#ፓርላማ
አበባው ደሳለው (ዶ/ር) የጠየቁት ምን ነበር ?
➡ በመላው ሀገሪቱ ያለው ጅምላ የንጹሃን ግድያ፣ ህጋወጥ ጅምላ እስር፣እገታ፣ ጾታዊ ጥቃት፣ መፈናቀል፣ ከፍተኛ የኑሮ ውድነት ፣ አግባብ ያልሆነ የቤቶች ፈረሳ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
➡ በአሁን ሰዓት በመላ ሀገሪቱ ከፍተኛ የህዝብ ብሶት አለ።
➡ በአማራ ክልል ያለው ችግር አጠቃላይ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ እና ማህበራዊ ህይወት ምስቅልቅል እንዲሆን ያደረገ ነው።
➡ በአማራ ክልል የመንግስት ኃይሎች ፀጥታውን በ2 ወር ጊዜ ውስጥ ለመቆጣጠር ነበር ዘመቻ የጀመሩት ነገር ይኸው ከአንድ ዓመት በላይ ሆነ እንጂ ችግሩ ይበልጥ እየከፋ ሄደ እንጂ እየተሻሻለ አይደለም።
➡ አማራ ክልል ንጹሃን ዜጎች በከባድ መሳሪያ እና በድሮን እየሞቱ ነው፣ሲቪል ተቋማት የሆኑ ጤና ጣቢያዎች፣ትምህርት ቤቶች እየወደሙ ነው።
➡ በአዲስ አበባ፣ በአማራ ክልልና በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች እስር ቤቶች የተጨናነቁት ያለ ፍርድ በታጎሩት አማራዎች ነው።
➡ ፖለቲከኞች፣ጋዜጠኞች፣አንቂዎች ለ2 ዓመት ያክል ያለ ፍርድ የተቀመጡ አሉ በወይኒ ቤቶች።
➡ አቶ ክርስቲያን ታደለን ጨምሮ የክልል ም/ቤቶች አባላት ሳይቀሩ ከአንድ አመት በላይ ሆነ ተብሎ በሚመስል ሁኔታ ያለ ፍርድ እየተመላለሱ ነው።
➡ መንግስት የሰላምና ፀጥታ ችግሩን ለመፍታት እየሄደ ያለው አካሄድ እስካሁን ወታደራዊ ነው፤ ፖለቲካዊ አካሄድ ለምን አልደፈረም? ለምንድነው ፖለቲካዊ መፍትሄ ላይ የደከመው?
➡ ለእውነተኛ ድርድርና ውይይት በይፋ ጥሪ አቅርቦ ችግሩን ለምንድነው ለመፍታት የማይጠጋው?
➡ የሰላም መፍትሄ አካል አንዱ የጅምላ እስር፣ የጅምላ ግድያ ማቆም ነው። ይሄ መቼ ነው የሚቆመው ?
የጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ምላሽ ምንድነው ?
🔵 ከኃይል ይልቅ ሰላም እጅግ በጣም አዋጭ ነው።
🔵 እኛ ከማንም በላይ ሰላም እንፈልጋለን።
🔵 ከልጅነት አንስቶ ክላሽ ተሸክመን ስለኖርን ጉዳቱ ይገባናል። ጦርነትን በወሬ ሳይሆን በተግባር እናውቀዋለንና አንፈልገውም። ብዙዎችን ቀጥፎብናል አንፈልገውም።
🔵 ህልም አለን በዚህ ሀገር የሚጨበጥ ለውጥ ለማምጣት ለዛ ሰላም ያስፈልጋል።
🔵 ' የሰላም አማራጭ አትመርጡም በግልጽ አታውጁም? ' ለተባለው በተደጋጋሚ ማወጃችንን እናተም ህዝቡም ያውቃል።
🔵 የሀገር ሽማግሌዎችን ልከን በእንብርክክ መመለሳቸውን እናተም እኛም እናውቃለን።
🔵 አሁንም ቢሆን በሰላም በኩል እርሶ (ዶ/ር አበባው) እኛንና የሚቃወሙትን ማቀራረብ ከቻሉ በሩ ክፍት ነው። የምንፈልገው ሰላም ነው። አነጋግረው ያምጧቸው።
🔵 በአማራም ሆነ በኦሮሚያ ከሚንቀሳቀሱ ኃይሎች ጋር ንግግር አለ ግን ንግግር የሚያደርጉትን እና ሰላም የሚፈልጉትን ሰዎች ' እንዴት ትነጋገራለህ ከዚህ መንግስት ጋር? ' ብለው የሚወቅሱ ሰዎች አሉ። እዚህም አሉ፤ እዛም አሉ። በዚህም ምክንያት ሰላም ፈላጊዎቹ ደበቅ ይላሉ።
🔵 መጠየቅ ብቻ አይደለም ንግግርም ጀምረናል። ለቀረው እርስዎም (ዶ/ር አበባውን) ያግዙን።
🔵 የምንፈልገው ሰላም ነው። አንድ ወንድም ገለን ምን እናገኛለን ? በዚያ መንገድ ማንም እንደማያሸንፈን እናውቃለን። ምንም ! ስጋት ኖሮብን አይደለም። ግን መገዳደል ምን ፋይዳ አለው ? አይጠቅምም።
🔵 ' በ2 ወር እንቆጣጠራለን ብላችሁ ገብታችሁ ' የሚለው ምኑን እንቆጣጠራለን ክልሉን በህጋዊ መንገድ በምርጫ ያሸነፍንበት ክልል ነው። ምንድነው? ከማን ነው? የምንቆጣጠረው። በአንጻሩ ያልተሳካው " በሁለት ሳምንት ይሄን አረፋ መንግስት አባርሬ 4 ኪሎ የአባቶቼን ርዕስት እወርሳለሁ " ያለው አልተሳካለትም። እንጂ አማራ ክልል ክልላችን ነው የአማራ ህዝብ ህዝባችን ነው። ምንም የምንቆጣጠረው አብረን ነው የኖርነው አብረን ነው ያታገልነው አብረን እኖራለን። 2 ወር 3 ወር የሚል እቅድ ከኛ ሳይሆን እኛን በቀላሉ ለመገፍተር ካሰቡ ሰዎች የመጣ ነው።
🔵 የአማራ እስር፣ ጉዳት፣ ችግር የሚለው የቁጫም ችግር ነው፣ የኦሮሞም ሲጠየቅ ችግር ነው ይሄ የሰፈሩን ብቻ የሚያስብ ኃይል ሁል ጊዜ እንደዛ ነው። የራሱን ብቻ ነው የሚያየው።
🔵 አማራን ባለፉት 6 ዓመታት የኢንዱስትሪ ማዕከል አድርገናታል። የማያምን ኮምቦልቻ፣ ደብረ ብርሃን፣ ባህር ዳር፣ ቡሬ ሄዶ ይቁጠር። ጨርቃ ጨርቅ፣ ሲሚንቶ፣ ማርብል፣ ግራናይት የዘይት ፋብሪካ ብዙ ብር አግዘን አማራ ክልል አቋቁመናል።
🔵 አማራ ክልል የብልጽግና መንግስት የፈጠረውን ኢንዱስትሪ በየትኛውም መንግስት አግኝቶ አያውቅም። በወሬ ስለተደባበቅ እንዳትሸወዱ።
🔵 ሁሉም ባይሟላም በመንገድ ዘርፍ ብዙ ስራ ተሰርቷል።
🔵 ባህር ዳር እኛን ሳይመርጠን በስራ ማስመስከር ስላለብን በኢትዮጵያ ሰርተን የማናቀውን ድልድይ ሰርተናል፣ መንገድ እየሰራን ነው፣ ኮሪደር ልማት፣ ኢንዱስትሪ ፓርክ ያለው ባህር ዳር ነው። ህዝባችን ሰርቪሱ ይገባዋል ብለን ስለምናስብ።
🔵 ጎንደር ቢሄዱ ያን ስልጡን ህዝብና ሀገር ከ70 እና 80 ዓመት በኃላ ዞር ብሎ የሚያየው መንግስት ያገኘው አሁን ነው። ፋሲል ቀንና ማታ እየተገነባ ነው፣ መስቀል አደባባይ የአዲስ አበባውን መስቀል አደባባይ በሚያክል መንገድ እየተገነባ ነው። ፓያሳ እያሸበረቀ ነው። መገጭን 18 ዓመት ከቆመ በኃላ 7 ቢሊዮን ብር መድበን ቀንና ማታ እየሰራን ነው።
🔵 ሃይቅን እየሰራን ነው፣ ጎርጎራን ሰርተናል።
🔵 ማዳበሪያ በከፍተኛ ሁኔታ በቀበሌው እያዳረስን ነው።
🔵 አማራ ክልል ልማት ነው እየሰራን ያለነው። እንደ ልብ እንዳንሰራ ግን የሚያደናቅፉን ሰዎች አሉ። እርሶ ያግዝኑንና ሰዎቹ ይመለሱ።
🔵 ፋሲልን የምንሰራው፣ ማዳበሪያ የምናዳርሰው በወታደራዊ እጀባ ነው። እንዴት ነው አሳሪ መንግስት የሚሆነው? ተቀናኛን የሚባለው ልማት የሚያደናቅፍ፣ ተማሪ የሚያደናቅፍ ነው።
🔵 ህዝቡ ማን እንደሚሰራ ማን እንደሚያወራ ያውቃል።
🔵 ሰላሙን እርሶም ጓደኞቾም ይሞክሩ፤ ይምጡ! ይመልሱ! ልማቱን ደግሞ ልክ እኛ ለምነን እንደምንሰራው (አዋሬ፣ ገበታ ለሀገር) እርሶም ፓርቲዎም ለምነው ተባብረን አማራን ወደ ልማት እናስገባው።
🔵 ጎርጎራን በወታደር ጠብቀን ነው የሰራነው ፣ ጎንደር ፒያሳን የምናድሰው ከኳሪ ሲሚንቶ ለማምጣት በወታደር አስጠብቀን ነው፤ ከየትኛው ወራሪ ሀገር ነው የምንጠብቀው ? ጎንደር እንዳይለማ፣ ባህር ዳር እንዳይለማ ፣ ወሎ እንዳይለማ የሚያደርገው የዚያው ሰፈር ሰው ነው።
🔵 አማራ ክልል እንዲቀየር እየሞከርን ነው።
🔵 ጋዜጠኛ አንቂ ለተባለው ጉዳይ አንድ እግር ሲኦል አንድ እግር ገነት አኑሮ መቀመጥ ሚቻል አይመስለኝም። ወይም የገነትን ፍሬ መብላት ወይም የሲኦልን እሳት መቅመስ ነው። አንዳንድ ሰዎች እዚህም ሰላም ውስጥ አሉ እዛም ጦርነት ውስጥ አሉ። የመረጃ ችግር ያለብን እንዳይመስላችሁ።
🔵 በጅምላ የፓርላማ አባላት፣ በጅምላ የፖለቲካ ሰዎችን የምናስር ከሆነ እርሶም ይታሰሩ ነበር። በጅምላ አይደለም በግብር ነው ሰው የሚታሰረው።
🔵 የግል ምርጫዬን ከጠየቁኝ እኔ ቢቀር ነው የምለው። ይቅር ተባብለን፣ ትተን፣ በደለኛ ካለ ክሰን በሰላም ሀገራችንን እናልማ። ከዚህም ይውጣ፣ ከዩኒቨርሲቲም ይውጣ ከከተማ እስር አይጠቅምም ግን መንግስት ነን፤ መኖሪያ ቤት እንገነባለን ማረሚያ ቤትም እንገነባለን።
🔵 "አሁንም ይናገሩ" ለተባለው ሁሌም በራችን ክፍት ነው። ሞከረናል የአማራ አካባቢ ሰዎችን አነጋግረናል፤ ሽማግሌ ልከናል። በአፍሪካ ህብረት፣ በኢጋድም ሙከራ ይደረጋል። እርሶም ቢያደርጉ በደስታ እንቀበላለን።
@tikvahethiopia
አበባው ደሳለው (ዶ/ር) የጠየቁት ምን ነበር ?
➡ በመላው ሀገሪቱ ያለው ጅምላ የንጹሃን ግድያ፣ ህጋወጥ ጅምላ እስር፣እገታ፣ ጾታዊ ጥቃት፣ መፈናቀል፣ ከፍተኛ የኑሮ ውድነት ፣ አግባብ ያልሆነ የቤቶች ፈረሳ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
➡ በአሁን ሰዓት በመላ ሀገሪቱ ከፍተኛ የህዝብ ብሶት አለ።
➡ በአማራ ክልል ያለው ችግር አጠቃላይ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ እና ማህበራዊ ህይወት ምስቅልቅል እንዲሆን ያደረገ ነው።
➡ በአማራ ክልል የመንግስት ኃይሎች ፀጥታውን በ2 ወር ጊዜ ውስጥ ለመቆጣጠር ነበር ዘመቻ የጀመሩት ነገር ይኸው ከአንድ ዓመት በላይ ሆነ እንጂ ችግሩ ይበልጥ እየከፋ ሄደ እንጂ እየተሻሻለ አይደለም።
➡ አማራ ክልል ንጹሃን ዜጎች በከባድ መሳሪያ እና በድሮን እየሞቱ ነው፣ሲቪል ተቋማት የሆኑ ጤና ጣቢያዎች፣ትምህርት ቤቶች እየወደሙ ነው።
➡ በአዲስ አበባ፣ በአማራ ክልልና በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች እስር ቤቶች የተጨናነቁት ያለ ፍርድ በታጎሩት አማራዎች ነው።
➡ ፖለቲከኞች፣ጋዜጠኞች፣አንቂዎች ለ2 ዓመት ያክል ያለ ፍርድ የተቀመጡ አሉ በወይኒ ቤቶች።
➡ አቶ ክርስቲያን ታደለን ጨምሮ የክልል ም/ቤቶች አባላት ሳይቀሩ ከአንድ አመት በላይ ሆነ ተብሎ በሚመስል ሁኔታ ያለ ፍርድ እየተመላለሱ ነው።
➡ መንግስት የሰላምና ፀጥታ ችግሩን ለመፍታት እየሄደ ያለው አካሄድ እስካሁን ወታደራዊ ነው፤ ፖለቲካዊ አካሄድ ለምን አልደፈረም? ለምንድነው ፖለቲካዊ መፍትሄ ላይ የደከመው?
➡ ለእውነተኛ ድርድርና ውይይት በይፋ ጥሪ አቅርቦ ችግሩን ለምንድነው ለመፍታት የማይጠጋው?
➡ የሰላም መፍትሄ አካል አንዱ የጅምላ እስር፣ የጅምላ ግድያ ማቆም ነው። ይሄ መቼ ነው የሚቆመው ?
የጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ምላሽ ምንድነው ?
🔵 ከኃይል ይልቅ ሰላም እጅግ በጣም አዋጭ ነው።
🔵 እኛ ከማንም በላይ ሰላም እንፈልጋለን።
🔵 ከልጅነት አንስቶ ክላሽ ተሸክመን ስለኖርን ጉዳቱ ይገባናል። ጦርነትን በወሬ ሳይሆን በተግባር እናውቀዋለንና አንፈልገውም። ብዙዎችን ቀጥፎብናል አንፈልገውም።
🔵 ህልም አለን በዚህ ሀገር የሚጨበጥ ለውጥ ለማምጣት ለዛ ሰላም ያስፈልጋል።
🔵 ' የሰላም አማራጭ አትመርጡም በግልጽ አታውጁም? ' ለተባለው በተደጋጋሚ ማወጃችንን እናተም ህዝቡም ያውቃል።
🔵 የሀገር ሽማግሌዎችን ልከን በእንብርክክ መመለሳቸውን እናተም እኛም እናውቃለን።
🔵 አሁንም ቢሆን በሰላም በኩል እርሶ (ዶ/ር አበባው) እኛንና የሚቃወሙትን ማቀራረብ ከቻሉ በሩ ክፍት ነው። የምንፈልገው ሰላም ነው። አነጋግረው ያምጧቸው።
🔵 በአማራም ሆነ በኦሮሚያ ከሚንቀሳቀሱ ኃይሎች ጋር ንግግር አለ ግን ንግግር የሚያደርጉትን እና ሰላም የሚፈልጉትን ሰዎች ' እንዴት ትነጋገራለህ ከዚህ መንግስት ጋር? ' ብለው የሚወቅሱ ሰዎች አሉ። እዚህም አሉ፤ እዛም አሉ። በዚህም ምክንያት ሰላም ፈላጊዎቹ ደበቅ ይላሉ።
🔵 መጠየቅ ብቻ አይደለም ንግግርም ጀምረናል። ለቀረው እርስዎም (ዶ/ር አበባውን) ያግዙን።
🔵 የምንፈልገው ሰላም ነው። አንድ ወንድም ገለን ምን እናገኛለን ? በዚያ መንገድ ማንም እንደማያሸንፈን እናውቃለን። ምንም ! ስጋት ኖሮብን አይደለም። ግን መገዳደል ምን ፋይዳ አለው ? አይጠቅምም።
🔵 ' በ2 ወር እንቆጣጠራለን ብላችሁ ገብታችሁ ' የሚለው ምኑን እንቆጣጠራለን ክልሉን በህጋዊ መንገድ በምርጫ ያሸነፍንበት ክልል ነው። ምንድነው? ከማን ነው? የምንቆጣጠረው። በአንጻሩ ያልተሳካው " በሁለት ሳምንት ይሄን አረፋ መንግስት አባርሬ 4 ኪሎ የአባቶቼን ርዕስት እወርሳለሁ " ያለው አልተሳካለትም። እንጂ አማራ ክልል ክልላችን ነው የአማራ ህዝብ ህዝባችን ነው። ምንም የምንቆጣጠረው አብረን ነው የኖርነው አብረን ነው ያታገልነው አብረን እኖራለን። 2 ወር 3 ወር የሚል እቅድ ከኛ ሳይሆን እኛን በቀላሉ ለመገፍተር ካሰቡ ሰዎች የመጣ ነው።
🔵 የአማራ እስር፣ ጉዳት፣ ችግር የሚለው የቁጫም ችግር ነው፣ የኦሮሞም ሲጠየቅ ችግር ነው ይሄ የሰፈሩን ብቻ የሚያስብ ኃይል ሁል ጊዜ እንደዛ ነው። የራሱን ብቻ ነው የሚያየው።
🔵 አማራን ባለፉት 6 ዓመታት የኢንዱስትሪ ማዕከል አድርገናታል። የማያምን ኮምቦልቻ፣ ደብረ ብርሃን፣ ባህር ዳር፣ ቡሬ ሄዶ ይቁጠር። ጨርቃ ጨርቅ፣ ሲሚንቶ፣ ማርብል፣ ግራናይት የዘይት ፋብሪካ ብዙ ብር አግዘን አማራ ክልል አቋቁመናል።
🔵 አማራ ክልል የብልጽግና መንግስት የፈጠረውን ኢንዱስትሪ በየትኛውም መንግስት አግኝቶ አያውቅም። በወሬ ስለተደባበቅ እንዳትሸወዱ።
🔵 ሁሉም ባይሟላም በመንገድ ዘርፍ ብዙ ስራ ተሰርቷል።
🔵 ባህር ዳር እኛን ሳይመርጠን በስራ ማስመስከር ስላለብን በኢትዮጵያ ሰርተን የማናቀውን ድልድይ ሰርተናል፣ መንገድ እየሰራን ነው፣ ኮሪደር ልማት፣ ኢንዱስትሪ ፓርክ ያለው ባህር ዳር ነው። ህዝባችን ሰርቪሱ ይገባዋል ብለን ስለምናስብ።
🔵 ጎንደር ቢሄዱ ያን ስልጡን ህዝብና ሀገር ከ70 እና 80 ዓመት በኃላ ዞር ብሎ የሚያየው መንግስት ያገኘው አሁን ነው። ፋሲል ቀንና ማታ እየተገነባ ነው፣ መስቀል አደባባይ የአዲስ አበባውን መስቀል አደባባይ በሚያክል መንገድ እየተገነባ ነው። ፓያሳ እያሸበረቀ ነው። መገጭን 18 ዓመት ከቆመ በኃላ 7 ቢሊዮን ብር መድበን ቀንና ማታ እየሰራን ነው።
🔵 ሃይቅን እየሰራን ነው፣ ጎርጎራን ሰርተናል።
🔵 ማዳበሪያ በከፍተኛ ሁኔታ በቀበሌው እያዳረስን ነው።
🔵 አማራ ክልል ልማት ነው እየሰራን ያለነው። እንደ ልብ እንዳንሰራ ግን የሚያደናቅፉን ሰዎች አሉ። እርሶ ያግዝኑንና ሰዎቹ ይመለሱ።
🔵 ፋሲልን የምንሰራው፣ ማዳበሪያ የምናዳርሰው በወታደራዊ እጀባ ነው። እንዴት ነው አሳሪ መንግስት የሚሆነው? ተቀናኛን የሚባለው ልማት የሚያደናቅፍ፣ ተማሪ የሚያደናቅፍ ነው።
🔵 ህዝቡ ማን እንደሚሰራ ማን እንደሚያወራ ያውቃል።
🔵 ሰላሙን እርሶም ጓደኞቾም ይሞክሩ፤ ይምጡ! ይመልሱ! ልማቱን ደግሞ ልክ እኛ ለምነን እንደምንሰራው (አዋሬ፣ ገበታ ለሀገር) እርሶም ፓርቲዎም ለምነው ተባብረን አማራን ወደ ልማት እናስገባው።
🔵 ጎርጎራን በወታደር ጠብቀን ነው የሰራነው ፣ ጎንደር ፒያሳን የምናድሰው ከኳሪ ሲሚንቶ ለማምጣት በወታደር አስጠብቀን ነው፤ ከየትኛው ወራሪ ሀገር ነው የምንጠብቀው ? ጎንደር እንዳይለማ፣ ባህር ዳር እንዳይለማ ፣ ወሎ እንዳይለማ የሚያደርገው የዚያው ሰፈር ሰው ነው።
🔵 አማራ ክልል እንዲቀየር እየሞከርን ነው።
🔵 ጋዜጠኛ አንቂ ለተባለው ጉዳይ አንድ እግር ሲኦል አንድ እግር ገነት አኑሮ መቀመጥ ሚቻል አይመስለኝም። ወይም የገነትን ፍሬ መብላት ወይም የሲኦልን እሳት መቅመስ ነው። አንዳንድ ሰዎች እዚህም ሰላም ውስጥ አሉ እዛም ጦርነት ውስጥ አሉ። የመረጃ ችግር ያለብን እንዳይመስላችሁ።
🔵 በጅምላ የፓርላማ አባላት፣ በጅምላ የፖለቲካ ሰዎችን የምናስር ከሆነ እርሶም ይታሰሩ ነበር። በጅምላ አይደለም በግብር ነው ሰው የሚታሰረው።
🔵 የግል ምርጫዬን ከጠየቁኝ እኔ ቢቀር ነው የምለው። ይቅር ተባብለን፣ ትተን፣ በደለኛ ካለ ክሰን በሰላም ሀገራችንን እናልማ። ከዚህም ይውጣ፣ ከዩኒቨርሲቲም ይውጣ ከከተማ እስር አይጠቅምም ግን መንግስት ነን፤ መኖሪያ ቤት እንገነባለን ማረሚያ ቤትም እንገነባለን።
🔵 "አሁንም ይናገሩ" ለተባለው ሁሌም በራችን ክፍት ነው። ሞከረናል የአማራ አካባቢ ሰዎችን አነጋግረናል፤ ሽማግሌ ልከናል። በአፍሪካ ህብረት፣ በኢጋድም ሙከራ ይደረጋል። እርሶም ቢያደርጉ በደስታ እንቀበላለን።
@tikvahethiopia
#RedSea
" ዓለም ዛሬ ይስማ የቀይ ባህር አክሰስ ሰላማዊ በሆነ መንገድ ኢትዮጵያ ያስፈልጋታል " - ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር)
🟢 " ወይ እኛ ወይም ልጆቻችን ይህንን ያሳኩታል "🟢
የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ጠቅላይ ሚኒስትሩ " ኢትዮጵያ የማይናወጥ ብሔራዊ ጥቅም አላት ዓለም ዛሬ ይስማ የቀይ ባህር አክሰስ ሰላማዊ በሆነ መንገድ ኢትዮጵያ ያስፈልጋታል " ሲሉ በዛሬው ፓርላማ ላይ ተናግረዋል።
ይህንን ሲናገሩ የፓርላማ አባላት ዘለግ ያለ ከፍተኛ ጭብጨባ አሰምተዋል።
" በዚህ (ቀይ ባህር) ጉዳይ የምንደብቅ የሚመስለው ካለ ተሳስቷል " ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ " በጦርነት ፣ በኃይል አንፈልግም በቂ ሪሶርስ ነው በማንኛውም ህግ በማንኛውም የሀገር ልምምድ ኢትዮጵያ ይገባታል " ብለዋል።
" ብዙዎች እኮ ይላሉ 120 ሚሊዮን ህዝብ መቆለፍ ነውር ነው ይላሉ ፤ አንዳንድ የተገዙ ኢትዮጵያውያን ባይገባቸውም ወይ እኛ ወይ ልጆቻችን ያሳኩታል ፤ ይሄ ምንም ጥርጥር የለውም እውነት ስለሆነና ሎጂካል ነገር ስለሆነ " ሲሉ ተደምጠዋል።
" ይህንን አስታኮ ' ነገ ውጊያ ይነሳል ' ብለው የሚያስቡ ሰዎች አንዋጋም ከማንም ጋር የመዋጋት ፍላጎት የለንም " ሲሉ ተናግረዋል።
" ' ኢትዮጵያን ሊወሩ ይችላሉ ሀገራት ' የሚል ስጋት ያለባቸው ሰዎች አልፎ አልፎ ስለሚነሱ ኢትዮጵያን ማንም ሰው ዛሬ በኃይል መውረር አይችልም ማንም !! " ሲሉ ገልጸዋል።
" ለመመከት የሚያስችል በቂ አቅም አለን። ስንገዛ ስንሸምት የነበርናቸውን በውጊያ ክፍተት የገጠሙንን ነገሮች ማምረት ጀምረናል። እናመርታለን ፣ ሰው አለን ጀግኖች ነን ከነኩን ግን ለማንም አንመለሰም " ብለዋል።
ይህንን ሲናገሩም የፓርላማ አባላት በጭብጨባ አቋርጠዋቸው ነበር።
ኢትዮጵያ የወረራ ስጋት እንደሌለባት የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ " በአጼ ሚኒሊክ ዘመነ መንግሥት ብዙ አቅም ባልነበረበት ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን አድዋ ላይ ሄደው አሸንፈው ነጻነት ማስከበር ከቻሉ ያኔ 5 ሚሊዮን ነበሩ ዛሬ 120 ሚሊዮን ነው የጀግንነት ደሙ እንዳለ ነው ስጋት አይግባችሁ ማንም ቢመጣ አሳፍረን እንመልሳለን እኛ ግን ማንንም አንነከም " ብለዋል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
" ዓለም ዛሬ ይስማ የቀይ ባህር አክሰስ ሰላማዊ በሆነ መንገድ ኢትዮጵያ ያስፈልጋታል " - ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር)
🟢 " ወይ እኛ ወይም ልጆቻችን ይህንን ያሳኩታል "🟢
የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ጠቅላይ ሚኒስትሩ " ኢትዮጵያ የማይናወጥ ብሔራዊ ጥቅም አላት ዓለም ዛሬ ይስማ የቀይ ባህር አክሰስ ሰላማዊ በሆነ መንገድ ኢትዮጵያ ያስፈልጋታል " ሲሉ በዛሬው ፓርላማ ላይ ተናግረዋል።
ይህንን ሲናገሩ የፓርላማ አባላት ዘለግ ያለ ከፍተኛ ጭብጨባ አሰምተዋል።
" በዚህ (ቀይ ባህር) ጉዳይ የምንደብቅ የሚመስለው ካለ ተሳስቷል " ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ " በጦርነት ፣ በኃይል አንፈልግም በቂ ሪሶርስ ነው በማንኛውም ህግ በማንኛውም የሀገር ልምምድ ኢትዮጵያ ይገባታል " ብለዋል።
" ብዙዎች እኮ ይላሉ 120 ሚሊዮን ህዝብ መቆለፍ ነውር ነው ይላሉ ፤ አንዳንድ የተገዙ ኢትዮጵያውያን ባይገባቸውም ወይ እኛ ወይ ልጆቻችን ያሳኩታል ፤ ይሄ ምንም ጥርጥር የለውም እውነት ስለሆነና ሎጂካል ነገር ስለሆነ " ሲሉ ተደምጠዋል።
" ይህንን አስታኮ ' ነገ ውጊያ ይነሳል ' ብለው የሚያስቡ ሰዎች አንዋጋም ከማንም ጋር የመዋጋት ፍላጎት የለንም " ሲሉ ተናግረዋል።
" ' ኢትዮጵያን ሊወሩ ይችላሉ ሀገራት ' የሚል ስጋት ያለባቸው ሰዎች አልፎ አልፎ ስለሚነሱ ኢትዮጵያን ማንም ሰው ዛሬ በኃይል መውረር አይችልም ማንም !! " ሲሉ ገልጸዋል።
" ለመመከት የሚያስችል በቂ አቅም አለን። ስንገዛ ስንሸምት የነበርናቸውን በውጊያ ክፍተት የገጠሙንን ነገሮች ማምረት ጀምረናል። እናመርታለን ፣ ሰው አለን ጀግኖች ነን ከነኩን ግን ለማንም አንመለሰም " ብለዋል።
ይህንን ሲናገሩም የፓርላማ አባላት በጭብጨባ አቋርጠዋቸው ነበር።
ኢትዮጵያ የወረራ ስጋት እንደሌለባት የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ " በአጼ ሚኒሊክ ዘመነ መንግሥት ብዙ አቅም ባልነበረበት ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን አድዋ ላይ ሄደው አሸንፈው ነጻነት ማስከበር ከቻሉ ያኔ 5 ሚሊዮን ነበሩ ዛሬ 120 ሚሊዮን ነው የጀግንነት ደሙ እንዳለ ነው ስጋት አይግባችሁ ማንም ቢመጣ አሳፍረን እንመልሳለን እኛ ግን ማንንም አንነከም " ብለዋል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
#DStvEthiopia
ጥቅምት 19 ቀን 2017 ዓም በኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት አዳራሽ ( ወመዘክር ) በተከናወነው “የአቦል አዳዲስ ይዘቶች ማስተዋወቂያና የአፋፍ ቴሌኖቬላ ማጠናቀቂያ” የአቦል አዳዲስ ተከታታይ ድራማዎች አዘጋጆች በመድረኩ ልምዳቸውንና የአቦልን አስተዋፅኦ ያጋሩ ሲሆን ይዘቶቻቸውንም አስተዋውቀዋል።
አንተህ ኃይሌ ስለ “የእሳት እራት” ቴሌኖቬላ፣ ኑር አክመል ስለ “አሻራ” ቴሌኖቬላ፣ ፌቨን ከተማ ስለ “የልቤ” ድራማ እንዲሁም ኡስማን አወል ስለ ማዲ አቦል ይዘቶች ገለፃ አድርገዋል።
የአቦል አዳዲስ ተከታታይ ድራማዎች አዘጋጆች በመድረኩ ልምዳቸውንና የአቦልን አስተዋፅኦ ያጋሩ ሲሆን ይዘቶቻቸውንም አስተዋውቀዋል።
አንተህ ኃይሌ ስለ “የእሳት እራት” ቴሌኖቬላ፣ ኑር አክመል ስለ “አሻራ” ቴሌኖቬላ፣ ፌቨን ከተማ ስለ “የልቤ” ድራማ እንዲሁም ኡስማን አወል ስለ ማዲ አቦል ይዘቶች ገለፃ አድርገዋል።
መርሃግብሩ አስተዋፅኦ ላደረጉና በአፋፍ የዝግጅት ሂደት ለተሳተፉ ባለሙያዎች የዕውቅና የምስክር ወረቀት በመስጠት ተጠናቋል።
#ሁሉምያለውእኛጋርነው
ጥቅምት 19 ቀን 2017 ዓም በኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት አዳራሽ ( ወመዘክር ) በተከናወነው “የአቦል አዳዲስ ይዘቶች ማስተዋወቂያና የአፋፍ ቴሌኖቬላ ማጠናቀቂያ” የአቦል አዳዲስ ተከታታይ ድራማዎች አዘጋጆች በመድረኩ ልምዳቸውንና የአቦልን አስተዋፅኦ ያጋሩ ሲሆን ይዘቶቻቸውንም አስተዋውቀዋል።
አንተህ ኃይሌ ስለ “የእሳት እራት” ቴሌኖቬላ፣ ኑር አክመል ስለ “አሻራ” ቴሌኖቬላ፣ ፌቨን ከተማ ስለ “የልቤ” ድራማ እንዲሁም ኡስማን አወል ስለ ማዲ አቦል ይዘቶች ገለፃ አድርገዋል።
የአቦል አዳዲስ ተከታታይ ድራማዎች አዘጋጆች በመድረኩ ልምዳቸውንና የአቦልን አስተዋፅኦ ያጋሩ ሲሆን ይዘቶቻቸውንም አስተዋውቀዋል።
አንተህ ኃይሌ ስለ “የእሳት እራት” ቴሌኖቬላ፣ ኑር አክመል ስለ “አሻራ” ቴሌኖቬላ፣ ፌቨን ከተማ ስለ “የልቤ” ድራማ እንዲሁም ኡስማን አወል ስለ ማዲ አቦል ይዘቶች ገለፃ አድርገዋል።
መርሃግብሩ አስተዋፅኦ ላደረጉና በአፋፍ የዝግጅት ሂደት ለተሳተፉ ባለሙያዎች የዕውቅና የምስክር ወረቀት በመስጠት ተጠናቋል።
#ሁሉምያለውእኛጋርነው
TIKVAH-ETHIOPIA
" በአስቸኳይ ተማሪዎቹ መብታቸው ተጠብቆ ወደ ትምህርት ገበታቸው ተመልሰው ያመለጣቸው ትምህርት ይካካስ " - ከፍተኛ ምክር ቤቱ ካለፋት 2 ሳምንታት ወዲህ በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ አንዳንድ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ላይ በአለባበሳቸው ምክንያትና በእምነታቸው ላይ ያነጣጠረ ከእለት ወደ እለት እየሰፋ ያለ ጫናና እንግልት እየተከሰተ መሆኑን የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር…
ዛሬም ድረስ አንዳንድ ተቋማት ኢ-ህገመንግስታዊ የሆኑ የአለባበስ (ድሬሲንግ) ኮዶችን በመጥቀስ ብዙ ሙስሊሞችን በትምህርት፣ በስራ ገበታ ላይ አስተዋፅኦ እንዳያደረጉ እንቅፋት እየሆኑ እንዳሉ የፓርላማ አባሉ ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ ተናግረዋል።
ይህንን ያሉት ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተገኙበት የምክር ቤቱ ስብሰባ ላይ ነው።
ዛሬ እንኳን አሉ ኡስታዝ " ዛሬ እንኳን እኛ እዚህ ቁጭ ብለን ተማሪዎች በኒቃባቸው በሂጃባቸው ምክንያት ከትምህርት ገበታቸው ተገለው አንዳንድ አካባቢዎች እስከ ሁለት ዓመት ድረስ የሄዱ በሺህ የሚቆጠሩ ተማሪዎች አሉ " ሲሉ ተናግረዋል።
ይህ አይነት ድርጊት እጅግ ጎጂ መሆኑን በማንሳት መንግሥት መሰል ድርጊቶች እንዲታረሙ እንዲያደርግ የሚያስገነዝብ ሃሳብና ጥያቄ በይፋ አቅርበዋል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
ይህንን ያሉት ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተገኙበት የምክር ቤቱ ስብሰባ ላይ ነው።
ዛሬ እንኳን አሉ ኡስታዝ " ዛሬ እንኳን እኛ እዚህ ቁጭ ብለን ተማሪዎች በኒቃባቸው በሂጃባቸው ምክንያት ከትምህርት ገበታቸው ተገለው አንዳንድ አካባቢዎች እስከ ሁለት ዓመት ድረስ የሄዱ በሺህ የሚቆጠሩ ተማሪዎች አሉ " ሲሉ ተናግረዋል።
ይህ አይነት ድርጊት እጅግ ጎጂ መሆኑን በማንሳት መንግሥት መሰል ድርጊቶች እንዲታረሙ እንዲያደርግ የሚያስገነዝብ ሃሳብና ጥያቄ በይፋ አቅርበዋል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#AddisAbaba
የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ ቤት ሰሞኑን በከተማው በሚገኙ አንዳንድ ትምህርት ቤቶች ከሙስሊም ሴት ተማሪዎች አለባበስ ጋር በተያያዘ የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት በመዋቅሮቹ አማካኝነት በየደረጃው ተከታታይ ውይይቶችን ሲያደርግ መቆየቱን ገልጿል።
ትላንትና የከፍተኛ ምክር ቤቱ ከፍተኛ አመራሮች እና ስራ አስፈፃሚዎች የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ፓሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር እንዲሁም የትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች በተገኙበት በጉዳዩ ላይ ውይይት መደረጉን ተገልጿል።
በዚሁም መሰረት ችግሩ በተደጋጋሚ እየተከሰተ ያለና ዘላቂ መፍትሔ የሚያሻው ከመሆኑ አንጻር ከፍተኛ ም/ቤቱ ከፌደራል መጅሊስ እንዲሁም ከሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ጋር በመሆን በጉዳዩ ላይ ዘላቂ እልባት የሚያመጣ የመፍትሔ ሀሳብ እንዲያቀርብ ከስምምነት መደረሱ ተነግሯል።
ከወሩ መጀመሪያ አካባቢ ጀምሮ ከትምህርት ገበታ የተገለሉ ተማሪዎችን በተመለከተ ግን በጊዜያዊነት ከመገለላቸው በፊት ይስተናገዱ በነበረበት ሁኔታ ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱና ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ ከስምምነት መደረሱን ምክር ቤቱ ይፋ አድርጓል።
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ ቤት ሰሞኑን በከተማው በሚገኙ አንዳንድ ትምህርት ቤቶች ከሙስሊም ሴት ተማሪዎች አለባበስ ጋር በተያያዘ የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት በመዋቅሮቹ አማካኝነት በየደረጃው ተከታታይ ውይይቶችን ሲያደርግ መቆየቱን ገልጿል።
ትላንትና የከፍተኛ ምክር ቤቱ ከፍተኛ አመራሮች እና ስራ አስፈፃሚዎች የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ፓሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር እንዲሁም የትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች በተገኙበት በጉዳዩ ላይ ውይይት መደረጉን ተገልጿል።
በዚሁም መሰረት ችግሩ በተደጋጋሚ እየተከሰተ ያለና ዘላቂ መፍትሔ የሚያሻው ከመሆኑ አንጻር ከፍተኛ ም/ቤቱ ከፌደራል መጅሊስ እንዲሁም ከሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ጋር በመሆን በጉዳዩ ላይ ዘላቂ እልባት የሚያመጣ የመፍትሔ ሀሳብ እንዲያቀርብ ከስምምነት መደረሱ ተነግሯል።
ከወሩ መጀመሪያ አካባቢ ጀምሮ ከትምህርት ገበታ የተገለሉ ተማሪዎችን በተመለከተ ግን በጊዜያዊነት ከመገለላቸው በፊት ይስተናገዱ በነበረበት ሁኔታ ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱና ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ ከስምምነት መደረሱን ምክር ቤቱ ይፋ አድርጓል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ሌሊት 10 ሰዓት ነው በትዳር አጋሯ የተገደለችው ፤ አንቆ ነው የገደላት " - የትግራይ ምሥራቃዊ ዞን ፖሊስ በትግራይ፣ በውቕሮ ከተማ ድል ባለ ሰርግ ከተሞሸረች በኃላ በአራተኛው ቀን በትዳር አጋሯ ታንቃ ስለተገደለችው ሊዲያ ዓለም ጉዳይ የትግራይ ምሥራቃዊ ዞን ፖሊስ አስተያየቱን ሰጥቷል። ለቢቢሲ አማርኛው ቃላቸውን የሰጡት የትግራይ ምሥራቃዊ ዞን ፖሊስ ኮማንደር ሙሉ ብርሃን ካህሳይ ፥ " ሊዲያ ረቡዕ፣ጥቅምት…
#መቐለ
መቐለ ከተማ ውስጥ በጭካኔ የተገደለች እንስት አስከሬንዋ ከ2 ቀን በኋላ መገኘቱን ፓሊስ አስታውቋል።
የጭካኔ ተግባሩ የት ፣ መቼ ፣ እንዴት ተፈፀመ ?
የጭካኔ ተግባሩ በትግራይ ፣ መቐለ ሓወልቲ ክፍለ ከተማ ዓዲሓ ተብሎ በሚጠራው ልዩ ሰፈር በሚገኝ የአንድ ሆቴል ክፍል ነው የተፈፀመው።
ሓበን የማነ የ19 ዓመት ወጣት ስትሆን በሆቴል ክፍል #በቢላዋ ተገድላ መገኘትዋና ጥቅምት 20 /2017 ዓ.ም ከሰአት በኋላ የቀብርዋ ስነ-ሰርዓት መከናወኑ ተሰምቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል የጭካኔ ተግባሩ የሚመለከት ተጨባጭ መረጃ ለማግኘት ወደ ሓወልቲ ክፍለ ከተማ ፓሊስ ፅህፈት ተጉዟል።
ፓሊስ የጭካኔ ተግባሩ የሚመለከት ዝርዝር መረጃ በማሰብባሰብ ላይ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
የጭካኔ ግድያ ተግባሩ በፍቅኛሞች መካከል መፈፀሙን እና በግድያ ወንጀል የተጠረጠረ ዳዊት ዘርኡ የተባለ ግለሰብ በህግ ቁጥጥር ስር እንዲውል ህዝቡ ጥቆማ በመስጠት እንዲተባበር ጠይቋል።
በተያያዘ በያዝነው ወር የመጀመሪያ ሳምንት ውቕሮ ከተማ ላይ እሁድ ጥቅምት 5 ተድራ ሓሙስ ጥቅምት 7/2017 ዓ.ም በባሏ በጭካኔ የተገደለችው ሙሽሪት ሊድያ ጉዳይ ተጣርቶ ወደ አቃቤ ህግ መተላለፉን የወቕሮ ከተማ ፓሊስ አሳውቋል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
መቐለ ከተማ ውስጥ በጭካኔ የተገደለች እንስት አስከሬንዋ ከ2 ቀን በኋላ መገኘቱን ፓሊስ አስታውቋል።
የጭካኔ ተግባሩ የት ፣ መቼ ፣ እንዴት ተፈፀመ ?
የጭካኔ ተግባሩ በትግራይ ፣ መቐለ ሓወልቲ ክፍለ ከተማ ዓዲሓ ተብሎ በሚጠራው ልዩ ሰፈር በሚገኝ የአንድ ሆቴል ክፍል ነው የተፈፀመው።
ሓበን የማነ የ19 ዓመት ወጣት ስትሆን በሆቴል ክፍል #በቢላዋ ተገድላ መገኘትዋና ጥቅምት 20 /2017 ዓ.ም ከሰአት በኋላ የቀብርዋ ስነ-ሰርዓት መከናወኑ ተሰምቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል የጭካኔ ተግባሩ የሚመለከት ተጨባጭ መረጃ ለማግኘት ወደ ሓወልቲ ክፍለ ከተማ ፓሊስ ፅህፈት ተጉዟል።
ፓሊስ የጭካኔ ተግባሩ የሚመለከት ዝርዝር መረጃ በማሰብባሰብ ላይ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
የጭካኔ ግድያ ተግባሩ በፍቅኛሞች መካከል መፈፀሙን እና በግድያ ወንጀል የተጠረጠረ ዳዊት ዘርኡ የተባለ ግለሰብ በህግ ቁጥጥር ስር እንዲውል ህዝቡ ጥቆማ በመስጠት እንዲተባበር ጠይቋል።
በተያያዘ በያዝነው ወር የመጀመሪያ ሳምንት ውቕሮ ከተማ ላይ እሁድ ጥቅምት 5 ተድራ ሓሙስ ጥቅምት 7/2017 ዓ.ም በባሏ በጭካኔ የተገደለችው ሙሽሪት ሊድያ ጉዳይ ተጣርቶ ወደ አቃቤ ህግ መተላለፉን የወቕሮ ከተማ ፓሊስ አሳውቋል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
#NBE : ዛሬ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ፤ ባንኮች እርስ በርሳቸው የሚበዳደሩበት የገንዘብ ግብይት ይፋ አድርጓል።
ንግድ ባንኮች የአጭር ጊዜ ማለትም ለአንድ ቀን ወይም ለሰባት ቀናት መቆየት የሚችል ገንዘብ መበደርና ማበደር የሚችሉ መሆናቸውንም አብስሯል።
በባንኮች መካከል የሚደረግ የገንዘብ ግብይት መጀመሩ ፦
➡️ ባንኮች የአጭር ጊዜ የገንዘብ ጉድለትን በመሸፈን ወይም ትርፍ ገንዘብን ለሌሎች ባንኮች በማበደር የገንዘብ ፍሰትን በብቃት እንዲያስተዳደሩ ያስችላቸዋል።
➡️ የገንዘብ ግብይቱ የአጭር ጊዜ ማለትም የአንድ ቀን ወይንም የሰባት ቀናት የመክፈያ ጊዜ ያላቸው ብድሮችን ያካትታል ፤ ይህ ባንኮች የአጭር ጊዜ የገንዘብ ጉድለትን በመሸፈን ወይም ትርፍ ገንዘብን ለሌሎች ባንኮች በማበደር የገንዘብ ፍሰትን በብቃት እንዲያስተዳደሩ ያስችላቸዋል።
➡️ የገንዘብ እጥረት ስጋትን በመቀነስና በተረጋጋ የወለድ ተመን ለደንበኞች የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት ያስችላል ሲል ብሔራዊ ባንክ አሳውቋል።
በባንኮች መካከል የሚደረግ የገንዘብ ግብይት በኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ንዋይ ገበያ የግብይት መድረክ ላይ ብቻ እንዲሆ ብሔራዊ ባንክ ፈቅዷል።
(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)
#NBE
@tikvahethiopia
ንግድ ባንኮች የአጭር ጊዜ ማለትም ለአንድ ቀን ወይም ለሰባት ቀናት መቆየት የሚችል ገንዘብ መበደርና ማበደር የሚችሉ መሆናቸውንም አብስሯል።
በባንኮች መካከል የሚደረግ የገንዘብ ግብይት መጀመሩ ፦
➡️ ባንኮች የአጭር ጊዜ የገንዘብ ጉድለትን በመሸፈን ወይም ትርፍ ገንዘብን ለሌሎች ባንኮች በማበደር የገንዘብ ፍሰትን በብቃት እንዲያስተዳደሩ ያስችላቸዋል።
➡️ የገንዘብ ግብይቱ የአጭር ጊዜ ማለትም የአንድ ቀን ወይንም የሰባት ቀናት የመክፈያ ጊዜ ያላቸው ብድሮችን ያካትታል ፤ ይህ ባንኮች የአጭር ጊዜ የገንዘብ ጉድለትን በመሸፈን ወይም ትርፍ ገንዘብን ለሌሎች ባንኮች በማበደር የገንዘብ ፍሰትን በብቃት እንዲያስተዳደሩ ያስችላቸዋል።
➡️ የገንዘብ እጥረት ስጋትን በመቀነስና በተረጋጋ የወለድ ተመን ለደንበኞች የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት ያስችላል ሲል ብሔራዊ ባንክ አሳውቋል።
በባንኮች መካከል የሚደረግ የገንዘብ ግብይት በኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ንዋይ ገበያ የግብይት መድረክ ላይ ብቻ እንዲሆ ብሔራዊ ባንክ ፈቅዷል።
(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)
#NBE
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኦርቶዶክስተዋሕዶ " ...አለመግባባት በዝቷል፤ ማኵረፍና መቀያየም ሰፍቷል ፤ ነገሩ ሁሉ ግራ የሚያጋባና የተመሰቃቀለ ሆኖ ይታያል፡፡ ችግሩ ከሕዝብ አልፎ የአምልኮ ስፍራዎችንና የአምልኮው ፈጻሚዎችን ዒላማ ያደረገ እግዚአብሔርን መዳፈር እየተለመደ መጥቷል " - ቅዱስነታቸው የጥቅምት 2017 ዓ/ም የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ተጀመረ። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተወሕዶ ቤተክርስቲያን ሁለንተናዊ አገልግሎትና የስራ…
#ቅዱስሲኖዶስ
" በጦርነትና በግጭት የመጣ ሰላም፣ የተገነባ ሀገር የለም !! ... ችግሩ በእርቅ እንዲፈታ ለሁሉም ወገኖቻችን የሰላም ጥሪ እናቀርባለን " - ቅዱስ ሲኖዶስ
የጥቅምት 2017 ዓ/ም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ስብሰባ ተጠናቋል።
ምልዓተ ጉባኤው ከጥቅምት 11 እስከ ጥቅምት 20 ቀን 2017 ዓ.ም. ድረስ መደበኛ ስብሰባውን ሲካሄድ ሰንብቷል፡፡
ቅዱስ ሲኖዶስ በመንፈሳዊ፣ በማኅበራዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ ማሳለፉ ተገልጿል።
የስብሰባውን መጠናቀቅ ተከትሎ በቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ ተሰጥቷል።
ከመግለጫው የተወሰደ ፦
" በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች እየተከሰተ ባለው የሰላም እጦት፣ የእርስ በርስ ግጭት ምክንያት የሰው ሕይወት እየተቀጠፈ፣ አካል እየጎደለ፣ ማኅበራዊ ትሥሥር እየተናደ፣ ሰብአዊ ክብር እየተጎዳ፣ መብት እየተጣሰ፣ በዜጎች ላይ ሥጋትና አለመረጋጋት እየበዛ ሀብትና ንብረት እየወደመ ስለሆነ ጉዳዩ አስቸኳይ መፍትሔ የሚያስፈልገው መሆኑ አጠያያቂ አይደለም፡፡
ስለሆነም በጦርነትና በግጭት የመጣ ሰላም፣ የተገነባ ሀገር የለምና በሀገራችን እያጋጠመ ያለውን ችግር ለመፍታት ካለፈው በመማር በጥበብ፣ በማስተዋልና በሰለጠነ አካሄድ በሰላማዊ መንገድ በመወያየት ችግሩ በእርቅ እንዲፈታ ለሁሉም ወገኖቻችን ቅዱስ ሲኖዶስ የሰላም ጥሪውን በአጽንኦት ያቀርባል፡፡ "
(ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት)
/ ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል /
@tikvahethiopia
" በጦርነትና በግጭት የመጣ ሰላም፣ የተገነባ ሀገር የለም !! ... ችግሩ በእርቅ እንዲፈታ ለሁሉም ወገኖቻችን የሰላም ጥሪ እናቀርባለን " - ቅዱስ ሲኖዶስ
የጥቅምት 2017 ዓ/ም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ስብሰባ ተጠናቋል።
ምልዓተ ጉባኤው ከጥቅምት 11 እስከ ጥቅምት 20 ቀን 2017 ዓ.ም. ድረስ መደበኛ ስብሰባውን ሲካሄድ ሰንብቷል፡፡
ቅዱስ ሲኖዶስ በመንፈሳዊ፣ በማኅበራዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ ማሳለፉ ተገልጿል።
የስብሰባውን መጠናቀቅ ተከትሎ በቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ ተሰጥቷል።
ከመግለጫው የተወሰደ ፦
" በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች እየተከሰተ ባለው የሰላም እጦት፣ የእርስ በርስ ግጭት ምክንያት የሰው ሕይወት እየተቀጠፈ፣ አካል እየጎደለ፣ ማኅበራዊ ትሥሥር እየተናደ፣ ሰብአዊ ክብር እየተጎዳ፣ መብት እየተጣሰ፣ በዜጎች ላይ ሥጋትና አለመረጋጋት እየበዛ ሀብትና ንብረት እየወደመ ስለሆነ ጉዳዩ አስቸኳይ መፍትሔ የሚያስፈልገው መሆኑ አጠያያቂ አይደለም፡፡
ስለሆነም በጦርነትና በግጭት የመጣ ሰላም፣ የተገነባ ሀገር የለምና በሀገራችን እያጋጠመ ያለውን ችግር ለመፍታት ካለፈው በመማር በጥበብ፣ በማስተዋልና በሰለጠነ አካሄድ በሰላማዊ መንገድ በመወያየት ችግሩ በእርቅ እንዲፈታ ለሁሉም ወገኖቻችን ቅዱስ ሲኖዶስ የሰላም ጥሪውን በአጽንኦት ያቀርባል፡፡ "
(ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት)
/ ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል /
@tikvahethiopia