TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የፖሊስ የዘፈቀደ እስር በአስቸኳይ ሊቆም እና የታሰሩትም ሊለቀቁ ይገባል!

(የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን)

በዛሬው እለት በአዲስ አበባ ከተማ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ሳያደርጉ የተገኙ ሰዎች በፖሊስ እየታሰሩ ከመሆናቸው ጋር በተያያዘ በሚዲያዎች የወጡ ዘገባዎችንና ለኮሚሽኑ የቀረቡ አቤቱታዎችን ተከትሎ የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ዶክተር ዳንኤል በቀለ የሚከተለውን ብለዋል ፦

የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ማድረግ የኮቪድ 19 ስርጭትን ለመከላከል አስፈላጊ የጤና መመርያ ሲሆን ሕብረተሰቡም ሊከተለው የሚገባ ነው፡፡

በእርግጥም የአስቸኳይ ጊዜ ደንቡ ማንኛውም ሰው እንደ ገበያ ቦታዎች፥ ሱቆች ፣ የትራንስፖርት አገልግሎቶች ባሉ የሕዝብ አገልግሎት መስጫ ቦታዎች እና በሌሎች ህዝብ በሚበዛባቸውና የአካል መራራቅን መጠበቅ በማይቻልባቸው አካባቢዎች የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ማድረግ እንዳለበት ይደነግጋል፡፡

ከዚህ ውጪ ግን በየትኛውም ቦታ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ሳያደርጉ የተገኙ ሰዎች ላይ ሁሉ የሚደረግ የዘፈቀደ እስር ከህግ ውጭ ከመሆኑም በላይ ለነገሩ ሁኔታ ተመጣጣኝ ያልሆነ እርምጃ እና የታለመለትን አላማ የሚቃረን በመሆኑ በአስቸኳይ ሊቆም ይገባል፣ በዚህ ሁኔታ የታሰሩ ሰዎችም በአስቸኳይ ሊፈቱ ይገባል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#DrRashidAman

በትላንትናው ዕለት በኬንያ 4 ተጨማሪ ሰዎች በኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ምክንያት መሞታቸውን የኬንያ ጤና ሚኒስቴር በሰጠው መግለጫ አሳውቋል ፤ አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር 40 ደርሷል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የፖሊስ የዘፈቀደ እስር በአስቸኳይ ሊቆም እና የታሰሩትም ሊለቀቁ ይገባል! (የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን) በዛሬው እለት በአዲስ አበባ ከተማ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ሳያደርጉ የተገኙ ሰዎች በፖሊስ እየታሰሩ ከመሆናቸው ጋር በተያያዘ በሚዲያዎች የወጡ ዘገባዎችንና ለኮሚሽኑ የቀረቡ አቤቱታዎችን ተከትሎ የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ዶክተር ዳንኤል በቀለ የሚከተለውን ብለዋል ፦ …
ከ1 ሺህ 300 በላይ ሰዎች ታስረዋል!

(በኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8)

በተለያዩ የአዲስ አበባ ከተማ አካባቢዎች የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በተላላፉ ከ1 ሺህ 300 በላይ ሰዎች የአፍና የአፍንጫ መከለያ ባለመጠቀማቸው ለእስር መዳረጋቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ገልጿል፡፡

የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ የሆኑት ኮማንደር ፋሲካ ፈንታ ለኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 እንደተናገሩት የታሳሩ ሰዎች ምን እርምጃ ይወሰድባቸዋል የሚለውን በቀጣይ ማብራሪያ እንሰጣለን ብለዋል፡፡

ህግ አስከባሪ የፖሊስ አባላት እራሳቸው የፊት መሸፈኛ ሳያደርጉ እና ርቀታቸውን ሳይጠብቁ ሲንቀሳቀሱ ይስተዋላል ፣ ለምን ሆኑ ተብለው ከሬድዮ ጣቢያው የተጠየቁት ኮማንደር ፋሲካ ለእነሱም አንደ ህዝቡ የግንዛቤ ትምህርት ይሰጣል ተላልፎ የሚገኝ የፖሊስ አባል ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ እንወስዳለን ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

እየወሰድን ባለው እርምጃ ከህዝቡ #ድጋፍ እያገኘን ነው ፣ እየታሰሩ ያሉትም ብዙ ህዝብ ከሚበዛባቸው አካባቢዎች የተያዙ ናቸውም ብለዋል፡፡

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በኩባ...

በተለያዩ ሀገራት የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ወረርሽኝን ለመግታት በሚደረገው ጥረት የጤና ባለሞያዎቿን እየላከች እገዛ እያደረገች በምትገኘው #ኩባ በኮቪድ-19 ከተያዙ 1,804 ሰዎች መካከል 1,277 ሰዎች #አገግመዋል። በሀገሪቱ በቫይረሱ ምክንያት የሞቱ ሰዎች 77 ናቸው።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አጫጭር መረጃዎች ፦

- በሩሲያ ባለፉት 24 ሰዓት ብቻ 10,028 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን ተከትሎ አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 242,271 ደርሰዋል።

- በኢራን ባለፉት 24 ሰዓት 1,958 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል (ከሚያዚያ 2 በኃላ የተመዘገበ ከፍተኛ ኬዝ ነው) ፤ አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 112,725 ደርሷል።

- በቻይና ባለፉት 24 ሰዓት 7 ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል።

- በደቡብ ኮሪያ ባለፉት 24 ሰዓት 26 ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል፤ 1 ሰው ሞቷል።

- በስፔን ባለፉት 24 ሰዓት 184 ሰዎች መሞታቸው ሪፖርት ተደርጓል፤ አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር 27,104 ደርሷል።

- በዩናይትድ ኪንግደም ባለፉት 24 ሰዓት 494 ሰዎች መሞታቸው ሪፖርት ተደርጓል ፤ አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር 33,186 ደርሷል።

- ሊባኖስ ከዛሬ ምሽት ጀምሮ ለተከታታይ አምስት ቀናት ማንም ሰው ከቤቱ እንዳይወጣ ደንግጋለች - #BBC

- በአሜሪካ የሟቾች ቁጥር ከ83,000 በላይ ሆኗል።

- በኳታር ባለፉት 24 ሰዓት 1,390 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 26,539 ደርሷል።

- በሳዑዲ አረቢያ በ24 ሰዓት 1,905 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ሲያዙ 9 ሰዎች ሞተዋል።

- እስካሁን ኮቪድ-19 ያልተገኘባት አፍሪካዊቷ ሀገር #ሌሴቶ ዛሬ ለመጀመሪያ ጊዜ የኮሮና ቫይረስ በሀገሪቱ እንደተገኘ አሳውቃለች።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#DrFawziyaAbikar

በሱማሊያ ተጨማሪ 49 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋገጠ!

ባለፉት 24 ሰዓት በሱማሊያ ተጨማሪ 49 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥርም 1,219 ደርሷል።

በሌላ በኩል በትላንትናው ዕለት አራት (4) ሰዎች ከበሽታው ማገገማቸውን ተከትሎ አጠቃላይ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 130 ደርሷል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በደቡብ ሱዳን በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች 203 ደረሱ!

በደቡብ ሱዳን በዛሬው ዕለት የ108 የላብራቶሪ ምርመራ ውጤት ይፋ ተደርጓል ፤ ዘጠኝ (9) ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል ፤ ይህም አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎችን ቁጥር ወደ 203 ከፍ አድርጎታል።

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
COVID_19_Prevention_and_Control_Job_Position_selected_Applicant.pdf
8.5 MB
ከደቡብ ክልል ጤና ቢሮ !

የደቡብ ክልል ጤና ቢሮ የኮሮና ቫይረስ (COVID-19) ወረርሽኝ ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የሚደረገውን ጥረት የሚያግዙ የጤና የባለሙያ ቅጥር ለመፈጸም ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት (በPDF በምታገኙት) ደብዳቤ መሰረት እስከ ግንቦት 12/2012 ዓ.ም ድረስ በተደመደባችሁበት ዞንና ልዩ ወረዳ በአካል በመቅረብ ቅጥር እንድትፈፅሙ አሳስቧል።

#SHARE #ሼር

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#FicheChambalala

ፊቼ ጫምባላላ የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ስርጭትን ለመከላከል በአደባባይ እንዳይከበር የሲዳማ የሀገር ሽማግሌዎች ወስነዋል። የሲዳማ የሀገር ሽማግሌዎች/አያንቶዎች በዓሉ ግንቦት 12 እና 13 ተከብሮ እንዲውልም ቀን ቆርጠዋል።

ወረርሽኝ፣ ጦርነት እና ርሀብ እንዲሁም የታላቅ ሰው ህልፈት ሲከሰት ፊቼ ጫምበላላ በዓል በአደባባይ የማይከበር መሆኑ ታሪካዊ አመጣጥ ያለው መሆኑን የገለፁት አያንቶዎቹ በዓሉ የኮቪድ 19 ስርጭትን ለመከላከል ዘንድሮ አደባባይ እንዳይከበር ወስነዋል፡፡

በኮሮና ወረርሽኝ አማካኝነት ሊከሰት የሚችለውን ችግር ከግምት ውስጥ በማስገባት በታላቁ (ሶሬሳ) ጉዱማሌም ሆነ በወረዳ እና በቀበሌ ደረጃ በዓሉን በአደባባይ ማክበር የማይቻል እንደሆነም የሀገር ሽማግሌዎች ገልፀዋል።

#fbc
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#BorisJhonson

275 የጤና ባለሞያዎች ህይወታቸውን አጥተዋል!

በዩናይትድ ኪንግደም 275 የጤና ባለሙያዎች በኮሮና ቫይረስ (COVID-19) ምክንያት ህይወታቸው አልፏል። ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን ኮሮና ቫይረስ በዩናይትድ ኪንግደም 144 የጤና ባለሙያዎችንና 131 የማህበረሰብ ክብካቤ (ሶሻል ወርክ) ሰራተኞችን ህይወት እንደቀጠፈ ገልጸዋል - #AlAin

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#COVID19

የኢትዮጵያና የጎረቤት ሀገራት የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ወቅታዊ መረጃ ፦

- ሱዳን በቫይረሱ የተያዙ 1,818፣ ሞት 90፣ ያገገሙ 198

- ጅቡቲ በቫይረሱ የተያዙ 1,268፣ ሞት 3 ፣ ያገገሙ 900

- ሶማሊያ በቫይረሱ የተያዙ 1,219፣ ሞት 52 ፣ ያገገሙ 130

- ኬንያ በቫይረሱ የተያዙ 737፣ ሞት 40 ፣ ያገገሙ 281

- ኢትዮጵያ በቫይረሱ የተያዙ 263 ፣ ሞት 5 ፣ ያገገሙ 108

- ደቡብ ሱዳን በቫይረሱ የተያዙ 203 ፣ ሞት 0፣ ያገገሙ 2

- ኤርትራ በቫይረሱ የተያዙ 39 ፣ ሞት 0 ፣ ያገገሙ 38

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ውድ ቤተሰቦቻችን ከኮቪድ-19 በተጨማሪ ሀገራዊ ጉዳዮችን በ @tikvahethmagazine ታገኛላችሁ!

የስፖርት ወዳጆች ከሆናችሁም ስፖርታዊ ጉዳዮችን በ @tikvahethsport ማግኘት ትችላላችሁ!

ቲክቫህ ኢትዮጵያ!
@tikvahethmagazine @tikvahethsport
ሱዳን ውስጥ በአንድ ቀን የ10 ሰዎች ህይወት አለፈ!

የሱዳን ጤና ሚንስቴር ባወጣዉ መግለጫ ባለፉት 24 ሰዓት የ10 ሰዎች ህይወት ማለፉን አሳውቋል ፤ አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር 90 ደርሷል።

ከዚህ በተጨማሪ በኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) የተያዙ ሰዎች 1,818 ደርሰዋል ፤ በ24 ሰዓት ውስጥ 157 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።

በሌላ በኩል ትላንት ሃያ አምስት (25) ሰዎች በተደረገላቸው ህክምና ከበሽታው (ኮቪድ-19) አገግመዋል ፤ አጠቃላይ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች 198 ደርሰዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#UPDATE

በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት የተቋረጠው የቤተክርስቲያን አገልግሎት ጥንቃቄ በተሞላበት መንገድ እንዲቀጥል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን መወሰኑን #ኢቢሲ ዘገበ።

ብፅዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ እንደገለፁት በቤተክስትያኗ አጥቢያዎች የሚሰጠው አገልግሎት መቋረጡ በምዕምኑ መንፈሳዊ ህይወት ላይ ችግር ማስከተሉን አብራርተዋል፡፡

እናም ፍፁም ጥንቃቄ በተሞላበት መንገድ አገልግሎቱ እንዲቀጥል ሲኖዶሱ መወሰኑን ተናግረዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#WHO

የኮሮና ቫይረስ ከዓለማችን ላይ እስከወዲያኛው ላይወደገድ እንደሚችል የዓለም ጤና ድርጅት አስታውቋል።

የዓለም ጤና ድርጅት የድንገተኛ ህክምናዎች ዳይሬክተር ዶክተር ማይክ ረያን በትናንትናው እለት በሰጡት ማብራሪያ፥ ቫይረሱ የሚያበቃበትን ጊዜ መተንበይ ትክክል እይደለም ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

ሁላችንም የኮሮናቫይረስ በዓለም ማህበረሰብ ዘንድ ሌላኛው ወረርሽኝ ሆኖ እስከወዲያኛው ሊቆይ ይችላል የሚለውን ከግምት ማስገባት አለብን ያሉት ዶክተር ረያን፥ ቫይረሱ እስከወዲያኛው አብሮን ሊኖርም ይችላል ብለዋል - #BBC

#AlJazeera
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን!

ከግንቦት 4 - ግንቦት 6 ድረስ የተካሄደው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ አስመልክቶ ከቅዱስ ሲኖዶሱ የተሰጠ መግለጫ!

Via @tikvahethmagazine

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia