TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.2K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ፎቶ፦ ዛሬ እየተከበረ በሚገኘው 127ኛው የዓድዋ ድል በዓል ላይ #የኢትዮጵያ 🇪🇹 የሀገር መከላከያ ሰራዊት ጥቅም ላይ ያዋላቸውን ቀላል እና ከባድ የጦር መሳሪያዎች በመስቀል አደባባይ በነበረው ትርኢት ላይ አሳይቷል።

Photo Credit : EBC

@tikvahethiopia
Aspiring entrepreneurs in #Ethiopia , attend this info session to learn how to actualize your entrepreneurial dreams through the Jasiri Talent Investor program. The Information Session will be happening next Tuesday, March 7th at 6PM EAT! Join to learn what it takes to be selected as a Jasiri fellow. Register here to attend: https://us02web.zoom.us/meeting/register/tZEtdeCsrjsoGdWRKNvlBNo_-lgft83DQwbp
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
መንግስት ምን አለ ?

የኢፌዴሪ መንግስት በኮሚኒኬሽን አገልግሎት በኩል ማምሻውን ባወጣው መግለጫ ፤ 127ኛው የዓድዋ በዓል በብሔራዊ ደረጃ በአዲስ አበባ ፣ በመላው ሀገሪቱ እንደአመቺነቱና እንደ ሁኔታው #በድምቀት ፣በታቀደለት ልክ ተከብሯል ብሏል።

አገልግሎቱ ዛሬ በምንሊክ አደባባይ ስለነበረው ሁኔታም በመግለጫው አብራርቷል።

በምኒልክ አደባባይ የሚደረገውን በዓል ለመረበሽ የፈለጉ አካላት ሁከት ለመቀስቀስ ሞክረው ነበር ያለው መንግስት " እነዚህ አካላት የአደባባዩን በዓል መረበሽ ሲያቅታቸው በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የሚደረገውን ሃይማኖታዊ በዓል ለመረበሽ ሞክረዋል " ብሏል።

" የጸጥታ አካላት ሑከት ፈጣሪዎችን ለማስታገሥ በሚያደርጉት ጥረት በቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ የነበረው ሃይማኖታዊ በዓል እንዳይስተጓጎልና ለሃይማኖታዊ በዓል የመጡ ምእመናን ለጉዳት እንዳይደረጉ ጥረት አድርጓል " ሲልም አሳውቋል።

በዚህም ጥቂት ምዕመናን ላይ ጉዳት ደርሷል ያለው መንግስት " ሆኖም የፀጥታ አካላት ባደረጉት ጥረት የከፋ ጉዳት ሳይደርስ የተሸረበዉ ሴራ ሊከሽፍ ችሏል " ሲል ገልጿል።

" ይሄንን መሰል ተግባር መፈጸም እንደሌለበት መንግስት ያምናል " ያለው የኮሚኒኬሽን አገልግሎት " " ሁኔታውን አጣርቶ በችግር ፈጣሪዎች ላይ ተገቢውን ርምጃ ይወስዳል " ብሏል።

ዛሬ በምንሊክ አደባባይ የድል በዓል ለማክበር የሄዱ ዜጎች እንዲመለሱ መደረጉን፣ ወጣቶች ላይ ድብደባ መፈፀሙን ፣ ዜጎችን ለመበተን የፀጥታ ኃይሎች አስለቃሽ ጭስ መጠቀማቸውን የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት መግለፃቸው ይታወሳል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
መንግስት ምን አለ ? የኢፌዴሪ መንግስት በኮሚኒኬሽን አገልግሎት በኩል ማምሻውን ባወጣው መግለጫ ፤ 127ኛው የዓድዋ በዓል በብሔራዊ ደረጃ በአዲስ አበባ ፣ በመላው ሀገሪቱ እንደአመቺነቱና እንደ ሁኔታው #በድምቀት ፣በታቀደለት ልክ ተከብሯል ብሏል። አገልግሎቱ ዛሬ በምንሊክ አደባባይ ስለነበረው ሁኔታም በመግለጫው አብራርቷል። በምኒልክ አደባባይ የሚደረገውን በዓል ለመረበሽ የፈለጉ አካላት ሁከት ለመቀስቀስ…
#ዓድዋ127

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ፦

" በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ዓመታዊውን የሊቀ ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ እና 127ኛውን የዓድዋ ድል መታሰቢያ ክብረ በዓል ለማክበር በርካታ ሕዝበ ክርስቲያን ከየአቅጣጫው ተሰብስቦ ነበር።

ታቦታተ ሕጉ ከመንበረ ክብራቸው  ወጥተው የዑደት ሥነ ሥርዓት ከተፈጸመ በኋላ ክብረ በዓሉ እየተከናወነ ባለበት ወቅት ከመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች ወደ ቅጽረ ቤተ ክርስቲያኑ በተወረወረ አስለቃሽ ጭስ የበዓሉ ሥነ-ሥርዓት ሳይጠነቀቅ ታቦታተ ሕጉ ወደ መንበረ ክብራቸው ተመልሰዋል።

ወደቅጽረ ቤተክርስቲያኑ በሚያስገቡ ሁለቱም መግቢያ በሮች በተወረወረው አስለቃሽ ጭስ በርካታ ምዕመናን በመጎዳታቸው ራሳቸውን ስተው ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል። "

ከኢፌዴሪ መንግስት መግለጫ ፦

" ... በምኒልክ አደባባይ የሚደረገውን በዓል ለመረበሽ የፈለጉ አካላት ሁከት ለመቀስቀስ ሞክረው ነበር።

እነዚህ አካላት የአደባባዩን በዓል መረበሽ ሲያቅታቸው በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የሚደረገውን ሃይማኖታዊ በዓል ለመረበሽ ሞክረዋል፡፡

የጸጥታ አካላት ሑከት ፈጣሪዎችን ለማስታገሥ በሚያደርጉት ጥረት በቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ የነበረው ሃይማኖታዊ በዓል እንዲስተጓጉልና ለሃይማኖታዊ በዓል የመጡ ምእመናን ለጉዳት እንዲዳረጉ ጥረት አደርጓል።

በዚህም ጥቂት ምዕመናን ላይ ጉዳት ደርሷል።

ሆኖም የፀጥታ አካላት ባደረጉት ጥረት የከፋ ጉዳት ሳይደርስ የተሸረበዉ ሴራ ሊከሽፍ ችሏል።

መንግሥት ይሄንን መሰል ተግባር መፈጸም እንደሌለበት ያምናል። ሁኔታውን አጣርቶ በችግር ፈጣሪዎች ላይ ተገቢውን ርምጃ ይወስዳል። "

ቪድዮ ፦ Addis

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

ቲክቫህ ኢትዮጲያ ከ Mercy Corps Ethiopia ጋር በመተባበር ከአፋር፣ ኦሮሚያና ሶማሌ ክልሎች 14 ወረዳዎች  ለተዉጣጡ 56 ወጣቶች በዲጂታል ሰላም ግንባታና መሰረታዊ የሚዲያ ክህሎት ላይ በየክልሉ የ4 ቀን የአሰልጣኞች ስልጠና ሰጥተዋል፡፡

ስልጠናው ቴክኖሎጂ በተለይ ማህበራዊ ሚዲያ እንዴት የግጭት መንስዔ ሊሆን እንደሚችልና ግጭቶችን እንደሚያባብስ፣ እንዴት የሰላም ግንባታ ጥረቶችን ሊደግፍ አንደሚችል እንዲሁም በዲጂታል ሰላም ግንባታ ላይ የወጣቶች ሚና ምን እንደሆነ፣ የወጣቶችን እምቅ አቅም እንዴት ለዲጂታል ሰላም ግንባታ መጠቀም እንደሚቻል ትኩረት ያደረገ ነበር፡፡

በስልጠናው ላይ ወጣቶቹ በየአከባቢያቸው ለግጭት መንስዔ የሆኑ ጉዳዮችን በመለየት፣  በመተንተንና ማህበራዊ ሚዲያው ግጭቶችን በማባባስ ረገድ ያለውን አስተዋጽኦ በመለየት የመፍትሄ ሃሳቦችን አስቀምጠዋል፡፡

ስልጠናውን የተከታተሉ 56 ወጣቶች ወደ የክልሎቻቸው በመውረድ በ14ቱም ወረዳ ለሚገኙ 280 ሌሎች አቻ ወጣቶቻቸውና ማኅበረሰቦቻቸው በቀጥታ መድረስ ተችሏል፡፡

ስልጠናውን ተከትሎ የአፋር ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ በክልሉ ውስጥ ለሚገኙ ሌሎች ወጣቶችና ማህበረሰቦች ስልጠናውን ለሰጡና ላመቻቹ ወጣቶች የታብሌትና ፓወር ባንክ የማበረታቻ ሽልማት ሰጥቷል፡፡

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#DigitalLottery አድማስ ዲጂታል ሎተሪ ዛሬ ጥር 25 ቀን 2015 በብሄራዊ ሎተሪ የዕጣ ማውጫ አዳራሽ በህዝብ ፊት ወጥቷል። 1.5 ሚሊዮን ብር ባለዕድለኛ የሚያደርገው የዕጣ ቁጥር 007235088931 ሆኖ ወጥቷል። 👉 1.5 ሚሊዮን ብር - 007235088931 👉 800 ሺህ ብር - 007311229183 👉 350 ሺህ ብር - 007308618207 👉 200 ሺህ ብር - 007209120515 👉
#DigitalLottery

አድማስ ዲጂታል ሎተሪ ትላንት የካቲት 23 ቀን 2015 በብሄራዊ ሎተሪ የዕጣ ማውጫ አዳራሽ በህዝብ ፊት ወጥቷል።

1.5 ሚሊዮን ብር ባለዕድለኛ የሚያደርገው የዕጣ ቁጥር 008143769160 ሆኖ ወጥቷል።

👉 1.5 ሚሊዮን ብር - 008143769160
👉 800 ሺህ ብር - 008275497401
👉 350 ሺህ ብር - 008164738097
👉 200 ሺህ ብር - 008144460138
👉 160 ሺህ ብር - 008176284647

(ተጨማሪ የዕጣ ቁጥሮች ከላይ ተያይዘዋል)

ምንጭ፦ የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር

@tikvahethiopia
#ትግራይ

በሰላም ስምምነቱ መሰረት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ማቋቋሚያ ኮንፈረንስ በዚህ ሳምንት ለሁለት ቀናት ተካሂዷል።

በኮንፈረንሱ የተለያዩ ውሳኔዎች መተላለፋቸው ተገልጿል።

የኮንፈረንሱ ውክልና አስተዳደር፣ የሚቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር ተልዕኮ፣ የአስተዳደሩ አደረጃጀትና የስልጣን ክፍፍል ላይ ውይይት እንደተደረገበት እና ስምምነት ላይ እንደተደረሰባቸው ተገልጿል።

ወደ ጦርነት ያስገቡ የትግራይ ህዝብ መሰረታዊ ጥያቄዎች በሰላም ምላሽ እንዲያገኙ ሁሉም የኮንፈረንሱ ተሳታፊዎች ከስምምነት ላይ መድረሳቸው ተመላክቷል።

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር በሁለቱም ተደራዳሪዎች ስምምነት ፀድቆ ወደ ተገባር የሚገባ ሲሆን አስተዳደሩ ከ6 ወር እስከ 1 ዓመት ይቆያል ተብሏል።

ኮንፈረንሱ 11 ነጥብ ያለው የአቋም መግለጫ በማውጣት የተጠናቀቀ ሲሆን የትግራይ ህዝብ ፍላጎት የሚሟላበት፣ የጦርነት ሰለባዎች ትኩረት የሚያገኙበት፣ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው የሚመለሱበት፣ በትግራይ ያጋጠሙ ሁለንተናዊ ችግሮች የሚፈታ እንዲሆን ሁሉም ለሚቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ ቀርቧል።

መላው የኢትዮጵያ ህዝብ እና የኢትዮጵያ መንግስት እንዲሁም ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለሚቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር ድጋፍ እንዲያደርጉ መጠየቁን የክልሉ ቴሌቪዥን ዘግቧል።

ጀነራል ታደሰ ወረደ ከቀናት በፊት ኮንፈረንሱ ሲካሄድ እንደተናገሩት ከሆነ የሚቋቋመው ጊዚያዊ አስተዳደር፦
👉 30 % ከህወሓት
👉 25 % ከትግራይ ታጣቂ ሐይሎች
👉 30 % የሲቪል ተቋማት
👉 15 % ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች የያዘ ነው።

ለ2 ቀናት ከተደረገው ኮንፈረንስ ጋር በተያያዘ ከዓሲምባ በስተቀር በክልሉ ያሉ የተቃዋሚ ኃይሎች እንዳልተካፈሉ በስፋት ተነግሯል።

ያንብቡ: https://telegra.ph/TG-03-03

@tikvahethiopia