TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.6K photos
1.6K videos
216 files
4.35K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
#Update

ዛሬ በህንድ አህመዳባድ በደረሰው የቦይንግ 787-8 ድሪምላይነር አውሮፕላን መከስከስ አደጋ የሞቱ ሰዎች ወደ 294 እንደሚጠጉ ተነግሯል።

በአውሮፕላሉ ውስጥ ከነበሩ 242 ሰዎች አንድ ሰው በህይወት ሲተርፍ ሌሎች ህይወታቸው አልፏል።

አውሮፕላኑ በተነሳ በትንሽ ደቂቃ የተከሰከሰው በአንድ የህክምና ኮሌጅ ውስጥ ነው። በኮሌጁ በሚገኝ ህንጻ ውስጥ የነበሩ የጤና ተማሪዎች ህይወታቸው ማለፉን ተከትሎ አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር 294 አካባቢ መሆኑን ፖሊስ ገልጿል።

@tikvahethiopia
😭1.5K406💔171😢92🙏40🕊38😱21🤔18👏16🥰10
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

ኮማንደር ተስፋዬ ዴቢሶ የሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሆነው ተሾሙ።

የሲዳማ ክልል ከሰሞኑ በፀጥታዉ ዘርፍ እየወሰደ እንደሆነ በተገለፀዉ ተቋማዊ ሪፎርም ዛሬ የቀድሞ የክልሉ ኮሚሽነር የነበሩትን ሽመልስ ቶማስ በዛሬዉ ዕለት ከስልጣን ማንሳቱ የተሰማ ሲሆን ማምሻዉን ኮማንደር ተስፋዬ ዴቢሶን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አድርጎ ሾሟቸዋል።

አዲሱ ኮሚሽነር ተስፋዬ ዴቢሶ ሲዳማ በዞን መዋቅር ከነበረበት ጊዜ ጀምሮ በልዩ ልዩ ፖሊሳዊ አመራሮች ተቋሙን ያገለገሉና በአሁኑም ወቅትም የሲዳማ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ሆነዉ ሲሰሩ እንደነበር ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከተለያዩ ምንጮች አረጋግጧል።

ይህ መረጃ በተዘጋጀበት ወቅት ስለ ቀድሞዉ የሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር ከኃላፊነት መነሳት ዙሪያ ይፋ የተደረገ መግለጫ የሌለ ሲሆን የፖሊስ ኮሚሽኑ የፌስቡክ ገፅ የአዲሱን ኮምሽነር ሹመት ከደቂቃዎች በፊት ይፋ አድርጎታል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም ከጉዳዩ ጋር የተያያዙ አዳዲስ መረጃዎችን እየተከታተለ የሚያቀርብ ይሆናል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
886😭58🤔36🕊33🙏32😢18👏15😡15🥰11😱3
TIKVAH-ETHIOPIA
አሜሪካ በቀጥታ ወደ ጦርነቱ ትገባ ይሁን ? እስራኤል በኢራን ላይ እያካሄደችው ባለው ጥቃት ውስጥ አሜሪካ ስለምትሳተፍበት ሁኔታ ለመወያየት ዶናልድ ትራምፕ በዋይት ሐውስ ውስጥ አስቸኳይ ስብሰባ ከከፍተኛ ባለሥልጣኖቻቸው ጋር አድርገዋል። አንድ ሰዓት ከ20 ደቂቃ በቆየው ስብሰባ ላይ ዋነኛ አጀንዳ የነበረው እስራኤል በኢራን የኒውክሌር ማዕከላት ላይ እየፈጸመችው ባለው ጥቃት ውስጥ አሜሪካ መሳትፍ እንዳለባት…
#Update

እስራኤል በኢራን ላይ በፈጸመችው ጥቃት እስከ እሁድ ምሽት ድረስ 224 ሰዎች መገደላቸውን 1 ሺህ 277 መጎዳታቸውን ኢራን አስታውቃለች።

እስራኤል በበኩሏ በኢራን ጥቃት 20 ሰዎች እንደተገደሉባት ገልጻለች።

ተባብሶ በቀጠለው የሁለቱ ሀገራት ጦርነት ምክንያት ነዋሪዎች ከአካባቢያቸው እንዲወጡ በሁለቱም በኩል መልዕክት እየተላለፈ ነው።

ኢራን የእስራኤሏ ሃይፋ ከተማ በተወሰነው ክፍል ያሉ ነዋሪዎች ለህይወታቸው አደጋ ስለሚኖር አካባቢያቸውን ለቀው እንዲወጡ ማስጠንቀቂያ ሰጥታለች።

እስራኤልም ነዋሪዎች ከተለያዩ የቴህራን ክፍሎች ለቀው እንዲወጡ እያስጠነቀቅች ነው። በዚህም ሰዎች በቻሉት አቅም ወደ አጎራባች ከተማ እየወጡ እንዳለ ተነግሯል።

መረጃው ቢቢሲ ነው።

@tikvahethiopia
853😭306🕊169😢46👏33🙏22😡22😱19🤔16💔12🥰5
TIKVAH-ETHIOPIA
" ኃይል ተቋርጧል ! " አዲስ አበባን ጨምሮ በሃገሪቱ አንዳንድ አካባቢዎች የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጧል። በዋናው የኤሌክትሪክ መስመር /ግሪድ/ ባጋጠመ ቴክኒካል ብልሽት ምክንያት አዲስ አበባን ጨምሮ በሃገሪቱ አንዳንድ አካባቢዎች የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጡን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታውቋል። የተቋረጠውን የኃይል አቅርቦት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለመመለስ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ነው…
" በተወሰኑ ቦታዎች ኃይል እየተመለሰ ነው " - የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል

አዲስ አበባን ጨምሮ በኢትዮጵያ በከፊል የተቋረጠው ኃይል በተወሰኑ አካባቢዎች መመለስ እንደጀመረ የኢትዮጵያ ኤሌትክሪክ ኃይል አሳውቋል።

" በተቀሩት አካባቢዎችም በየደረጃው መልሶ ኃይል የማገናኘት ስራ እየተሰራ ነው " ብሏል።

#Update : ሙሉ በሙሉ ኃይል ተመልሷል።

@tikvahethiopia
799👏191😭103😡90🙏66🤔41🥰24🕊24😢22😱14💔13
TIKVAH-ETHIOPIA
" ፍቅረኛዉን በቅናት ተነሳስቶ የገደላት ግለሰብ ማምለጥ እንደማይችል ሲያውቅ እጁን ለፖሊስ ሰጥቷል " - የኮንሶ ዞን ከና ወረዳ ፖሊስ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮንሶ ዞን ከና ወረዳ የገዛ ፍቅረኛዉን በስለት በመዉጋት ሕይወቷ እንዲያልፍ ያደረገው ግለሰብ ከሕግ እንደማያመልጥ ሲገባዉ እጁን ለፖሊስ መስጠቱን የከና ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ምክትል ኢንስፔክተር ገዛኸኝ ካራተ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ። ግለሰቡና…
#Update

" የመምህርት ተዋበች ገዳይ በ25 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጥቷል " - የኮንሶ ዞን ፖሊስ

በኮንሶ ዞን ኬና ወረዳ ፋሻ ቀበሌ ልዩ ስሙ ኮቶላ ወንዝ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከአንድ ወር በፊት የገዛ ፍቅረኛዉን መምህርት ተዋበች ኩሲያን ሌላ " የፍቅር አጋራ ይዘሻል " በሚል ጥርጣሬ በአሰቃቂ ሁኔታ የገደላት ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዉሎ በተመሰረተበት ከባድ የግድያ ወንጀል ጥፋተኛ በመባል የፍርድ ዉሳኔ እንደተላለፈበት የኮንሶ ዞን ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ሰለሞን ካማይታ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ተከሳሹ ወንጀሉን የፈፀመበት ሁኔታ፣ ሰዓት እና የድርጊቱን አሰቃቂነት ዐቃቤ ህግ በሰዉና ኤግዚቢት እንዲሁም የምርመራ ማስረጃ በማቅረቡ የኮንሶ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተከሳሽ ኩሻቦ ኩራዎ ጥፋተኛ በማለት በ25 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም የወንጀል ድርጊቱን በተፈፀመበት ወቅት የኬና ወረዳዉ ፖሊስ ምላሽ አካቶ በጉዳዩ ላይ ዘገባ ማቅረቡ አይዘነጋም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
689😡174😭119👏79💔58🙏35🕊26😢18🥰14🤔13
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

የኢራን መገናኛ ብዙኃን በሰሜናዊ ኢራን ፍንዳታዎች በመሰማታቸው " ተኩስ አቁሙ ተጥሷል " አሉ።

በኢራን እና በእስራኤል መካከል የተኩስ አቁም መደረጉ ቢነገርም በሰሜናዊ ኢራን ማዛንዳራን ግዛት ውስጥ ፍንዳታዎች መሰማታቸውን ነዋሪዎች ተናግረዋል።

ለኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ጓድ ቅርብ የሆነው 'ፋርስ' የተባለው የዜና ወኪል እንዳለው ከዋና ከተማዋ ቴህራን በስተሰሜን ማዛንዳራን ግዛት ውስጥ በምትገኘው ባቦልሳር ከተማ ውስጥ ፍንዳታዎች ተሰምተዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ከፊል መንግሥታዊ የሆኑት 'መህር' እና 'ኢስና' የተባሉት የዜና ወኪሎች በሰሜናዊ ግዛት ውስጥ በሚገኙ የተለያዩ ስፍራዎች ፍንዳታዎች መከሰታቸውን እና የአየር መከላከያ መሳሪያዎች ተኩስ መሳማቱን በመጥቀስ የተኩስ አቁሙ “ተጥሷል” ብለዋል።

በተጨማሪም የኢራን መንግሥት ቴሌቪዥን ፍንዳታዎች መከሰታቸውን እና የግዛቲቱን አስተዳዳሪ ቃል አቀባይ ክስተቱን በተመለከተ ዝርዝር ጉዳዮች ገና አለመታወቃቸውን መናጋራቸው ገልጿል።

በሌላ በኩል ፥ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ " እስራኤል በኢራን ላይ ጥቃት መፈጸም የለባትም " በማለት ማስጠንቀቂያ አስተላልፈዋል።

ፕሬዝዳንቱ  " እስራኤል፤ እነዚያን ቦምቦች አትጣይ። በጥቃቱ የምትቀጥይ ከሆነ ከፍተኛ ጥሰት ነው። የጦር አውሮፕላን አብራሪዎችሽን አሁኑኑ ወደ ቤታቸው መልሺ! " ብለዋል።

ይህ የፕሬዝዳንቱ ማስጠንቀቂያ የመጣው ከዛሬ ጠዋት ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆን የተኩስ አቁም በኢራን እና በእስራኤል መካከል መደረጉን ካስታወቁ በኋላ ነው።

እስራኤል በትራምፕ ሃሳብ መስማማቷን ስታሳውቅ፣ ኢራን ደግሞ ጥቃቱን የምታቆመው እስራኤል ካቆመች ብቻ ነው ብላለች።

ምንጭ ፦ ቢቢሲ

@tikvahethiopia
746🕊79😡34🙏23😭13🤔6👏4💔4😱2😢2🥰1
TIKVAH-ETHIOPIA
" የጉዞ ታሪክ በሌላቸው ሁለት ታዳጊዎች ላይ የMpox ምልክት መታየቱ ስጋት ፈጥሮብናል " - የሰገን ዙሪያ ወረዳ ነዋሪዎች ➡️ " በኮንሶ ዞን የኤም ፖክስ(Mpox) በሽታ ምልክት በሁለት ሰዎች ላይ ታይቶ ናሙና ተወስዶባቸው ዉጤት እየተጠባበቅን ነዉ " - የዞኑ ጤና መምሪያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡ የሰገን ዙሪያ ወረዳ ነዋሪዎች ስለዝንጀሮ ፈንጣጣ (Mpox) በሽታ ምልክቶች በተለያዩ አጋጣሚዎች…
#Update

" በሰገን ዙሪያ ወረዳ በሁለት ሰዎች ላይ የታየዉ ምልክት የMpox በሽታ ስላልሆነ ሕብረተሰቡ ከስጋት ነፃ ሆኖ ጥንቃቄ ማድረግ አለበት " - የኮንሶ ዞን ጤና መምሪያ


ከሰሞኑ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮንሶ ዞን ሰገን ዙሪያ ወረዳ አማራይታ ተብሎ በሚጠራዉ አከባቢ በሁለት እህታማምች ላይ የታየዉን የሰዉነት ላይ ምልክትን ተከትሎ ሕብረተሰቡ " የኤም ፖክስ በሽታ ሊሆን ይችላል " በሚል ስጋት ዉስጥ መግባቱንና የዞኑ ጤና መምሪያ በበኩሉ ከተጠረጠሩት ሁለት የአንድ ቤተሰብ አባላት ላይ ናሙና ወስዶ ለምርመራ መላኩን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳቆ ነበር።

የኮንሶ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ግርማ በሌ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለፁት ከሁሉቱ እህታማሞች የተወሰደዉ ናሙና ዉጤት ከአዲስ አበባ መምጣቱንና በዉጤቱ መሰረት ምልክቱ MPox (የዝንጀሮ ፈንጣጣ) አለመሆኑ ተረጋግጧል ብለዋል።

አቶ ግርማ ሕብረተሰቡ በሽታዉን መጠንቀቁ አግባብ ቢሆንም ልጆቹንና ቤተሰቦቻቸውን ያገለለበት መንገድ ተገቢ አለመሆኑን ገልፀዋል።

ዉጤቱን ተከትሎም ስለ በሽታው የግንዛቤ ማስፋትና የጥንቃቄ ስራዎች እየተሰሩ ያለ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ልጆቹ ከቤተሰቦቻቸው ጋር እንዲቀላቀሉ መደረጉንም አስታውቀዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
376🙏57😭14🤔6😱6🕊5🥰4😢4👏2
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

ከጎንደር መተማ በሚወስደው መንገድ በአንድ ቀን ልዩነት በመንግስት የፀጥታ ሀይሎች ላይና በንፁሀን ላይ " ዘግናኝ " ሲል የጠራው ጭፍጨፋ መፈጸሙን የምዕራብ ጎንደር ዞን አስተዳደር አስታውቋል።

የዞኑ ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ለጥቃቱ " ፅንፈኛው ቅማንት " ሲል የጠራውን ታጣቂ ኃይል ተጠያቂ አድርጓል።

ዞኑ ሰኔ 19 ባወጣው መግለጫ በቀን ሰኔ 16/2017 ዓ.ም 11:00 ገደማ  ከጎንደር ገንዳ ዉሃ በሚወስደው መንገድ " መቃ " በተባለ ቦታ ጥቃቱ መፈጸሙን ገልጿል።

በቀን 16/10/2017 ዓ/ም ከቀኑ11:30 ገደማ ለአርሶ አደሩ እና በአካባቢው በእርሻ ስራ በኢንቨስትመት ለተሰማሩ የሚከፋፈፍል የአፈር ማዳበሪያ የጫኑ ተሽከርካሪ እና ሌሎች የህዝብ መጓጓዣዎችን አጅበው የነበሩ  መከላከያ፣ የፌደራል ፖሊስና የአድማ ብተና ፖሊስ አባላት እንዲሁም አሽከርካሪዎችና ተሳፋሪዎችን " ዘግናኝ በሆነ ጭካኔ ጨፍጭፏቸዋል " ሲል ገልጿል።

" ታጅበዉ እና ማዳበሪያ ጭነዉ ሲመጡ የነበሩ 16 ሹፌሮችን ከመኪና እያስወረደ ዘግናኝ በሆነ ጭካኔ ጨፍጭፏቸዋል። የተወሠኑትንም አግቶ በመውሠድ አድራሻቸውን አጥፍቷል " ሲል መግለጫው ይጠቅሳል።

አክሎሞ " ይህው ታጣቂ ኃይል በቀን 18/10/2017 ዓ/ም ከፍተኛ የመከላከያ ሠራዊታችን አመራሮችና አባላት ላይ አቅዶና ተዘጋጅቶ ድጋሜ በጀግናው የመከላከያ ሠራዊት አባላት ላይ ግጭት አድርጓል " ብሏል።

የዞኑ አስተዳደር " ታቅዶበት የተፈፀመና ዘግናኝ " ብሎ በጠራው በዚህ ጥቃት በመጀመሪያው ቀን የሟቾች ቁጥር 16 ሹፌሮች መሆኑን ሲጠቅስ በሁለተኛው ቀን በተፈፀመው ጥቃት የሟቾችን ቁጥር ከመግለፅ ተቆጥቧል።

በመጀመሪያው ቀን በንፁሃን ላይ ደረሰ ባለው ጥቃት ቁጥራቸውን ያልገለፃቸው ሹፌሮች ታግተው መወሰዳቸውንም አክሏል።

ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስተያየታቸውን የሰጡ የአይን እማኝ ግን  ሰኔ 16፤ 2017 ዓ.ም በተፈፀመው ጥቃት የሟቾችን ቁጥር ከመቶ በላይ እንደሚደርስ ተናግረዋል።

ይህዉ የአይን እማኝ እንደሚለው " በእለቱ ከታጣቂ ሀይሉ ጋር መሬት ላይ ሲጨቃጨቁ የነበሩት አድማ ብተና ፖሊስና በFSR መኪና ተጭነው የነበሩ የፀጥታ ሀይሎችን ከጫካ እየወጡ ነው መኪና ላይ እያሉ የጨፈጨፏቸው " ብሏል።

" እነሱን ሲጨርሱ ደግሞ በየመኪናው ባሉ ሹፌሮችና ተሳፋሪዎች ላይ ጥቃቱን ፈፅመዋል" ሲል ገልጿል።

የዞኑ አስተዳደር " ፅንፈኛ " ሲል የሚጠራውን የቅማንት ታጣቂ ኃይል በአካባቢው ከ2008 ዓ.ም ጀምሮ በንፁሀን ዜጎች ላይ ግድያና እገታ እንደሚፈፅም በመግለጫው አንስቷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ባሕር ዳር
#TikvahEthiopiaFamilyBD

@tikvahethiopia
588😭323😡32💔27🕊21👏12😢10🙏9🤔7😱3🥰2
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

ሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴን ውሳኔ " ተገቢና ህግን ያልተከተለ ውሳኔ " ሲል ተቃወመ።

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፈዴሬሽን የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ ዋንጫ ከሲዳማ ቡና ተነጥቆ ለወላይታ ዲቻ እንዲመለስ ሲል ውሳኔ አሳልፏል።

ይህ ተከትሎ የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ቦርድ ውሳኔውን " ተገቢነት የለሌው ውሳኔ ነው። ውሳኔው እጅግ አሳዝኖናል " ብሏል።

" ብርቅዬ የክለባችን ተጫዋቾች በጨዋታ ሜዳ የገጠሙትን ሁሉንም ከጨዋታ ብልጫ ጋር በማሸነፍ የ2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ ዋንጫ ማሸነፉ የአደባባይ ምስጥር ነዉ " ሲል ገልጿል።

" ይሁን እንጂ ' የሊግ ካምፓኒ ያወጣውን የፋይናንስ ደንብ አላከበራችሁም ' በሚል በክለቡና በተጫዋቾች ላይ ቅጣት ተጥሎባቸዋል ቢባልም ክለቡ  ያነሳዉ ዋንጫ የኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ በ48 ክለቦች መካከል የተደረገው መሆኑ ዕሙን ነው " ብሏል።

" የሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ የታገዱ ተጫዋቾችን አሰልፎ ከሆነ በጥሎ ማለፉ ያሸነፋቸው ክለቦች በሙሉ ፎርፌ አግኝተው ጉዳያቸው እንደገና መታየት አለበት እንደ ማለትም ይሆናል " ብሏል።

" እርስ በርስ የሚጣረሱ ሀሳቦችን በማገናኘት ውጤቱን ለመቀማት መሞከር  ተገቢና ህግን የተከተለ ውሳኔ ነው ብለን አናምንም " ሲል ቦርዱ አሳውቋል።

" ፌዴሬሽኑ ዉሳኔውን ከህግጋቱ ጋር በማገናዘብ እንደገና እንዲያጠነዉ ቅሬታችንን እናሰማለን " ብሏል።

" ህዝባችን በፌደሬሽኑ ውሳኔ የተከፋ ቢሆንም የአፊኒ ባህል ያለው ታላቅ ህዝብ ስለሆነ ክስተቶችን በመረጋጋት መርምሮ በተገቢው እንዲያጠነውና  ሂደቱን  በትዕግሥት እንዲጠባበቅ በአክብሮት እየጠይቃል " ሲል ገልጿል።

" የተነፈግነው ፍትህ እስኪረጋገጥ ድረስ ጉዳዩን እስከ ፊፋ ገላጋይ ፍርድ ቤት ድረስ በይግባኝ ወስደን ለጉዳዩ  ተገቢው እልባት እስኪሰጥ ድረስ የክለቡ ቦርድ ቁርጠኛ መሆኑን እናረጋግጣለን " ሲል አሳውቋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
#TikvahEthiopiaFamily

@tikvahethiopia
1.11K🤔144👏77😭48😡47🙏31🕊23😢10😱8💔6🥰1
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

19 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈርዶበታል !

ታዳጊዋ አያንቱ ቱና ላይ የግበረስጋ ድፍረት የፈጸመው ግለሰብ በ19 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል።

በሲዳማ ክልል ማዕከላዊ ሲዳማ ዞን ሻፋሞ ወረዳ የ13 ዓመቷን ታዲጊ አያንቱ ቱና ላይ የግብረስጋ ድፍረት ወንጀል በመፈጸም የተጠረጠረውና በፖሊስ ተባባሪነት ጭምር አምልጦ ከ1 ዓመት በላይ ተሰዉሮ የነበረዉ ወጣት በቲክቫህ ኢትዮጵያ ላይ መረጃው ከተሰራጨ በኋላ በተደረገ ክትትልና ፍለጋ ተጠርጣሪዉ በቁጥጥር ስር ዉሎ ክስ ተመስርቶበት እንደነበር የአያንቱ ታላቅ ወንድም ወጣት ጴጥሮስ ቱና ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

ይኸው ግለሰብ አርብ ዕለት ፍርድ ቤት ቀርቦ ዉሳኔ እንደተላለፈበት የአያንቱ ወንድም ተናግሯል።

የሻፋሞ ወረዳ ዐቃቤ ሕግ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደምሴ ፉና ስለጉዳዩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሲያስረዱ " የወረዳዉ ፖሊስ እና ዐቃቤ ሕግ በተከሳሹ ላይ ያቀረቡትን ጠንከር ያለ ምርመራ፣ የሰነድ እንዲሁም የሕክምና ማስረጃዎችን የተመለከተዉ የወረዳዉ ፍርድ ቤት ግለሰቡን ጥፋተኛ ነዉ በማለት በ19 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል " ብለዋል።

" ተጠርጣሪዉ በቁጥጥር ስር ከዋለ በኋላ በማቆያ ዉስጥ የምትገኘዉ አያንቱ ደፋሪዋ እንደተያዘ ከተነገራት በኋላ ጥሩ መሻሻል ታይቶባታል " የሚለዉ የታዳጊዋ ወንድም ጴጥሮስ " ከዚህ በኋላ ከማቆያ ወጥታ ወደ ትምህርት ገበታዋ ትመለሳለች " ብሏል

" የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላትን ጨምሮ ለታዳጊዋ ድምፅ ለሆናችሁ ሁሉ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ " ብሏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
1.69K😡1.16K👏344🙏161😭65💔60🕊45😢26🤔16🥰14
TIKVAH-ETHIOPIA
የዘውዱ ሃፍቱ ጉዳይ ከምን ደረሰ ? ከዘውዱ ሃፍቱ የግድያ ወንጀል ጋር በተያያዘ የመጨረሻ ውሳኔ ዛሬ ሰኔ 3/2017 ዓ.ም ሊሰጥ ቀጠሮ ቢያዝለትም ለሰኔ 30/2017 ዓ.ም ተሸጋግሯል። ዛሬ የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል የችሎት ውሎውን ተከታትሏል። የእንስት ዘውዱ ሃፍቱ የግድያ ወንጀል ግንቦት 8/2017 ዓ.ም ለመጨረሻ ውሳኔ ተቀጥሮ ነበር ሆኖም የተከሳሽ ቤተሰቦች በቀሰቀሱት ግርግርና ረብሻ…
#Update

" የዘገየ ፍትህ እንዳልተሰጠ ይቆጠራል ! " - ሂደቱን የሚከታተሉ ታዛቢዎች

አሁንም የእንስት ዘወዱ ሃፍቱ የግድያ ወንጀል የፍርድ ውሳኔ ሌላ ቀጠሮ ተይዞለታል።

የግድያ ወንጀሉ ከተፈፀመ የፊታችን ነሀሴ ወር የሚከበረው የአሸንዳ 2017 ዓ.ም በዓል ሁለት ዓመት ይሞላዋል።

አሰቃቂ የግድያ ወንጀሉ የአሸንዳ በዓል በሚከበርበት ወርሃ ነሀሴ 2015 ዓ.ም ነበር የተፈፀመው።  

የእንስት ዘውዱ ሃፍቱ የግድያ ወንጀል ችሎት የትላንት ውሎ ምን ይመስል ነበር ? 

የእንስት ዘውዱ ሃፍቱ የግድያ ወንጀል በመመልከት ላይ የሚገኘው የመቐለ ማእከላዊ ፍርድ ቤት ግንቦት 8 ቀን 2017 ዓ.ም በተከሳሾች ላይ ያስተላለፈው ውሳኔ ላይ ጥፋተኛ የተባሉት ግለሰቦች የሚያቀርቡት የፍርድ የማቅለያ ለመስማት ነው ለሰኔ 30 ቀን 2017 ዓ.ም የተቀጠረው።

የችሎቱ ዳኞች በያዙት ቀጠሮ ተከሳሾች ለፍርድ ማቅለያ የሚሆናቸውን የህክምናና ሌሎች ሰነድ እንዲያቀርቡ ባዘዙት መሰረት በጠበቃቸው በኩል አቅርበዋል።

አንደኛ ተከሳሽ የልብ ህመም ታማሚና የኪንታሮት ህመምተኛ ፣ ሁለተኛው ተከሳሽ ደግሞ የስኳርና የኪንታሮት ህመምተኛ መሆናቸውን በቃል ቢገልጹም በሃኪሞች ማስረጃ እንዲረጋገጥ ለሀምሌ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷል።

በግድያ ወንጀሉ በመፈፀመ የተጠረጠሩ ሁለቱ ወጣቶች ሀምሌ 3 ቀን 2017 ዓ/ም በሃኪም የተረጋገጠ የፅሁፍ ማስረጃ ያቀርቡ እንደሆነ ያኔ የሚታይ ሆኖ የችሎት ሂደቱን የተከታታሉ የሚድያ ባለሙያዎች ፣ የሴቶች ጥቃት እንዲቆም የሚሰሩ ግለሰቦችና ተቋማት " ይህንን ሁሉ በሽታ ተቋቁመው ይህን መሰል ዘግናኝ ግድያ ለመፈፀም እንዴት ጉልበትና አቅም አገኙ ? " የሚል ጥያቄ ጭረዋል።

የችሎቱ የውሎ መረጃ  በማህበራዊ ሚዲያ የተከታተሉ በርካቶች የፍርድ ሂደቱ ለሁለት አመታት መራዘሙ በመቃወም "  የዘገየ ፍትህ እንዳልተሰጠ ይቆጠራል " ብለዋል።

የአሰቃቂ የግድያ ወንጀሉ የፍርድ ሂደት ሀምሌ 3 ቀን 2017 ዓ.ም መቋጫ ይብጀለት ይሆን ? ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ጉዳዩ ተከታትሎ ያቀርባል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
785😭196😡57🕊23🙏19😢10🥰9💔9😱5👏4
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " የዘገየ ፍትህ እንዳልተሰጠ ይቆጠራል ! " - ሂደቱን የሚከታተሉ ታዛቢዎች አሁንም የእንስት ዘወዱ ሃፍቱ የግድያ ወንጀል የፍርድ ውሳኔ ሌላ ቀጠሮ ተይዞለታል። የግድያ ወንጀሉ ከተፈፀመ የፊታችን ነሀሴ ወር የሚከበረው የአሸንዳ 2017 ዓ.ም በዓል ሁለት ዓመት ይሞላዋል። አሰቃቂ የግድያ ወንጀሉ የአሸንዳ በዓል በሚከበርበት ወርሃ ነሀሴ 2015 ዓ.ም ነበር የተፈፀመው።   የእንስት ዘውዱ…
#Update

የመቐለ ማእከላዊ ፍርድ ቤት በእንስት ዘውዱ ሃፍቱ የግድያ ወንጀል ጉዳይ ላይ የመጨረሻ ያለውን ቀነ ቀጠሮ ሰጠ።

ሰኔ 30 ቀን 2017 ዓ.ም በእስር የሚገኙ ተከሳሽ ተጠርጣሪዎች ለውሳኔ ማቅለያ የሚሆን የህክምና ማስረጃ እናቀርባለን ባሉት መሰረት ለዛሬ ሀምሌ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ቀጠሮ መስጠቱ ይታወሳል።

ይሁን እንጂ ዛሬ ችሎት ላይ የቀረቡት የተከሳሽ ጠበቆች " የመቐለ ዓይደር ሰፔሻላይዝድ ሆስፒታል ነገ አርብ ሀምሌ 4 ቀን 2017 ዓ.ም የህክምና ማስረጃ ለመስጠት ቀጠሮ ሰጥቶናል " ብለዋል።

ፍርድ ቤቱም ይህን አድምጦና ተቀብሎ የመጨረሻ ቀነ ቀጠሮ ለነገ ሰጥቷል።

በእንስት ዘውዱ ሃፍቱ የግድያ ወንጀል ላይ የመጨረሻ ውሳኔ ይሰጣል በሚል ዛሬ በመቐለ ማእከላይ ፍርድ ቤት የተበዳይና ተከሳሽ ቤተሰቦች ፣ በርካታ ሚድያዎች ፣ በሴት ጥቃት መከላከል ዙሪያ የሚሰሩ ስቪክ ማህበራት አመራሮችና አባላት ተገኝተው ነበር ።

ሁለት አመት ያስቆጠረው የእንስት ዘውዱ ሃፍቱ አሰቃቂ የግድያ ወንጀል ነገ ሀምሌ 4 ቀን 2017 ዓ.ም የመጨረሻ መቋጫ የፍርድ ውሳኔ ያገኝ ይሆን ? ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ የችሎቱን ውሳኔ ተከታትሎ ያቀርባል።

ቲክቫህ ኢትጵዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
556😭158🙏35😡30🕊19🤔17😢15💔13🥰6👏6
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

የእድሜ ልክ ፅኑ እስራት ተፈርዶባቸዋል !

በእንስት ዘውዱ ሃፍቱ የጭካኔ የግድያ የተከሰሱት ተጠርጣሪዎች ጥፋተኞች ተብለው የፍርድ ውሳኔ ተላለፈባቸው።

ተከሳሾቹ ለፍርድ ውሳኔ ማቅለያ ይሆነናል በማለት " የቆየ ህመም አለብን " ቢሉም የመቐለ ዓይደር ስፔሻላይዝድ ሪፈራል ሆስፒታል ሃኪሞች የምርመራ ማስረጃ " የቆየ ህመም የለባቸውም " ሲል ምላሽ ሰጥቷል።

የመቐለ ማእላዊ ፍርድ ቤት በእንስት ዘውዱ ሃፍቱ አሰቃቂ ግድያ የመጨረሻ የፍርድ ውሳኔ ውሎ ምን ይመስል ነበር ?

የተጠርጣሪ ጠበቆች ትናንት ሀምሌ 3 " ደምበኞቻችን የቆየ ህመም አለባቸው ይህንን ለማረጋገጥ የህክምና ማስረጃ ለአርብ ሀምሌ 4 እናቀርባለን " ብለው ነበር።

ፍርድ ቤቱ ይህን ተቀብሎ ለዛሬ የመጨረሻ ውሳኔ ለመስጠት ቀነ ቀጠሮ ሰጥቶ ነበር።

ዛሬ አርብ ሀምሌ 4/2017 ዓ.ም ከመንግስት ሰራተኞች የስራ ሰዓት በፊት ቤተሰብ የሚገኙባቸው የሚድያና የሴቶች መብት ተቆርቋሪዎች በፍርድ ቤቱ በራፍ ደርሰው ተሰባስበዋል።

ተከሳሾች ለውሳኔ ማቅለያ ይሆነናል ብለው የጠየቁት የህክምና ማስረጃ የቆየ ህመም እንደሌለባቸው አረጋግጧል።

ዳኞችም ይህን ካረጋገጡ በኋላ በተከሳሾች ላይ ውሳኔ ሰጥተዋል።

አንደኛና ሁለተኛ ተከሳሾች ያሬድ ገብረስላሰ በላይ እና ኣንገሶም ሃይለማርያም በእድሜ ልክ ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ፍርድ ቤቱ ወስኗል።

በፍርድ ቤቱ ውሳኔ አለመርካታቸው የገለፁት አስተያየት ሰጪዎች የወንጀል ደርጊቱን ከማጠራት እስከ ምርመራና ውሳኔ ድረስ በችግሮች የተተበተበ እንደነበር በመግለፅ ማረሚያ ቤት የፍርድ ውሳኔውን በጥብቅ እንዲተገብረው ጠይቀዋል። 

" የጭካኔ ግድያው የሞት ፍርድ ያሰጥ ነበር " ያሉ ሌሎች አስተያየት ሰጪዎች ደግሞ " የተበዳይ ቤተሰቦች ወደ ቀጣዩ የፍርድ ቤት ይግባኝ ይጠይቁ " ብለዋል።

ከነሀሴ 2015 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሀምሌ 4/2017 ዓ.ም የተጓዘው የእንስት ዘውዱ ሃፍቱ ግድያ በዚሁ ተቋጭቷል ሲል የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ መረጃውን ልኳል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ የእንስቷን ግድያ ከመነሻው እስከ ፍርድ ሂደቱ ሲከታተል ቆይቷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
2.11K👏453🙏121😡71😭56🕊44😢17😱16💔14🥰6🤔2
TIKVAH-ETHIOPIA
#ጥቆማ (ለሚመለከተው አካል - አዲስ አበባ) " በሰውና መኪና ላይ ወድቆ ጉዳት እንዳይደርስ መፍትሄ ይፈለግለት ! " " ይህ በቪድዮው ላይ የምትመለከቱት የመብራት ኮንክሪት ፖል ታቹ ተበልቶ አልቆ ለመውደቅ ጫፍ ላይ ደርሷል። ከጎኑ ትራንስፎርመርንም አለ። ቦታው ከጋርመንት ወደ ጀሞ አንድ ሲኬድ መብራት ተሻግሮ (ቫርኔሮ የመኖሪያ መንደር አካባቢ) ዘመን ማደያ ጋር ነው ሲሆን ብዙ ሰው የሚመላለስበት…
#Update

አ/አ ከጋርመንት ወደ ጀሞ አንድ ሲኬድ መብራት ተሻግሮ (ቫርኔሮ የመኖሪያ መንደር አካባቢ) ዘመን ማደያ ጋር የመብራት ኮንክሪት ፖል ለመውደቅ ጫፍ ላይ መድረሱን በመጠቆም መፍትሔ ይፈለግለት ሲሉ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦች መጠየቃቸው ይታወሳል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በደረሰው መረጃ መሰረት ይህንን ፖል የመቀየር ሥራ በምሽት እየተሰራ ይገኛል።

" ባለሞያዎቻችን አሁንም እዛው ሳይት ናቸው " ሲል ጥገናው ምሽቱን እየተከናወነ መሆኑን የገለጸልን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ፥ ፖሉ ተበልቶ ሳይሆን በመኪና ተገጭቶ ጉዳት ደርሶበት እንደነበር መረጃውን አጋርቶናል።

@eeuethiopia

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ

@tikvahethiopia
21.5K👏730🙏129🤔21🕊18😡14😢13🥰10😭8
ከ3 ጊዜያት በላይ ሲራዘም የቆየዉ ቶምቦላ ሎቶሪ ዛሬ ይወጣል ተባለ።

የሀዋሳ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ግንባታን ለማጠናቀቅ ታስቦ ለሽያጭ የቀረበዉ ቶምቦላ ሎተሪ ከሶስት ጊዜያት በላይ ሲራዘም ቆይቶ ዛሬ በብሔራዊ ሎተሪ አደራሽ እንደሚወጣ የሀዋሳ ከተማ የሕብረተሰብ ተሳትፎ ልማት ፈንድ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ዘሪሁን ቃሚሶ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታውቀዋል።

አስቀድሞ ጥር ‎20/2017 ዓ/ም ከዚያም ሚያዚያ 19 ቀን 2017 ዓ.ም ሌላ ጊዜ ደግሞ ሰኔ 30/2017 ዓ/ም ዕጣዉ እንደሚወጣ ተገልፆ ሲራዘም የቆየዉ ሎተሪ 500 ሺህ ትኬቶች ለገበያ የቀረቡ ሲሆን 1 መቶ ሚሊዮን ብር ለመሰብሰብም ዕቅድ ተይዞበት ነበር።

" ሶስቱንም ዙሮች ትኬቶቹ በበቂ ሁኔታ ስላልተሸጡና በተለያዩ አከባቢዎች የተሰራጩ የቲኬት ወረቀቶችም ተሰብስበዉ ስላላለቁ " በሚል መውጫው ሲራዘም ነበር ተብሏል።

250 ካ.ሜ ለንግድ እና 200 ካ.ሜ ለመኖሪያ የሚሆን መሬትን ጨምሮ ኩዊት ባጃጅ፣ ሞተር፣ ቴሌቪዥን፣ ፍሪጅ ዕጣ የሚወጣባቸው ሲሆኑ 14 ዕድለኞች ይታወቃሉ።

#Update ዕጣው ወጥቷል።

በዚህ መሰረት፦
‎1ኛ ዕጣ 0189833 ➡️ 250 ካሬ ለንግድ አገልግሎት የሚሆን መሬት
‎2ኛ  ዕጣ 0385625 ➡️ ለመኖሪ አገልግሎት የሚሆን መሬት
‌‎3ኛ ዕጣ 0122191 ➡️ ኪዉ ባጃጅ
‎4ኛ ዕጣ 0274157 ➡️ ባለ 3 እግር ባጃጅ
‌‎5ኛ ዕጣ 0043656 ➡️ አፓች ሞተር ሣይክል
‎6ኛ ዕጣ 0116134 ➡️ ኤል (ሊፋን) ሞተር ሣይክል
‎7ኛ ዕጣ 0176687 ➡️ ማቀዝቀዣ ፍሪጅ
‎8ኛ ዕጣ 0185323 ➡️ HP Cori i5 ላፕቶፕ
‎9ኛ ዕጣ  0367397 / 0023129 ➡️ ለሁለት ሰዎች 54 ኢንች ቴሌቪዥን
‎10ኛ ዕጣ 0480480 ፣ 0263409፣  0041937፣ 0208319፣ 0273773 ➡️ ለ5ቱ ለእያንዳንዳቸው ሞባይል ቀፎ

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamliyHawassa

@tikvahethiopia
354😡38🙏20😭12😢6🥰5💔2
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

" ዛሬ ወሬ የለም " - ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ

የሃይማኖት አባቶች ልዑክ በመቐለ !


ከአዲስ አበባ ተነስቶ በጥዋቱ ትግራይ ክልል መቐለ አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፍያ የደረሰው የሃይማኖት አባቶች ልዑክ ከሁሉም የሃይማኖት ተቋማት የተወጣጣ ሲሆን አጠቃላይ ልዑኩ ከ20 በላይ አባላት አሉት።

የሰላም ልኡኩ ከአውሮፕላን ማረፍያ በቀጥታ ወደ መቐለ ፕላኔት ሆቴል አዳራሽ በማመራት በፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀነራል) ከሚመራው የጊዚያዊ አስተዳደሩ የካቢኔ አባላት ጋር #በዝግ ተወያይቷል።

ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጄነራል) ከሰላም ልኡካኑ ጋር የነበራቸውን ቆይታ አጠቃልለው ሲወጡ የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ የሚገኙባቸው የጋዜጠኞች ቡድን መረጃ ፍለጋ ተጠግተው ነበር።

ፕሬዝዳንቱ በሳቅ ታጅበው " ዛሬ ወሬ የለም " በማለት ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

የሰላም ልኡኩ በሆቴሉ ጥቂት ደቂቃዎች እረፍት ወስዶ መልሶ በተመሳሳይ አዳራሽ ከትግራይ ፐብሊክ ዲፕሎማሲ ተወካዮች ጋር ተወያይቷል።

በዚሁ ወቅት በቦታው ላይ የነበሩ ጋዜጠኞች ውይይቱን ለመከታተል ጥያቄ ቢያቀርቡም መከታተል ይቅርና አዳራሹ ውስጥ እንዳይዘልቁና ፎቶም እንዳያነሱ ተከልክለዋል።

ከሰዓት በኃላ ከውይይቱ ተሳታፊዎች በተገኘው መረጃ የሰላም ልኡካኑ በመጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ ተፈናቃዮች ጎብኝተው የማወያየት ፕሮግራም የነበራቸው ቢሆንም ባልታወቀ ምክንያት ይሄ ፕሮግራም ሳይካሄድ ቀርቷል።

የሰላም ልኡኩ ቀጥሎ ከህወሓት ከፍተኛ አመራሮች ነው የተወያየው። ውይይቱ እንደ ጠዋቱ
#በዝግ መካሄዱን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተረድቷል።

የድርጅቱ / የህወሓት ልሳን የሆነው የወይን ጋዜጣ ጋዜጠኞችም ጭምር ወደ ስብሰባው አዳራሽ እንዳይገቡ ተከልክለው ነው ውይይቱ የተካሄደው።

ከአዲስ አበባ የተጓዘው የሰላም ልኡክ ያካሄዳቸው የውይይቱ ርእሰ ጉዳዮች አልታወቁም። ከግምት ባሻገር የተሰጠ ይፋዊ መረጃ የለም። 

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ የሰላም ልኡኩ ቀኑን ሙሉ ከተለያዩ አካላት ጋር ያካሄደውን ውይይት በማስመልከት የሚሰጥ ጋዜጣዊ መግለጫ ይኖር እንደሆነ ለጊዚያዊ አስተዳደሩ የሚድያ ዴስክ ጠይቆ ያገኘው አመርቂ መልስ የለም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

ፎቶ፦ ትግራይ ቴሌቪዥን

@tikvahethiopia
836🕊174🤔50😡29😢22🙏17👏14🥰9😭5
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

የፌደራል ገቢ ግብር አዋጅ ፀደቀ።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፌደራል ገቢ ግብር አዋጅን ለማሻሻል የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ አፀደቀ።

ረቂቅ አዋጁ በአብላጫ ድምጽ ነው የፀደቀው።

ረቂቅ አዋጁ ላይ ሰፊ ክርክር ሲነሳበት እንደነበር ይታወቃል። በተለይ የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማሕበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሰማኮ) ረቂቅ አዋጁ ላይ የደመወዝ ገቢ ግብር መነሻ ተብሎ የተቀመጠው 2,000 ብር ወደ 8,324 ብር ከፍ እንዲል ፤ አጠቃላይ አዋጁ የኑሮ ውድነቱንና ጫናውን ታሳቢ ባደረገ መልኩ እንዲታረም ሲወተውት ነበር።

ከ0 ጀምሮ 10% ፣ 15% ፣ 20% ፣ 25% ፣ 30% ፣ 35% ይቀጥል የነበርው የግብር ምጣኔም በረቂቅ አዋጁ 10% ከመሃል ወጥቶ ከ0 ጀምሮ ቀጥታ ባከፍተኛው 15% መጀመሩንም ታቃውሞ ነበር።

ሌላው 14,100 በላይ የሚያገኝ ሰው 35% ግብር ይከፍላል በሚለው ላይም ጥያቄ ተነስቶ ነበር።

በአሁኑ የኑሮ ውድነት ሰራተኛው በእያንዳንዱ ነገር በምግብ ዋጋ፣ በሚገዛው እቃ 15% ይጨምራል ይሄ በ35% ላይ ሲደመር 50% ይመጣል፤ 7% የጡረታ አለ ሲደመር 57% ከደመወዙ ላይ ይሄዳል በቀረችው 43% ልጆች ያስተምራል ፣ ምግብ ይበላል ፣ ልብስ ይገዛል ፣ ቤት ይከራያል ምንድነው የሚያደርገው ? የሚል የሰራተኛውን ጥያቄ በማንሳት ረቂቁ እንዲታረም ጠይቆ ነበር።

ኮንፌዴሬሽኑ ፤ " መኖር ከማይችል እና በልቶ ከማያድር ሰው ግብር አይሰብሰብም " ብሎም የነበረ ሲሆነ " እንደ ሀገር ግብር መሰብሰብና ልማትም መቀጠል አለበት ፤ የሰው ህይወትም ግን መቀጠል አለበት ፤ ሰው እየተራበ መስራት አይችልም ምርታማ መሆን አይችልም " በማለት ረቂቁ እንዲታረም ብርቱ ጥያቄ አቅርቦ ነበር።

ሌሎችም አካላት ሰፊ ክርክር ሲያደርጉበት የነበረው ረቂቅ አዋጅ በዛሬው ዕለት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአብላጭ ድምጽ ፀድቋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamliyAA

@tikvahethiopia
😭2.23K801😡674💔83👏57😱37🤔34🙏34🥰19😢13🕊5
TIKVAH-ETHIOPIA
ሰኞ ሀምሌ 7/2017 ዓ.ም በትግራይ እንዳስላሰ - ሽረ ከተማ ሁለት እንስቶች አሲድ ተደፍቶባቸው ጉዳት እንደደረሰባቸው ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለመስማት ችሏል። ለጊዜው ስሙ ይፋ ያልተደረገ አንድ ግለሰብ በከተማዋ በሚገኘው አንድ መጠጥ ቤት በሚሰሩ ሁለት እንስቶች ላይ አሲድ በመድፋት ከባድ የአካል ጉዳት አድርሶባቸዋል። ድርጊቱ በርካቶችን አስደንግጧል። የተፈጠረው ምንድነው ? በማለት ቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ…
#Update

በሁለት እንስቶች ላይ አሲድ በመድፋት አረሜናዊ ድርጊት የፈፀመው ተጠርጣሪ " እስካሁን በቁጥጥር ስር አልዋለም " ሲሉ የትግራይ እንዳስላሰ - ሽረ ከተማ ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።

" አሲድ የተደፋባቸው ወገኖች በከፍተኛ ስቃይ ላይ ይገኛሉ " ሲሉ አክለዋል።

አሲድ የተደፋባቸው እንስቶቹ ለተሻለ ህክምና ከእንዳስላሰ - ሽረ ወደ አክሱም ቅድስት ማርያም ሆስፒታል ሪፈር መባላቸውን ገልጸዋል።

ባለፈው ሀምሌ 7/2017 ዓ/ም እስካሁን ማንነቱ ያልታወቀ ግለሰብ በአንድ መጠጥ ቤት በሁለት እንስቶች ላይ አሲድ በመድፋት ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃው ማድረሱ ይታወሳል።

የድርጊቱ ፈፃሚ ግለሰብና ?  አስቃቂ ተግባር የተፈፀመባቸው እንስቶች በምን ሁኔታ እንደሚገኙ ለማጣራት ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ኣባል ዛሬ ሀምሌ 10/2017 ዓ.ም ወደ ከተማዋ ፓሊስ ስልክ ደውሎ ነበር።

ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ የከተማዋ ፓሊስ አመራር " በአካል ወደ ከተማችን ካልመጣችሁ በስቀር በስልክ መረጃ አንሰጥም " በማለት መረጃውን ከልክለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የከተማዋ ነዋሪ ከሆኑ ታማኝ ምንጮቹ ያገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው የጭካኔ ድርጊቱን የፈፀመው ግለሰብ የሚታወቅ የከተማዋ ነዋሪ ሆኖ እያለ እስካሁን በቁጥጥር ስር አለመዋሉ ሁኔታውን አሳሳቢ አድርጎታል።

" ተጠርጣሪ ወንጀለኛው እስካሁን በከተማዋ ተደብቆ እንደሚገኝ የሚሰሙ ጭምጭምታዎች አሉ " ያሉት የቲክቫህ ኢትዮጵያ ምንጮች ፤ ፓሊስ የጭካኔ ድርጊቱ የፈፀመው ግለሰብ አድኖ በመያዝ ህግ እንዲያስከብር አደራ ብለዋል።

የከተማዋ ነዋሪ ተጥርጣሪውን ለፓሊስ አሳልፎ በመስጠት ዜግነታዊ ሃላፊነቱ እንዲወጣም ነዋሪዎቹ ጥሪ አቅርበዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ የእንዳስላሰ - ሽረ ከተማ ፓሊስ ለሚድያ የሚፈቀድ መረጃ በመስጠት እንዲተባበር እየጠየቀ ጉዳዩ ተከታትሎ መዘገቡ እንደሚቀጥል ቃል ይገባል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamliyMekelle

@tikvahethiopia
465😢139😭89😡54🙏18🕊13💔13🤔6😱5👏4🥰3
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
#አርባምንጭ

ተከሳሾች ያቀረቡት የመከላከያ ማስረጃ ዉድቅ ተደርጓል።

የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዛሬ ጠዋት ባካሄደዉ ችሎት የብሔራዊ ቡድን እግር ኳስ ተጫዋች በነበረው አለልኝ አዘነ የግድያ ወንጀል የተጠረጠሩት ባለቤቱና የባለቤቱ እህት ባል ያቀረቡትን የመከላከያ ማስረጃ ሙሉ በሙሉ ዉድቅ በማድረግ የፍርድ ዉሳኔ ለመስጠት ከሰዓት በኋላ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

በርካታ የአርባ ምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ችሎቱን ለመታደም ፍርድ ቤት መጥተዉ የነበረ ቢሆንም የችሎት አደራሽ ከልክ በላይ በመሙላቱ አብዛኛዉ ሰው ከግቢ ዉጪ በመሆን የፍርድ ውሳኔውን በመጠባበቅ እንደሆነ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተመልክቷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በቦታው ተገኝቶ ችሎቱን እየተከታተለ ያለ ሲሆን መረጃዎችን ተከታትሎ የሚያደርስ ይሆናል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አርባ ምንጭ
#TikvahEthiopiaFamliyArbaminch

@tikvahethiopia
863🙏59😢45🕊45👏29😱17😭17🤔16😡15🥰2
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

ፍርድ ቤቱ አለልኝ አዘነ በሰዉ እጅ ስለመገደሉ አረጋግጦ ባለቤቱንና የባለቤቱን እህት ባል ጥፋተኛ ብሎ ብይን ሰጥቷል።

በእግር ኳስ ተጫዋቹ አለልኝ አዘነ ግድያ ላይ ዛሬ በሁለት ፈረቃዎች የፍርድ ውሳኔ ለመስጠት የተሰየመው የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ ተከሳሽ የአለልኝ ባለቤት እና 2ኛ ተከሳሽ የባለቤቱ እህት ባል መጋቢት 17 ቀን 2016 ዓ/ም ከሌሊቱ 5፡30 እስከ 8 ሰዓት ገደማ ባለዉ ጊዜ በአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደር ነጭ ሳር ቀበሌ ልማት ሰፈር ' ሃይላንድ ' ተብሎ በሚጠራው አከባቢ በተቀነባበረ ሁኔታ የ26 አመቱን ወጣት አለልኝ አዘነን በመግደል እራሱን ያጠፋ እንዲመስል በማድረግ የግዲያ ወንጀል መፈፀማቸው በሰውና በሰነድ ማስረጃዎች በመረጋገጡ ጥፋተኛ እንዳላቸው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል መረጃውን ልኳል።

ዛሬ ከሰዓት በኋላ የፍርድ ድሳኔ ለመስጠት ቀጠሮ ይዞ የነበረዉ የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት መደበኛ ችሎት የዐቃቤ ሕግና የተከሳሾችን ጠበቃ የቅጣት አስተያየት ካደመጠ በኋላ ዉሳኔዉን ወደ ሀምሌ 15/2017 ዓ/ም አሸጋግሯል።


ምን የሚሉ የቅጣት አስተያየቶች ተሰጡ ?

የተከሳሾች ጠበቃ (የቅጣት ማቅለያ) ፦
👉 ተከሳሾች የወንጀል ሪከርድ የሌለባቸው መሆኑን
👉 የቤተሰብ አስተዳዳሪ መሆናቸዉንና
👉 1ኛ ተከሳሽ የሟች አለልኝ አዘነ ባለቤት የአስም ታማሚ መሆኗ በቅጣት ማቅለያነት አቅርቧል።

የጋሞ ዞን ከፍተኛ ዐቃቤ ሕግ (የቅጣት ማክበጃ) ፦
ዐቃቤ ሕግ የወንጀል አወሳሰን መመሪያ ማንዋል 03/2017ዓ/ም እና የወንጀል ሕጉን አንቀፅ 84 (1) ለ፣ ሐ፣ ሠ በመጥቀስ
➡️ የአገዳደሉ አደገኛነት
➡️ ወንጀል ፈፃሚዎች ለወንጀል ድርጊቱ የመረጡት ሰዓት አሳቻና ሰዎች የማይደርሱበትን ሰዓት መሆኑን
➡️ በዘመድ ላይ የተፈፀመ የጭካኔ ወንጀል መሆኑን በመግለፅ እንዲሁም ሟቹ አለልኝ አዘነ ለብሔራዊ ቡድኑ (ለሀገር) ሲሰጥ የነበረዉን ግልጋሎት ከግምት ዉስጥ በማስገባት ፍርድ ቤቱ ቅጣቱን እንዲያከብድ ጠይቋል።

የግራ ቀኙን የቅጣት አስተያየት ያደመጠዉ ፍርድ ቤት የፍርድ ቅጣት እርከኑን ለመወሰን ለሀምሌ 15/2017 ዓ/ም ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱን የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ከስፍራው መረጃውን ልኳል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አርባ ምንጭ
#TikvahEthiopiaFamliyArbaminch

@tikvahethiopia
1.1K😭506💔104😡50🙏42🕊20👏19😱16😢7🥰5🤔4