አስደሳች ዜና ከሳፋሪኮም !
🎁 ልዩ ልዩ የኢንተርኔት ጥቅሎችን ከ M-PESA ሳፋሪኮም APP ላይ በመግዛት 50% ተጨማሪ ዳታ አግኝተን በነጻ ከሳፋሪኮም ወደ ሳፋሪኮም እንደዋወል! 🤳 ዳታ እንግዛ! በነጻ እንደዋወል!
🔗የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናዉርድ: https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle
ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን https://t.iss.one/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!
የሳፋሪኮም ኢትዮጵያን ትክክለኛ መረጃዎችን በቀላሉ ለማግኘት ቀጥሎ በሚገኙት ይፋዊ የማህበራዊ ሚዲያዎች እንዲከታተሉ እንጋብዛለን።
👉Facebook: https://www.facebook.com/SafaricomET
👉Twitter:
https://x.com/SafaricomET?t=y2XAHAhPNvFeZqXa2YE6aQ&s=08
👉Instagram: https://www.instagram.com/safaricomet?igsh=MWJtcjJrMzNhMzVsNg==
👉 YouTube: https://youtube.com/@safaricomethiopia2751?si=w2o8uz61oHeZM9gm
🎁 ልዩ ልዩ የኢንተርኔት ጥቅሎችን ከ M-PESA ሳፋሪኮም APP ላይ በመግዛት 50% ተጨማሪ ዳታ አግኝተን በነጻ ከሳፋሪኮም ወደ ሳፋሪኮም እንደዋወል! 🤳 ዳታ እንግዛ! በነጻ እንደዋወል!
🔗የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናዉርድ: https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle
ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን https://t.iss.one/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!
የሳፋሪኮም ኢትዮጵያን ትክክለኛ መረጃዎችን በቀላሉ ለማግኘት ቀጥሎ በሚገኙት ይፋዊ የማህበራዊ ሚዲያዎች እንዲከታተሉ እንጋብዛለን።
👉Facebook: https://www.facebook.com/SafaricomET
👉Twitter:
https://x.com/SafaricomET?t=y2XAHAhPNvFeZqXa2YE6aQ&s=08
👉Instagram: https://www.instagram.com/safaricomet?igsh=MWJtcjJrMzNhMzVsNg==
👉 YouTube: https://youtube.com/@safaricomethiopia2751?si=w2o8uz61oHeZM9gm
#Mekelle
በመቐለ የሚገኘው " ፍሬምናጦስ የአረጋውያን የአእምሮ ህሙማን የህፃናት እንክብካቤ ማእከል " በእሳት ቃጠሎ አደጋ ምክንያት ከፍተኛ ወድመት አጋጥሞታል።
አደጋው ያጋጠመው ሚያዝያ 7/ 2016 ዓ.ም ሲሆን ለበጎ አድራጊዎች ሁሉ የእርዳታ ጥሪ ተማጽኖ አቅርቧል።
የምግባረ ሰናይ ድርጅቱን የተለያዩ በጎ አድራጊዎች ሲረዱት ቆይተዋል።
የሚያዘያ 7ቱ የእሳት አደጋ ከአጋዦቹ አንዱ የሆነው መስፍን ኢንዳስትሪያል ኢንጅነሪንግ ሚሊዮን ብሮች በመስጠት ባሰራው አዳራሽ ነው የደረሰው።
በተነሳው ቃጠሎም አዳራሹ ሙሉ በሙሉ ሲወድም በተረጂዎች ማደሪያ ፣ መመገብያና ፣ መስሪያ ክፍሎች ወድመት ደርሷል።
በከፍተኛ ውጪ የተሰራው አዳራሽ ሚያዝያ 6/2016 ዓ.ም. የተመረቀ ሲሆን በነጋታው ሚያዝያ 7/2016 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ሰዓት ነው በእሳት ሙሉ በሙሉ የወደመው።
የአደጋው መንስኤ በኤሌክትሪክ ማስተላለፍያ በተነሳ ቃጠሎ ነው ተብሏል።
ያጋጠመው ቃጠሎ ከፍተኛ የነበረ ቢሆንም በህዝብና በመቐለ የእሳት አደጋ መከላከያ ብርጌድ የተቀናጀ ርብርብ በማእከሉ በሚገኙ አቅመ ደካሞች የህይወት ማጣት አደጋ አልደረሰም።
ምግባረ ሰናይ ድርጅቱ በእሳት አደጋ ቃጠሎ ምክንያት የመኝታ፣ መመግብያ ክፍሎቻቸው የተቃጠለባቸው የሚንከባከባችው አቅሞ ደካሞች ሜዳ ላይ ተጥለው እንደሚገኙ በመጠቆም በአገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ሰብአውያን ሁሉ እንዲረዱት ጥሪ አቅርበዋል።
መርዳት የሚፈልጉ ወገኖች ፍሬምናጦስ የአረጋውያን የእአምሮ ህሙማንና የህፃናት እንክብካቤ ማእከል በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000622132404 ሂሳብ ቁጥር መጠቀም ይችላሉ።
#TikvahFamilyMekelle
@tikvahethiopia
በመቐለ የሚገኘው " ፍሬምናጦስ የአረጋውያን የአእምሮ ህሙማን የህፃናት እንክብካቤ ማእከል " በእሳት ቃጠሎ አደጋ ምክንያት ከፍተኛ ወድመት አጋጥሞታል።
አደጋው ያጋጠመው ሚያዝያ 7/ 2016 ዓ.ም ሲሆን ለበጎ አድራጊዎች ሁሉ የእርዳታ ጥሪ ተማጽኖ አቅርቧል።
የምግባረ ሰናይ ድርጅቱን የተለያዩ በጎ አድራጊዎች ሲረዱት ቆይተዋል።
የሚያዘያ 7ቱ የእሳት አደጋ ከአጋዦቹ አንዱ የሆነው መስፍን ኢንዳስትሪያል ኢንጅነሪንግ ሚሊዮን ብሮች በመስጠት ባሰራው አዳራሽ ነው የደረሰው።
በተነሳው ቃጠሎም አዳራሹ ሙሉ በሙሉ ሲወድም በተረጂዎች ማደሪያ ፣ መመገብያና ፣ መስሪያ ክፍሎች ወድመት ደርሷል።
በከፍተኛ ውጪ የተሰራው አዳራሽ ሚያዝያ 6/2016 ዓ.ም. የተመረቀ ሲሆን በነጋታው ሚያዝያ 7/2016 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ሰዓት ነው በእሳት ሙሉ በሙሉ የወደመው።
የአደጋው መንስኤ በኤሌክትሪክ ማስተላለፍያ በተነሳ ቃጠሎ ነው ተብሏል።
ያጋጠመው ቃጠሎ ከፍተኛ የነበረ ቢሆንም በህዝብና በመቐለ የእሳት አደጋ መከላከያ ብርጌድ የተቀናጀ ርብርብ በማእከሉ በሚገኙ አቅመ ደካሞች የህይወት ማጣት አደጋ አልደረሰም።
ምግባረ ሰናይ ድርጅቱ በእሳት አደጋ ቃጠሎ ምክንያት የመኝታ፣ መመግብያ ክፍሎቻቸው የተቃጠለባቸው የሚንከባከባችው አቅሞ ደካሞች ሜዳ ላይ ተጥለው እንደሚገኙ በመጠቆም በአገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ሰብአውያን ሁሉ እንዲረዱት ጥሪ አቅርበዋል።
መርዳት የሚፈልጉ ወገኖች ፍሬምናጦስ የአረጋውያን የእአምሮ ህሙማንና የህፃናት እንክብካቤ ማእከል በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000622132404 ሂሳብ ቁጥር መጠቀም ይችላሉ።
#TikvahFamilyMekelle
@tikvahethiopia
#ኮሬ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፤ በኮሬ ዞን በተፈጸመ ጥቃት 3 ታዳጊ ልጆችን ጨምሮ 4 ሰዎች ተገደሉ።
ጥቃቱ የተፈጸመው ትላንት በጎርካ ወረዳ ፤ " ቆቦ ቀበሌ " ነው ተብሏል።
የኮሬ ዞን አስተዳደር ባወጣው መግለጫ ፥ ለንጹሐን አርሶ አደሮች ሞት ምክንያት ለሆነው ጥቃት " በምዕራብ ጉጂ ዞን ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ ጽንፈኛ እና ፀረ-ሰላም " ሲል የጠራቸውን አካላት ተጠያቂ አድርጓል።
እንደ አካባቢው ነዋሪዎች ገለጻ ጥቃት ከደረሰባቸው ነዋሪዎች መካከል አንድ የ14 ዓመት ታዳጊ የሚገኝበት ሲሆን ሁለቱ ደግሞ እድሜያቸው ከ17 እስከ 19 ባለው ውስጥ ይገመታል።
አንድ ነዋሪ ፤ ታጣቂዎቹ ቀደም ብለው ማታ ላይ ገብተው ቦታ ይዘው እንደነበርና 7 ክላሽ የታጠቁ ሰዎች እንደሆኑ ገልጸዋል።
" ሟቾቹ ከብት ሊያግዱ ይዘው እየሄዱ እያለ፤ ከብት የሚታገድበት ቆላ የሚባል ቦታ ሲደርሱ እዚያ ጋር ነው ተኩስ የጀመሩት " ሲሉ አስረድተዋል።
ታጣቂዎቹ ጥቃት ከፈጸሙ በኋላ አራቱ ታዳጊዎች እያገዱ የነበሯቸውን ከብቶች ለመውሰድ ቢሞክሩም ተኩሱን ሰምተው በመጡ የአካባቢው ነዋሪዎች እንዲመለሱ ተደርገዋል።
የዞኑ አስተዳደር ባወጣው መግለጫ ፥ የኮሬ ሕዝብ በሚያዝያ ወር ብቻ ብዙ ሞቶችን ማስተናገዱን ገልጿል።
ምን ያህል የሚለውን በቁጥር አልገለጸም።
ነዋሪዎች ግን ከመጋቢት ወር ጀምሮ ቢያንስ አራት ጊዜ በተፈጸሙ ጥቃቶች ነዋሪዎች መገደላቸውን ገልጸዋል።
መረጃው የቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት ነው።
@tikvahethiopia
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፤ በኮሬ ዞን በተፈጸመ ጥቃት 3 ታዳጊ ልጆችን ጨምሮ 4 ሰዎች ተገደሉ።
ጥቃቱ የተፈጸመው ትላንት በጎርካ ወረዳ ፤ " ቆቦ ቀበሌ " ነው ተብሏል።
የኮሬ ዞን አስተዳደር ባወጣው መግለጫ ፥ ለንጹሐን አርሶ አደሮች ሞት ምክንያት ለሆነው ጥቃት " በምዕራብ ጉጂ ዞን ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ ጽንፈኛ እና ፀረ-ሰላም " ሲል የጠራቸውን አካላት ተጠያቂ አድርጓል።
እንደ አካባቢው ነዋሪዎች ገለጻ ጥቃት ከደረሰባቸው ነዋሪዎች መካከል አንድ የ14 ዓመት ታዳጊ የሚገኝበት ሲሆን ሁለቱ ደግሞ እድሜያቸው ከ17 እስከ 19 ባለው ውስጥ ይገመታል።
አንድ ነዋሪ ፤ ታጣቂዎቹ ቀደም ብለው ማታ ላይ ገብተው ቦታ ይዘው እንደነበርና 7 ክላሽ የታጠቁ ሰዎች እንደሆኑ ገልጸዋል።
" ሟቾቹ ከብት ሊያግዱ ይዘው እየሄዱ እያለ፤ ከብት የሚታገድበት ቆላ የሚባል ቦታ ሲደርሱ እዚያ ጋር ነው ተኩስ የጀመሩት " ሲሉ አስረድተዋል።
ታጣቂዎቹ ጥቃት ከፈጸሙ በኋላ አራቱ ታዳጊዎች እያገዱ የነበሯቸውን ከብቶች ለመውሰድ ቢሞክሩም ተኩሱን ሰምተው በመጡ የአካባቢው ነዋሪዎች እንዲመለሱ ተደርገዋል።
የዞኑ አስተዳደር ባወጣው መግለጫ ፥ የኮሬ ሕዝብ በሚያዝያ ወር ብቻ ብዙ ሞቶችን ማስተናገዱን ገልጿል።
ምን ያህል የሚለውን በቁጥር አልገለጸም።
ነዋሪዎች ግን ከመጋቢት ወር ጀምሮ ቢያንስ አራት ጊዜ በተፈጸሙ ጥቃቶች ነዋሪዎች መገደላቸውን ገልጸዋል።
መረጃው የቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
🍲 " የምግብ በጀት እጥረት አጋጥሞናል " 🍲 ሰሞኑን በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ከተማሪ የምግብ አገልግሎት ጋር ተያይዞ ፤ " የምግብ በጀት እጥረት ገጥሞናል ያለውን ብሉ " አይነት ማስታዎቂያዎች መለጠፋቸውን ተከትሎ በበርካቶችን አነጋግሯል። ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የተለጠፉ ማስታወቂያዎች ምንድነው የሚሉት ? - " እንደ ሀገር የምግብ በጀት እጥረት አጋጥሞናል። የምግብ ጥሬ ዕቃ ዋጋም በየቀኑ #ከመጨመሩ…
#Update
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በተቋሙ በማህተም ተደግፎ ስለተለጠፈው " የምግብ በጀት እጥረት አጋጥሞናል ስለዚህ የሜኑ ማሻሻያ አድርገናል " የሚለውን ማስታወቂያ በተመለከተ መግለጫ አውጥቷል።
ተቋሙ በመግለጫው ምን አለ ?
- " ከዚህ ቀደምም ቢሆን በየወቅቱና እንዳስፈላጊነቱ ' የምግብ ሜኑ ማሻሻያ ' ሲደረግ ነበር። "
- " አንዳንድ ኃላፊነት የማይሰማቸው የማህበራዊ ትስስር ገጾች እንዲሁም የሚድያ ተቋማት ዩኒቨርሲቲው ያደረገውን የምግብ ማሻሻያ ሜኑ አስመልክቶ ተጨባጭነት የሌለውን መረጃ በማሰራጨት የተቋሙን በጎ ገጽታ ለማጠልሸት እና የፖለቲካ መጠቀሚያ ለማድረግ እየተንቀሳቀሱ ነው። "
🔴 የትኞቹ ማህበራዊ ትስስር ገጾችና ሚዲያዎች ተጨባጭነት የሌለው መረጃ እንዳሰራጩ በግልጽ ስም አልጠቀሰም።
- " ከወራት በፊት የተደረገ የሜኑ ማሻሻያ ለማሳወቅ ማስታወቂያ ወጥቷል። ይህም የቀን ስህተት የነበረበት መሆኑን እና ' አዲስ የተደረገ የምግብ ሜኑ ማሻሻያ ' እንደሌለ እንገልጻለን። "
- " ኃላፊነት በማይሰማቸው የማህበራዊ ትስስር ገጾች እንዲሁም የሚድያ ተቋማት ' ዩኒቨርሲቲው በምግብ እጥረት ምክንያት ተማሪዎችን ሊበትን ነው ' እየተባለ የሚሰራጨው ሀሰተኛ መረጃ በተቋሙ ዘንድ በፍጹም ተቀባይነት የለውም። "
🔴 የትኛው የማህበራዊ ትስስር ገጽ እና ሚዲያ ተማሪዎች ሊበተኑ ነው ብሎ እንዳሰራጨ ስም አልጠቀሰም።
- " ለተማሪዎቻችን ከምንጊዜውም በላይ የተቋሙ አቅም በሚፈቅደው መጠን ጥራት ያለውን ምግብ በበቂ ሁኔታ በማቅረብ የመማር ማስተማር ሥራው እንዳይስተጓጎል አበክረን እንሰራለን። "
- " ለተማሪዎቹ ወቅቱ በሚፈቅደው አግባብ ጥራቱን የጠበቀ ምግብ ለማቅረብ የሜኑ ማሻሻያ ከማድረግ ያለፈ በተማሪ ምገባ ላይ አንዳች ጉዳት አይፈጽምም። "
- " አንዳንድ ኃላፊነት የጎደላቸው የማህበራዊ ትስስር ገጾች እና መገናኛ ብዙሃን ተቋሙን የፖለቲካ መጠቀሚያ ለማድረግ በዩኒቨርሲቲው ላይ የከፈቱትና እየከፈቱ የሚገኙት የገጽታ ማጠልሸት ድርጊት በፍጹም ተቀባይነት የሌለውም፤ በህግ አግባብ ያስጠይቃል። "
🔴 እዚህም ጋር የትኞቹ እንደሆኑ በግልጽ ስም አልተጠቀሰም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፤ ከሰሞኑን በወላይታ ሶዶ እና በዲላ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የተለጠፉትን ማህተም ያረፈባቸውን ተመሳሳይ ይዘት ስላላቸው ማስታወቂያዎች በተመለከተ መረጃ ማጋራቱ ይታወሳል።
ተቋማቱ ውስጥ የተለጠፉ ማስታወቂያዎች ፥ " እንደ ሀገር የምግብ በጀት እጥረት አጋጥሞናል። የምግብ ጥሬ ዕቃ ዋጋም በየቀኑ ከመጨመሩ ጋር በተያያዘ የተማሪዎች የምግብ በጀታቸው ሙሉ በሙሉ ካለቀ ወራት ተቆጥሯል " ይላል።
ይቀጥልና ፥ " ተቋሟችን የሚያደርገው ድጎማ ተማሪዎቻችን ትምህርታቸውን አቋርጠው እንዳይወጡ ባሉን የምግብ ጥሬ እቃዎች አገልግሎት እየሰጠን ነው " ሲል ይገልጻል።
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ማስታወቂያ ደግሞ " ባሉን የምግብ ጥሬ ዕቃዎች አገልግሎት እየሰጠን ቢሆንም በአሁን ሰዓት እጅግ በጣም #እየከበደ ስለሆነ የሜኑ ማሻሻያ ለማድረግ ተገደናል " ይላል።
ይህ በተመለከተ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የምርምር እና ቴክኖሎጂ ምክትል ፕሬዝደንት ዶ/ር ሀብታሙ ተመስገን ፥ ማስታወቂያውን ሆነ ሀሳቡን #እንደማያዉቁት በመግለጽ " ማን ይህን ሀሳብ እንዳመጣ እንዲሁም ማስታወቂያ እስከ መለጠፍ ድረስ እንደደረሰ እናጣራለን " የሚል ምላሽ ነው የሰጡት።
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲው ምክትል ፕሬዝደንት ዶ/ር አክብር ጩፋ ደግሞ ፤ " ሶሻል ሚዲያ ላይ መረጃው ሲንሸራሸር እያየን ነው " ካሉ በኃላ ሁኔታዉን ለማጣራት #ማኔጅመንቱ ስብሰባ እንደሚቀመጥ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸው ነበር።
@tikvahethiopia
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በተቋሙ በማህተም ተደግፎ ስለተለጠፈው " የምግብ በጀት እጥረት አጋጥሞናል ስለዚህ የሜኑ ማሻሻያ አድርገናል " የሚለውን ማስታወቂያ በተመለከተ መግለጫ አውጥቷል።
ተቋሙ በመግለጫው ምን አለ ?
- " ከዚህ ቀደምም ቢሆን በየወቅቱና እንዳስፈላጊነቱ ' የምግብ ሜኑ ማሻሻያ ' ሲደረግ ነበር። "
- " አንዳንድ ኃላፊነት የማይሰማቸው የማህበራዊ ትስስር ገጾች እንዲሁም የሚድያ ተቋማት ዩኒቨርሲቲው ያደረገውን የምግብ ማሻሻያ ሜኑ አስመልክቶ ተጨባጭነት የሌለውን መረጃ በማሰራጨት የተቋሙን በጎ ገጽታ ለማጠልሸት እና የፖለቲካ መጠቀሚያ ለማድረግ እየተንቀሳቀሱ ነው። "
🔴 የትኞቹ ማህበራዊ ትስስር ገጾችና ሚዲያዎች ተጨባጭነት የሌለው መረጃ እንዳሰራጩ በግልጽ ስም አልጠቀሰም።
- " ከወራት በፊት የተደረገ የሜኑ ማሻሻያ ለማሳወቅ ማስታወቂያ ወጥቷል። ይህም የቀን ስህተት የነበረበት መሆኑን እና ' አዲስ የተደረገ የምግብ ሜኑ ማሻሻያ ' እንደሌለ እንገልጻለን። "
- " ኃላፊነት በማይሰማቸው የማህበራዊ ትስስር ገጾች እንዲሁም የሚድያ ተቋማት ' ዩኒቨርሲቲው በምግብ እጥረት ምክንያት ተማሪዎችን ሊበትን ነው ' እየተባለ የሚሰራጨው ሀሰተኛ መረጃ በተቋሙ ዘንድ በፍጹም ተቀባይነት የለውም። "
🔴 የትኛው የማህበራዊ ትስስር ገጽ እና ሚዲያ ተማሪዎች ሊበተኑ ነው ብሎ እንዳሰራጨ ስም አልጠቀሰም።
- " ለተማሪዎቻችን ከምንጊዜውም በላይ የተቋሙ አቅም በሚፈቅደው መጠን ጥራት ያለውን ምግብ በበቂ ሁኔታ በማቅረብ የመማር ማስተማር ሥራው እንዳይስተጓጎል አበክረን እንሰራለን። "
- " ለተማሪዎቹ ወቅቱ በሚፈቅደው አግባብ ጥራቱን የጠበቀ ምግብ ለማቅረብ የሜኑ ማሻሻያ ከማድረግ ያለፈ በተማሪ ምገባ ላይ አንዳች ጉዳት አይፈጽምም። "
- " አንዳንድ ኃላፊነት የጎደላቸው የማህበራዊ ትስስር ገጾች እና መገናኛ ብዙሃን ተቋሙን የፖለቲካ መጠቀሚያ ለማድረግ በዩኒቨርሲቲው ላይ የከፈቱትና እየከፈቱ የሚገኙት የገጽታ ማጠልሸት ድርጊት በፍጹም ተቀባይነት የሌለውም፤ በህግ አግባብ ያስጠይቃል። "
🔴 እዚህም ጋር የትኞቹ እንደሆኑ በግልጽ ስም አልተጠቀሰም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፤ ከሰሞኑን በወላይታ ሶዶ እና በዲላ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የተለጠፉትን ማህተም ያረፈባቸውን ተመሳሳይ ይዘት ስላላቸው ማስታወቂያዎች በተመለከተ መረጃ ማጋራቱ ይታወሳል።
ተቋማቱ ውስጥ የተለጠፉ ማስታወቂያዎች ፥ " እንደ ሀገር የምግብ በጀት እጥረት አጋጥሞናል። የምግብ ጥሬ ዕቃ ዋጋም በየቀኑ ከመጨመሩ ጋር በተያያዘ የተማሪዎች የምግብ በጀታቸው ሙሉ በሙሉ ካለቀ ወራት ተቆጥሯል " ይላል።
ይቀጥልና ፥ " ተቋሟችን የሚያደርገው ድጎማ ተማሪዎቻችን ትምህርታቸውን አቋርጠው እንዳይወጡ ባሉን የምግብ ጥሬ እቃዎች አገልግሎት እየሰጠን ነው " ሲል ይገልጻል።
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ማስታወቂያ ደግሞ " ባሉን የምግብ ጥሬ ዕቃዎች አገልግሎት እየሰጠን ቢሆንም በአሁን ሰዓት እጅግ በጣም #እየከበደ ስለሆነ የሜኑ ማሻሻያ ለማድረግ ተገደናል " ይላል።
ይህ በተመለከተ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የምርምር እና ቴክኖሎጂ ምክትል ፕሬዝደንት ዶ/ር ሀብታሙ ተመስገን ፥ ማስታወቂያውን ሆነ ሀሳቡን #እንደማያዉቁት በመግለጽ " ማን ይህን ሀሳብ እንዳመጣ እንዲሁም ማስታወቂያ እስከ መለጠፍ ድረስ እንደደረሰ እናጣራለን " የሚል ምላሽ ነው የሰጡት።
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲው ምክትል ፕሬዝደንት ዶ/ር አክብር ጩፋ ደግሞ ፤ " ሶሻል ሚዲያ ላይ መረጃው ሲንሸራሸር እያየን ነው " ካሉ በኃላ ሁኔታዉን ለማጣራት #ማኔጅመንቱ ስብሰባ እንደሚቀመጥ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸው ነበር።
@tikvahethiopia
“ ... ‘ ልጄ በአጋቾች እየተሰቃየች ነው። ገንዘብ ካላክሽ ልጅሽን እንገድላታለን ’ አሉኝ። አጋቾቹ 300 ሺሕ ብር ጠየቁኝ ” - እንባ የሚተናነቃቸው እናት
የ20 ዓመት ሴት ልጃቸው በሳዑዲ አረቢያ እና የመን ድንበር በደላሎች እንደታገተችባቸው፣ አጋቾቹ የጠየቁት ገንዘብ ሰሞኑን ካልተላከላቸው እንደሚገድሏት ማስጠንቀቂያ መስጠታቸውን፣ አጋቾቹ ይህን ያሉት ከአንድ ቀን በፊት መሆኑን የታጋቿ እናት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
እያለቀሱ ቃላቸውን የሰጡት እኚሁ እናት፣ “ ‘ልጄ በአጋቾች እየተሰቃየች ነው። ገንዘብ ካላክሽ ልጅሽን እንገድላታለን’ አሉኝ። አጋቾቹ 300 ሺሕ ብር ጠየቁኝ። ይህን ገንዘብ ለመላክ አቅሙ የለኝም። እባካችሁ ወገኖቼ ልጄን አድኑልኝ ” ሲሉ በውስጥም በውጪም ላሉ ወገኖች የእርዳታ ጥሪ አቅርበዋል።
አክለውም፣ “ ልጄም ‘እማዬ ገንዘቡን ካላክሽ ይገድሉኛልና እባክሽ ከዚህ ጉድ አውጪኝ’ አለችኝ። አጋቾቹም ‘ልጅሽ ያለችው በሳዑዲና የመን ድንበር ራጎ ነው’ የልጅሽን ደህንነት የምትፈልጊ ከሆነ ገንዘቡን ላኪ’ ብለው ስልኩን ዘጉት። ልጄን በሕይወት ላጣት ነው። እባካችሁ ወገን ድረሱልኝ ” ሲሉ ተማጸነዋል።
ልጃቸው ይህ ችግር የገጠማት ሕይወቷን ለመለወጥ ወደ ሳዑዲ አረቢያ #እየተሰደደች በነበረበት ወቅት መሆኑን ገለጸው፣ “ የቀን ሥራ እየሰራሁ ነው ያስተማርኳት። የልጄ ደህንነት አስጨንቆኛል። ወላጆች፣ እህት ወንድም ያላች ሁሉ፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ እጃችሁን ዘርጉልኝ ” ሲሉ ተማጽነዋል።
የወጣቷን ቤተሰብ መርዳት ለምትፈልጉ በታጋቿ ወንድም መስፍን መኮንን ባዬ ንግድ ባንክ አካውንት 1000264883893 ዳግፋችሁን መላክ ትችላላችሁ።
የታጋቿ ቤተሰብ በስልክ ማነጋገር ለምትፈልጉ በ0945592726 ፍቅር ምስጋንን ማግኘት ይቻላል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፥ ስለጉዳዩ ያነጋገራቸው አንድ ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ ወደ ሳዑዲ የሚሄዱ ኢትዮጵያዊያንን ደህንነት በተመለከተ በሳዑዲ አስተባባሪ በሰጡት ቃል ፣ “ራጎ ረግረጋማና ከባድ ምሽግ ነው። ደላሎች ተጓዦችን አግተው ከ250 ሺሕ ብር ጀምሮ ይጠይቃሉ ” ብለዋል።
እኝሁ አካል አክለውም ፣ #በርካታ_ኢትዮጵዊያን ስደተኞች “ #ራጎ ” በሌሎች አካባቢዎች በስቃይ እንደሚገኙ፣ ወጣቱ ከእነዚህ ወገኖች ትሞህርት ወስዶ በእንዲህ አይነት መንገድ ወደ ሳዑዲ አረቢያ ከመሰደድ እንዲቆጠብ አስገንዝበዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የ20 ዓመት ሴት ልጃቸው በሳዑዲ አረቢያ እና የመን ድንበር በደላሎች እንደታገተችባቸው፣ አጋቾቹ የጠየቁት ገንዘብ ሰሞኑን ካልተላከላቸው እንደሚገድሏት ማስጠንቀቂያ መስጠታቸውን፣ አጋቾቹ ይህን ያሉት ከአንድ ቀን በፊት መሆኑን የታጋቿ እናት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
እያለቀሱ ቃላቸውን የሰጡት እኚሁ እናት፣ “ ‘ልጄ በአጋቾች እየተሰቃየች ነው። ገንዘብ ካላክሽ ልጅሽን እንገድላታለን’ አሉኝ። አጋቾቹ 300 ሺሕ ብር ጠየቁኝ። ይህን ገንዘብ ለመላክ አቅሙ የለኝም። እባካችሁ ወገኖቼ ልጄን አድኑልኝ ” ሲሉ በውስጥም በውጪም ላሉ ወገኖች የእርዳታ ጥሪ አቅርበዋል።
አክለውም፣ “ ልጄም ‘እማዬ ገንዘቡን ካላክሽ ይገድሉኛልና እባክሽ ከዚህ ጉድ አውጪኝ’ አለችኝ። አጋቾቹም ‘ልጅሽ ያለችው በሳዑዲና የመን ድንበር ራጎ ነው’ የልጅሽን ደህንነት የምትፈልጊ ከሆነ ገንዘቡን ላኪ’ ብለው ስልኩን ዘጉት። ልጄን በሕይወት ላጣት ነው። እባካችሁ ወገን ድረሱልኝ ” ሲሉ ተማጸነዋል።
ልጃቸው ይህ ችግር የገጠማት ሕይወቷን ለመለወጥ ወደ ሳዑዲ አረቢያ #እየተሰደደች በነበረበት ወቅት መሆኑን ገለጸው፣ “ የቀን ሥራ እየሰራሁ ነው ያስተማርኳት። የልጄ ደህንነት አስጨንቆኛል። ወላጆች፣ እህት ወንድም ያላች ሁሉ፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ እጃችሁን ዘርጉልኝ ” ሲሉ ተማጽነዋል።
የወጣቷን ቤተሰብ መርዳት ለምትፈልጉ በታጋቿ ወንድም መስፍን መኮንን ባዬ ንግድ ባንክ አካውንት 1000264883893 ዳግፋችሁን መላክ ትችላላችሁ።
የታጋቿ ቤተሰብ በስልክ ማነጋገር ለምትፈልጉ በ0945592726 ፍቅር ምስጋንን ማግኘት ይቻላል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፥ ስለጉዳዩ ያነጋገራቸው አንድ ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ ወደ ሳዑዲ የሚሄዱ ኢትዮጵያዊያንን ደህንነት በተመለከተ በሳዑዲ አስተባባሪ በሰጡት ቃል ፣ “ራጎ ረግረጋማና ከባድ ምሽግ ነው። ደላሎች ተጓዦችን አግተው ከ250 ሺሕ ብር ጀምሮ ይጠይቃሉ ” ብለዋል።
እኝሁ አካል አክለውም ፣ #በርካታ_ኢትዮጵዊያን ስደተኞች “ #ራጎ ” በሌሎች አካባቢዎች በስቃይ እንደሚገኙ፣ ወጣቱ ከእነዚህ ወገኖች ትሞህርት ወስዶ በእንዲህ አይነት መንገድ ወደ ሳዑዲ አረቢያ ከመሰደድ እንዲቆጠብ አስገንዝበዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia