TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ከጀማ🔝

"እሁድ እለት የሆኑ ግለሰቦች የጅማ ህክምና ማዕከል ውስጥ ሁለት ኢንተርኖች (ሀኪሞች) ላይ #ድብደባ ካደረሱ በኻላ ከዛሬ 01/8/11 ጀምሮ ኢንተርኖች #የሥራ_ማቆም አድማ አድርገዋል። በመቀጠለም ከላይ ያለውን #የአቋም_መግለጫ አውጥተዋል።”

@tsegabwolde @tikvahethiopia
“ሰሞኑን በውጥረት ውስጥ የከረሙት አጣዬ ከተማ፣ ሞሉ ሜዳ፣ ይምልዎ፣ አላላ አማን ገበያ፣ አላላ ኩቢ ቢያ፣ እዝግዬ እና ሰንበቴ ከተማ ሰላም አየር መተንፈስ ጀምረዋል፡፡ የሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ የፌዴራል ልዩ ሃይል፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሀይማኖት አባቶች፣ የወረዳ አመራሮች፣ ቄሮዎች እና ህዝቡ በየደረጃው በመመካከር ችግሩን ለመፍታት እየተሰራ ነው፡፡ የተሽከርካሪ መንገዶች ተከፍተዋል፡፡ ከአጣዬ ከተማ እና አካባቢዋ በግጭቱ ምክኒያት የሸሹ ሰዎችን ወደ እየቤታቸው እየተመለሱ ነው፡፡ በማህበራዊ መዲያዎች የሚለቀቁ የሀሰት ወሬዎች ውሸት መሆናቸውን መላው ህብረተሰብ በመረዳት ተረጋግቶ የግል ስራውን እንዲሰራ መልዕክታችን ነው፡፡”

Via ጅሌ ጥሙጋ ወረዳ መ/ኮሚኒኬሽን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በአፋር ክልል አዋሽ አካባቢ ተጥልለው የሚገኙ ከመተሐራ አካባቢ የተፈናቀሉ ዜጎች ችግር ላይ ወድቀናል ብለዋል፡፡ የአማራና አርጎባ ብሄረሰብ ተወላጅ መሆናቸውን የገለጹት #ተፈናቃዮቹ ቤት ለቤት ጥቃት ስለመፈጸሙባቸው #እንደተፈናቀሉ ለDW ተናግረዋል፡፡ ብዛታቸው 748 ያህል ይሆናል፡፡ ተፈናቃዮቹ የተፈናቀሉት ከአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ምንጃር ወረዳ እና ከኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ፈንታሌ ወረዳ የወሰን ግጭት በቅርቡ መቀስቀሱን ተከትሎ ነበር፡፡

Via የጀርመን ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የአልኮል መጠጥ በብሮድካስት አማካኝነት ማስተዋወቅ የሚከለክለው ድንጋጌ ከግንቦት 21 ጀምሮ ተፈጻሚ እንደሚሆን ተገልፃል::

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ነዋሪዎች ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች 400 ሺህ ብር የሚገመት የዕለት ደራሽ ቀለብ ዕርዳታ አደረጉ፡፡ ድጋፉን ከከተማዋ ነዋሪዎች በማሰባሰብ በኩል የከተማዋ ወጣቶች ከፍተኛ ሚና እንደነበራቸው ታውቋል፡፡ ነዋሪዎቹ ዕርዳታ ያደረጉት በሰሜን ሸዋ ዞን አጣዬ፣ ማጀቴ፣ ካራ ቆሬና አካባቢው በሰሞኑ ግጭት ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ዕለታዊ ድጋፍ ነው፡፡ ድጋፉንም ወደ አካባቢው ወስደው ለተጎጂዎቹ ማስረከባቸው ታውቋል፡፡ የደብረ ብርሃን ከተማ ነዋሪዎች በንጹኃን ወገኖች ላይ የደረሰውን ጉዳት በሰላማዊ ሰልፍ ማውገዛቸው የሚታወስ ነው፡፡

Via AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ስሜን ተራሮች🔝

የስሜን ተራሮች ቃጠሎ ከቁጥጥር ውጭ እየሆነ ነው:: የስሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ ግጭ አካባቢ ከትናንት ምሽት ጀምሮ እየተቃጠለ ነው። በፓርኩ አስተርጓሚና አስጎብኝ የሆነው ወጣት አስረሳኸኝ ሞላ ለአብመድ እንደገለፀው ቃጠሎው ሰፊ ቦታን ያካለለና #ለመቆጣጠር የከበደ ነው።

ከትናንት ጀምሮ እሳቱን ለመቆጣጠር ጥረት ቢደረግም ከዛሬ እኩለ ቀን በኋላ ከአቅም በላይ መሆኑን ተነግራል። በቃጠሎው ምክንያት በአካባቢው ያለውን ማረፊያ ካምፕ ጥለው መውጣታቸውንም ነግሮናል።

የፓርኩ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊ አቶ ታደሰ ይግዛው ደግሞ እሳቱ በከፍተኛ ነፋስ እየታገዘ በመሆኑ ለመቆጣጠር ማስቸገሩን ተናግረዋል። በተለይ ከቀኑ 6:00 ገደማ ጀምሮ እሳቱ ሰፊ ቦታን እያካለለ መሆን ተናግረዋል።

ከፍተኛ የሰው ኃይል እሳቱን ለመቆጣጠር መሠማራቱን የገለጹት አቶ ታደሰ ምግብ እየቀረበላቸው አሁንም ከዚያው ሥራ ላይ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

Via አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ነዳጅ እና የነዳጅ ውጤቶችን የሚያስተዳድር ባለሥልጣን ለማቋቋም ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ረቂቅ ሕግ እንደቀረበ ሸገር ዘግቧል፡፡ ረቂቁ የአዲሱ ተቋም ዐላማ በመላ ሀገሪቱ ነዳጅና የነዳጅ ውጤቶች አቅርቦትን እና ሥርጭትን መቆጣጠር እንደሚሆን ይገልጻል፡፡ ደረጃውን የጠበቀ ነዳጅ ወደ ሀገር እንዲገባ እና ፍትሃዊ ሥርጭት እንዲኖር የቁጥጥር ሥርዓትም ይዘረጋል፡፡ ረቂቅ ሕጉ ከጸደቀ የባለሥልጣኑ ተጠሪነት ለንግድና ኢንዱስትሪ ሚንስቴር ይሆናል፡፡

Via Sheger FM
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የአልጀርያ ምክር ቤት ዛሬ አዲስ #የሽግግር ጊዜ መሪ ሰየመ። ባለፈው ሳምንት ሥልጣናቸውን በለቀቁት በቀድሞው የአልጀሪያ ፕሬዝዳንት አቤደላዚዝ ቡተፍሊካ ምትክ አብዱልቃድር ቤንሳላህን በጊዜያዊ ፕሬዝዳንትነት መርጧል።

Via DW
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ፕሬዝዳንት ሣሕለ ወርቅ ዘውዴ እና ጠ/ሚር #ዐቢይ_አሕመድ በ43ኛው የዓለም አቀፍ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የሀገር አቋራጭ ሻምፒዮና ላይ የተሳተፉ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሠልጣኞችና የቡድን መሪዎችን ዛሬ ማምሻውን በተደገ የእራት ግብዣ ላይ አመሰገኑ። አትሌቶቹ ለሀገራቸው 5 ወርቅ፣ 3 ብርና 3 የመዳብ ሜዳልያዎችን በማስገኘት ከ63 ተሳታፊ ሀገራት በሜዳሊያ ሰንጠረዥ 1ኛ ደረጃ ላይ እንድትሆን አስችለዋል። ጠ/ሚሩ ለኮሚቴው አመራርና አብላጫ ውጤት ላስመሰገቡ አትሌቶች የምስክር ወረቀትና የገንዘብ ሽልማት አበርክተዋል።

#PMOEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
‹‹አማራ ክልል ውስጥ ወንጀል ሠርተው ሌላ ክልል #እንደበቃለን ብለው የሚያስቡ ካሉ #ተስፋቸውን ይቁረጡ፡፡›› የአዴፓ ማዕከላዊ ኮሚቴ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ #ዮሐንስ_ቧያለው
.
.
የአማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (አዴፓ) ማዕከላዊ ኮሚቴ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዮሐንስ ቧያለው በክልሉ በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር እና በሰሜን ሸዋ ዞን በተከሰተው #ግጭት ዙሪያ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

በግጭቱ ሕይወታቸውን ባጡ ወገኖች እና በደረሰው የንብረት ውድመት አዴፓ ማዘኑን የገለፁት አቶ ዮሐንስ ለተጎጅ ቤተሰቦችና ወገኖች #መፅናትን ተመኝተዋል፡፡

ጉዳቱ ከመድረሱ በፊት የክልሉ መንግሥት ሥጋቱን ያውቀው እንደነበር ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱም ‹‹እንደስጋት በክልሉ የፖለቲካ ኃይሎች ግጭትን ለዓላማቸው መጠቀሚያ ሊያደርጉ እንደሚችሉ ግምቶች ነበሩን፤ ግን ከገመትነው #የፈጠነ ሆኖብናል›› ብለዋል። ይህን ያክል የንብረት እና የሰው ሕይወት ጠፍቷል ለማለት የቴክኒክ ቡድኑ የጥናት ምላሽ እንደሚጠበቅም ተናግረዋል፡፡

ሕዝቡ ሕግና ሰላምን በማስጠበቅ ረገድ በአዴፓ እና በክልሉ መንግሥት እምነት አጥቷል የሚሉ ሐሳቦች ይደመጣሉ በእናንተ በኩል ምን ግምገማ አለ? ተብሎ ከጋዜጠኞች ለተነሱ ጥያቄዎችም አቶ ዮሐንስ ‹‹እንዲያውም አሁን ሕዝቡ በአዴፓ ላይ ከፍተኛ #እምነት የጣለበት ወቅት ነው፤ አዴፓ በሕዝቡ አመኔታ ማግኘቱን ተከትሎ #ለመነጣጠል የሚፈልጉ ኃይሎች የፈጠሩት ሴራ በመሆኑ ሕዝቡ ከጎናችን ሊሆን ይገባል›› ብለዋል፡፡ ‹‹በተለያዩ አካባቢዎች የተፈጠሩ ግጭቶች የአዴፓ እና የአማራ ሕዝብ አንድነት የሚያስፈራቸው ኃይሎች የፈጠሩት ሴራ ነው›› በማለትም ተናግረዋል፡፡

ሕዝቡ መራር በሆነው በዚህ ጊዜ #አብሮነቱን እንዲያጠናክር የጠየቁት አቶ ዮሐንስ ‹‹አማራ ክልል ውስጥ ወንጀል ሠርተው በሌላ ክልል እንደበቃለን ብለው የሚያስቡ ካሉ ተስፋቸውን ይቁረጡ፤ ከአጐራበች ክልሎች እስከ ፌዴራል መንግሥት ድረስ ወንጀለኞችን ለመያዝ በጥምረት እየሠራን ነው›› ብለዋል፡፡ በክልሉ መሠል ችግር እንዳይከሰት ብቁ ዝግጅት እንደተደረም ተናግረዋል፡፡

Via AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ያማል---እጅግ በጣም ያማል‼️

በዚህ ሳምንት #የመን ርዕሠ-ከተማ #ሰነዓ ውስጥ በሁለት ትምሕርት ቤቶች አቅራቢያ በተጣለ #ቦምብ 14 ህጻናት መገደላቸዉን የተመድ #የህጻናት መርጃ ድርጅት ዩኒሴፍ አወገዘ።

የድርጅቱ የመካከለኛ ምሥራቅ እና የሰሜን አፍሪቃ ክፍል ሃላፊ ጊርት ካፔላሬ እንዳሉት ህጻናትን መግደል እና አካለቸዉን ማጉደል የህጻናትን መብቶች የሚጻረሩ እጅግ ከባድ ወንጀሎች ናቸው። እርምጃው ወላጆችም ልጆቻቸውን ወደ ትምሕርት ቤት እንዳይልኩ የሚያደርግ መሆኑን ጠቅሰዋል። በጥቃቱ ሌሎች 16 ተማሪዎች ጉዳት ደርሶባቸዋል። አብዛናዎቹ እድሜያቸው ከ9 ዓመት በታች ነው። #ሰንአ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ ከሚደረግላቸው ክፉኛ ከተጎዱት ውስጥ በአስጊ ሁኔታ ላይ የሚገኙም እንዳሉ ገልጸዋል።

ባለፈው እሁድ የየመን አማጽያንን የሚወጋው ሳዑዲ መራሹ ህብረት ሰንአ ውስጥ በመኖሪያ አካባቢዎች ላይ ባካሄደው የአየር ድብደባ ቢያንስ 11 ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸውን በኢራን ይደገፋሉ የሚባሉት የሁቲ አማጽያን ተናግረዋል። እንደ አማጽያኑ ከተገደሉት አብዛኛዎቹ ተማሪዎች ናቸው።

Via የጀርመን ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia