TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.5K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ጅማ ዩኒቨርሲቲ🔝ጠ/ሚር #ዐቢይ_አሕመድ የጅማ ዩኒቨርስቲ የህክምና ትምህርት ተመራቂዎችን የእንኳን ደስ አላችሁ በማለት ይህን የአዲስ ህይወት መጀመሪያ ምእራፍ ለማገልገልና ለውጥ ለማምጣት እንዲጠቀሙበት ጥሪ አቅርበዋል።

#PMOETHIOPIA
@tseegabwolde @tikahethiopia
#update ሰላማዊ ሰልፉ #በሰላም ተጠናቋል። በመቀለ ኢንተርናሽናል ስታዲየም በተካሄደው ህዝባዊ ሰልፍ ላይ የህወሃት ሊቀመንበርና የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር #ደብረፅዮን_ገብረሚካኤልን ጨምሮ፥ የክልሉ መንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ የከተማዋ እና በዙሪያ የሚገኙ ነዋሪዎች ተገኝተው ነበር።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጅማ🔝የኢትዮጵያ፣ የሱዳንና የጂቡቲ መሪዎች የጅማ - አጋሮ - ደዴሳ ወንዝ ድልድይ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክትን አስጀምረዋል።

@tsegabwolde @tikahethiopia
ሰበር ዜና‼️

የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ከፍተኛ አመራሮች የነበሩት አቶ #መዓሾ_ኪዳኔ_ዓለሙ እና አቶ #ሀዱሽ_ካሳ_ደስታ በቁጥጥር ስር ዋሉ። ከፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ የተገኘው መረጃ እንዳመለከተው ግለሰቦቹ በከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ወንጀል ተጠርጥረው ነው በቁጥጥር ስር የዋሉት።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሀዋሳ-ሪፈራል ሆስፒታል አካባቢ!
#update ዛሬ ጥዋት በኩየራ እና በአርሲ ነጌሌ መሀል በደረሰው የመኪና አደጋ እስካሁን ባለው መረጃ የ4 ሰዎች ህይወት እንዳለፈ ተረጋግጧል። የሟቾች አስክሬን ሀዋሳ ከተማ ሲገባም በርካታ ሰዎች ሀዘናቸውን ገልፀዋል። በአደጋው ህይወታቸው ያለፈው ሰዎች በነገው ዕለት ወደሀገር የሚገቡትን በዶክተር #ዎላሳ_ላዊሶ የሚመራ የሙሁራን ቡድን ለመቀበል ወደአዲስ አበባ ከተማ ሲጓዙ የነበሩ ናቸው።

ተጨማሪ መረጃ እንደደረሰኝ አቀርባለሁ!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update በ 1 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር የተገነባው የጅማ ኢንዱስትሪ ፓርክ የሱዳንና ጅቡቲ መሪዎች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጅማ ከተማ🔝የሱዳኑ ፕሬዚዳንት ኦማር ሀሰን አልበሽር እና የጅቡቲው ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌ በጅማ ከተማ የተለያዩ ስጦታዎች ተበርክቶላቸዋል።

ፎቶ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የ5 ሰዎችን ህይወት አልፏል!

ከሀዋሳ ወደ አርሲ ነጌሌ በመጓዝ ላይ የነበረ ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ የትራፊክ አደጋ #የአምስት ሰዎች ህይወት ማለፉን የምዕራብ አርሲ ዞን የትራፊክ መምርያ አስታወቀ ።

ዛሬ ጠዋት 1 ሰዓት ከ30 ላይ በውጭ ሀገር ሆነው ለሲዳማ ህዝብ እኩልነት ሲታገሉ የቆዩትን እነ ፕሮፌሰር #ወላሳ_ላዊሶነንና ሌሎች የመብት ተሟጓቾችን ለመቀበል ሲጓዙ የነበሩ ሰዎችን የያዘ ላንድ ኩሩዘር ከአርሲ ነጌሌ ወደ ሻሻመኔ በመጓዝ ላይ ከነበረ አይሱዙ የጭነት መኪና ጋር አርሲ ነጌለ ወረዳ ቀርሳ #እላላ_ቀበሌ በመጋጨታቸው የደረሳ አደጋ መሆኑን የምዕራብ አርሲ ዞን የትራፊክ ዲቪዥን ሀላፊ ኢንስፔክተር #ጎሴ_ድኮ ገልፀዋል፡፡

በዚህ አደጋም የአምስት ሰዎች ህይወት ሲያልፍ በአንድ ሰዉ ከባድ የአካል አደጋ ደርሷል፡፡

የተጋጩት ሁለቱ መኪናዎች ሙሉ በሙሉ እንደወደሙ የገለፁት ኢንስፔክተሩ የአደጋው መንስኤ እየተጣራ ነዉ ብሏል፡፡

ምንጭ፦ fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia