኒስቴር ማረጋገጫን አግኝቷል።
የሩሲያው ፕሬዘዳንት ሀገራቸው በቅርብ ጊዜያት የኮቪድ-19 ክትባቱን በብዛት ማምረት እንደምትጀምር አሳውቀዋል።
ፑቲን የመጀመሪያውን የኮሮና ቫይረስ ክትባት ልጃቸው መውሰዷን መናገራቸውን የኢንደፔንዳት እና አርቲ ዘገባ ያመለክታል።
ልጃቸው ክትባቱን ከወሰደች በኋላ መጠነኛ ሙቀን እንደነበራት የገለፁቱት ፕሬዚዳንቱ ከቆይታ በኋላ ግን መጠናኛ ሙቀቱ መጥፋቱን ተናግረዋል - #ኤፍቢሲ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#NewZealand
በኒው ዚላንድ ከ102 ቀን በኃላ የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) የማህበረሰብ ስርጭት ተገኘ።
ስካይ ኒውስ የሀገሪቱን ጠ/ሚ ጀሲንዳ አርደንን ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው በደቡብ ኦውክላንድ 4 ሰዎች ከአንድ ቤተሰብ በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።
የቫይረሱ ስርጭት አሁን ካለበት እንዳይስፋፋ ትልቋ የኒው ዚላንድ ከተማ ኦውክላድ የእቅስቃሴ ገደብ ተጥሎባታል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በኒው ዚላንድ ከ102 ቀን በኃላ የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) የማህበረሰብ ስርጭት ተገኘ።
ስካይ ኒውስ የሀገሪቱን ጠ/ሚ ጀሲንዳ አርደንን ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው በደቡብ ኦውክላንድ 4 ሰዎች ከአንድ ቤተሰብ በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።
የቫይረሱ ስርጭት አሁን ካለበት እንዳይስፋፋ ትልቋ የኒው ዚላንድ ከተማ ኦውክላድ የእቅስቃሴ ገደብ ተጥሎባታል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#WOLAITA
በወላይታ ዞን በተከሰተው አለመረጋጋት በትንሹ ከ10 በላይ ሰዎች ሞተዋል። የቲክቫህ ኢትዮጵያ ኦቶና ሆስፒታል አባላት እንደገለፁት ደግሞ እስካሁን ባሉበት ሆስፒታል ብቻ ከ80 በላይ ሰዎች ተጎድተው ህክምና እየተደረገላቸው ይገኛል።
ዛሬም በወላይታ ሶዶ እንዲሁም በሌሎችም ከተሞች 'የዳታ ኢንተርኔት አገልግሎት' እንደተዘጋ ነው። ከበርካታ የወላይታ ዞን የቲክቫህ አባላት ጋር መገናኘት አልቻልንም።
የወላይታ ሶዶ፣ አረካ፣ ቦዲቲ ቲክቫህ አባላት በስልክ ደውለው ያለውን ሁኔታ ያሳወቁ ሲሆን አሁንም የትንራስፖርት ፣ የንግድ እንቅስቃሴ የለም ፤ አንዳንድ ቦታ ውስጥ ለውስጥ አልፎ አልፎ ሱቆች ክፍት ናቸው ፣ ባንክ ቤቶች ዛሬም እንደተዘጉ ናቸው ፣ የሰዎች እንቅስቃሴ ግን ይታያል ካለፈው ቀን የተሻለ መረጋጋት አለ ብለዋል።
የየከተማው ነዋሪ በተፈጠረው ክስተት ክፉኛ ልቡ ተሰብሯል ፤ በዚህ ምክንያት እንደዋዛ ህይወታቸው በተቀጠፈውና በተጎዱት ወጣቶች ምክንያትም መሪር ሀዘን ላይ ይገኛል ብለዋል።
ከሶስቱም ከተሞች (ወ/ሶዶ፣አረካ፣ ቦዲቲ) የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት ማረጋገጥ እንደቻልነው አሁንም ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የፀጥታ አስከባሪዎች መከላከያ ሰራዊትና የደቡብ ክልል ልዩ ኃይል እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በወላይታ ዞን በተከሰተው አለመረጋጋት በትንሹ ከ10 በላይ ሰዎች ሞተዋል። የቲክቫህ ኢትዮጵያ ኦቶና ሆስፒታል አባላት እንደገለፁት ደግሞ እስካሁን ባሉበት ሆስፒታል ብቻ ከ80 በላይ ሰዎች ተጎድተው ህክምና እየተደረገላቸው ይገኛል።
ዛሬም በወላይታ ሶዶ እንዲሁም በሌሎችም ከተሞች 'የዳታ ኢንተርኔት አገልግሎት' እንደተዘጋ ነው። ከበርካታ የወላይታ ዞን የቲክቫህ አባላት ጋር መገናኘት አልቻልንም።
የወላይታ ሶዶ፣ አረካ፣ ቦዲቲ ቲክቫህ አባላት በስልክ ደውለው ያለውን ሁኔታ ያሳወቁ ሲሆን አሁንም የትንራስፖርት ፣ የንግድ እንቅስቃሴ የለም ፤ አንዳንድ ቦታ ውስጥ ለውስጥ አልፎ አልፎ ሱቆች ክፍት ናቸው ፣ ባንክ ቤቶች ዛሬም እንደተዘጉ ናቸው ፣ የሰዎች እንቅስቃሴ ግን ይታያል ካለፈው ቀን የተሻለ መረጋጋት አለ ብለዋል።
የየከተማው ነዋሪ በተፈጠረው ክስተት ክፉኛ ልቡ ተሰብሯል ፤ በዚህ ምክንያት እንደዋዛ ህይወታቸው በተቀጠፈውና በተጎዱት ወጣቶች ምክንያትም መሪር ሀዘን ላይ ይገኛል ብለዋል።
ከሶስቱም ከተሞች (ወ/ሶዶ፣አረካ፣ ቦዲቲ) የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት ማረጋገጥ እንደቻልነው አሁንም ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የፀጥታ አስከባሪዎች መከላከያ ሰራዊትና የደቡብ ክልል ልዩ ኃይል እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia