TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Amahra

" የባልደረባችንን አስክሬን ማምጣት አልቻልንም ፤ እዛው ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል ውስጥ ነው ያለው " -ዶ/ር ፋሪስ ደሊል

ተቋማት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ለመፈተን ወደ አማራ ክልል ዩኒቨርሲቲዎች ተመድበው የሄዱ እና በክልሉ ባለው ግጭት ምክንያት  መመለስ ያልቻሉ መምህራንን በተመለከተ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየተነጋገሩ መሆኑን አሳውቀዋል።

በርከታ የዩኒቨርሲቲ መምህራን የ12ኛ ክፍል ፈተና ለመፈተን ወደ አማራ ክልል በሄዱበት በተባባሰው ግጭት ምክንያት ከክልሉ መውጣት ባለመቻላቸው ችግር ላይ መሆናቸውን እየገለፁ ናቸው።

መምህራኖቹ አማራ ክልል ከሚገኙ ተቋማት አንዱ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሲሆን ፤ መምህራኑን በተመለከተ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ንግግር እየተደረገ መሆኑን ገልጿል።

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዜዳንት ዶ/ር ፋሪስ ደሊል ለቪኦኤ በሰጡት ቃል ፤ ባለፈው ሳምንት በጎንደር የተገደለው መምህር የተቋማቸው ባልደረባ መሆኑን ገልጸው እስካሁን እስክሬኑ ከከተማው እንዳልወጣ ጠቁመዋል።

ሌሎችም መምህራን ጎንደር እንደሚገኙ ገልጸዋል።

ዶ/ር ፋሪስ ፤ " ለመፈተን ከሄዱ መምህራን አንዱ መምህር ታደሰ አበበ አስክሬኑን ማምጣት አልቻልንም እዛው ነው ያለው ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል ውስጥ " ያሉ ሲሆን " ሌሎች ለመፈተን የሄዱ መምህራንም አሉ እነሱን በስልክ እያገኘናቸው ነው መመልስ አልቻሉም " ብለዋል።

ካሉበት ወጥተው ለመምጣት ደህንነት የለም ያሉት ፕሬዜዳንቱ " የጥይት ድምፅ በተለያየ ቦታ ይሰማል ዩኒቨርሲቲው ባላችሁበት ቆዩ ነው ያላቸው። " ሲሉ ገልጸዋል።

ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመምህራኑ ጉዳይ እየተነጋገርን ነው ያሉት ዶ/ር ፋሪስ " መንገዱ ሰላም ሆኖ መውጣት የሚችሉበት ሰዓት ደርሶ እስኪመጡ በትግዕስት መጠበቅ እንዳለብን ነው የምንነጋገረው ፤ እዛው ከለው የዩኒቨርሲቲ አመራር ፣ ፕሬዜዳንቱም ጋር እየተደዋወልን ነው በትዕግስት ጠብቀን መንቀሳቀስ ሲችሉ መምህራኖቻችን እና የባልደረባችንን አስክሬን እንደምናገኝ ነው የምንነጋገርው " ብለዋል

የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዜዳንት ዶ/ር ጀማል አባፊጣ ፤ 53 መምህራን በጎንደር ፣ ደባርቅ እና ደብረታቦር ዩኒቨርሲቲዎች እንደተመደቡና ሁኔታቸውን በቅርበት እየተከታተልን ነው ብለዋል።

ደህንነታቸው ተጠብቆ በሚወጡበት ሁኔታ ላይ ከትምህርት ሚኒስቴር እና ከትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ጋር እየተነጋገርን ነው ሲሉ አሳውቀዋል።

የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፤ ፈታኝ መምህራንን ቀደሞ ወደመጡበት መሸኘቱን ተፈታኝ ተማሪዎች ግን በመንገድ መዘጋት ምክንያት ከግቢ መውጣት አልቻሉም ብሏል። ተቋሙ ባህር ዳር ነዋሪ የሆኑትን እና ቤተሰብ ያላቸውን የሸኘ ሲሆን ወደ ወረዳ እና ዞን መመለስ የነበረባቸውን በመንገድ መዘጋት መሄድ ስላልቻሉ ግቢ ውስጥ እንዲቆዩ መደረጉን ለሬድዮ ጣቢያው (ቪኦኤ) ገልጿል።

የአውሮፕላን በረራ በተቋረጠባቸው አካባቢዎች የሚገኙ የፈተና አስፈጻሚዎች / መምህራን " ያለው ሁኔታ እስከሚረጋጋ ድረስ ትንሽ ቀን " መጠበቅ እንደሚኖርባቸው የትምህርት ሚኒስትሩ ባለፈው አርብ በሰጡት መግለጫ መግለጻቸው ይታወሳል፡፡

@tikvahethiopia
Visa Everywhere Initiative (VEI) ልዩ የኢትዮጵያ ውድድር: ቢዝነሳችሁን ወደ ላቀ ደረጃ ለመውሰድ ዝግጁ ናችሁ?

ለVisa Everywhere Initiative 2015/16 በመመዝገብ እውቅና ማግኘት፣ የቬንቸር ካፒታሊስቶችን ዐይን መሳብ ፣ ኢንቬስትመንት እና አጋሮችን ማግኘት ይቻላል።

የVEI ልዩ የኢትዮጵያ ውድድር ምዝገባ እስከ ነሐሴ 14 ድረስ ክፍት ነው። https://africa.visa.com/visa-everywhere/everywhere-initiative/initiative.html

#EverywhereInitiative8
#ሰከላ_ስኩል_ሲስተም

የግልና የመንግስት የትምህርት ተቋማትን ሁለንተናዊ ክንውን የሚያዘምነውን የሰከላ ሲስተምን (SIMS) በአዲሱ የት/ት ዘመን ይተግብሩ!

ክፍያዎችን በኦንላይን ለመፈፀም፣ መረጃ አያያዝና አስተዳደርን ዲጂታል ለማድርግ ሁሉን በአንድ የያዘ አስተማማኝ መተግበርያ!

ይህንን https://sekela.app ወይንም https://sekela.app/school-registration ሊንክ በመከተልና በመመዝገብ ያለምንም ኢንስታሌሽንና ቅድመ ክፍያ ካሉበት ይጠቀሙ
እስራኤል ዜጎቿን ከአማራ ክልል ወደ #ትግራይ ክልል ማስወጣቷን " ጄሩሳሌም ፖስት " ዘግቧል።

እስራኤል በአማራ ክልል ውስጥ ያለውን ግጭትና የታወጀውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በቅርበት እየተከታተለችው መሆኑ ተነግሯል።

ባለፈው ሰኞ ከአካባቢው የመንግሥት ኃላፊዎች ጋር በመሆን ተጓዥ ዜጎቿን ከአማራ ክልል ወደ ትግራይ እንዲወጡ ማድረጓ ተገልጿል።

ዘገባው ተካሂዷል ባለው የእስራኤል ዜጎችን ከግጭት ቀጠና የማስወጣት ኦፕሬሽን 13 ተጓዥ እስራኤላውያን እና ሌሎች 7 ሌሎች የውጭ ሀገር ዜጎች ከደባርቅ ወደ ትግራይ ሽረ ከተማ እንዲወጡ ተደርጓል።

ከሽረ ከተማም በአውሮፕላን በረራ ወደ አዲስ አበባ እንደሚጓዙ ተነግሯል።

በሌሎች የአማራ ክልል አካባቢዎች እስራኤላውያን መኖራቸው የተመላከተ ሲሆን ሀገሪቱ ክትትል እያደረገችና ከግጭት ቀጠና ደህንነታቸው ተጠብቆ ለማስወጣት በሚቻልበት ሁኔታ መንገድ እየተፈለገ መሆኑ ተነግሯል።

በአማራ ክልል በተለይም በጎንደር ከተማ ፤ ወደ እስራኤል ለመሄድ የሚጠባበቁ አባላት በርከታ ቤተእስራኤላውያን ማህበረሰብ አባላት አሉ።

#ጄሩሳሌም_ፖስት

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NewsAlert በአዲስ አበባ ሞተር ብስክሌት እስከ ረቡዕ ድረስ ታገደ። የአዲስ አበባ የትራንስፖርት ቢሮ ፤ በከተማው ለሚገኙ የሞተር ብስክሌተኞች በሙሉ ባስተላለፈው መልዕክት ከነገ ሐምሌ 28/2015 ዓ.ም ከጠዋቱ 12:00 ጀምሮ እስከ እሮብ ነሀሴ 3/2015 ዓ.ም እስከ ምሽት 12:00 ድረስ ሞተር ብስክሌት ማሽከርከር ፍፁም የተከለከለ መሆኑን አሳውቋል። ቢሮው ፤ ክልከላው በምን ምክንያት እንደተጣለ…
እገዳው ተራዘመ።

የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የሞተር ብስክሌት ማሽከርከርን እስከ እሮብ ነሐሴ 3/2015 ዓ.ም ማገዱ ይታወቃል።

ዛሬ ባሰራጨው መልዕክት እግዱ ላልተወሰነ ጊዜ የተራዘመ መሆኑን አሳውቋል።

ክልከላው የፀጥታና የትራፊክ ቁጥጥር የሚሰሩ አካላትን የማያካትት ሲሆን ፤ የሞተር ብስክሌት ባለንብረቶችም ሆኑ አሽከርካሪዎች እግዱ እሰኪነሳ በትዕግስት እንዲጠብቁ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።

ይህንን መልእክት በሚተላለፉ አካላት ላይ ጥብቅ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን ቢሮው አስጠንቅቋል።

በከተማዋ ሞተር ለምን እንደታገደ በቢሮው በኩል የተሰጠ ማብራሪያም ይሁን ገለፃ የለም።

በርካታ ወጣቶች በሞተር በመንቀሳሰቅ በሚሰራ የስራ ዘርፍ / እቃ በማድረስ ተሰማርተው ገቢ እንደሚያገኙ ይታወቃል።

እገዳውን በተመለከተ ቃላቸውን የሰጡን ሞተረኞች " ሰርተን ቤተሰብ ከላስተዳደርን እንዴት እንኖራለን ፤ ችግሮች ካሉም ማስተካከያ ማድረግ ይቻለል ፤ ከዚህ ቀደምም በተደጋጋሚ ጊዜ እየታገድን ነበር ፤ አሁንም ታግዷል ምክንያቱ ደግሞ ግልጽ አይደለም ፤ አስተዳደሩ ስለኛም ህይወት ያስብልን " ብለዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Gondar የጎንደር ግጭት ከተማዋን አስከፊ ሁኔታ ላይ እንደጣላት አንድ በጎንደር ሆስፒታል የሚሰራ የቲክቫህ የቤተሰብ አባል የሆነ የሕክምና ዶክተር አሳውቆናል። የጎንደር ሁኔታ #እጅግ_አስከፊ እንደነበር የገለፀልን የህክምና ዶክተሩ " በግጭቱ ምክንያት የመጨረሻ ኢሰብአዊ ድርጊት ተፈጽሟል ፤ ሰላማዊ ዜጎች እዚህም እዚያም ተገድለዋል " ሲል አስረድቷል። በሆስፒታሉ ውሃ ፣ ኦክስጂን ፣ እንዲሁም ደግሞ…
#GONDAR

በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል የህክምና ዶክተር የሆነው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል በከተማው ስላለው ሁኔታ መረጃዎችን አጋርቶናል።

- ታማሚዎች በኦክስጂን እና ደም እጥረት እየሞቱ መሆኑን ገልጿል።

- ለአምቡላንስ ጨምር ምንምአይነት የትራንስፖርት አማራጭ እንደሌለ ፤ ታማሚዎች በሰው ኃይል በሸክም ወደ ሆስፒታሉ እየመጡ መሆኑን አስረድቷል።

- ወደ 20 (ሰላማዊ ሰዎች) ወደ ሆስፒታሉ ከደረሱ በኃላ እንደሞቱ እንዲሁም ከ200 በላይ ሰዎች ተጎድተው ሆስፒታል እንደሚጡ ከነዚህ ውስጥ አብዛኞቹ ሰላማዊ ሰዎች መሆናቸውን ገልጿል።

- በርከታ ሰዎች በቤታቸው ሞተው፣ ቀብራቸውም በአካባቢያቸው በተለይም በቀበሌ 4 ፣ 12 ፣ 11 እና 18 መፈፀሙን አመልክቷል።

- ባለፈው ሰኞ በነበረ ግጭት ከሆስፒታሉ የተወሰኑ ህፃዎች በመሳሪያ ቢመቱትም የተጎዳ ሰው ግን እንዳልነበር ገልጿል።

- ሆስፒታሉ ምግብ እንዲሁም መድሃኒት እያለቀበት መሆኑን አመልክቷል።

ዛሬ ጎንደር እንዴት ናት ?

አሁን ላይ በጎንደር ከተማ ከየትኛውም አቅጣጫ የተኩስ ድምፅ እየተሰማ አይደለም። ጥዋት ላይ ለጥቂት ሰከንድ ፒያሳ እና ቀበሌ 18 አካባቢ ተኩስ ተሰምቶ ነበር።

ከትላንት ማታ አንስቶ ዛሬም ጥዋት በከተማው አብዛኛው ክፍል ላይ የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሰራዊት ያለ ሲሆን ሰራዊቱ በሆስፒታሉ አካባቢም መኖሩን ይኸው ዶክተር ገልጿል።

የህክምና ዶክተሩ ከምንም በላይ በሆስፒታል ያለው የኦክስጅን ፣ የደም እጥረት እንዲሁም የአምቡላንስ ትራንስፖርት ጉዳይ እጅግ አሳሳቢ መሆኑን በመግለፅ መፍትሄ እንዲፈለግ ጥሪ አቅርቧል።

ጥንታዊቷ እና ታሪካዊቷ #ጎንደር ባለፉት ቀናት ከፍተኛ የሆነ ግጭት ካስተናገዱ የአማራ ክልል ከተሞች መካከል አንዷ ናት።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመጪው ረቡዕ፣ ሐሙስ እና ዓርብ ወደ ፦ - ደሴ (ኮምቦልቻ) - ጎንደር - ላሊበላ - ባህርዳር የሚደረጉ በረራዎች #የተሰረዙ መሆናቸውን አሳውቋል። ወደሥፍራው ለመጓዝ ትኬት የቆረጡ ደንበኞቹ ትኬታቸው ለአንድ (1) ዓመት ያህል የሚያገለግል መሆኑን አውቀው ወደፊት በፈለጉበት ቀን ያለምንም ተጨማሪ ክፍያ መቀየር የሚችሉ መሆኑን ገልጿል። ነገር ግን ገንዘብ ተመላሽ…
#NewsAlert

ወደ ጎንደር እና ባህር ዳር በረራ ነገ ይጀምራል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ባህር ዳር እና ጎንደር ከተሞች በጊዜያዊነት ተቋርጦ የነበረው መደበኛ በረራ ነገ ነሐሴ 4 ቀን 2015 ዓ.ም. የሚጀምር መሆኑን ዛሬ አሳውቋል።

መንገደኞች በአቅራቢያቸው በሚገኙት የአየር መንገዱ ሽያጭ ቢሮዎች ወይም ወደጥሪ ማዕከሉ የስልክ ቁጥሮች 6787 / +251116179900 በመደወል መስተናገድ እንደሚችሉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ገልጿል።

@tikvahethiopia
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
#መነሻዬ

ልጆችዎ ህልማቸውን እውን የሚያደርጉባቸው ትምህርታዊ መጫወቻዎች በየዕድሜያቸው እና እንደየፍላጎታቸው ከመነሻዬ አማርጠው ይግዙ!

አድራሻ፦
📍ጉርድ ሾላ ሆሊ ሲቲ ሴንተር 3ኛ ፎቅ
ይምጡ በመነሻዬ የልጅዎን መነሻ ያቅልሉ!

ይደውሉ 0989939393 ወይም 0930323334

Telegram > https://t.iss.one/meneshayeofficial
Tiktok > https://tiktok.com/@meneshayeofficial
Facebook > https://facebook.com/@meneshayeofficial
#HamaqPLC
Car Hand Break And Gear Shift Lock -ለመኪናዎ የሚያገለግል አስተማማኝ መቆለፊያ  
-በአሁኑ ጊዜ እየተበራከተ ለመጣው የመኪና ስርቆት ሁነኛ መፍትሄ
-በኮንዶሚኒየም፣አፓርታማና በጋራ መኪና ማሳደሪያ ለሚጠቀሙ ተመራጭ
-የእጅ ፍሬንን ከማርሽ ጋር የሚቆልፍ    

ዋጋ =3000 ብር  ☎️ 0912917632 ከየማይቀረፅ ቁልፎች ጋር ያሉበት ቦታ በነፃ እናደርሳለን::👉Free delivery

አድራሻ:- አቢሲኒያ ፕላዛ
TIKVAH-ETHIOPIA
#State_of_Emergency ዛሬ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በ " አማራ ክልል " የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲደነገግ ውሳኔ ማሳለፉ ይታወቃል። አመሻሹን ደግሞ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዴት ተግባራዊ እንደሚደረግ እንዲሁም የሚወሰዱ እርምጃዎች እና ተከለከሉ ተግባራት ዝርዝር ይፋ ተደርጓል። በዚህም ፤ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን የሚያስፈፅም በብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዳይሬከተር ጄነራል የሚመራ…
#State_of_Emergency

የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ ባወጣው መግለጫ ፤ በ " መጀመሪያ ምዕራፍ " ዕቅድ በትልልቆቹ የአማራ ክልል ከተሞች ፦
- ባሕር ዳር፣
- ደብረ ማርቆስ፣
- ደብረ ብርሃን፣
- ላሊበላ፣
- ጎንደር
- ሸዋ ሮቢት ላይ አስፈላጊውን እርምጃ በመውሰድ " የሕግ የበላይነት እንዲከበር አስደርጌያለሁ " ብሏል።

በእነዚህ ከተሞች " በዘረፋ እና በጥፋት የተሰማራ ቡድንን በመምታት በከተሞቹ ላይ የሕግ የበላይነትን ማስከበር ተችሏል " ሲል ገልጿል።

በአሁኑ ሰዓት ከተሞቹ ከስጋት ነጻ መሆናቸውን የገለፀው ዕዙ  ፤ የመከላከያ ሠራዊቱ እና የክልሉ ህግ አስከባሪ አካላት የማጥራት ስራ እየሰሩ ነው ብሏል።

የመጨረሻውን የማጽዳት እና የመልቀም ተግባር በማከናወን ከተሞቹ በአጭር ጊዜ ወደ ተሟላ ሰላማዊ እንቅስቃሴ እንዲመለሱ ይደረጋል ሲልም አሳውቋል።

የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዙ ፦

- ከነገ ሐሙስ ነሐሴ 4 ጀምሮ ከላይ በተጠቀሱት ከተሞች መደበኛ የአውሮፕላን በረራ እንደሚጀምር፤

- ከባጃጅና ከሞተር ሳይክል በስተቀር ሁሉም ዓይነት የከተማ የትራንስፖርት አገልግሎቶች ወደ  አገልግሎት እንደሚገቡ፤

- የመንግሥት ፣ የማኅበረሰብ አገልግሎት ፣ የንግድ፣ የጤና፣ የፋይናንስ፣ ወዘተ. ተቋማት አገልግሎት እንዲሰጡ እንደሚደረግ አሳውቋል።

በሌላ በኩል ፤ እስካሁን 14 ተጠርጣሪዎችን በአዲስ አበባ ከተማ በቁጥጥር ሥር ማዋሉንና ወደፊትም እንደሁኔታው በቁጥጥር ሥር የሚያውላቸውን ግለሰቦች አስመልክቶ አስፈላጊውን መረጃ ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ ገልጿል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#State_of_Emergency የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ ባወጣው መግለጫ ፤ በ " መጀመሪያ ምዕራፍ " ዕቅድ በትልልቆቹ የአማራ ክልል ከተሞች ፦ - ባሕር ዳር፣ - ደብረ ማርቆስ፣ - ደብረ ብርሃን፣ - ላሊበላ፣ - ጎንደር - ሸዋ ሮቢት ላይ አስፈላጊውን እርምጃ በመውሰድ " የሕግ የበላይነት እንዲከበር አስደርጌያለሁ " ብሏል። በእነዚህ ከተሞች " በዘረፋ እና በጥፋት የተሰማራ ቡድንን…
#State_of_Emergency

ሰዓት እላፊ ገደብ ተጣለ።

በባሕር ዳር ፣ ጎንደር እና ደብረ ብርሃን ጨምሮ በሌሎች ከተሞች የሰዓት እላፊ ገደብ ተጣለ።

የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ ትዕዛዝና ክልከላ አውጥቷል።

በዚህም ፤ ባሕር ዳር ፣ ጎንደር ፣ ደብረ ብርሃን ፣ ደብረ ማርቆስ፣ ሸዋ ሮቢትና ላሊበላ እስከ ነሐሴ 17/2015 የሚቆይ የሠዓት እላፊ ገደብ ጥሏል።

- የድንገተኛ ህክምና አገልግሎት ከሚሰጡ ተሽከርካሪዎች፣
- የድንገተኛ ህክምና አገልግሎት ሰጪ ባለሞያዎች
- የፀጥታ አስከባሪ ተቋማት ባልደረቦች ውጪ ለማንኛውም ሰው እና ተሽከርካሪ ከምሽቱ #አንድ_ሰዐት_በኋላ መንቀሳቀስ በጥብቅ ተከልክሏል።

የባጃጅ እና የሞተር ሳይክል እንቅስቃሴ ከነሐሴ 4 እስከ ነሐሴ 17 2015 ድረስ ፈጽሞ መከልከሉ ተገልጿል።

ከባጃጆችና ከሞተር ሳይክሎች በስተቀር ሌሎች የከተማ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች ከነሐሴ 4 ጀምሮ ወደ ሥራ የመመለስ እና አገልግሎት የመስጠት ግዴታ ተጥሎባቸዋል።

ከዚህ ባለፈ ፤ በባሕርዳር፣ ጎንደር፣ ደብረ ብርሃን፣ ደብረ ማርቆስ፣ ሸዋ ሮቢትና ላሊበላ የሕዝብ የአገልግሎት ሰጪ፣ የመንግሥት፣ የማኅበረሰብና የንግድ ተቋማት ከነሐሴ 4/2015 ጀምሮ ክፍት እንዲሆኑ ታዟል።

የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዙ ከፈቃዴ ውጪ በአማራ ብሔራዊ ክልል ከተሞች የአደባባይ ስብሰባ፣ ሰልፍና መሰል እንቅስቃሴዎችን ማድረግ ፈጽሞ የተከለከለ ነው ብሏል።

በማንኛውም መልኩ የህዝብ እንቅስቃሴን የሚያስተጓጉል እና የትራንስፖርት አገልግሎትን የሚያሰናክል ድርጊትም በጥብቅ የተከለከለ ነው ሲል አስጠንቅቋል።

በተጨማሪ ፤ በክልሉ ለጸጥታ ሥራ ከሚንቀሳቀሱ የህግ አስከባሪ አካላት እና ከነዚህ አካላት ፈቃድ ውጭ የጦር መሣሪያ ይዞ መዘዋወር ፈጽሞ ተከልክሏል።

በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሽፋን ከአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ ትእዛዝ ውጭ ወቅታዊ ሁኔታን ሰበብ በማድረግ ግለሰቦችን ከመደበኛው ህግ አግባብ ውጪ ማሰር እና ማቆየት፣ የንግድ ቤቶችን ማሸግ እና መሰል እርምጃዎችን መውሰድ በጥብቅ የተከለከለ መሆኑን አሳውቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ባህርዳር #ጎንደር

ባህር ዳር ከተማ ከትላንት ለሊት ጀምሮ ዝምታ ሰፍኖባት እንደምትገኝና ዛሬ የሟቾች ስርዓተ ቀብር ሲፈፀም እንደነበር ነዋሪዎቿ ተናግሩ።

ባለፉት ቀናት በከፍተኛ የተኩስ ልውውጥ ስትናጥ የነበረችው ባህር ዳር ከተማ ከለሊት ጀምሮ ፀጥ ብላ መዋሏን ነዋሪዎች መናገራቸውን ዶቼ ቨለ ሬድዮ ዘግቧል።

በሌላ በኩል ፤ ዛሬ በባህር ዳር በግጭቱ የሞቱ ሰዎች ስርዓተ ቀብር ሲፈፀም መዋሉን ነዋሪዎቹ አመልክተዋል።

ትላንት በቀበሌ 13 ፣ 14 እና 16 በነበረ ውጊያ በርካታ ሰዎች #መሞታቸው እና #መጎዳታቸው ተነግሯል። እነዚሁ ሟቾች ስርዓተ ቀብራቸው ዛሬ በተለያዩ ስፍራዎች ሲፈፀም ውሏል።

ነዋሪዎቹ በጦርነቱ ሳቢያ ህይወታቸው ያለፈው አብዛኞቹ ከጦርነቱ ጋር ምንም ግንኙነት የሌላቸው ሰዎች መሆናቸውን ገልጽዋል።

የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት (AFP) ያነጋገራቸው ሁለት ዶክተሮች በውጊያው ሰላማዊ ሰዎች ስለመገደላቸው ተናግረዋል።

ከዚህ በተጨማሪ ፤ የባህር ዳር ነዋሪዎች ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ሬድዮ በሰጡት ቃል ከከተማው ማረሚያ ቤት 2 ሺህ የሚጠጉ ታራሚዎች ሲወጡ መመልከታቸውን ጠቁመዋል።

በጎንደር ዳግሞ ዛሬ ከሰሞኑን የተሻለ መረጋጋት እንዳለ ነዋሪዎች ገልጸዋል። የመንግሥት ጦር በከተማው ውስጥ እየተንቀሳቀሰ ሲሆን የተደረደሩ ድንጋዮችን ሲያነሱ መዋላቸውን ነዋሪዎች ጠቁመዋል።

@tikvahethiopia