#ቀነኒሳ_በቀለ👏
አንጋፋው የኢትዮጵያ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በ41 ዓመቱ ዛሬ በለንደን የተካሄደ የማራቶን ውድድርን በ2ኛነት አጠናቋል።
በርካቶች ለአትሌቱን ትጋት ፣ ጥንካሬና ቁርጠኝነት አድናቆት እያጎረፉ ይገኛሉ።
አንጋፋው አትሌት ቀነኒሳ በቀለ የለንደን ማራቶን ውድድርን 2 ሰዓት ከ4 ደቂቃ ከ15 ሰከንድ በመግባት ነው ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው።
የዓለም አትሌቲክስም አትሌቱ ላሳየው ድንቅ ብቃት አድናቆቱን ችሯል።
የዛሬው ማራቶን የገባበት ሰዓት ከ2019 ወዲህ ከ40 ዓመት በላይ በሆናቸው አትሌቶች ዘንድ የተመዘገበ የመጀመሪያው እንደሆነም ጠቁሟል።
@tikvahethsport @tikvahethiopia
አንጋፋው የኢትዮጵያ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በ41 ዓመቱ ዛሬ በለንደን የተካሄደ የማራቶን ውድድርን በ2ኛነት አጠናቋል።
በርካቶች ለአትሌቱን ትጋት ፣ ጥንካሬና ቁርጠኝነት አድናቆት እያጎረፉ ይገኛሉ።
አንጋፋው አትሌት ቀነኒሳ በቀለ የለንደን ማራቶን ውድድርን 2 ሰዓት ከ4 ደቂቃ ከ15 ሰከንድ በመግባት ነው ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው።
የዓለም አትሌቲክስም አትሌቱ ላሳየው ድንቅ ብቃት አድናቆቱን ችሯል።
የዛሬው ማራቶን የገባበት ሰዓት ከ2019 ወዲህ ከ40 ዓመት በላይ በሆናቸው አትሌቶች ዘንድ የተመዘገበ የመጀመሪያው እንደሆነም ጠቁሟል።
@tikvahethsport @tikvahethiopia
🔥ከባድ ትንቅንቅ የማያጣው የየኤፍ ኤ ካፕ ጨዋታዎች ወደ ሜዳ ተመልሰዋል🔥
Coventry vs Manchester United እሁድ ሚያዚያ 13 ከሰዓት 11፡30 ይፋለማሉ!
🔥 ማን ዩናይትድ ወደ ፍፃሜ መቀጥል ይችላል?
👉 ዛሬውኑ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ። ጨዋታዎችን ከትንታኔ ፣ ከተጫዋች ብቃት እስከ ቡድን ወኔ በሱፐርስፖርት ይከታተሉ!
የዲኤስቲቪ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ!
👇
https://mydstv.onelink.me/vGln/eth2
#FACupAllOnDStv #ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia #DStvSelfServiceET
Coventry vs Manchester United እሁድ ሚያዚያ 13 ከሰዓት 11፡30 ይፋለማሉ!
🔥 ማን ዩናይትድ ወደ ፍፃሜ መቀጥል ይችላል?
👉 ዛሬውኑ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ። ጨዋታዎችን ከትንታኔ ፣ ከተጫዋች ብቃት እስከ ቡድን ወኔ በሱፐርስፖርት ይከታተሉ!
የዲኤስቲቪ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ!
👇
https://mydstv.onelink.me/vGln/eth2
#FACupAllOnDStv #ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia #DStvSelfServiceET
#ATTENTION🚨
" አንዳንድ ወጣት ሴቶች ከቫይረሱ በላይ #እርግዝናን_ይፈራሉ "
ስለኤች አይቪ/ኤድስ ስርጭት የሚሰጠው የግንዛቤ ፈጠራ ሥራ ከጊዜ ወደጊዜ እየተቀዛቀዘ መሆኑን በጤና ሚኒስቴር የኤች አይቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ገልጿል።
ችግሮች ከመባባሳቸው በፊት ትኩረት ሰጥቶ መሥራት እንደሚገባ አሳስቧል።
ቫይረሱ ኢትዮጵያ መግባቱ ከተረጋገጠበት ጊዜ አንስቶ በተሰራው እንቅስቃሴ ብዙ ለውጦች መመዝገባቸውን አስታውሷል።
ይሁን እንጂ የተመዘገቡት ለውጦች በተወሰነ ደረጃም ቢሆን መዘናጋት እንደፈጠሩ ፤ የሚዲያዎች ተሳትፎም መቀዛቀዙን ጠቁሟል።
በአሁኑ ወቅት ኤች አይ ቪ ቫይረስን በተመለከተ እየተሠሩ ያሉ ሥራዎች ትኩረት የሚሹና በይበልጥ ተጋላጭ የሆኑ የማኅበረሰብ ክፍሎች ላይ ብቻ ትኩረት ያደረጉ ናቸው ብሏል።
እነዚህም ፦
- ሴተኛ አዳሪዎች፣
- አደንዛዥ እፅ የሚጠቀሙ ሰዎች፣
- የረጅም ርቀት አሽከርካሪዎች፣
- አፍላ ወጣቶች በተለይ (ከማኅበራዊ ሚዲያ ጋር በተያያዘ)፣
- የቀን ሠራተኞች፣
- ከማኅበራዊ ችግሮች ጋር ተያይዞ ተጋላጭ የሆኑት እንደሆኑ አመልክቷል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ የስርጭት መጠኑ ከ1 በመቶ በላይ ቢሆንም ከቦታ ቦታ በፆታ፣ በኅብረተሰብ ክፍል፣ በገጠርና በከተማ ከፍተኛ ልዩነት አለው ብሏል።
በከተሞች ያለው ስርጭት በገጠር ካለው በሰባት እጥፍ እንደሚበልጥም ጠቁሟል።
ይህንን ልዩነት መሠረት ያደረገ አጠቃላይ ማኅበረሰቡን ተደራሽ የሚያደርግ የግንዛቤ ፈጠራ ሥራ እየተከናወነ አይደለም ብሏል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ ፦
° የመጠጥ ቤቶች ፣
° የጫት ቤቶች
° በሺሻ ቤቶች መስፋፋት ሌላ ተግዳሮቶች እየሆኑ መምጣታቸውን ገልጿል።
" አንዳንድ ወጣት ሴቶች ከቫይረሱ በላይ እርግዝናን ይፈራሉ። የወጣቶች አዲስ የመያዝ ምጣኔ ጨመረ ባይባልም እየቀነሰ አይደለም፤ ይህ በራሱ ችግር ለመኖሩ አመላካች ነው "ም ብሏል።
በተለይ በወጣቶች በኩል ሁሉን አቀፍ ሥራ ባለመሠራቱ እንደ ሀገር ዋጋ ሊያስከፍሉ የሚችሉ አጋላጭ ባሕሪያት እየተስተዋሉ መሆኑን አመልክቷል።
የኤች አይ ቪ ቫይረስን በተመለከተ ጠንካራ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን እንደሀገር ማከናወን እንደሚጠበቅ አሳስቧል። #ኢፕድ
@tikvahethiopia
" አንዳንድ ወጣት ሴቶች ከቫይረሱ በላይ #እርግዝናን_ይፈራሉ "
ስለኤች አይቪ/ኤድስ ስርጭት የሚሰጠው የግንዛቤ ፈጠራ ሥራ ከጊዜ ወደጊዜ እየተቀዛቀዘ መሆኑን በጤና ሚኒስቴር የኤች አይቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ገልጿል።
ችግሮች ከመባባሳቸው በፊት ትኩረት ሰጥቶ መሥራት እንደሚገባ አሳስቧል።
ቫይረሱ ኢትዮጵያ መግባቱ ከተረጋገጠበት ጊዜ አንስቶ በተሰራው እንቅስቃሴ ብዙ ለውጦች መመዝገባቸውን አስታውሷል።
ይሁን እንጂ የተመዘገቡት ለውጦች በተወሰነ ደረጃም ቢሆን መዘናጋት እንደፈጠሩ ፤ የሚዲያዎች ተሳትፎም መቀዛቀዙን ጠቁሟል።
በአሁኑ ወቅት ኤች አይ ቪ ቫይረስን በተመለከተ እየተሠሩ ያሉ ሥራዎች ትኩረት የሚሹና በይበልጥ ተጋላጭ የሆኑ የማኅበረሰብ ክፍሎች ላይ ብቻ ትኩረት ያደረጉ ናቸው ብሏል።
እነዚህም ፦
- ሴተኛ አዳሪዎች፣
- አደንዛዥ እፅ የሚጠቀሙ ሰዎች፣
- የረጅም ርቀት አሽከርካሪዎች፣
- አፍላ ወጣቶች በተለይ (ከማኅበራዊ ሚዲያ ጋር በተያያዘ)፣
- የቀን ሠራተኞች፣
- ከማኅበራዊ ችግሮች ጋር ተያይዞ ተጋላጭ የሆኑት እንደሆኑ አመልክቷል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ የስርጭት መጠኑ ከ1 በመቶ በላይ ቢሆንም ከቦታ ቦታ በፆታ፣ በኅብረተሰብ ክፍል፣ በገጠርና በከተማ ከፍተኛ ልዩነት አለው ብሏል።
በከተሞች ያለው ስርጭት በገጠር ካለው በሰባት እጥፍ እንደሚበልጥም ጠቁሟል።
ይህንን ልዩነት መሠረት ያደረገ አጠቃላይ ማኅበረሰቡን ተደራሽ የሚያደርግ የግንዛቤ ፈጠራ ሥራ እየተከናወነ አይደለም ብሏል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ ፦
° የመጠጥ ቤቶች ፣
° የጫት ቤቶች
° በሺሻ ቤቶች መስፋፋት ሌላ ተግዳሮቶች እየሆኑ መምጣታቸውን ገልጿል።
" አንዳንድ ወጣት ሴቶች ከቫይረሱ በላይ እርግዝናን ይፈራሉ። የወጣቶች አዲስ የመያዝ ምጣኔ ጨመረ ባይባልም እየቀነሰ አይደለም፤ ይህ በራሱ ችግር ለመኖሩ አመላካች ነው "ም ብሏል።
በተለይ በወጣቶች በኩል ሁሉን አቀፍ ሥራ ባለመሠራቱ እንደ ሀገር ዋጋ ሊያስከፍሉ የሚችሉ አጋላጭ ባሕሪያት እየተስተዋሉ መሆኑን አመልክቷል።
የኤች አይ ቪ ቫይረስን በተመለከተ ጠንካራ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን እንደሀገር ማከናወን እንደሚጠበቅ አሳስቧል። #ኢፕድ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
' ቲክቶክ ' አሜሪካ ውስጥ ከታገድኩኝ " የ170 ሚሊዮን አሜሪካውያን የመናገርና ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ይረገጣል " አለ።
ይህን ያለው የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት መተግበሪያው ከቻይና ካልተፋታ እንዲታገድ ረቂቅ ህግ ካጸደቁ በኃላ ነው።
የ 'ቲክቶክ' ቃል አቀባይ መተገበሪያው እንዲታገድ የሚለውን ረቂቅ ህግ አውግዘዋል።
" ከታገደ ፦
- የ170 ሚሊዮን አሜሪካውያንን የመናገር መብት ይረግጣል፣
- 7 ሚሊዮን ንግዶች እንዲጠፉ ይሆናል፣
- ለአሜሪካ ኢኮኖሚ በዓመት የሚገባውን 24 ቢሊዮን ዶላር ያሳጣል " ብለዋል።
አክለው ፤ " ባይትዳንስ የቻይና ወይም የሌላ አገር ወኪል አይደለም " ሲሉ ገልጸዋል። " የቻይና ኩባንያ እንዳልሆነም በተደጋጋሚ ተናግረናል " ሲሉ አክለዋል።
ጉዳዩን የሚከታተሉ አካላት ግን ' ቲክቶክ ' ከቻይና ተፋቶ ድርሻው ለአሜሪካ ሰዎች ካልተሸጠ የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ #የመታገዱ ነገር አይቀሬ ነው ብለዋል።
ትላንት የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት ' ቲክቶክ ' በመላው ሀገሪቱ እንዲታገድ የሚያደርግ ረቂቅ ህግ አጽድቋል።
@tikvahethiopia
' ቲክቶክ ' አሜሪካ ውስጥ ከታገድኩኝ " የ170 ሚሊዮን አሜሪካውያን የመናገርና ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ይረገጣል " አለ።
ይህን ያለው የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት መተግበሪያው ከቻይና ካልተፋታ እንዲታገድ ረቂቅ ህግ ካጸደቁ በኃላ ነው።
የ 'ቲክቶክ' ቃል አቀባይ መተገበሪያው እንዲታገድ የሚለውን ረቂቅ ህግ አውግዘዋል።
" ከታገደ ፦
- የ170 ሚሊዮን አሜሪካውያንን የመናገር መብት ይረግጣል፣
- 7 ሚሊዮን ንግዶች እንዲጠፉ ይሆናል፣
- ለአሜሪካ ኢኮኖሚ በዓመት የሚገባውን 24 ቢሊዮን ዶላር ያሳጣል " ብለዋል።
አክለው ፤ " ባይትዳንስ የቻይና ወይም የሌላ አገር ወኪል አይደለም " ሲሉ ገልጸዋል። " የቻይና ኩባንያ እንዳልሆነም በተደጋጋሚ ተናግረናል " ሲሉ አክለዋል።
ጉዳዩን የሚከታተሉ አካላት ግን ' ቲክቶክ ' ከቻይና ተፋቶ ድርሻው ለአሜሪካ ሰዎች ካልተሸጠ የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ #የመታገዱ ነገር አይቀሬ ነው ብለዋል።
ትላንት የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት ' ቲክቶክ ' በመላው ሀገሪቱ እንዲታገድ የሚያደርግ ረቂቅ ህግ አጽድቋል።
@tikvahethiopia
🍲 " የምግብ በጀት እጥረት አጋጥሞናል " 🍲
ሰሞኑን በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ከተማሪ የምግብ አገልግሎት ጋር ተያይዞ ፤ " የምግብ በጀት እጥረት ገጥሞናል ያለውን ብሉ " አይነት ማስታዎቂያዎች መለጠፋቸውን ተከትሎ በበርካቶችን አነጋግሯል።
ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የተለጠፉ ማስታወቂያዎች ምንድነው የሚሉት ?
- " እንደ ሀገር የምግብ በጀት እጥረት አጋጥሞናል። የምግብ ጥሬ ዕቃ ዋጋም በየቀኑ #ከመጨመሩ ጋር በተያያዘ የተማሪዎች የምግብ በጀታቸው ሙሉ በሙሉ ካለቀ ወራት ተቆጥሯል። "
- " ተቋማችን የሚያደርገው ድጎማ ተማሪዎቻችን ትምህርታቸውን አቋርጠው እንዳይወጡ ባሉን የምግብ ጥሬ እቃዎች አገልግሎት እየሰጠን ቢሆንም በአሁን ሰዓት እጅግ በጣም #እየከበደ ስለሆነ የሜኑ ማሻሻያ ለማድረግ ተገደናል። "
- " ከአሁን በኃላ የተሻሻለው ሜኑ ተግባራዊ ይሆናል። "
- " በተወሰኑ በስቶራችን ውስጥ ባሉ የምግብ ጥሬ ዕቃዎች እና በአትክልት የምግብ አገልግሎት እየሰጠን ነው። በአስቸኳይ የምግብ ጥሬ ዕቃ ግዥ አቅርቦት እንዲሟላ ጠይቀናል እስከዛ ታገሱ። "
... ይላሉ ማስታወቂያዎቹ።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፥ በዲላ እንዲሁም በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲዎች ካሉ የቤተሰቡ አባላት ማህተም ያረፈባቸውን ማስታወቂያዎች ተልኮለት ተመልክቷል።
ይህ ነገር የቤተሰብ የጭንቀት ምንጭ ከመሆኑ በላይ ፦
° ዩኒቨርሲቲን የሚያክል እጅግ ትልቅ ተቋም እንዴት መጭውን የዋጋ ንረት እንዲሁም የዓመቱ የምግብ ወጪ ያላገናዘበ በጀት ይይዛል ?
° ለረጅም ዓመታት ለተማሪ በቀን የሚመደበው ገንዘብ አነስተኛ ሆኖ ሳለ እንዴት ይህ ሊፈጠር ቻለ ? የሚሉና ሌሎች ነቀፌታዎች ተሰምተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፤ " የምግብ በጀት እጥረት ገጥሞናል " የሚል ማስታወቂያ ከተለጠፈባቸው ተቋማት አንዱ ወደሆነው ዲላ ዩኒቨርሲቲ ደውሏል።
▪️የተከሰተው ችግር ምንድነው ❓
▪️በዚህ አይነት ሁኔታ ተማሪዎች ከመጎዳታቸው በላይ ወላጆችንስ አያስጨንቅም ወይ ❓ ... ሲል ለዩኒቨርስቲው የምርምር እና ቴክኖሎጂ ምክትል ፕሬዝደንት ዶ/ር ሀብታሙ ተመስገን ጥያቄ አቅርቧል።
ዶ/ር ሀብታሙ ፤ ማስታወቂያውንም ሆነ ሀሳቡን እንደማያዉቁት በመግለጽ " ማን ይህን ሀሳብ እንዳመጣ እንዲሁም ማስታወቂያ እስከ መለጠፍ ድረስ እንደደረሰ እናጣራለን " ብለዋል።
" ተማሪዎች ሆኑ ወላጆች ምንም የሚያሳስባቸዉ ነገር ሊኖር አይገባም " ያሉ ሲሆን ዩኒቨርሲቲዉም ሆነ እርሳቸዉ የሚመሩት የተማሪዎችን ጉዳይ የሚመለከት ቢሮ ችግሩ እንደሌለበት ገልጸዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በተመሳሳይ ማስታወቂያ ወደ ተለጠፈበት የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ደውሏል።
የዩኒቨርሲቲው ምክትል ፕሬዝደንት ዶ/ር አክብር ጩፋ ፥ " ሶሻል ሚዲያ ላይ መረጃው ሲንሸራሸር እያየን ነው " ብለዋል።
" ሁኔታዉን ለማጣራት #ማኔጅመንቱ ስብሰባ ይቀመጣል። የስብሰባዉን ወጤት የተመለከተ መረጃ በፍጥነት አደርሳችኋለሁ " ሲሉ ገልጸዋል።
NB. ከላይ ተየያያዙት ማስታወቂያዎች ማህተም ያረፈባቸው ናቸው።
መረጃው በሀዋሳው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ተዘጋጅቶ ነው የተላከው።
@tikvahethiopia
ሰሞኑን በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ከተማሪ የምግብ አገልግሎት ጋር ተያይዞ ፤ " የምግብ በጀት እጥረት ገጥሞናል ያለውን ብሉ " አይነት ማስታዎቂያዎች መለጠፋቸውን ተከትሎ በበርካቶችን አነጋግሯል።
ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የተለጠፉ ማስታወቂያዎች ምንድነው የሚሉት ?
- " እንደ ሀገር የምግብ በጀት እጥረት አጋጥሞናል። የምግብ ጥሬ ዕቃ ዋጋም በየቀኑ #ከመጨመሩ ጋር በተያያዘ የተማሪዎች የምግብ በጀታቸው ሙሉ በሙሉ ካለቀ ወራት ተቆጥሯል። "
- " ተቋማችን የሚያደርገው ድጎማ ተማሪዎቻችን ትምህርታቸውን አቋርጠው እንዳይወጡ ባሉን የምግብ ጥሬ እቃዎች አገልግሎት እየሰጠን ቢሆንም በአሁን ሰዓት እጅግ በጣም #እየከበደ ስለሆነ የሜኑ ማሻሻያ ለማድረግ ተገደናል። "
- " ከአሁን በኃላ የተሻሻለው ሜኑ ተግባራዊ ይሆናል። "
- " በተወሰኑ በስቶራችን ውስጥ ባሉ የምግብ ጥሬ ዕቃዎች እና በአትክልት የምግብ አገልግሎት እየሰጠን ነው። በአስቸኳይ የምግብ ጥሬ ዕቃ ግዥ አቅርቦት እንዲሟላ ጠይቀናል እስከዛ ታገሱ። "
... ይላሉ ማስታወቂያዎቹ።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፥ በዲላ እንዲሁም በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲዎች ካሉ የቤተሰቡ አባላት ማህተም ያረፈባቸውን ማስታወቂያዎች ተልኮለት ተመልክቷል።
ይህ ነገር የቤተሰብ የጭንቀት ምንጭ ከመሆኑ በላይ ፦
° ዩኒቨርሲቲን የሚያክል እጅግ ትልቅ ተቋም እንዴት መጭውን የዋጋ ንረት እንዲሁም የዓመቱ የምግብ ወጪ ያላገናዘበ በጀት ይይዛል ?
° ለረጅም ዓመታት ለተማሪ በቀን የሚመደበው ገንዘብ አነስተኛ ሆኖ ሳለ እንዴት ይህ ሊፈጠር ቻለ ? የሚሉና ሌሎች ነቀፌታዎች ተሰምተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፤ " የምግብ በጀት እጥረት ገጥሞናል " የሚል ማስታወቂያ ከተለጠፈባቸው ተቋማት አንዱ ወደሆነው ዲላ ዩኒቨርሲቲ ደውሏል።
▪️የተከሰተው ችግር ምንድነው ❓
▪️በዚህ አይነት ሁኔታ ተማሪዎች ከመጎዳታቸው በላይ ወላጆችንስ አያስጨንቅም ወይ ❓ ... ሲል ለዩኒቨርስቲው የምርምር እና ቴክኖሎጂ ምክትል ፕሬዝደንት ዶ/ር ሀብታሙ ተመስገን ጥያቄ አቅርቧል።
ዶ/ር ሀብታሙ ፤ ማስታወቂያውንም ሆነ ሀሳቡን እንደማያዉቁት በመግለጽ " ማን ይህን ሀሳብ እንዳመጣ እንዲሁም ማስታወቂያ እስከ መለጠፍ ድረስ እንደደረሰ እናጣራለን " ብለዋል።
" ተማሪዎች ሆኑ ወላጆች ምንም የሚያሳስባቸዉ ነገር ሊኖር አይገባም " ያሉ ሲሆን ዩኒቨርሲቲዉም ሆነ እርሳቸዉ የሚመሩት የተማሪዎችን ጉዳይ የሚመለከት ቢሮ ችግሩ እንደሌለበት ገልጸዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በተመሳሳይ ማስታወቂያ ወደ ተለጠፈበት የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ደውሏል።
የዩኒቨርሲቲው ምክትል ፕሬዝደንት ዶ/ር አክብር ጩፋ ፥ " ሶሻል ሚዲያ ላይ መረጃው ሲንሸራሸር እያየን ነው " ብለዋል።
" ሁኔታዉን ለማጣራት #ማኔጅመንቱ ስብሰባ ይቀመጣል። የስብሰባዉን ወጤት የተመለከተ መረጃ በፍጥነት አደርሳችኋለሁ " ሲሉ ገልጸዋል።
NB. ከላይ ተየያያዙት ማስታወቂያዎች ማህተም ያረፈባቸው ናቸው።
መረጃው በሀዋሳው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ተዘጋጅቶ ነው የተላከው።
@tikvahethiopia
አስደሳች ዜና ከሳፋሪኮም !
🎁 ልዩ ልዩ የኢንተርኔት ጥቅሎችን ከ M-PESA ሳፋሪኮም APP ላይ በመግዛት 50% ተጨማሪ ዳታ አግኝተን በነጻ ከሳፋሪኮም ወደ ሳፋሪኮም እንደዋወል! 🤳 ዳታ እንግዛ! በነጻ እንደዋወል!
🔗የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናዉርድ: https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle
ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን https://t.iss.one/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!
የሳፋሪኮም ኢትዮጵያን ትክክለኛ መረጃዎችን በቀላሉ ለማግኘት ቀጥሎ በሚገኙት ይፋዊ የማህበራዊ ሚዲያዎች እንዲከታተሉ እንጋብዛለን።
👉Facebook: https://www.facebook.com/SafaricomET
👉Twitter:
https://x.com/SafaricomET?t=y2XAHAhPNvFeZqXa2YE6aQ&s=08
👉Instagram: https://www.instagram.com/safaricomet?igsh=MWJtcjJrMzNhMzVsNg==
👉 YouTube: https://youtube.com/@safaricomethiopia2751?si=w2o8uz61oHeZM9gm
🎁 ልዩ ልዩ የኢንተርኔት ጥቅሎችን ከ M-PESA ሳፋሪኮም APP ላይ በመግዛት 50% ተጨማሪ ዳታ አግኝተን በነጻ ከሳፋሪኮም ወደ ሳፋሪኮም እንደዋወል! 🤳 ዳታ እንግዛ! በነጻ እንደዋወል!
🔗የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናዉርድ: https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle
ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን https://t.iss.one/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!
የሳፋሪኮም ኢትዮጵያን ትክክለኛ መረጃዎችን በቀላሉ ለማግኘት ቀጥሎ በሚገኙት ይፋዊ የማህበራዊ ሚዲያዎች እንዲከታተሉ እንጋብዛለን።
👉Facebook: https://www.facebook.com/SafaricomET
👉Twitter:
https://x.com/SafaricomET?t=y2XAHAhPNvFeZqXa2YE6aQ&s=08
👉Instagram: https://www.instagram.com/safaricomet?igsh=MWJtcjJrMzNhMzVsNg==
👉 YouTube: https://youtube.com/@safaricomethiopia2751?si=w2o8uz61oHeZM9gm
#Mekelle
በመቐለ የሚገኘው " ፍሬምናጦስ የአረጋውያን የአእምሮ ህሙማን የህፃናት እንክብካቤ ማእከል " በእሳት ቃጠሎ አደጋ ምክንያት ከፍተኛ ወድመት አጋጥሞታል።
አደጋው ያጋጠመው ሚያዝያ 7/ 2016 ዓ.ም ሲሆን ለበጎ አድራጊዎች ሁሉ የእርዳታ ጥሪ ተማጽኖ አቅርቧል።
የምግባረ ሰናይ ድርጅቱን የተለያዩ በጎ አድራጊዎች ሲረዱት ቆይተዋል።
የሚያዘያ 7ቱ የእሳት አደጋ ከአጋዦቹ አንዱ የሆነው መስፍን ኢንዳስትሪያል ኢንጅነሪንግ ሚሊዮን ብሮች በመስጠት ባሰራው አዳራሽ ነው የደረሰው።
በተነሳው ቃጠሎም አዳራሹ ሙሉ በሙሉ ሲወድም በተረጂዎች ማደሪያ ፣ መመገብያና ፣ መስሪያ ክፍሎች ወድመት ደርሷል።
በከፍተኛ ውጪ የተሰራው አዳራሽ ሚያዝያ 6/2016 ዓ.ም. የተመረቀ ሲሆን በነጋታው ሚያዝያ 7/2016 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ሰዓት ነው በእሳት ሙሉ በሙሉ የወደመው።
የአደጋው መንስኤ በኤሌክትሪክ ማስተላለፍያ በተነሳ ቃጠሎ ነው ተብሏል።
ያጋጠመው ቃጠሎ ከፍተኛ የነበረ ቢሆንም በህዝብና በመቐለ የእሳት አደጋ መከላከያ ብርጌድ የተቀናጀ ርብርብ በማእከሉ በሚገኙ አቅመ ደካሞች የህይወት ማጣት አደጋ አልደረሰም።
ምግባረ ሰናይ ድርጅቱ በእሳት አደጋ ቃጠሎ ምክንያት የመኝታ፣ መመግብያ ክፍሎቻቸው የተቃጠለባቸው የሚንከባከባችው አቅሞ ደካሞች ሜዳ ላይ ተጥለው እንደሚገኙ በመጠቆም በአገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ሰብአውያን ሁሉ እንዲረዱት ጥሪ አቅርበዋል።
መርዳት የሚፈልጉ ወገኖች ፍሬምናጦስ የአረጋውያን የእአምሮ ህሙማንና የህፃናት እንክብካቤ ማእከል በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000622132404 ሂሳብ ቁጥር መጠቀም ይችላሉ።
#TikvahFamilyMekelle
@tikvahethiopia
በመቐለ የሚገኘው " ፍሬምናጦስ የአረጋውያን የአእምሮ ህሙማን የህፃናት እንክብካቤ ማእከል " በእሳት ቃጠሎ አደጋ ምክንያት ከፍተኛ ወድመት አጋጥሞታል።
አደጋው ያጋጠመው ሚያዝያ 7/ 2016 ዓ.ም ሲሆን ለበጎ አድራጊዎች ሁሉ የእርዳታ ጥሪ ተማጽኖ አቅርቧል።
የምግባረ ሰናይ ድርጅቱን የተለያዩ በጎ አድራጊዎች ሲረዱት ቆይተዋል።
የሚያዘያ 7ቱ የእሳት አደጋ ከአጋዦቹ አንዱ የሆነው መስፍን ኢንዳስትሪያል ኢንጅነሪንግ ሚሊዮን ብሮች በመስጠት ባሰራው አዳራሽ ነው የደረሰው።
በተነሳው ቃጠሎም አዳራሹ ሙሉ በሙሉ ሲወድም በተረጂዎች ማደሪያ ፣ መመገብያና ፣ መስሪያ ክፍሎች ወድመት ደርሷል።
በከፍተኛ ውጪ የተሰራው አዳራሽ ሚያዝያ 6/2016 ዓ.ም. የተመረቀ ሲሆን በነጋታው ሚያዝያ 7/2016 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ሰዓት ነው በእሳት ሙሉ በሙሉ የወደመው።
የአደጋው መንስኤ በኤሌክትሪክ ማስተላለፍያ በተነሳ ቃጠሎ ነው ተብሏል።
ያጋጠመው ቃጠሎ ከፍተኛ የነበረ ቢሆንም በህዝብና በመቐለ የእሳት አደጋ መከላከያ ብርጌድ የተቀናጀ ርብርብ በማእከሉ በሚገኙ አቅመ ደካሞች የህይወት ማጣት አደጋ አልደረሰም።
ምግባረ ሰናይ ድርጅቱ በእሳት አደጋ ቃጠሎ ምክንያት የመኝታ፣ መመግብያ ክፍሎቻቸው የተቃጠለባቸው የሚንከባከባችው አቅሞ ደካሞች ሜዳ ላይ ተጥለው እንደሚገኙ በመጠቆም በአገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ሰብአውያን ሁሉ እንዲረዱት ጥሪ አቅርበዋል።
መርዳት የሚፈልጉ ወገኖች ፍሬምናጦስ የአረጋውያን የእአምሮ ህሙማንና የህፃናት እንክብካቤ ማእከል በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000622132404 ሂሳብ ቁጥር መጠቀም ይችላሉ።
#TikvahFamilyMekelle
@tikvahethiopia
#ኮሬ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፤ በኮሬ ዞን በተፈጸመ ጥቃት 3 ታዳጊ ልጆችን ጨምሮ 4 ሰዎች ተገደሉ።
ጥቃቱ የተፈጸመው ትላንት በጎርካ ወረዳ ፤ " ቆቦ ቀበሌ " ነው ተብሏል።
የኮሬ ዞን አስተዳደር ባወጣው መግለጫ ፥ ለንጹሐን አርሶ አደሮች ሞት ምክንያት ለሆነው ጥቃት " በምዕራብ ጉጂ ዞን ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ ጽንፈኛ እና ፀረ-ሰላም " ሲል የጠራቸውን አካላት ተጠያቂ አድርጓል።
እንደ አካባቢው ነዋሪዎች ገለጻ ጥቃት ከደረሰባቸው ነዋሪዎች መካከል አንድ የ14 ዓመት ታዳጊ የሚገኝበት ሲሆን ሁለቱ ደግሞ እድሜያቸው ከ17 እስከ 19 ባለው ውስጥ ይገመታል።
አንድ ነዋሪ ፤ ታጣቂዎቹ ቀደም ብለው ማታ ላይ ገብተው ቦታ ይዘው እንደነበርና 7 ክላሽ የታጠቁ ሰዎች እንደሆኑ ገልጸዋል።
" ሟቾቹ ከብት ሊያግዱ ይዘው እየሄዱ እያለ፤ ከብት የሚታገድበት ቆላ የሚባል ቦታ ሲደርሱ እዚያ ጋር ነው ተኩስ የጀመሩት " ሲሉ አስረድተዋል።
ታጣቂዎቹ ጥቃት ከፈጸሙ በኋላ አራቱ ታዳጊዎች እያገዱ የነበሯቸውን ከብቶች ለመውሰድ ቢሞክሩም ተኩሱን ሰምተው በመጡ የአካባቢው ነዋሪዎች እንዲመለሱ ተደርገዋል።
የዞኑ አስተዳደር ባወጣው መግለጫ ፥ የኮሬ ሕዝብ በሚያዝያ ወር ብቻ ብዙ ሞቶችን ማስተናገዱን ገልጿል።
ምን ያህል የሚለውን በቁጥር አልገለጸም።
ነዋሪዎች ግን ከመጋቢት ወር ጀምሮ ቢያንስ አራት ጊዜ በተፈጸሙ ጥቃቶች ነዋሪዎች መገደላቸውን ገልጸዋል።
መረጃው የቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት ነው።
@tikvahethiopia
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፤ በኮሬ ዞን በተፈጸመ ጥቃት 3 ታዳጊ ልጆችን ጨምሮ 4 ሰዎች ተገደሉ።
ጥቃቱ የተፈጸመው ትላንት በጎርካ ወረዳ ፤ " ቆቦ ቀበሌ " ነው ተብሏል።
የኮሬ ዞን አስተዳደር ባወጣው መግለጫ ፥ ለንጹሐን አርሶ አደሮች ሞት ምክንያት ለሆነው ጥቃት " በምዕራብ ጉጂ ዞን ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ ጽንፈኛ እና ፀረ-ሰላም " ሲል የጠራቸውን አካላት ተጠያቂ አድርጓል።
እንደ አካባቢው ነዋሪዎች ገለጻ ጥቃት ከደረሰባቸው ነዋሪዎች መካከል አንድ የ14 ዓመት ታዳጊ የሚገኝበት ሲሆን ሁለቱ ደግሞ እድሜያቸው ከ17 እስከ 19 ባለው ውስጥ ይገመታል።
አንድ ነዋሪ ፤ ታጣቂዎቹ ቀደም ብለው ማታ ላይ ገብተው ቦታ ይዘው እንደነበርና 7 ክላሽ የታጠቁ ሰዎች እንደሆኑ ገልጸዋል።
" ሟቾቹ ከብት ሊያግዱ ይዘው እየሄዱ እያለ፤ ከብት የሚታገድበት ቆላ የሚባል ቦታ ሲደርሱ እዚያ ጋር ነው ተኩስ የጀመሩት " ሲሉ አስረድተዋል።
ታጣቂዎቹ ጥቃት ከፈጸሙ በኋላ አራቱ ታዳጊዎች እያገዱ የነበሯቸውን ከብቶች ለመውሰድ ቢሞክሩም ተኩሱን ሰምተው በመጡ የአካባቢው ነዋሪዎች እንዲመለሱ ተደርገዋል።
የዞኑ አስተዳደር ባወጣው መግለጫ ፥ የኮሬ ሕዝብ በሚያዝያ ወር ብቻ ብዙ ሞቶችን ማስተናገዱን ገልጿል።
ምን ያህል የሚለውን በቁጥር አልገለጸም።
ነዋሪዎች ግን ከመጋቢት ወር ጀምሮ ቢያንስ አራት ጊዜ በተፈጸሙ ጥቃቶች ነዋሪዎች መገደላቸውን ገልጸዋል።
መረጃው የቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት ነው።
@tikvahethiopia