#Somalia
• " የትውልድ ሀገሬ እየሄደችበት ያለው አቅጣጫ በዚህ መጠን አስግቶኝ አያውቅም "- ሙርሳል ካሊፍ
ጎረቤት ሶማሊያ በሀገሪቱ የጸጥታ ክፍተት ሊፈጠር ይችላል ስትል አስጠንቅቃ ፤ የአፍሪካ ሰላም አሰከባሪ ኃይሎች ከሶማሊያ ለቀው የሚወጡበትን ፍጥነት እንዲቀንሱ መጠየቋ ተሰምቷል።
ሮይተርስ ተመለከትኳቸው ያላቸው ሰነዶች እንደሚያሳዩት ከሶማሊያ ጋር ድንበር የሚዋሰኑ አጎራባች ሀገሮች፣ ዳግም እያንሰራራ የሚገኘው የአል-ሻባብ ቡድን ስልጣን ሊቆጣጠር ይችላል የሚል ስጋት ገብቷቸዋል።
በሶማሊያ የሚገኘው የአፍሪካ ህብረት የሽግግር ተልዕኮ (አትሚስ) ሰላም አስከባሪ ኃይል እ.አ.አ በታህሳስ መጨረሻ ሙሉ ለሙሉ ሶማሊያን ለቆ ለመውጣት ዝግጅቱን የጨረሰ ሲሆን በቁጥር አነስተኛ የሆነ ኃይል በቦታው እንደሚተካ ይጠበቃል።
ሆኖም የሶማሊያ መንግስት ለአፍሪካ ህብረት ሰላም እና ጸጥታ ም/ቤት ጊዜያዊ ሊቀመንበር ባለፈው ወር በላከው ደብዳቤ፣ አሁን ካሉት 4 ሺህ ወታደሮች ግማሽ የሚሆኑትን እስከ ሰኔ ወር መጨረሻ ለማስወጣት የተያዘውን እቅድ ወደ መስከረም እንዲያሻግር ጠይቋል።
መንግስት ቀድም ሲል ለህብረቱ አስገብቶት በነበረው እና ሮይተርስ በተመልከተው ሰነድም፣ ሰላም አስከባሪው ኃይል ለቆ የሚወጣበት ጊዜ በሶማሊያ ኃይሎች " ዝግጁነት እና አቅም ላይ እንዲመሠረት " ጠይቆ ነበር።
በተመድ የፀጥታው ም/ቤት ተልዕኮ የተሰጠው ቡድን ባካሄደው የጋር ግምገማም " የአፍሪካ ህብረት ሰላም አስከባሪ ኃይል በችኮላ መውጣታቸው የፀጥታ ክፍተት እንደሚፈጥር " አስጠንቅቋል።
የፓርላማው መከላከያ ኮሚቴ ገለልተኛ አባል የሆኑት ሙርሳል ካሊፍ ፤ " የትውልድ ሀገሬ እየሄደችበት ያለው አቅጣጫ በዚህ መጠን አስግቶኝ አያውቅም " ብለዋል።
ሶማሊያ ለሚገኘው የአፍሪካ ህብረት ጸጥታ ኃይል ከፍተኛ የሆነ የገንዘብ ደጋፊ የሆኑት አሜሪካ እና የአውሮፓ ህብረት የሰላም አስከባሪውን ኃይል ለመቀነስ የወሰኑት ዘላቂነት ያለው የረጅም ጊዜ የገንዘብ ድጋፍ የማድረጉ ሁኔታ ስጋት ውስጥ ስለከተታቸው መሆኑን አራት የዲፕሎማቲክ ምንጮች እና አንድ የዩጋንዳ ከፍተኛ ባለስልጣን ለሮይተርስ ተናግረዋል።
የሶማሊያ ፕሬዝዳንትና የጠ/ሚ ፅ/ ቤት በጉዳዩ ላይ አስተያየት እንዲሰጡ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ አልሰጡም።
#ሮይተርስ #ቪኦኤ
@tikvahethiopia
• " የትውልድ ሀገሬ እየሄደችበት ያለው አቅጣጫ በዚህ መጠን አስግቶኝ አያውቅም "- ሙርሳል ካሊፍ
ጎረቤት ሶማሊያ በሀገሪቱ የጸጥታ ክፍተት ሊፈጠር ይችላል ስትል አስጠንቅቃ ፤ የአፍሪካ ሰላም አሰከባሪ ኃይሎች ከሶማሊያ ለቀው የሚወጡበትን ፍጥነት እንዲቀንሱ መጠየቋ ተሰምቷል።
ሮይተርስ ተመለከትኳቸው ያላቸው ሰነዶች እንደሚያሳዩት ከሶማሊያ ጋር ድንበር የሚዋሰኑ አጎራባች ሀገሮች፣ ዳግም እያንሰራራ የሚገኘው የአል-ሻባብ ቡድን ስልጣን ሊቆጣጠር ይችላል የሚል ስጋት ገብቷቸዋል።
በሶማሊያ የሚገኘው የአፍሪካ ህብረት የሽግግር ተልዕኮ (አትሚስ) ሰላም አስከባሪ ኃይል እ.አ.አ በታህሳስ መጨረሻ ሙሉ ለሙሉ ሶማሊያን ለቆ ለመውጣት ዝግጅቱን የጨረሰ ሲሆን በቁጥር አነስተኛ የሆነ ኃይል በቦታው እንደሚተካ ይጠበቃል።
ሆኖም የሶማሊያ መንግስት ለአፍሪካ ህብረት ሰላም እና ጸጥታ ም/ቤት ጊዜያዊ ሊቀመንበር ባለፈው ወር በላከው ደብዳቤ፣ አሁን ካሉት 4 ሺህ ወታደሮች ግማሽ የሚሆኑትን እስከ ሰኔ ወር መጨረሻ ለማስወጣት የተያዘውን እቅድ ወደ መስከረም እንዲያሻግር ጠይቋል።
መንግስት ቀድም ሲል ለህብረቱ አስገብቶት በነበረው እና ሮይተርስ በተመልከተው ሰነድም፣ ሰላም አስከባሪው ኃይል ለቆ የሚወጣበት ጊዜ በሶማሊያ ኃይሎች " ዝግጁነት እና አቅም ላይ እንዲመሠረት " ጠይቆ ነበር።
በተመድ የፀጥታው ም/ቤት ተልዕኮ የተሰጠው ቡድን ባካሄደው የጋር ግምገማም " የአፍሪካ ህብረት ሰላም አስከባሪ ኃይል በችኮላ መውጣታቸው የፀጥታ ክፍተት እንደሚፈጥር " አስጠንቅቋል።
የፓርላማው መከላከያ ኮሚቴ ገለልተኛ አባል የሆኑት ሙርሳል ካሊፍ ፤ " የትውልድ ሀገሬ እየሄደችበት ያለው አቅጣጫ በዚህ መጠን አስግቶኝ አያውቅም " ብለዋል።
ሶማሊያ ለሚገኘው የአፍሪካ ህብረት ጸጥታ ኃይል ከፍተኛ የሆነ የገንዘብ ደጋፊ የሆኑት አሜሪካ እና የአውሮፓ ህብረት የሰላም አስከባሪውን ኃይል ለመቀነስ የወሰኑት ዘላቂነት ያለው የረጅም ጊዜ የገንዘብ ድጋፍ የማድረጉ ሁኔታ ስጋት ውስጥ ስለከተታቸው መሆኑን አራት የዲፕሎማቲክ ምንጮች እና አንድ የዩጋንዳ ከፍተኛ ባለስልጣን ለሮይተርስ ተናግረዋል።
የሶማሊያ ፕሬዝዳንትና የጠ/ሚ ፅ/ ቤት በጉዳዩ ላይ አስተያየት እንዲሰጡ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ አልሰጡም።
#ሮይተርስ #ቪኦኤ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia ይህ በኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ስም በተለይ በ X መተግበሪያ ላይ እየተራጨ ያለው መግለጫ ሀሰተኛ እና የተቀነባበረ ነው። የሚኒስቴሩን የቀድሞ ሎጎ በመጠቀም እየተሰራጨ ያለው ይህ መረጃ ኢትዮጵያ ከራስ ገዟ ሶሌላንድ ጋር የተፈራረመችውን የመግባቢያ ስምምነት (MoU) ፦ - በUN - በEU - BRICS (ኢትዮጵያ እራሷ አባል የሆነችበት) - በኢስላሚክ ሀገራት ከፍተኛ ጫና እንደሰረዘችው…
#Ethiopia #Somalia
" ልዑካኑ የቀጥታ የፊት ለፊት ንግግር / ውይይት አላደረጉም " - የሶማሊያው ፕሬዜዳንት
ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ በቱርክ አሸማጋይነት ትላንት አንካራ ውስጥ ውይይት ማድረጋቸው ተሰምቷል።
በቱርክ ጋባዥነት በተደረገው ውይይት የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታየ አጽቀስላሴ እና የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር አህመድ ሞሊም የመሯቸው ልዑካን አንካራ ተገኝተው ነበር።
ከውይይቱ በኃሏ የሶስቱ ሀገራት የጋራ መግለጫ ወጥቷል።
መግለጫው ፥ ሚኒስትሮቹ ያላቸውን ልዩነቶች ለሁለቱም ተቀባይነት ባለው ማዕቀፍ ውስጥ ለመፍታት ያሉ ሁኔታዎችን እንደዳሰሱ ገልጿል።
ሚኒስትሮቹ በተናጥል በግልጽነት ፣ ወዳጅነት ባለው እና የወደፊቱን ያለመ ውይይት እንደነበራቸው ነው የተመላከተው።
ሁለቱ አገራት ችግሮቻቸውን ለመፍታትና ቀጣናው እንዲረጋጋ የጀመሩትን ውይይት ለመቀጠል ተስማምተዋል የተባለ ሲሆን ለሁለተኛ ዙር ውይይት በአንካራ ነሐሴ 27/ 2016 ዓ.ም እንደሚገናኙ ተገልጿል።
ኢትዮጵያ ራሷን በነጻ አገርነት ካወጀችው ሶማሊላንድ ጋር ከ6 ወራት በፊት የመግባቢያ ስምምነት ከተፈራረመች ወዲህ በይፋ ተገናኝተው ሲመጋገሩ ይህ የመጀመሪያቸው ነው።
የጋራ መግለጫው ሁለቱ አገራት ልዩነታቸውን ለሁለቱም ተቀባይነት ባለው ማዕቀፍ ለመፍታት ያሉ ሁኔታዎችን እንደዳሰሰ ቢገልጽም እነዚህ ተቀባይነት አላቸው ስለተባሉ ጉዳዮች የተጠቀሰ ጉዳይ የለም።
በሌላ በኩል ፥ የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐሙድ ትላንት ውይይቱ ካበቃ በኃሏ ባሰሙት ንግግር ፦
- ኢትዮጵያ ከሶማሌላንድ ጋር ከተፈራረመችው የመግባቢያ ስምምነት (MoU) ወደኋላ የምትመለስበትን ምንም ምልክት አላሳየችም፤
- ከያዘችው መንገድ እየተመለሳች ስለመሆኑ ምንም ምልክት የለም ፤
- አንካራ ውስጥ የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ ልዑካን ቀጥተኛ ንግግር አላደረጉም ይልቅም ቱርክ በመሃል እንደ አስታራቂ ሆና እየሰራች ነበር ብለዋል።
ከሰሞኑን የኢትዮጵያ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤትና ከዛም የውጭ ጉዳይ መ/ቤትን ሎጎ በመጠቀም አንካራ ውስጥ በተደረገ ውይይት " ኢትዮጵያ ከሶማሌላንድ ጋር የገባችውን ስምምነት ሰርዛለች " የሚሉ ሀሰተኛ መረጃዎች ሲሰራጩ ነበር።
#Ethiopia #Somalia #Turkey
@tikvahethiopia
" ልዑካኑ የቀጥታ የፊት ለፊት ንግግር / ውይይት አላደረጉም " - የሶማሊያው ፕሬዜዳንት
ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ በቱርክ አሸማጋይነት ትላንት አንካራ ውስጥ ውይይት ማድረጋቸው ተሰምቷል።
በቱርክ ጋባዥነት በተደረገው ውይይት የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታየ አጽቀስላሴ እና የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር አህመድ ሞሊም የመሯቸው ልዑካን አንካራ ተገኝተው ነበር።
ከውይይቱ በኃሏ የሶስቱ ሀገራት የጋራ መግለጫ ወጥቷል።
መግለጫው ፥ ሚኒስትሮቹ ያላቸውን ልዩነቶች ለሁለቱም ተቀባይነት ባለው ማዕቀፍ ውስጥ ለመፍታት ያሉ ሁኔታዎችን እንደዳሰሱ ገልጿል።
ሚኒስትሮቹ በተናጥል በግልጽነት ፣ ወዳጅነት ባለው እና የወደፊቱን ያለመ ውይይት እንደነበራቸው ነው የተመላከተው።
ሁለቱ አገራት ችግሮቻቸውን ለመፍታትና ቀጣናው እንዲረጋጋ የጀመሩትን ውይይት ለመቀጠል ተስማምተዋል የተባለ ሲሆን ለሁለተኛ ዙር ውይይት በአንካራ ነሐሴ 27/ 2016 ዓ.ም እንደሚገናኙ ተገልጿል።
ኢትዮጵያ ራሷን በነጻ አገርነት ካወጀችው ሶማሊላንድ ጋር ከ6 ወራት በፊት የመግባቢያ ስምምነት ከተፈራረመች ወዲህ በይፋ ተገናኝተው ሲመጋገሩ ይህ የመጀመሪያቸው ነው።
የጋራ መግለጫው ሁለቱ አገራት ልዩነታቸውን ለሁለቱም ተቀባይነት ባለው ማዕቀፍ ለመፍታት ያሉ ሁኔታዎችን እንደዳሰሰ ቢገልጽም እነዚህ ተቀባይነት አላቸው ስለተባሉ ጉዳዮች የተጠቀሰ ጉዳይ የለም።
በሌላ በኩል ፥ የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐሙድ ትላንት ውይይቱ ካበቃ በኃሏ ባሰሙት ንግግር ፦
- ኢትዮጵያ ከሶማሌላንድ ጋር ከተፈራረመችው የመግባቢያ ስምምነት (MoU) ወደኋላ የምትመለስበትን ምንም ምልክት አላሳየችም፤
- ከያዘችው መንገድ እየተመለሳች ስለመሆኑ ምንም ምልክት የለም ፤
- አንካራ ውስጥ የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ ልዑካን ቀጥተኛ ንግግር አላደረጉም ይልቅም ቱርክ በመሃል እንደ አስታራቂ ሆና እየሰራች ነበር ብለዋል።
ከሰሞኑን የኢትዮጵያ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤትና ከዛም የውጭ ጉዳይ መ/ቤትን ሎጎ በመጠቀም አንካራ ውስጥ በተደረገ ውይይት " ኢትዮጵያ ከሶማሌላንድ ጋር የገባችውን ስምምነት ሰርዛለች " የሚሉ ሀሰተኛ መረጃዎች ሲሰራጩ ነበር።
#Ethiopia #Somalia #Turkey
@tikvahethiopia
#Egypt #Somalia : የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ ' ለሁለት ቀን የስራ ጉብኝት ' ብለው ግብፅ ይገኛሉ።
የፕሬዜዳንቱ ቢሮ እንዳለው በሁለትዮሽና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ ግንኙነታቸው በማጠናከር ላይ ከግብጹ ፕሬዝዳንት አብዱል ፈታህ አልሲሲ ጋር መክረዋል።
ስምምነታቸው ይዘቱ ምን እንደሆነ በዝርዝር ባይታወቅም ሀገራቱ #ወታደራዊ ትብብር ፕሮቶኮል ስምምነትም ተፈራርመዋል።
ግብፅ በሞቃዲሾ ኤምባሲ መክፈቷም ተነግሯል።
የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሙሀሙድ ወደ ፕሬዜዳንትነት ስልጣን ከመጡ በኃላ ከግብፅ ጋር የተለየ ወዳጅነት ለመመስረት ሲሰሩ ታይቷል።
በተለይም ደግሞ ኢትዮጵያ ከራስ ገዟ ሶማሌላንድ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ከተፈራረመች በኋላና ሀገሪቱ ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነቷ ከሻከረ በኃላ ወደ ግብፅ ብዙ ጊዜ እየተመላሳለሱ ይገኛሉ።
Photo Credit - Villa Somalia
Via @thiqahEth
የፕሬዜዳንቱ ቢሮ እንዳለው በሁለትዮሽና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ ግንኙነታቸው በማጠናከር ላይ ከግብጹ ፕሬዝዳንት አብዱል ፈታህ አልሲሲ ጋር መክረዋል።
ስምምነታቸው ይዘቱ ምን እንደሆነ በዝርዝር ባይታወቅም ሀገራቱ #ወታደራዊ ትብብር ፕሮቶኮል ስምምነትም ተፈራርመዋል።
ግብፅ በሞቃዲሾ ኤምባሲ መክፈቷም ተነግሯል።
የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሙሀሙድ ወደ ፕሬዜዳንትነት ስልጣን ከመጡ በኃላ ከግብፅ ጋር የተለየ ወዳጅነት ለመመስረት ሲሰሩ ታይቷል።
በተለይም ደግሞ ኢትዮጵያ ከራስ ገዟ ሶማሌላንድ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ከተፈራረመች በኋላና ሀገሪቱ ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነቷ ከሻከረ በኃላ ወደ ግብፅ ብዙ ጊዜ እየተመላሳለሱ ይገኛሉ።
Photo Credit - Villa Somalia
Via @thiqahEth
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia #Somalia " ልዑካኑ የቀጥታ የፊት ለፊት ንግግር / ውይይት አላደረጉም " - የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ በቱርክ አሸማጋይነት ትላንት አንካራ ውስጥ ውይይት ማድረጋቸው ተሰምቷል። በቱርክ ጋባዥነት በተደረገው ውይይት የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታየ አጽቀስላሴ እና የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር አህመድ ሞሊም የመሯቸው ልዑካን…
#Ethiopia #Somalia #Turkey
ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ልዑካቸው አንካራ ቱርክ ይገኛሉ።
የቱርክ ፕሬዚዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በጽሕፈት ቤታቸው አቀባበል ያደረጉላቸው ሲሆን ሁለቱ መሪዎች ከልዑካን ቡድናቸው ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል።
በሌላ በኩል ፤ የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ሼክ መሐመድ አንካራ ይገኛሉ።
እሳቸውም ከኤርዶጋን ጋር ተነጋግረዋል።
መሪዎቹ አንካራ የሄዱበት ሶማሊያ እና ኢትዮጵያ የገቡበትን ውጥረት ለማርገብ እንዲቻል ኤርዶጋን የንግግር መድረክ አመቻችተውላቸእ ነው።
መሪዎቹ ፊት ለፊት ይነጋገራሉ እየተባለ ይገኛል።
ሮይተርስ የሶማሊያ ዜና አገልግሎት ሶናን ጠቅሶ እንደዘገበው የሁለቱ መሪዎች የፊት ለፊት ንግግር እየተካረረ የሄደውን የሁለቱን ሃገራት ዲፕሎማሲያዊ ቀውስ ለማርገብ ያስችላል ብሏል።
እንደ ተባለው ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ከሀሰን ሼክ መሀመድ ጋር ፊት ለፊት የሚገናኙ ከሆነ ኢትዮጵያ ከራስ ገዟ ሶማሌ ላንድ ጋር የወደብ ባለቤት የሚያደርጋትን ስምምነት ከተፈራረሙ ወዲህ ይህ የመጀመሪያዉ ይሆናል።
መረጃው ከጠ/ሚ ፅ/ቤት ፣ ዶቼ ቨለ ፣ ሮይተርስ የተሰባሰበ ነው።
@tikvahethiopia
ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ልዑካቸው አንካራ ቱርክ ይገኛሉ።
የቱርክ ፕሬዚዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በጽሕፈት ቤታቸው አቀባበል ያደረጉላቸው ሲሆን ሁለቱ መሪዎች ከልዑካን ቡድናቸው ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል።
በሌላ በኩል ፤ የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ሼክ መሐመድ አንካራ ይገኛሉ።
እሳቸውም ከኤርዶጋን ጋር ተነጋግረዋል።
መሪዎቹ አንካራ የሄዱበት ሶማሊያ እና ኢትዮጵያ የገቡበትን ውጥረት ለማርገብ እንዲቻል ኤርዶጋን የንግግር መድረክ አመቻችተውላቸእ ነው።
መሪዎቹ ፊት ለፊት ይነጋገራሉ እየተባለ ይገኛል።
ሮይተርስ የሶማሊያ ዜና አገልግሎት ሶናን ጠቅሶ እንደዘገበው የሁለቱ መሪዎች የፊት ለፊት ንግግር እየተካረረ የሄደውን የሁለቱን ሃገራት ዲፕሎማሲያዊ ቀውስ ለማርገብ ያስችላል ብሏል።
እንደ ተባለው ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ከሀሰን ሼክ መሀመድ ጋር ፊት ለፊት የሚገናኙ ከሆነ ኢትዮጵያ ከራስ ገዟ ሶማሌ ላንድ ጋር የወደብ ባለቤት የሚያደርጋትን ስምምነት ከተፈራረሙ ወዲህ ይህ የመጀመሪያዉ ይሆናል።
መረጃው ከጠ/ሚ ፅ/ቤት ፣ ዶቼ ቨለ ፣ ሮይተርስ የተሰባሰበ ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia #Somalia #Turkey ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ልዑካቸው አንካራ ቱርክ ይገኛሉ። የቱርክ ፕሬዚዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በጽሕፈት ቤታቸው አቀባበል ያደረጉላቸው ሲሆን ሁለቱ መሪዎች ከልዑካን ቡድናቸው ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። በሌላ በኩል ፤ የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ሼክ መሐመድ አንካራ ይገኛሉ። እሳቸውም ከኤርዶጋን ጋር ተነጋግረዋል።…
#Ethiopia #Somalia
ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ስምምነት ላይ ደረሱ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ በቱርክ ፕሬዜዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን አሸማጋይነት በቱርክ አንካራ ስምምነት ላይ ደርሰዋል።
(ዝርዝር መረጃዎችን ይጠብቁ)
@tikvahethiopia
ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ስምምነት ላይ ደረሱ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ በቱርክ ፕሬዜዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን አሸማጋይነት በቱርክ አንካራ ስምምነት ላይ ደርሰዋል።
(ዝርዝር መረጃዎችን ይጠብቁ)
@tikvahethiopia
#Ethiopia #Somalia #Egypt
የሶማሊያ ናሽናል ኢንተለጀንስ ኤንድ ሴኪዩሪቲ ኤጀንሲ ዳይሬክተር አብዱላሂ ሞሐመድ ዓሊ ኢትዮጵያ ይገኛሉ።
አብዱላሂ ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዳይሬክተር አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ጋር መክረዋል።
ውይይቱ የአንካራውን ስምምነት ተግባራዊ ከማድረግ ጋር በተያያዘ ከሁለቱ ሀገራት አቻ ተቋማት የሚጠበቁ የትብብርና የአጋርነት መስኮች ላይ ትኩረት ያደረገ ነበር።
በውይይቱ የኢትዮጵያና ሶማሊያ የደኅንነትና የጸጥታ ተቋማት ስምምነቱ ተግባራዊ እንዳይሆን እንቅፋት የሚፈጥሩ አካላትን ለመከላከል የሚጠበቅባቸውን ሚና ለመወጣት የጋራ መግባባት እና ስምምነት ላይ መድረሳቸው ተነግሯል።
በሌላ በኩል ፥ የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር ዴኤታ አሊ ሞሃመድ ኦማር ኢትዮጽያ ይገኛሉ።
በውይይታቸው ሁለቱ ወገኖች የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ማሻሻል እና በቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ማስጠበቅ ላይ ያላቸውን ትብብር ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መምከራቸውን ኤፍ ኤም ሲ ዘግቧል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን ሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታዋን ወደ ኢትዮጵያ በላከችበት በዚህ ወቅት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯን ግብፅ ካይሮ ልካለች።
ሚኒስትሯ አሕመድ ፊቂ ከግብጹ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ባድር አብደላቲ ጋር ከመከሩ በኃላ የጋራ መግለጫ ሰጥተው ነበር።
በዚሁ መግለጫ ፤ የግብፁ ሚኒስትር " የቀይ ባሕርን ዳርቻ መጠቀም የሚችሉት ከባሕሩ ጋር የሚዋሰኑ አገራት ብቻ መሆን ይገባል ፤ የቀይ ባሕር ዳርቻ አዋሳኝ ላልሆኑ ሀገሮች ክፍት ሊሆን አይችልም " በማለት መናገራቸውን " ኢጂፕት ዴይሊ " ዘግቧል።
ግብፅ ይህን አስተያየት የሰጠችው ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ በአንካራ ኢትዮጵያ የባህር በርን ልታገኝ የምትችልበትን ስምምነት ፈርመው ፊርማ ሳይደርቅ ነው። በቀጣይ ወር ደግሞ ለዚሁ ጉዳይ ንግግር እንደሚጀመር ይታወቃል።
ከዚህ ባለፈ የግብፁ ሚኒስትር ፤ " የሱማሊያ ፌደራል መንግሥት መላው የሀገሪቱን ግዛቶች ሙሉ እንዲቆጣጠር " በሚችልበት አግባብ ላይ መምክራቸውን ተናግረዋል።
ከዚህ ባለፈ ግብፅ የአፍሪካ ህብረት በሶማሊያ በሚያደረገው ተልዕኮ " ወታደሮቼን አወጣላሁ " ብላለች።
የሶማሊያው ሚኒስትር በሰጡት አስተያየት " ግንኙነታቸን ወደ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለማሸጋገር ተስማምተናል " ሲሉ መናገራቸውን ኢጂይፕት ዴይሊ አስነብቧል።
#Ethiopia #Somalia #Egypt
@tikvahethiopia
የሶማሊያ ናሽናል ኢንተለጀንስ ኤንድ ሴኪዩሪቲ ኤጀንሲ ዳይሬክተር አብዱላሂ ሞሐመድ ዓሊ ኢትዮጵያ ይገኛሉ።
አብዱላሂ ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዳይሬክተር አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ጋር መክረዋል።
ውይይቱ የአንካራውን ስምምነት ተግባራዊ ከማድረግ ጋር በተያያዘ ከሁለቱ ሀገራት አቻ ተቋማት የሚጠበቁ የትብብርና የአጋርነት መስኮች ላይ ትኩረት ያደረገ ነበር።
በውይይቱ የኢትዮጵያና ሶማሊያ የደኅንነትና የጸጥታ ተቋማት ስምምነቱ ተግባራዊ እንዳይሆን እንቅፋት የሚፈጥሩ አካላትን ለመከላከል የሚጠበቅባቸውን ሚና ለመወጣት የጋራ መግባባት እና ስምምነት ላይ መድረሳቸው ተነግሯል።
በሌላ በኩል ፥ የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር ዴኤታ አሊ ሞሃመድ ኦማር ኢትዮጽያ ይገኛሉ።
በውይይታቸው ሁለቱ ወገኖች የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ማሻሻል እና በቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ማስጠበቅ ላይ ያላቸውን ትብብር ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መምከራቸውን ኤፍ ኤም ሲ ዘግቧል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን ሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታዋን ወደ ኢትዮጵያ በላከችበት በዚህ ወቅት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯን ግብፅ ካይሮ ልካለች።
ሚኒስትሯ አሕመድ ፊቂ ከግብጹ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ባድር አብደላቲ ጋር ከመከሩ በኃላ የጋራ መግለጫ ሰጥተው ነበር።
በዚሁ መግለጫ ፤ የግብፁ ሚኒስትር " የቀይ ባሕርን ዳርቻ መጠቀም የሚችሉት ከባሕሩ ጋር የሚዋሰኑ አገራት ብቻ መሆን ይገባል ፤ የቀይ ባሕር ዳርቻ አዋሳኝ ላልሆኑ ሀገሮች ክፍት ሊሆን አይችልም " በማለት መናገራቸውን " ኢጂፕት ዴይሊ " ዘግቧል።
ግብፅ ይህን አስተያየት የሰጠችው ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ በአንካራ ኢትዮጵያ የባህር በርን ልታገኝ የምትችልበትን ስምምነት ፈርመው ፊርማ ሳይደርቅ ነው። በቀጣይ ወር ደግሞ ለዚሁ ጉዳይ ንግግር እንደሚጀመር ይታወቃል።
ከዚህ ባለፈ የግብፁ ሚኒስትር ፤ " የሱማሊያ ፌደራል መንግሥት መላው የሀገሪቱን ግዛቶች ሙሉ እንዲቆጣጠር " በሚችልበት አግባብ ላይ መምክራቸውን ተናግረዋል።
ከዚህ ባለፈ ግብፅ የአፍሪካ ህብረት በሶማሊያ በሚያደረገው ተልዕኮ " ወታደሮቼን አወጣላሁ " ብላለች።
የሶማሊያው ሚኒስትር በሰጡት አስተያየት " ግንኙነታቸን ወደ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለማሸጋገር ተስማምተናል " ሲሉ መናገራቸውን ኢጂይፕት ዴይሊ አስነብቧል።
#Ethiopia #Somalia #Egypt
@tikvahethiopia
#Somalia #Eritrea
የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ኤርትራ ናቸው።
ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሙሀሙድ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ኤርትራ ፣ አስመራ መግባታቸው ተነግሯል።
አስመራ ሲደርሱ ፕሬዜዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ነው ኤርፖርት ተገኝተው የተቀበሏቸው።
የኤርትራው የማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገ/መስቀል ሁለቱ መሪዎች በሁለትዮሽ ፣በቀጠናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ይመክራሉ ብለዋል።
ፕሬዜዳንቱ በቱርክ፣ አንካራ ከኢትዮጵያ ጋር ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ጋር በኢትዮጵያ የባህር በር ተጠቃሚነት ጉዳይ ላይ ስምምነት ከፈረሙ በኃላ ነው ኤርትራ የሄዱት።
አንደንድ ዘገባዎች የኤርትራው እና የሱማሊያው መሪ የአንካራውን ስምምነት አጀንዳቸው ሊያደርጉት እንደሚችሉ አሳይተዋል።
የሶማሊያው መሪ ከዚህ ቀደም ወደ ኤርትራ በመመላለስ የሚታወቁ ሲሆን በተለይ ግን ኢትዮጵያ እና ሶማሌላንድ የመግባቢያ ስምምነት ከፈረሙ በኃላ እንዲሁም ኢትዮጵያ ለህዝቦቼ የባህር በር ያስፈልጋቸዋል ይህ የህልውና ጉዳይ ጭምር ነው በማለት አቋማን ይፋ ካደረገችና ዓለም አቀፍ አጀንዳ ካደረገችው በኃላ ደጋግመው ኤርትራ ፣ አስመራ ኢሳያስ ጋር ተመላልሰዋል።
የኤርትራው መሪ በነዚህ ወቅቶች አንድም ጊዜ ሶማሊያ፣ ሙቃዲሾ ለጉብኝት ብለው ሄደው አያውቁም።
ባለፈው ጥቅምት ወር ላይ የግብፅ፣ የኤርትራ እና የሶማሊያ መሪዎች በአስመራ የሶስትዮሽ ጉባኤ አካሂደው የሶማሊያ ተቋማት እና ጦር ድንበሯን ለመጠበቅ እና የግዛት አንድነቷን ለማስጠበቅ የሚያስችል ስምምነት ላይ መድረሳቸው የሚዘነጋ አይደለም።
#Somlaia #Eritrea
@tikvahethiopia
የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ኤርትራ ናቸው።
ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሙሀሙድ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ኤርትራ ፣ አስመራ መግባታቸው ተነግሯል።
አስመራ ሲደርሱ ፕሬዜዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ነው ኤርፖርት ተገኝተው የተቀበሏቸው።
የኤርትራው የማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገ/መስቀል ሁለቱ መሪዎች በሁለትዮሽ ፣በቀጠናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ይመክራሉ ብለዋል።
ፕሬዜዳንቱ በቱርክ፣ አንካራ ከኢትዮጵያ ጋር ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ጋር በኢትዮጵያ የባህር በር ተጠቃሚነት ጉዳይ ላይ ስምምነት ከፈረሙ በኃላ ነው ኤርትራ የሄዱት።
አንደንድ ዘገባዎች የኤርትራው እና የሱማሊያው መሪ የአንካራውን ስምምነት አጀንዳቸው ሊያደርጉት እንደሚችሉ አሳይተዋል።
የሶማሊያው መሪ ከዚህ ቀደም ወደ ኤርትራ በመመላለስ የሚታወቁ ሲሆን በተለይ ግን ኢትዮጵያ እና ሶማሌላንድ የመግባቢያ ስምምነት ከፈረሙ በኃላ እንዲሁም ኢትዮጵያ ለህዝቦቼ የባህር በር ያስፈልጋቸዋል ይህ የህልውና ጉዳይ ጭምር ነው በማለት አቋማን ይፋ ካደረገችና ዓለም አቀፍ አጀንዳ ካደረገችው በኃላ ደጋግመው ኤርትራ ፣ አስመራ ኢሳያስ ጋር ተመላልሰዋል።
የኤርትራው መሪ በነዚህ ወቅቶች አንድም ጊዜ ሶማሊያ፣ ሙቃዲሾ ለጉብኝት ብለው ሄደው አያውቁም።
ባለፈው ጥቅምት ወር ላይ የግብፅ፣ የኤርትራ እና የሶማሊያ መሪዎች በአስመራ የሶስትዮሽ ጉባኤ አካሂደው የሶማሊያ ተቋማት እና ጦር ድንበሯን ለመጠበቅ እና የግዛት አንድነቷን ለማስጠበቅ የሚያስችል ስምምነት ላይ መድረሳቸው የሚዘነጋ አይደለም።
#Somlaia #Eritrea
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Somalia #Eritrea የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ኤርትራ ናቸው። ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሙሀሙድ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ኤርትራ ፣ አስመራ መግባታቸው ተነግሯል። አስመራ ሲደርሱ ፕሬዜዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ነው ኤርፖርት ተገኝተው የተቀበሏቸው። የኤርትራው የማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገ/መስቀል ሁለቱ መሪዎች በሁለትዮሽ ፣በቀጠናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ይመክራሉ ብለዋል። ፕሬዜዳንቱ በቱርክ፣…
#Somalia #Djibouti
ከቀናት በፊት ኤርትራ አስመራ የነበሩት የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሙሀመድ ዛሬ ጅቡቲ ገብተዋል።
ወደ ጅቡቲ ያቀኑት በፕሬዜዳንት ኢስማኤል ኡማር ጌሌህ ግብዣ እንደሆነ ተነግሯል።
ሁለቱ መሪዎች በሁለትዮሽ እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ እንደሚወያዩ ተገልጿል።
@tikvahethiopia
ከቀናት በፊት ኤርትራ አስመራ የነበሩት የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሙሀመድ ዛሬ ጅቡቲ ገብተዋል።
ወደ ጅቡቲ ያቀኑት በፕሬዜዳንት ኢስማኤል ኡማር ጌሌህ ግብዣ እንደሆነ ተነግሯል።
ሁለቱ መሪዎች በሁለትዮሽ እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ እንደሚወያዩ ተገልጿል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" መልሼ አጤነዋለሁ " - ሶማሊያ የሶማሊያ መንግሥት የኢትዮጵያ ወታደሮች በአፍሪካ ኅብረት ልዑክ ውስጥ መካተታቸውን በተመለከተ " መልሶ ለማጤን " ዝግጁ መሆኑን አስታውቋል። አንድ የሶማሊያ መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣን ለቪኦኤ ሬድዮ በሰጡት ቃል፤ " የሶማሊያ መንግሥት ለልዑኩ ኅይል ከሚያዋጡት ሀገራት ዩጋንዳ፣ ኬንያ፣ ጂቡቲ እና ቡሩንዲ ወታደሮችን አግኝቶ ደልድሏል " ሲሉ አስታውቀዋል። ኢትዮጵያ…
#Ethiopia #Somalia
ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ የ #AUSSOM ተልዕኮ ውጤታማ ለማድረግ በትብብር ለመስራት መስማማታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳወቀ።
በመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሀመድ የተመራ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በሶማሊያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጉ ተነግሯል።
ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባሰራጨው መረጃ ፥ የልዑካን ቡድኑ ከሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼኽ ማህሙድ ጋር ውጤታማ ውይይት አድርገዋል።
ከኢፌዴሪ. ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ለፕሬዚዳንቱ የተላከ መልዕክትን አድርሰዋል።
" በውይይቱ ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ በሶማሊያ እና በቀጣናው ሰላም እና መረጋጋትን ለማረጋገጥ በጋራ ለመስራት ያላቸውን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል " ያለው ሚኒስቴሩ " ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ የAUSSOM ተልዕኮ ውጤታማ ለማድረግ በትብብር ለመስራት ተስማምተዋል " ሲል ገልጿል።
በቅርቡ የሶማሊያ ከፍተኛ ኃላፊዎች በአዲስ አበባ ጉብኝት በማድረግ ውይይት ለማካሄድ መስማማታቸውም ተመላክቷል።
የሶማሊያ መከላከያ ሚኒስትር አብድርቋድር ኑር ጃማ ፤ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የሶማሊያን ሰላም ለማረጋገጥ ለከፈለው መስዋትነት እና ላበረከተው አስተዋጽዖ ያላቸው አክብሮት እና ምስጋና ማቅረባቸው ተነግሯል።
#MinistryofForeignAffairsofEthiopia
#FDREDefenseForce
@tikvahethiopia
ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ የ #AUSSOM ተልዕኮ ውጤታማ ለማድረግ በትብብር ለመስራት መስማማታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳወቀ።
በመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሀመድ የተመራ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በሶማሊያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጉ ተነግሯል።
ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባሰራጨው መረጃ ፥ የልዑካን ቡድኑ ከሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼኽ ማህሙድ ጋር ውጤታማ ውይይት አድርገዋል።
ከኢፌዴሪ. ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ለፕሬዚዳንቱ የተላከ መልዕክትን አድርሰዋል።
" በውይይቱ ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ በሶማሊያ እና በቀጣናው ሰላም እና መረጋጋትን ለማረጋገጥ በጋራ ለመስራት ያላቸውን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል " ያለው ሚኒስቴሩ " ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ የAUSSOM ተልዕኮ ውጤታማ ለማድረግ በትብብር ለመስራት ተስማምተዋል " ሲል ገልጿል።
በቅርቡ የሶማሊያ ከፍተኛ ኃላፊዎች በአዲስ አበባ ጉብኝት በማድረግ ውይይት ለማካሄድ መስማማታቸውም ተመላክቷል።
የሶማሊያ መከላከያ ሚኒስትር አብድርቋድር ኑር ጃማ ፤ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የሶማሊያን ሰላም ለማረጋገጥ ለከፈለው መስዋትነት እና ላበረከተው አስተዋጽዖ ያላቸው አክብሮት እና ምስጋና ማቅረባቸው ተነግሯል።
#MinistryofForeignAffairsofEthiopia
#FDREDefenseForce
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ መሪዎች በምን ጉዳዮች ላይ መከሩ ፤ ምንስ ተስማሙ ?
የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) እና የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሙሀሙድ ዛሬ በአዲስ አበባ የሁለትዮሽ ምክክር አድርገዋል።
ከውይይቱ በኃላ የጋራ መግለጫ ወጥቷል።
ምን ተባለ ?
- በሁለትዮሽ እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ መክረዋል።
- በሁለቱ ሀገራት ህዝቦች መካከል ያለውን ወንድማማችነትና ግንኙነት በማጠናከር ላይ ገንቢ ውይይት አድርገዋል።
- የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ወደነበረበት ለመመለስ እና በየመዲኖቻቸው ሙሉ ዲፕሎማሲያዊ ውክል እንዲኖር ለማድረግ ተስማምተዋል።
- መሪዎቹ ለቀጣናው መረጋጋት የሁለቱ ሀገራት የጋራ የእርስ በርስ እምነት ፣ መተማመን እና መከባበር ላይ የተመሰረተ ጠንካራ ትብብር እንደሚያስፈልግ አረጋግጠዋል።
- ቀጠናዊ ግንኙነቶችን ለማሻሻል፣ የጋራ መግባባትን ለመፍጠር እና የጋራ እድገትን ለማስቀጠል በትብብር ለመስራት ተስማምተዋል።
- መሪዎቹ የጸጥታ ትብብር ማስቀጠልና ማጠናከር በሚቻልበት ጉዳይ ላይ ያተኮረ ውይይት አድርገዋል። በቀጠናው ፅንፈኛ ታጣቂ ሃይሎች እየፈጠሩ ያሉትን አሳሳቢና እየጨመሩ ያሉ ስጋቶችን በመገምገም መሪዎቹ በቀጠናው ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን የሚደረገውን ትብብር ለማጠናከር ለጸጥታ ተቋሞቻቸው መመሪያ ለመስጠት ተስማምተዋል።
- በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የኢኮኖሚ ትብብር፣ ንግድ እና ኢንቨስትመንት ማጠናከር ያለውን ጠቀሜታ ላይ ተወያይተዋል ፤ አጽንኦትም ሰጥተዋል። የበለጠ ጠንካራ ኢኮኖሚያዊ ትብብር በማድረግ የንግድ ልውውጥን ለማሳለጥ እና የጋራ ብልጽግናን ለመፍጠር የመሰረተ ልማት ትስስሮችን ለማስፋት ተስማምተዋል።
- ለአንካራው ስምምነት በጓደኝነት እና በአብሮነት መንፈስ ቁርጠኝነታቸውን ዳግም ያረጋገጡ ሲሆን በስምምነቱ ላይ የታቀዱትን የቴክኒክ ድርድሮችን ለማፋጠንም ተስማምተዋል።
#Ethiopia #Somalia #Peace
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) እና የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሙሀሙድ ዛሬ በአዲስ አበባ የሁለትዮሽ ምክክር አድርገዋል።
ከውይይቱ በኃላ የጋራ መግለጫ ወጥቷል።
ምን ተባለ ?
- በሁለትዮሽ እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ መክረዋል።
- በሁለቱ ሀገራት ህዝቦች መካከል ያለውን ወንድማማችነትና ግንኙነት በማጠናከር ላይ ገንቢ ውይይት አድርገዋል።
- የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ወደነበረበት ለመመለስ እና በየመዲኖቻቸው ሙሉ ዲፕሎማሲያዊ ውክል እንዲኖር ለማድረግ ተስማምተዋል።
- መሪዎቹ ለቀጣናው መረጋጋት የሁለቱ ሀገራት የጋራ የእርስ በርስ እምነት ፣ መተማመን እና መከባበር ላይ የተመሰረተ ጠንካራ ትብብር እንደሚያስፈልግ አረጋግጠዋል።
- ቀጠናዊ ግንኙነቶችን ለማሻሻል፣ የጋራ መግባባትን ለመፍጠር እና የጋራ እድገትን ለማስቀጠል በትብብር ለመስራት ተስማምተዋል።
- መሪዎቹ የጸጥታ ትብብር ማስቀጠልና ማጠናከር በሚቻልበት ጉዳይ ላይ ያተኮረ ውይይት አድርገዋል። በቀጠናው ፅንፈኛ ታጣቂ ሃይሎች እየፈጠሩ ያሉትን አሳሳቢና እየጨመሩ ያሉ ስጋቶችን በመገምገም መሪዎቹ በቀጠናው ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን የሚደረገውን ትብብር ለማጠናከር ለጸጥታ ተቋሞቻቸው መመሪያ ለመስጠት ተስማምተዋል።
- በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የኢኮኖሚ ትብብር፣ ንግድ እና ኢንቨስትመንት ማጠናከር ያለውን ጠቀሜታ ላይ ተወያይተዋል ፤ አጽንኦትም ሰጥተዋል። የበለጠ ጠንካራ ኢኮኖሚያዊ ትብብር በማድረግ የንግድ ልውውጥን ለማሳለጥ እና የጋራ ብልጽግናን ለመፍጠር የመሰረተ ልማት ትስስሮችን ለማስፋት ተስማምተዋል።
- ለአንካራው ስምምነት በጓደኝነት እና በአብሮነት መንፈስ ቁርጠኝነታቸውን ዳግም ያረጋገጡ ሲሆን በስምምነቱ ላይ የታቀዱትን የቴክኒክ ድርድሮችን ለማፋጠንም ተስማምተዋል።
#Ethiopia #Somalia #Peace
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ መሪዎች በምን ጉዳዮች ላይ መከሩ ፤ ምንስ ተስማሙ ? የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) እና የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሙሀሙድ ዛሬ በአዲስ አበባ የሁለትዮሽ ምክክር አድርገዋል። ከውይይቱ በኃላ የጋራ መግለጫ ወጥቷል። ምን ተባለ ? - በሁለትዮሽ እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። - በሁለቱ ሀገራት ህዝቦች መካከል ያለውን ወንድማማችነትና ግንኙነት በማጠናከር…
#Ethiopia #Somalia
የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ዛሬ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።
ለአንድ ቀን ይፋዊ የስራ ጉብኝት ትላንት አዲስ አበባ የገቡት የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሙሀሙድ ዛሬ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።
ወደ ሀገራቸው ሲመለሱም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ቦሌ ኤርፖርት ተገኝተው ሸኝተዋቸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ " በይፋዊ ጉብኝታቸው ወቅት የሁለትዮሽ ግንኙነቶቻችንን ለማጠናከር ውጤታማ ውይይቶች አድርገናል " ብለዋል።
@tikvahethiopia
የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ዛሬ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።
ለአንድ ቀን ይፋዊ የስራ ጉብኝት ትላንት አዲስ አበባ የገቡት የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሙሀሙድ ዛሬ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።
ወደ ሀገራቸው ሲመለሱም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ቦሌ ኤርፖርት ተገኝተው ሸኝተዋቸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ " በይፋዊ ጉብኝታቸው ወቅት የሁለትዮሽ ግንኙነቶቻችንን ለማጠናከር ውጤታማ ውይይቶች አድርገናል " ብለዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia #Somalia ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ የ #AUSSOM ተልዕኮ ውጤታማ ለማድረግ በትብብር ለመስራት መስማማታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳወቀ። በመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሀመድ የተመራ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በሶማሊያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጉ ተነግሯል። ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባሰራጨው መረጃ ፥ የልዑካን ቡድኑ ከሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼኽ ማህሙድ ጋር ውጤታማ ውይይት…
#Ethiopia 🤝 #Somalia
በሶማሊያ በሁለትዮሽ ስምምነት መሠረት ተሰማርቶ የሚገኘው የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ሁኔታን በተመለከተ አሠራር ለመዘርጋት የሁለቱ አገራት የጦር አዛዦች ስምምነት ላይ ደርሰዋል።
በኢትዮጵያው መከላከያ ሠራዊት ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እና በሶማሊያ ብሔራዊ ጦር ኃይሎች የመከላከያ ሠራዊት አዛዥ ሜጀር ጄኔራል ኦዳዋ ዩሱፍ ራጌ መካከል የተደረሰው ስምምነት በሶማሊያ ያለው የኢትዮጵያ ጦር ስምሪትን፣ እንቅስቃሴዎችን እንዲሁም አጠቃላይ ክንዋኔዎች የሚመለከተውን 'ስታተስ ኦፍ ፎርስ አግሪመንት' ተግባራዊ ለማድረግ ያለመ ነው።
አንዲት አገር ጦሯን በሌላ ውጭ አገር በምታሰማራበት ወቅት የጦሩ ስምሪት፣ ተግባራት፣ ኃላፊነት፣ መብቶችን የሚመለከተው በአገራቱ መካከል የሚደረስ አሳሪ (ሕጋዊ ስምምነት) ስታተስ ኦፍ ፎርስ አግሪመንት ይሰኛል።
ይህ 'ስታተስ ኦፍ ፎርስ' ስምምነት በአውሮፓውያኑ 2023 በአገራቱ መካከል የተፈረመው የመከላከያ ትብብር የመግባቢያ ስምምነት ዋና አካል እንደሚሆን ተነግሯል።
በፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የሚመራ ልዑክ በሶማሊያ መዲና ሞቃዲሾ የካቲት 15/2017 ዓ.ም. ባደረገው የአንድ ቀን ይፋዊ ጉብኝት ይህንን ስምምነት ጨምሮ ከአገሪቱ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር በሶማሊያ እና በቀጠናው ሰላም፣ ደኅንነት፣ ፀጥታ እና የመረጋጋት ጉዳዮች ላይ መክረዋል።
ሁለቱ የጦር አዛዦች የአፍሪካ ኅብረት የሶማሊያ ድጋፍ እና ማረጋጋት ተልዕኮ (ኤዩሶም) ጅማሮ አድንቀው ከዚህ ቀደም በነበረው የአፍሪካ ኅብረት የሰላም እና የፀጥታው ምክር ቤት አትሚስ ስኬቶች ማስቀጠል አስፈላጊ ነው ብለዋል።
የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል በኤዩሶም ስምሪት ላይ እንዲካተት የጦር አዛዦቹ በዚህ ወቅት ስምምነት ላይ መድረሳቸው ተገልጿል።
በሶማሊያ እና ኢትዮጵያ መካከል ያለው ውዝግብ በአንካራ ስምምነት መፈታቱን ተከትሎ ሶማሊያ የኢትዮጵያ ወታደሮችን በአዲሱ የአፍሪካ ኅብረት የድጋፍ እና የማረጋጋት ተልዕኮ (ኤዩሶም) ውስጥ ላለማካተት አሳልፋው የነበረውን ውሳኔ ልትቀለብስ እና በተልዕኮው ለማካተት እያጤነች እንደሆነ ከዚህ ቀደም ተዘግቦ ነበር።
#SomaliaNationalTV #BBCAMAHRIC
@tikvahethiopia
በሶማሊያ በሁለትዮሽ ስምምነት መሠረት ተሰማርቶ የሚገኘው የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ሁኔታን በተመለከተ አሠራር ለመዘርጋት የሁለቱ አገራት የጦር አዛዦች ስምምነት ላይ ደርሰዋል።
በኢትዮጵያው መከላከያ ሠራዊት ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እና በሶማሊያ ብሔራዊ ጦር ኃይሎች የመከላከያ ሠራዊት አዛዥ ሜጀር ጄኔራል ኦዳዋ ዩሱፍ ራጌ መካከል የተደረሰው ስምምነት በሶማሊያ ያለው የኢትዮጵያ ጦር ስምሪትን፣ እንቅስቃሴዎችን እንዲሁም አጠቃላይ ክንዋኔዎች የሚመለከተውን 'ስታተስ ኦፍ ፎርስ አግሪመንት' ተግባራዊ ለማድረግ ያለመ ነው።
አንዲት አገር ጦሯን በሌላ ውጭ አገር በምታሰማራበት ወቅት የጦሩ ስምሪት፣ ተግባራት፣ ኃላፊነት፣ መብቶችን የሚመለከተው በአገራቱ መካከል የሚደረስ አሳሪ (ሕጋዊ ስምምነት) ስታተስ ኦፍ ፎርስ አግሪመንት ይሰኛል።
ይህ 'ስታተስ ኦፍ ፎርስ' ስምምነት በአውሮፓውያኑ 2023 በአገራቱ መካከል የተፈረመው የመከላከያ ትብብር የመግባቢያ ስምምነት ዋና አካል እንደሚሆን ተነግሯል።
በፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የሚመራ ልዑክ በሶማሊያ መዲና ሞቃዲሾ የካቲት 15/2017 ዓ.ም. ባደረገው የአንድ ቀን ይፋዊ ጉብኝት ይህንን ስምምነት ጨምሮ ከአገሪቱ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር በሶማሊያ እና በቀጠናው ሰላም፣ ደኅንነት፣ ፀጥታ እና የመረጋጋት ጉዳዮች ላይ መክረዋል።
ሁለቱ የጦር አዛዦች የአፍሪካ ኅብረት የሶማሊያ ድጋፍ እና ማረጋጋት ተልዕኮ (ኤዩሶም) ጅማሮ አድንቀው ከዚህ ቀደም በነበረው የአፍሪካ ኅብረት የሰላም እና የፀጥታው ምክር ቤት አትሚስ ስኬቶች ማስቀጠል አስፈላጊ ነው ብለዋል።
የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል በኤዩሶም ስምሪት ላይ እንዲካተት የጦር አዛዦቹ በዚህ ወቅት ስምምነት ላይ መድረሳቸው ተገልጿል።
በሶማሊያ እና ኢትዮጵያ መካከል ያለው ውዝግብ በአንካራ ስምምነት መፈታቱን ተከትሎ ሶማሊያ የኢትዮጵያ ወታደሮችን በአዲሱ የአፍሪካ ኅብረት የድጋፍ እና የማረጋጋት ተልዕኮ (ኤዩሶም) ውስጥ ላለማካተት አሳልፋው የነበረውን ውሳኔ ልትቀለብስ እና በተልዕኮው ለማካተት እያጤነች እንደሆነ ከዚህ ቀደም ተዘግቦ ነበር።
#SomaliaNationalTV #BBCAMAHRIC
@tikvahethiopia
#Ethiopia #Somalia
ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ ረፋድ በሶማሊያ ዋና ከተማ ሞቃዲሾ የሥራ ጉብኝት አድርገዋል።
ሁለቱ ሀገራት ገብተውበት ከነበረው የዲፕሎማሲ እና የፖለቲካ ውጥረት በኋላ ለመጀመርያ ጊዜ መሆኑ ነው።
የሶማሊያው ፕሬዚደንት ሐሰን ሼክ መሐሙድም ቱርክ ሁለቱን ሀገራት አንካራ ላይ ካስማማች በኋላ ባለፈው ጥር 3 ቀን አዲስ አበባን ጎብኝተዋል።
አስከትለውም በአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ታድመው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር ተነጋግረዋል።
በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ በጋራ በወጣው መግለጫ " ይህ ጉብኝት ባለፉት ጥቂት ወራት ውስጥ የተደረጉ ተከታታይ ግንኙነቶችን የተከተለ፣ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነትም ወደ መደበኛ ሁኔታ የሚመልስ ነው " ብሏል።
ሁለቱ መሪዎች ለጋራ ጥቅም ትብብራቸውን ለማጠናከር ቁርጠኝነታቸውን ስለማረጋገጣቸው እና በዲፕሎማሲያዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ትብብር " መተማመንን ማሳደግ አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል " ተብሏል።
የዚህ ጉብኝት እንደምታን በሚመለከት ቃላቸውን ለዶቼ ቨለ ሬድዮ የሰጡት ፤ በውጭ ጉዳይ ኢንስቲቲዩት የአፍሪካ ጉዳዮች የሥራ ክፍል ኃላፊ እና ከፍተኛ ተመራማሪ የሆኑት ዶክተር ግዛቸው አስራት ፥ ሁለቱ ሀገራት መተማመን በሚያስችል ሁኔታ መነጋገር የሚችሉበት ዕድል እንደሚሆን ገልፀዋል።
" የቴክኒክ ቡድኑ (የአንካራ ስምምነት) ከሁለት ሳምንት በፊት አንካራ ላይ ተገናኝቶ ሲነጋገር ተመልክተናል። መስማማቶች እና መግባባቶች ላይ የደረሱበት፣ መተማመን በሚያስችል ሁኔታ ንግግሮች እያደረጉ ያሉበት ሂደት ነው " ብለዋል።
" የቱርክ መንግሥት አካባቢውን ካላስፈላጊ ውጥረት ታድጓል " ያሉት ተመራማሪው እንዲህ ያሉ መልካም ልምዶች በዚህ ቀጣና ብዙም አይታዩም ብለዋል። ይህን መሳይ የውይይት፣ የድርድር እና የሰላም መንገዶች ሲታዩ ማመስገን ያስፈልጋል ብለዋል።
ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ የጋራ ጥቅሞችን በማሳደግ፣ ሰላምና ደህንነትን በማስፈን እና የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን በማጠናከር ለዜጎቻቸውና ለሰፊው የአፍሪካ ቀንድ ቀጣና በጋራ ለመስራት ቁርጠኛ መሆናቸውም ጉብኝቱን ተከትሎ በወጣው የጋራ መግለጫ ላይ ተጠቅሷል።
ዶክተር ግዛቸው አስራት " ቀጣናዊ ትብብርን " የተመለከቱ ውይይቶች እንደሚኖሩ ገልፀዋል።
የዛሬውን ጉብኝት በሚመለከት አስቀድመው የወጡ ዘገባዎች ሞቃዲሾ ውስጥ ከፍተኛ የፀጥታ ጥበቃ መደረጉን ያመለክታሉ። #DW
@TIKVAHETHIOPIA
ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ ረፋድ በሶማሊያ ዋና ከተማ ሞቃዲሾ የሥራ ጉብኝት አድርገዋል።
ሁለቱ ሀገራት ገብተውበት ከነበረው የዲፕሎማሲ እና የፖለቲካ ውጥረት በኋላ ለመጀመርያ ጊዜ መሆኑ ነው።
የሶማሊያው ፕሬዚደንት ሐሰን ሼክ መሐሙድም ቱርክ ሁለቱን ሀገራት አንካራ ላይ ካስማማች በኋላ ባለፈው ጥር 3 ቀን አዲስ አበባን ጎብኝተዋል።
አስከትለውም በአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ታድመው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር ተነጋግረዋል።
በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ በጋራ በወጣው መግለጫ " ይህ ጉብኝት ባለፉት ጥቂት ወራት ውስጥ የተደረጉ ተከታታይ ግንኙነቶችን የተከተለ፣ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነትም ወደ መደበኛ ሁኔታ የሚመልስ ነው " ብሏል።
ሁለቱ መሪዎች ለጋራ ጥቅም ትብብራቸውን ለማጠናከር ቁርጠኝነታቸውን ስለማረጋገጣቸው እና በዲፕሎማሲያዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ትብብር " መተማመንን ማሳደግ አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል " ተብሏል።
የዚህ ጉብኝት እንደምታን በሚመለከት ቃላቸውን ለዶቼ ቨለ ሬድዮ የሰጡት ፤ በውጭ ጉዳይ ኢንስቲቲዩት የአፍሪካ ጉዳዮች የሥራ ክፍል ኃላፊ እና ከፍተኛ ተመራማሪ የሆኑት ዶክተር ግዛቸው አስራት ፥ ሁለቱ ሀገራት መተማመን በሚያስችል ሁኔታ መነጋገር የሚችሉበት ዕድል እንደሚሆን ገልፀዋል።
" የቴክኒክ ቡድኑ (የአንካራ ስምምነት) ከሁለት ሳምንት በፊት አንካራ ላይ ተገናኝቶ ሲነጋገር ተመልክተናል። መስማማቶች እና መግባባቶች ላይ የደረሱበት፣ መተማመን በሚያስችል ሁኔታ ንግግሮች እያደረጉ ያሉበት ሂደት ነው " ብለዋል።
" የቱርክ መንግሥት አካባቢውን ካላስፈላጊ ውጥረት ታድጓል " ያሉት ተመራማሪው እንዲህ ያሉ መልካም ልምዶች በዚህ ቀጣና ብዙም አይታዩም ብለዋል። ይህን መሳይ የውይይት፣ የድርድር እና የሰላም መንገዶች ሲታዩ ማመስገን ያስፈልጋል ብለዋል።
ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ የጋራ ጥቅሞችን በማሳደግ፣ ሰላምና ደህንነትን በማስፈን እና የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን በማጠናከር ለዜጎቻቸውና ለሰፊው የአፍሪካ ቀንድ ቀጣና በጋራ ለመስራት ቁርጠኛ መሆናቸውም ጉብኝቱን ተከትሎ በወጣው የጋራ መግለጫ ላይ ተጠቅሷል።
ዶክተር ግዛቸው አስራት " ቀጣናዊ ትብብርን " የተመለከቱ ውይይቶች እንደሚኖሩ ገልፀዋል።
የዛሬውን ጉብኝት በሚመለከት አስቀድመው የወጡ ዘገባዎች ሞቃዲሾ ውስጥ ከፍተኛ የፀጥታ ጥበቃ መደረጉን ያመለክታሉ። #DW
@TIKVAHETHIOPIA