#MohammedrafieAbaraya
በጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት የውጭ ፖሊሲ እና ዴፕሎማሲ ተንታኝ የነበሩት አቶ ሙሐመድራፊዕ አባራያ የጠ/ሚንስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ አማካሪ ሆነው መሾማቸው በዛሬው ዕለት ተሰምቷል።
@tikvahethiopia
በጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት የውጭ ፖሊሲ እና ዴፕሎማሲ ተንታኝ የነበሩት አቶ ሙሐመድራፊዕ አባራያ የጠ/ሚንስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ አማካሪ ሆነው መሾማቸው በዛሬው ዕለት ተሰምቷል።
@tikvahethiopia
#AU2022Summit
እስካሁን የየት ሀገር ሚኒስትሮች ገቡ ?
ነገ ለሚጀምረው የአፍሪካ ሀገራት ሚኒስትሮች የሚሳተፉበት የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈፃሚ ም/ቤት ስብሰባ የተለያዩ ሀገራት ሚኒስትሮች ወደ ኢትዮጵያ እየገቡ ናቸው።
እስካሁን የገቡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ፦
🇿🇼 ፍሬድሪክ ሻቫ (ዝምባብዌ)
🇸🇹 ኤዲቴ ራሞስ ቴንዡዋ (የሳዖቶሜና ፒሪንሲፔ)
🇨🇲 ሌዡን ቤላ ቤላ (ካሜሩን)
🇹🇩 ማህማት ዜኑ ሸሪፍ (ቻድ)
🇨🇮 ካንዲያ ካሚስኮ ካማራ (ኮትዲቯር)
🇸🇴 አብዲሳድ ሙሴ አሊ (ሶማሊያ)
🇨🇬 ዢያን ክላውዴ ጋኮሶ (የሪፐብሊክ ኮንጎ)
🇳🇪 ሀሱሚ ማሹዱ (ኒጀር ምክትል ጠ/ሚ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር)
🇿🇦 ዶ/ር ናለዲ ፓንዶር (ደቡብ አፍሪካ)
🇸🇳 አሲታ ቶል ሳል (ሴኔጋል)
🇲🇷 እስማኤል ኡልድ ሼክ አህመድ (ሞሪታኒያ)
🇩🇯 ሙሀሙድ አሊ የሱፍ (ጂቡቲ)
🇱🇾 ናጅላ አልማንጉሽ (ሊቢያ)
🇦🇴 ሜንዶንካ ኤስሜራልዳ ዢያን ክላውዴ ጋኮሶ (አንጎላ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር)
@tikvahethiopia
እስካሁን የየት ሀገር ሚኒስትሮች ገቡ ?
ነገ ለሚጀምረው የአፍሪካ ሀገራት ሚኒስትሮች የሚሳተፉበት የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈፃሚ ም/ቤት ስብሰባ የተለያዩ ሀገራት ሚኒስትሮች ወደ ኢትዮጵያ እየገቡ ናቸው።
እስካሁን የገቡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ፦
🇿🇼 ፍሬድሪክ ሻቫ (ዝምባብዌ)
🇸🇹 ኤዲቴ ራሞስ ቴንዡዋ (የሳዖቶሜና ፒሪንሲፔ)
🇨🇲 ሌዡን ቤላ ቤላ (ካሜሩን)
🇹🇩 ማህማት ዜኑ ሸሪፍ (ቻድ)
🇨🇮 ካንዲያ ካሚስኮ ካማራ (ኮትዲቯር)
🇸🇴 አብዲሳድ ሙሴ አሊ (ሶማሊያ)
🇨🇬 ዢያን ክላውዴ ጋኮሶ (የሪፐብሊክ ኮንጎ)
🇳🇪 ሀሱሚ ማሹዱ (ኒጀር ምክትል ጠ/ሚ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር)
🇿🇦 ዶ/ር ናለዲ ፓንዶር (ደቡብ አፍሪካ)
🇸🇳 አሲታ ቶል ሳል (ሴኔጋል)
🇲🇷 እስማኤል ኡልድ ሼክ አህመድ (ሞሪታኒያ)
🇩🇯 ሙሀሙድ አሊ የሱፍ (ጂቡቲ)
🇱🇾 ናጅላ አልማንጉሽ (ሊቢያ)
🇦🇴 ሜንዶንካ ኤስሜራልዳ ዢያን ክላውዴ ጋኮሶ (አንጎላ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር)
@tikvahethiopia
#NewsAlert
የከፍተኛ ትምህርት ጥራትን ለማሻሻል ለሁሉም የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች የመውጫ ፈተና እንደሚሰጥ ተገለፀ።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፕሬዚዳንቶች ጋር ተወያይተዋል።
ውይይቱ በተቋማት ተጠያቂነትና የመረጃ ፍሰትን ለመዘርጋት እንዲሁም ውጤታማ እና ቀልጣፋ ሥራ እንዲያከናወኑ ያስችላል በተባለ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ረቂቅ መዋቅር ላይ ያተኮረ ነው።
በመንግስትም ሆነ በግል የከፍተኛ ትምህርት ጥራትን ወደሚፈለገው ደረጃ ከፍ ለማድረግ በቀጣይ የትምህርት ዘመን የመውጫ ፈተና ለሁሉም የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች ሊሰጥ መሆኑን ሚኒስትሩ ጠቁመዋል፡፡
#MoE
@tikvahethiopia
የከፍተኛ ትምህርት ጥራትን ለማሻሻል ለሁሉም የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች የመውጫ ፈተና እንደሚሰጥ ተገለፀ።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፕሬዚዳንቶች ጋር ተወያይተዋል።
ውይይቱ በተቋማት ተጠያቂነትና የመረጃ ፍሰትን ለመዘርጋት እንዲሁም ውጤታማ እና ቀልጣፋ ሥራ እንዲያከናወኑ ያስችላል በተባለ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ረቂቅ መዋቅር ላይ ያተኮረ ነው።
በመንግስትም ሆነ በግል የከፍተኛ ትምህርት ጥራትን ወደሚፈለገው ደረጃ ከፍ ለማድረግ በቀጣይ የትምህርት ዘመን የመውጫ ፈተና ለሁሉም የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች ሊሰጥ መሆኑን ሚኒስትሩ ጠቁመዋል፡፡
#MoE
@tikvahethiopia
#GendaRira
9 የፌዴራል ፖሊስ አባላት በትራፊክ አደጋ ህይወታቸው አለፈ።
በባሌ ዞን ጎባ ወረዳ ልዩ ስሙ ገንዳ ሪራ በተባለ ስፍራ በደረሰው የተሽከርካሪ አደጋ የዘጠኝ ሰዎች ሕይወት ማለፉን የጎባ ወረዳ ፖሊስ አስታወቀ።
አደጋው የደረሰው በትናንትናው ዕለት ከቀኑ 9:00 ሰዓት ገደማ ነው።
አደጋው ከደሎ መና ወደ ሮቤ ዶዘር እየጎተተ ሲጓዝ ከነበረ የሰሌዳ ቁጥሩ ክሬን ተሽከርካሪ በተቃራኒ አቅጣጫ ከሮቤ ወደ ደሎ መና በመጓዝ ላይ ከነበረው የፖሊስ ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ ነው።
በደረሰው የተሽከርካሪ አደጋ 9 የፌዴራል ፖሊስ አባላት ህይወት ሲያልፍ ፥ በአራቱ ላይ ደግሞ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት ደርሷል።
በአደጋው ክሬኑን ሲያሽከረክር የነበረው ረዳት በቁጥጥር ስር ውሎ ጉዳዩ እየተጣራ መሆኑን ፖሊስ አሳውቋል።
የአደጋው መንስኤ እየተጣራ ነው ተብሏል።
ከባድና ቀላል አደጋ የደረሰባቸው የፖሊስ አባላት ጎባ ሪፌራል ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው መሆኑን ኢዜአ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
9 የፌዴራል ፖሊስ አባላት በትራፊክ አደጋ ህይወታቸው አለፈ።
በባሌ ዞን ጎባ ወረዳ ልዩ ስሙ ገንዳ ሪራ በተባለ ስፍራ በደረሰው የተሽከርካሪ አደጋ የዘጠኝ ሰዎች ሕይወት ማለፉን የጎባ ወረዳ ፖሊስ አስታወቀ።
አደጋው የደረሰው በትናንትናው ዕለት ከቀኑ 9:00 ሰዓት ገደማ ነው።
አደጋው ከደሎ መና ወደ ሮቤ ዶዘር እየጎተተ ሲጓዝ ከነበረ የሰሌዳ ቁጥሩ ክሬን ተሽከርካሪ በተቃራኒ አቅጣጫ ከሮቤ ወደ ደሎ መና በመጓዝ ላይ ከነበረው የፖሊስ ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ ነው።
በደረሰው የተሽከርካሪ አደጋ 9 የፌዴራል ፖሊስ አባላት ህይወት ሲያልፍ ፥ በአራቱ ላይ ደግሞ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት ደርሷል።
በአደጋው ክሬኑን ሲያሽከረክር የነበረው ረዳት በቁጥጥር ስር ውሎ ጉዳዩ እየተጣራ መሆኑን ፖሊስ አሳውቋል።
የአደጋው መንስኤ እየተጣራ ነው ተብሏል።
ከባድና ቀላል አደጋ የደረሰባቸው የፖሊስ አባላት ጎባ ሪፌራል ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው መሆኑን ኢዜአ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
ተፈርዶበታል !
በገቢዎች ሚንስቴር ውስጥ የኦዲት ባለሙያ ሆኖ ሲሰራ 1.5 ሚሊየን ብር ጉቦ ለመቀበል ተስማምቶ ግማሽ ሚሊየን ብር በጥሬ ገንዘብ ሲቀበል እጅ ከፍንጅ የተያዘው ተከሳሽ በፅኑ እስራትና በገንዘብ ተቀጣ።
መላኩ ሸዋረጋ የተባለው ተከሳሽ በገቢዎች ሚንስቴር አዳማ ቅ/ፅ/ቤት የኦዲት ባለሙያ ሆኖ ሲሰራ አንድ ሚሊየን ብር በባንክ አካውንት እንዲገባለትና 5 መቶ ሺህ ብር ደግሞ በጥሬው ለመቀበል ተስማምቶ በቦሌ ክፍለ ከተማ ካፒታል ሆቴል ገንዘብ ሲቀበል የተገኘው ተከሳሽ በፈፀመው ጉቦ መቀበል የሙስና ወንጀል በፅኑ እስራትና በገንዘብ እንዲቀጣ ተወስኖበታል።
ተከሳሹ የተጣለበትን የስራ ኃላፊነቱን ተጠቅሞ ኽርበርግ ሮዝ ኃ/የተ/የግ/ማህበር የተባለው ድርጅት የ2 ዓመት የንግድ ስራ ትርፍ ግብር ብር 66‚616‚818 ብር ከ93 ሳንቲም አንዲከፍል ሲወሰንበት የድርጅቱ የአስተዳደር ሰራተኛ የሆነችው 1ኛ የዐቃቤ ህግ ምስክር በውሳኔው ላይ ለቅ/ፅ/ቤቱ ቅሬታ ታቀርባለች፡፡
ተከሳሹ በበኩሉ የቀረበውን ቅሬታ ውሳኔውን ዝቅተኛ በሆነ መልኩ መወሰን እንደሚቻልና ለዚህም ብር 1‚000‚000 ብር በባንክ ለመቀበልና ቀሪውን 500‚000 ብር ደግሞ እጅ በእጅ ለመቀበል ከተደራደረና ከተስማማ በኋላ ጥቅምት 24/3013 ዓ.ም ከቀኑ 8:30 ሰዓት ሲሆን በቦሌ ክፍለ ከተማ ካፒታል ሆቴል ውስጥ 500‚000 ብሩን ሲቀበል እጅ ከፍንጅ ተይዟል።
በፈፀመው ጉቦ መቀበል የሙስና ወንጀል በፍትሕ ሚኒስቴር ክስ መስርቶበታል።
በከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ በአንደኛ የሙስና ወንጀል ችሎት የቀረበው ተከሳሽ መላኩ ሸዋረጋ የጥፋተኝነት ፍርድ ተላልፎበት በ4 ዓመት ከ10 ወር ፅኑ እሥራት እና በ2500 ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጣ ተወስኗል።
እንዲሁም በጉቦ የተሰጠው ገንዘብ ለተበዳይ እንዲመለስ ዐቃቤ ህግ በጠየቀው መሰረት ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ሰጥቶ ገንዘቡ ለተበዳይ እንዲመለስ ተደርጓል፡፡
ምንጭ፦ ፍትህ ሚኒስቴር
@tikvahethiopia
በገቢዎች ሚንስቴር ውስጥ የኦዲት ባለሙያ ሆኖ ሲሰራ 1.5 ሚሊየን ብር ጉቦ ለመቀበል ተስማምቶ ግማሽ ሚሊየን ብር በጥሬ ገንዘብ ሲቀበል እጅ ከፍንጅ የተያዘው ተከሳሽ በፅኑ እስራትና በገንዘብ ተቀጣ።
መላኩ ሸዋረጋ የተባለው ተከሳሽ በገቢዎች ሚንስቴር አዳማ ቅ/ፅ/ቤት የኦዲት ባለሙያ ሆኖ ሲሰራ አንድ ሚሊየን ብር በባንክ አካውንት እንዲገባለትና 5 መቶ ሺህ ብር ደግሞ በጥሬው ለመቀበል ተስማምቶ በቦሌ ክፍለ ከተማ ካፒታል ሆቴል ገንዘብ ሲቀበል የተገኘው ተከሳሽ በፈፀመው ጉቦ መቀበል የሙስና ወንጀል በፅኑ እስራትና በገንዘብ እንዲቀጣ ተወስኖበታል።
ተከሳሹ የተጣለበትን የስራ ኃላፊነቱን ተጠቅሞ ኽርበርግ ሮዝ ኃ/የተ/የግ/ማህበር የተባለው ድርጅት የ2 ዓመት የንግድ ስራ ትርፍ ግብር ብር 66‚616‚818 ብር ከ93 ሳንቲም አንዲከፍል ሲወሰንበት የድርጅቱ የአስተዳደር ሰራተኛ የሆነችው 1ኛ የዐቃቤ ህግ ምስክር በውሳኔው ላይ ለቅ/ፅ/ቤቱ ቅሬታ ታቀርባለች፡፡
ተከሳሹ በበኩሉ የቀረበውን ቅሬታ ውሳኔውን ዝቅተኛ በሆነ መልኩ መወሰን እንደሚቻልና ለዚህም ብር 1‚000‚000 ብር በባንክ ለመቀበልና ቀሪውን 500‚000 ብር ደግሞ እጅ በእጅ ለመቀበል ከተደራደረና ከተስማማ በኋላ ጥቅምት 24/3013 ዓ.ም ከቀኑ 8:30 ሰዓት ሲሆን በቦሌ ክፍለ ከተማ ካፒታል ሆቴል ውስጥ 500‚000 ብሩን ሲቀበል እጅ ከፍንጅ ተይዟል።
በፈፀመው ጉቦ መቀበል የሙስና ወንጀል በፍትሕ ሚኒስቴር ክስ መስርቶበታል።
በከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ በአንደኛ የሙስና ወንጀል ችሎት የቀረበው ተከሳሽ መላኩ ሸዋረጋ የጥፋተኝነት ፍርድ ተላልፎበት በ4 ዓመት ከ10 ወር ፅኑ እሥራት እና በ2500 ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጣ ተወስኗል።
እንዲሁም በጉቦ የተሰጠው ገንዘብ ለተበዳይ እንዲመለስ ዐቃቤ ህግ በጠየቀው መሰረት ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ሰጥቶ ገንዘቡ ለተበዳይ እንዲመለስ ተደርጓል፡፡
ምንጭ፦ ፍትህ ሚኒስቴር
@tikvahethiopia
#AU
የአፍሪካ ህብረት ሰንደቅዓላማ ...
የአፍሪካ የራሱ ሰንደቅዓላማ ያልነበረው ሲሆን በ2004 ግን መለያ ሰንደቅዓላማ አዘጋጅቶ ነበር።
በ8ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እኤአ ጥር 29 እና 30 ቀን 2007 በአዲስ አበባ ሲካሄድ ነባሩን ሰንደቅዓላማ የሚተካ አዲስ የህብረቱ ሰንደቅዓላማ እንዲዘጋጅ ውሳኔ ተላለፈ።
በወቅቱ የሊቢያ መሪና የህብረቱ ሊቀመንበር ሙአመር ጋዳፊ የሚመራው የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ኃላፊነቱን ወስዶ ለህብረቱ ሰንደቅዓላማ ንድፍ መስራት ለሚፈልጉ ጥሪ አቀረበ።
የኮሚሽኑን ጥሪ ተከትሎ ከ19 የአፍሪካ ሀገራት ከ100 በላይ ግለሰቦች፣ ከዳያስፖራ 2 ግለሰቦች ከ100 በላይ ንድፎችን አስገቡ።
የሰንደቅዓላማ ንድፎቹ በባለሙያዎች ተመዘኑ። በትውልድ ኢትዮጵያዊ በዜግነት አሜሪካዊ የሆነው የግራፊክ ጠቢብ ያዴሳ ቦጂያ ያቀረበው ንድፍ አሸናፊ ሆነ።
ያሸነፈው የያዴሳ ንድፍ ሰንደቅዓላማ እንዲሆን እኤአ ጥር 31 ቀን 2010 በአዲስ አበባ በተካሄደው 14ኛው መደበኛ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ተወሰነ።
ያዴሳ ቦጂያ ያረቀቀውና አሁን በስራ ላይ ያለው የህብረቱ ሰንደቅዓላማ አረንጓዴ መደብ፣ በ55 ወርቃማ ኮከቦች የተከበበችና በነጭ የፀሐይ ጨረሮች ላይ ያረፈች አረንጓዴ የአፍሪካ ካርታን የያዘ ነው።
የአፍሪካ ካርታ በአረንጓዴ መወከሉ አህጉራዊ ተስፋን ለማሳየት ሲሆን፣ ነጭ የፀሐይ ጨረሮች ደግሞ አፍሪካውያንን ከተቀረው ዓለም ጋር በወዳጅነት፣ በጋራ የመኖር ግልፅ ፍላጎትን የሚያሳይ ነው።
አረንጓዴው የአፍሪካ ካርታ በ55 ወርቃማ ኮከቦች የተከበበ ሲሆን ተምሳሌትነቱ 55ቱን የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራትን፥ የአፍሪካን ፀጋዎችና ብሩህ ተስፋን የሚያሳይ ነው።
Credit : #ኢዜአ
@tikvahethiopia
የአፍሪካ ህብረት ሰንደቅዓላማ ...
የአፍሪካ የራሱ ሰንደቅዓላማ ያልነበረው ሲሆን በ2004 ግን መለያ ሰንደቅዓላማ አዘጋጅቶ ነበር።
በ8ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እኤአ ጥር 29 እና 30 ቀን 2007 በአዲስ አበባ ሲካሄድ ነባሩን ሰንደቅዓላማ የሚተካ አዲስ የህብረቱ ሰንደቅዓላማ እንዲዘጋጅ ውሳኔ ተላለፈ።
በወቅቱ የሊቢያ መሪና የህብረቱ ሊቀመንበር ሙአመር ጋዳፊ የሚመራው የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ኃላፊነቱን ወስዶ ለህብረቱ ሰንደቅዓላማ ንድፍ መስራት ለሚፈልጉ ጥሪ አቀረበ።
የኮሚሽኑን ጥሪ ተከትሎ ከ19 የአፍሪካ ሀገራት ከ100 በላይ ግለሰቦች፣ ከዳያስፖራ 2 ግለሰቦች ከ100 በላይ ንድፎችን አስገቡ።
የሰንደቅዓላማ ንድፎቹ በባለሙያዎች ተመዘኑ። በትውልድ ኢትዮጵያዊ በዜግነት አሜሪካዊ የሆነው የግራፊክ ጠቢብ ያዴሳ ቦጂያ ያቀረበው ንድፍ አሸናፊ ሆነ።
ያሸነፈው የያዴሳ ንድፍ ሰንደቅዓላማ እንዲሆን እኤአ ጥር 31 ቀን 2010 በአዲስ አበባ በተካሄደው 14ኛው መደበኛ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ተወሰነ።
ያዴሳ ቦጂያ ያረቀቀውና አሁን በስራ ላይ ያለው የህብረቱ ሰንደቅዓላማ አረንጓዴ መደብ፣ በ55 ወርቃማ ኮከቦች የተከበበችና በነጭ የፀሐይ ጨረሮች ላይ ያረፈች አረንጓዴ የአፍሪካ ካርታን የያዘ ነው።
የአፍሪካ ካርታ በአረንጓዴ መወከሉ አህጉራዊ ተስፋን ለማሳየት ሲሆን፣ ነጭ የፀሐይ ጨረሮች ደግሞ አፍሪካውያንን ከተቀረው ዓለም ጋር በወዳጅነት፣ በጋራ የመኖር ግልፅ ፍላጎትን የሚያሳይ ነው።
አረንጓዴው የአፍሪካ ካርታ በ55 ወርቃማ ኮከቦች የተከበበ ሲሆን ተምሳሌትነቱ 55ቱን የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራትን፥ የአፍሪካን ፀጋዎችና ብሩህ ተስፋን የሚያሳይ ነው።
Credit : #ኢዜአ
@tikvahethiopia
#ETHIOPIA #FRANCE
ፈረንሳይ በኢትዮጵያ የመልሶ ማቋቋም ጥረቶችን እንዲሁም የታቀደውን ብሔራዊ ውይይት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኗን ገለፀች።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የፈረንሳይ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ፍሬደሪክ ክላቪየርን ተቀብለው አነጋግረዋል።
ሁለቱ ወገኖች በኢትዮጵያ ሁኔታ፣ በቀጠናዊ እና በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ መክረዋል።
አቶ ደመቀ የኢትዮጵያ መንግስት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያካሄደ ስላለው የሰላም ጥረት ለልዩ ልዑኩ ገለፃ አድርገዋል።
በዚህ ረገድ ወሳኝ አገራዊ ጉዳዮችን ለመፍታት እና በህዝብ መካከል መግባባት ለመፍጠር ያለመ የብሔራዊ ውይይት ኮሚሽን መቋቋሙን ጠቅሰዋል።
ከፍተኛ የሆኑ የፖለቲካ ሰዎች ከእስር መፈታታቸው የውይይት መድረኩን ስኬታማነት እንደሚያፋጥነው ገልፀዋል።
ምንም እንኳን መንግስት ወታደሮቹ ወደ ትግራይ እንዳይገቡ መከልከሉ የሰላሙን ጥረት እንደሚያጠናክር ቢገለፅም ህወሓት በአጎራባች ክልሎች ላይ እያደረሰ ያለው አዲስ ጥቃት የሚጠበቀውን የሰላም ጥረት እንዳይቀንስ ስጋት ፈጥሯል ብለዋል።
ልዩ መልዕክተኛው ሀገራቸው ፈረንሳይ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር ፍላጎት እንዳላት አሳውቀዋል።
ሀገራቸው ፤ የመልሶ ማቋቋም ስራዎችን እና በሀገሪቱ ዘላቂ ሰላም ለማምጣት የታቀደውን ሁሉን አቀፍ ውይይት ለመደገፍ ያላትን ቁርጠኝነት ገልፀዋል።
@tikvahethiopia
ፈረንሳይ በኢትዮጵያ የመልሶ ማቋቋም ጥረቶችን እንዲሁም የታቀደውን ብሔራዊ ውይይት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኗን ገለፀች።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የፈረንሳይ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ፍሬደሪክ ክላቪየርን ተቀብለው አነጋግረዋል።
ሁለቱ ወገኖች በኢትዮጵያ ሁኔታ፣ በቀጠናዊ እና በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ መክረዋል።
አቶ ደመቀ የኢትዮጵያ መንግስት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያካሄደ ስላለው የሰላም ጥረት ለልዩ ልዑኩ ገለፃ አድርገዋል።
በዚህ ረገድ ወሳኝ አገራዊ ጉዳዮችን ለመፍታት እና በህዝብ መካከል መግባባት ለመፍጠር ያለመ የብሔራዊ ውይይት ኮሚሽን መቋቋሙን ጠቅሰዋል።
ከፍተኛ የሆኑ የፖለቲካ ሰዎች ከእስር መፈታታቸው የውይይት መድረኩን ስኬታማነት እንደሚያፋጥነው ገልፀዋል።
ምንም እንኳን መንግስት ወታደሮቹ ወደ ትግራይ እንዳይገቡ መከልከሉ የሰላሙን ጥረት እንደሚያጠናክር ቢገለፅም ህወሓት በአጎራባች ክልሎች ላይ እያደረሰ ያለው አዲስ ጥቃት የሚጠበቀውን የሰላም ጥረት እንዳይቀንስ ስጋት ፈጥሯል ብለዋል።
ልዩ መልዕክተኛው ሀገራቸው ፈረንሳይ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር ፍላጎት እንዳላት አሳውቀዋል።
ሀገራቸው ፤ የመልሶ ማቋቋም ስራዎችን እና በሀገሪቱ ዘላቂ ሰላም ለማምጣት የታቀደውን ሁሉን አቀፍ ውይይት ለመደገፍ ያላትን ቁርጠኝነት ገልፀዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ዶ/ር ደብረፅዮን በቢቢሲ ኒውስ ሀወር ላይ ቀርበው ምን አሉ ? የህወሓት ሊቀመንበር የሆኑት ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ዛሬ ከቢቢሲ ኒውስ ሀወር ጋር በነበራቸው ቆይታ ከፌዴራል መንግስቱ ጋር በሌሎች አካላት አማካኝነት (ቀጥተኛ ባልሆነ መንገድ ) ንግግርና ውይይት መደረግ መጀመሩን ገልፀዋል። በዚህም ተስፋ ሰጪ ውጤቶች ተገኝተዋል ብለዋል። ከፌዴራል መንግስት ጋር በሌሎች አካላት አማካኝነት (በUN ፣AU…
#Update
መንግስት በቅርቡ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል በተናገሩት ንግግር ላይ ምላሽ ሰጠ።
የኢትዮጵያ መንግስት ከትግራይ ህዝብ ነፃ አውጪ ግንባር (ህወሓት) ጋር ድርድር አለመጀመሩን ዛሬ አስታውቋል።
የህወሓት ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ባለፈዉ ሳምንት ከቢቢሲ ኒውስ ሀወር ጋር ባደረጉት ቃለ መጠይቅ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በሌሎች አካላት (ቀጥተኛ ባልሆነ መንገድ) ንግግር መጀመራቸውን አስታዉቀዉ ነበር።
ዶክተር ደብረፅዮን የተጀመረው ንግግርም "ተስፋ ሰጪ ውጤቶች እያሳየ " መሆኑን ገልፀው ነበር።
የኢትዮጵያ መንግስት የኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚንስትር ዶ/ር ለገሰ ቱሉ ዛሬ ለጀርመን ድምፅ ሬድዮ ጣቢያ (ዶቼቨለ) በሰጡት ቃል የኢትዮጵያ መንግስት ሰላምን ለሚያመጣ ለየትኛዉም አማራጭ በሩ ክፍት ነዉ ብለዋል።
ነገር ግን እስካሁን ድረስ ከህወሓት ጋር የተደረገ ንግግር የለም ሲሉ ዶ/ር ለገሰ ቱሉ ለሬድዮ ጣቢያው ተናግረዋል።
@tikvahethiopia
መንግስት በቅርቡ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል በተናገሩት ንግግር ላይ ምላሽ ሰጠ።
የኢትዮጵያ መንግስት ከትግራይ ህዝብ ነፃ አውጪ ግንባር (ህወሓት) ጋር ድርድር አለመጀመሩን ዛሬ አስታውቋል።
የህወሓት ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ባለፈዉ ሳምንት ከቢቢሲ ኒውስ ሀወር ጋር ባደረጉት ቃለ መጠይቅ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በሌሎች አካላት (ቀጥተኛ ባልሆነ መንገድ) ንግግር መጀመራቸውን አስታዉቀዉ ነበር።
ዶክተር ደብረፅዮን የተጀመረው ንግግርም "ተስፋ ሰጪ ውጤቶች እያሳየ " መሆኑን ገልፀው ነበር።
የኢትዮጵያ መንግስት የኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚንስትር ዶ/ር ለገሰ ቱሉ ዛሬ ለጀርመን ድምፅ ሬድዮ ጣቢያ (ዶቼቨለ) በሰጡት ቃል የኢትዮጵያ መንግስት ሰላምን ለሚያመጣ ለየትኛዉም አማራጭ በሩ ክፍት ነዉ ብለዋል።
ነገር ግን እስካሁን ድረስ ከህወሓት ጋር የተደረገ ንግግር የለም ሲሉ ዶ/ር ለገሰ ቱሉ ለሬድዮ ጣቢያው ተናግረዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በአንደኛው ዙር በፀጥታ ችግር የ12ኛ ክፍል ፈተና መውሰድ ያልቻሉ ተማሪዎች ዛሬ ፈተናቸውን ጀምረዋል። መልካም ፈተና! @tikvahethiopia
#Update
የመጀመሪያው ቀን የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ሲሰጥ ውሏል።
ፈተናው በአማራ፣ ኦሮሚያ፣ አፋር እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ተሰጥቷል።
#Amahra
በአማራ ክልል ከ37 ሺ በላይ ለሆኑ ተማሪዎች ዛሬ ፈተና ሲሰጥ ውሏል። ፈተናው በደቡብና ሰሜን ወሎ፣ ዋግኸምራ፣ ኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞኖችና በደሴ ከተማ ፣ የሰሜን ሸዋ ዞን 3 ወረዳዎች፣ በሰሜን ጎንደር ዞን በ1 የፈተና ጣቢያ ፈተናው ነው የተሰጠው።
በሌላ በኩል ከኦሮሚያ ክልል ምስራቅና ምዕራብ ወለጋ ዞኖች ተፈናቅለው ለመጡ 220 ተማሪዎችም በልዩ ሁኔታ በቡሬ በተቋቋመ የመፈተኛ ጣቢያ ተፈትነዋል።
#OromiaRegion
በኦሮሚያ ክልል በቄለም ወለጋ ዞን በ12 ወረዳዎች በ42 የፈተና ጣቢያዎች 14,228 ተማሪዎች ለፈተና መቀመጣቸው ፤ ፈተናውን እንደሚወስዱ ከተጠበቁት 16,608 ተማሪዎች መካከል 1, 243 በተለያዩ ምክንያቶች ፈተና ላይ አለመቀመጣቸው ተገልጿል።
በምዕራብ ወለጋ የቤጊ እና ቆንደላ ወረዳዎች 1,137 ተማሪዎች በአራት የፈተና ጣቢያ ፈተናው ላይ የተቀመጡ ሲሆን በተለያዩ ምክንያቶች 931 ተማሪዎች ፈተናው ላይ እንዳልተቀመጡ ተገልጿል።
#Afar
በአፋር ክልል ፈተናውን ይወስዳሉ ተብለው ከተጠበቁት 257 ተማሪዎች 154 ተማሪዎች ፈተናውን መውሰድ ጀምረዋል።
#BenishangulGumuz
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ካማሺ ዞን አንፃራዊ ሠላም ተመዝግቦባቸዋል በተባሉ አካባቢዎች የ12ኛ ክፍል የዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና ሲሰጥ ውሏል።
• የሁለተኛው ቀን ፈተና ይቀጥላል።
መረጃ ፦ ኢብኮ፣ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ፣ የአማራክ ክልል ትምህርት ቢሮ
ፎቶ ፦ የደሴ፣ ኮምቦልቻ፣ የወልዲያ ከተማ ፣ የጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ኮሚኒኬሽን ቢሮዎች ፣ የቤ/ጉ ክልል ትምህርት ቢሮ
@tikvahethiopia
የመጀመሪያው ቀን የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ሲሰጥ ውሏል።
ፈተናው በአማራ፣ ኦሮሚያ፣ አፋር እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ተሰጥቷል።
#Amahra
በአማራ ክልል ከ37 ሺ በላይ ለሆኑ ተማሪዎች ዛሬ ፈተና ሲሰጥ ውሏል። ፈተናው በደቡብና ሰሜን ወሎ፣ ዋግኸምራ፣ ኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞኖችና በደሴ ከተማ ፣ የሰሜን ሸዋ ዞን 3 ወረዳዎች፣ በሰሜን ጎንደር ዞን በ1 የፈተና ጣቢያ ፈተናው ነው የተሰጠው።
በሌላ በኩል ከኦሮሚያ ክልል ምስራቅና ምዕራብ ወለጋ ዞኖች ተፈናቅለው ለመጡ 220 ተማሪዎችም በልዩ ሁኔታ በቡሬ በተቋቋመ የመፈተኛ ጣቢያ ተፈትነዋል።
#OromiaRegion
በኦሮሚያ ክልል በቄለም ወለጋ ዞን በ12 ወረዳዎች በ42 የፈተና ጣቢያዎች 14,228 ተማሪዎች ለፈተና መቀመጣቸው ፤ ፈተናውን እንደሚወስዱ ከተጠበቁት 16,608 ተማሪዎች መካከል 1, 243 በተለያዩ ምክንያቶች ፈተና ላይ አለመቀመጣቸው ተገልጿል።
በምዕራብ ወለጋ የቤጊ እና ቆንደላ ወረዳዎች 1,137 ተማሪዎች በአራት የፈተና ጣቢያ ፈተናው ላይ የተቀመጡ ሲሆን በተለያዩ ምክንያቶች 931 ተማሪዎች ፈተናው ላይ እንዳልተቀመጡ ተገልጿል።
#Afar
በአፋር ክልል ፈተናውን ይወስዳሉ ተብለው ከተጠበቁት 257 ተማሪዎች 154 ተማሪዎች ፈተናውን መውሰድ ጀምረዋል።
#BenishangulGumuz
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ካማሺ ዞን አንፃራዊ ሠላም ተመዝግቦባቸዋል በተባሉ አካባቢዎች የ12ኛ ክፍል የዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና ሲሰጥ ውሏል።
• የሁለተኛው ቀን ፈተና ይቀጥላል።
መረጃ ፦ ኢብኮ፣ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ፣ የአማራክ ክልል ትምህርት ቢሮ
ፎቶ ፦ የደሴ፣ ኮምቦልቻ፣ የወልዲያ ከተማ ፣ የጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ኮሚኒኬሽን ቢሮዎች ፣ የቤ/ጉ ክልል ትምህርት ቢሮ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update እንሆ ከ3 ዓመት በኃላ የቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን ወደ በረራ ተመልሷል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ3 ዓመታት በኋላ የቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን የመጀመሪያ የሙከራ በረራ በተሳካ ሁኔታ ማከናወኑን አስታውቋል። የሙከራ በረራውን ያከናወነው ከአዲስ አበባ ወደ ኬንያ ባካሔደው የደርሶ መልስ በረራ ነው። ለሙከራ በረራው እ.አ.አ በ2018 የቦይንግ አውሮፕላን በረራ መቆጣጠሪያ ክፍሉ…
#EthiopianAirlines
በአፍሪካ ታላቁ እና የአህጉሪቱ የአቪየሽን መሪ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የ " ቦይንግ 737 ማክስ " አውሮፕላኑን ዛሬ ጥር 24 ቀን 2014 ዓ.ም ዳግም ወደ አየር መለሰ።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የቦርድ ሰብሳቢ፣ የአየር መንገዱ የማኔጅመንት አባላት፣ የቦይንግ የስራ ኃላፊዎች፣ ሚኒስትሮች፣ አምባሳደሮች፣ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ ጋዜጠኞች እና የአየር መንገዱ ደንበኞች በዚህ የመጀመሪያ በረራ ላይ መታደማቸው ተገልጿል።
አቶ ተወልደ ገብረማርያም፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ የቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላንን ወደ አገልግሎት መመለስ አስመልክተው ፥ “የበረራ ደህንነት የአየር መንገዳችን ተቀዳሚና ወሳኝ ጉዳይ ነው፤ እያንዳንዷ የምንሰራት ስራና የምንወስናት ውሳኔ በበረራ ደህንነት አብይ ጉዳይ የተቃኘ ነው። በዚህ መርህ ላይ በመመስረት ነው ዛሬ ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላናችንን ወደ አገልግሎት የመለስነው።" ብለዋል።
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ
@tikvahethiopia
በአፍሪካ ታላቁ እና የአህጉሪቱ የአቪየሽን መሪ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የ " ቦይንግ 737 ማክስ " አውሮፕላኑን ዛሬ ጥር 24 ቀን 2014 ዓ.ም ዳግም ወደ አየር መለሰ።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የቦርድ ሰብሳቢ፣ የአየር መንገዱ የማኔጅመንት አባላት፣ የቦይንግ የስራ ኃላፊዎች፣ ሚኒስትሮች፣ አምባሳደሮች፣ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ ጋዜጠኞች እና የአየር መንገዱ ደንበኞች በዚህ የመጀመሪያ በረራ ላይ መታደማቸው ተገልጿል።
አቶ ተወልደ ገብረማርያም፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ የቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላንን ወደ አገልግሎት መመለስ አስመልክተው ፥ “የበረራ ደህንነት የአየር መንገዳችን ተቀዳሚና ወሳኝ ጉዳይ ነው፤ እያንዳንዷ የምንሰራት ስራና የምንወስናት ውሳኔ በበረራ ደህንነት አብይ ጉዳይ የተቃኘ ነው። በዚህ መርህ ላይ በመመስረት ነው ዛሬ ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላናችንን ወደ አገልግሎት የመለስነው።" ብለዋል።
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ
@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የጊኒ ቢሳው መዲና በተኩስ ስትናጥ ነበር።
በጊኒ ቢሳው ርዕሰ መዲና በሀገሪቱ መንግስት መቀመጫ አቅራቢያ ከፍተኛ የተኩስ ድምፅ ይሰማ እንደነበር ተነግሯል።
በከፍተኛ ሁኔታ የታጠቁ ሰዎች ዛሬ ማክሰኞ ቤተ መንግስቱን መክበባቸው ነው የተሰማው።
ይህ የሆነው ፕሬዝዳንት ኡማሮ ሲሶኮ ኢምባሎ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ኑኖ ጎሜስ ናቢያም በካቢኔ ስብሰባ ላይ ለመሳተፍ ሄደው በነበረበት ወቅት ሳይሆን እንዳልቀረ ተገልጿል።
በነበረው ሁኔታ የተደናገጡ ሰዎች ከአካባቢው ሲሸሹ መታየቱን፣ የንግድ እንቅስቃሴ መቋረጡ ፣ ባንኮች መዘጋታቸውንና ወታደሮችን የጫኑ ተሽከርካሪዎች ደግሞ በጎዳናዎች ላይ ሲዘዋወሩ መታየታቸውን AFP ዘግቧል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በጊኒ ቢሳው ዋና ከተማ ግጭት መኖሩን የሚገልፁ ዜናዎች በእጅጉ እንዳሳሰባቸው ገልፀዋል።
አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ግጭቱ በአስቸኳይ እንዲቆምና የሀገሪቱ የዲሞክራሲ ተቋማት ሙሉ በሙሉ እንዲከበሩ ጠይቀዋል።
ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ECOWAS ባወጣው መግለጫ በቢሳው ክስተቱን " የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ " ሲል በመጥራት አውግዟል።
በምዕራብ አፍሪካ ውስጥ ያሉት ሦስት ሀገራት - ማሊ ፣ ጊኒ እና ቡርኪናፋሶ - ከ18 ወራት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት አጋጥሟቸዋል።
@tikvahetheng
በጊኒ ቢሳው ርዕሰ መዲና በሀገሪቱ መንግስት መቀመጫ አቅራቢያ ከፍተኛ የተኩስ ድምፅ ይሰማ እንደነበር ተነግሯል።
በከፍተኛ ሁኔታ የታጠቁ ሰዎች ዛሬ ማክሰኞ ቤተ መንግስቱን መክበባቸው ነው የተሰማው።
ይህ የሆነው ፕሬዝዳንት ኡማሮ ሲሶኮ ኢምባሎ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ኑኖ ጎሜስ ናቢያም በካቢኔ ስብሰባ ላይ ለመሳተፍ ሄደው በነበረበት ወቅት ሳይሆን እንዳልቀረ ተገልጿል።
በነበረው ሁኔታ የተደናገጡ ሰዎች ከአካባቢው ሲሸሹ መታየቱን፣ የንግድ እንቅስቃሴ መቋረጡ ፣ ባንኮች መዘጋታቸውንና ወታደሮችን የጫኑ ተሽከርካሪዎች ደግሞ በጎዳናዎች ላይ ሲዘዋወሩ መታየታቸውን AFP ዘግቧል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በጊኒ ቢሳው ዋና ከተማ ግጭት መኖሩን የሚገልፁ ዜናዎች በእጅጉ እንዳሳሰባቸው ገልፀዋል።
አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ግጭቱ በአስቸኳይ እንዲቆምና የሀገሪቱ የዲሞክራሲ ተቋማት ሙሉ በሙሉ እንዲከበሩ ጠይቀዋል።
ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ECOWAS ባወጣው መግለጫ በቢሳው ክስተቱን " የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ " ሲል በመጥራት አውግዟል።
በምዕራብ አፍሪካ ውስጥ ያሉት ሦስት ሀገራት - ማሊ ፣ ጊኒ እና ቡርኪናፋሶ - ከ18 ወራት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት አጋጥሟቸዋል።
@tikvahetheng
220131_humanitarian_bulletin_final (2).pdf
244.5 KB
#UN
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ (UNOCHA) ፦
• በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ያለው ግጭት በህብረተሰቡ ህይወት እና ኑሮ ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ እያሳደረ እና የሰብአዊ ፍላጎቶችን እያሳደገው ይገኛል።
• በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ፣ ምዕራብ እና ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞኖች ያለው ያልተረጋጋ የጸጥታ ችግር (የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል አጎራባች አካባቢዎችን ጨምሮ) በርካቶችን ከቀያቸው እንዲፈናቀሉ እያደረገ ነው።
• በኦሮሚያ ክልል ምስራቅና ምዕራብ ወለጋ ዞኖች ከ250,000 በላይ ሰዎች የእህል ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል። እስካሁን ያለው ምላሽ በቂ አይደለም፤ ሽፋኑም ውስን ነው።
@tikvahethiopia
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ (UNOCHA) ፦
• በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ያለው ግጭት በህብረተሰቡ ህይወት እና ኑሮ ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ እያሳደረ እና የሰብአዊ ፍላጎቶችን እያሳደገው ይገኛል።
• በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ፣ ምዕራብ እና ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞኖች ያለው ያልተረጋጋ የጸጥታ ችግር (የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል አጎራባች አካባቢዎችን ጨምሮ) በርካቶችን ከቀያቸው እንዲፈናቀሉ እያደረገ ነው።
• በኦሮሚያ ክልል ምስራቅና ምዕራብ ወለጋ ዞኖች ከ250,000 በላይ ሰዎች የእህል ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል። እስካሁን ያለው ምላሽ በቂ አይደለም፤ ሽፋኑም ውስን ነው።
@tikvahethiopia
#Oromia, #WestGuji 📍
በምዕራብ ጉጂ ዞን ገላና ወረዳ ነዋሪዎች አካባቢያቸውን በሸኔ በመከበቡ ውሎ መግባት አስቸጋሪ መሆኑን አመለከቱ።
ነዋሪዎች የታጣቂ ቡዱን በርካታ የወረዳውን ቀበሌዎችን መቆጣጠሩን በመግለፅ ሰዎች እንደሚገደሉ፣ ንብረትም እንደሚወድም እና እንደሚዘረፍ ገልፀዋል።
ወረዳው ነዋሪ ፦
" ያለንበት ሁኔታ አሰቃቂ እና ተስፋ የሌለው ነው።
በአሁን ጊዜ አስከፊ ሁኔታ ውስጥ ነን። ታጣቂዎች ቤት አይሉ ማህበረሰቡ የሚገለገልባቸው የመንግስት ተቋማንት እያቃጠሉ እና እያወደሙ ነው።
በየቀኑ የ4 እና 5 ሰዎች መገደል ይሰማል። አርሶ አደር በከብቶቹ መሃል ይገደላል።
ተሽከርካሪ እንደልብ አይንቀሳቀስም ይዘረፋል። ለማን አቤት እንደምንል አናውቅም እያለቅን እየተሰቃየን ነው። "
ሌላ ነዋሪ ፦
" ከወረዳው ከታጣቂዎች ንፁህ የሚባለው ሁለት ቀበሌ ብቻ ናቸው።
እዚህ ደረጃ ከደረሰ ቆይቷል። የወረዳ የፀጥታ ኃላፊን ጨምሮ ልዩ ኃይሎች፣ ሚሊሻዎች፣ የቀበሌ ሊቀመንበሮች በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች አልቀዋል "
የገላና ወረዳ አስተዳደሪ አቶ ሞርከታ ሴሮ ፦
" እነዚህ ታጣቂዎች የሸኔ ታጣቂዎች ናቸው።
እንቅስቃሴያቸውን መግታት አልቻልንም ስለዚህ ችግሩ በጣም እየከፋ በመምጣቱ እኛም ለመንግስት አካል አመልክተናል።
በተለይ የወታደር ኃይል ገብቶ ይህን ኃይል እንዲመታው እና ህብረተሰቡ በነፃነት ወጥቶ እንዲገባ የሚደረግበትን ሁኔታ እየፈጠርን ነው።
ሁኔታው ትንሽ ከበድ ይላል። እውነቱን ለመናገር የወረዳው ብዙ ቀበሌዎች ላይ ገብተዋል።
የመከላከያ ሰራዊት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ይገባሉ ብለን ተስፋ እናደርጋለን። ከሚመለከተው አካል ጋር እየተነጋገርን ነው። "
ያንብቡ : https://telegra.ph/Gelana-Woreda-02-01
በምዕራብ ጉጂ ዞን ገላና ወረዳ ነዋሪዎች አካባቢያቸውን በሸኔ በመከበቡ ውሎ መግባት አስቸጋሪ መሆኑን አመለከቱ።
ነዋሪዎች የታጣቂ ቡዱን በርካታ የወረዳውን ቀበሌዎችን መቆጣጠሩን በመግለፅ ሰዎች እንደሚገደሉ፣ ንብረትም እንደሚወድም እና እንደሚዘረፍ ገልፀዋል።
ወረዳው ነዋሪ ፦
" ያለንበት ሁኔታ አሰቃቂ እና ተስፋ የሌለው ነው።
በአሁን ጊዜ አስከፊ ሁኔታ ውስጥ ነን። ታጣቂዎች ቤት አይሉ ማህበረሰቡ የሚገለገልባቸው የመንግስት ተቋማንት እያቃጠሉ እና እያወደሙ ነው።
በየቀኑ የ4 እና 5 ሰዎች መገደል ይሰማል። አርሶ አደር በከብቶቹ መሃል ይገደላል።
ተሽከርካሪ እንደልብ አይንቀሳቀስም ይዘረፋል። ለማን አቤት እንደምንል አናውቅም እያለቅን እየተሰቃየን ነው። "
ሌላ ነዋሪ ፦
" ከወረዳው ከታጣቂዎች ንፁህ የሚባለው ሁለት ቀበሌ ብቻ ናቸው።
እዚህ ደረጃ ከደረሰ ቆይቷል። የወረዳ የፀጥታ ኃላፊን ጨምሮ ልዩ ኃይሎች፣ ሚሊሻዎች፣ የቀበሌ ሊቀመንበሮች በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች አልቀዋል "
የገላና ወረዳ አስተዳደሪ አቶ ሞርከታ ሴሮ ፦
" እነዚህ ታጣቂዎች የሸኔ ታጣቂዎች ናቸው።
እንቅስቃሴያቸውን መግታት አልቻልንም ስለዚህ ችግሩ በጣም እየከፋ በመምጣቱ እኛም ለመንግስት አካል አመልክተናል።
በተለይ የወታደር ኃይል ገብቶ ይህን ኃይል እንዲመታው እና ህብረተሰቡ በነፃነት ወጥቶ እንዲገባ የሚደረግበትን ሁኔታ እየፈጠርን ነው።
ሁኔታው ትንሽ ከበድ ይላል። እውነቱን ለመናገር የወረዳው ብዙ ቀበሌዎች ላይ ገብተዋል።
የመከላከያ ሰራዊት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ይገባሉ ብለን ተስፋ እናደርጋለን። ከሚመለከተው አካል ጋር እየተነጋገርን ነው። "
ያንብቡ : https://telegra.ph/Gelana-Woreda-02-01
Telegraph
Gelana Woreda
#ገለና_ወረዳ በምዕራብ ጉጂ ዞን ገላና ወረዳ ነዋሪዎች አካባቢያቸውን በሸኔ በመከበቡ ውሎ መግባት አስቸጋሪ መሆኑን አመለከቱ። ነዋሪዎች የታጣቂ ቡዱን በርካታ የወረዳውን ቀበሌ መቆጣጠሩን በመግለፅ ሰዎች እንደሚገደሉ፣ ንብረትም እንደሚወድም እና እንደሚዘረፍ ገልፀዋል። ከወረዳው ከታጣቂዎች ንፁህ የሚባለው ሁለት ቀበሌ ብቻ መሆኑን የሚናገሩት ነዋሪዎች ነገሩ እዚህ ደረጃ ከደረሰ መቆየቱንና የወረዳ የፀጥታ…
#ETHIOPIA
የ24 ሰዓት የኮቪድ-19 ሪፖርት ፦
• የተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ 👉 7,696
• ቫይረሱ የተገኘባቸው 👉 319
• ህይወታቸው ያለፈ 👉 6
• ከበሽታው ያገገሙ 👉 576
• ፅኑ ታማሚዎች 👉 252
በኢትዮጵያ ውስጥ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ከተከሰተ ጊዜ አንስቶ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች 465,477 የደረሰ ሲሆን ከነዚህ መካከል 7,343 ህይወታቸው አልፏል፤ 399,021 ከበሽታው አገግመዋል።
በአሁን ሰዓት ቫይረሱ ያለባቸው 59,111 ሰዎች ናቸው።
በኢትዮጵያ ክትባት መሰጠት ከጀመረ አንስቶ የተከተቡ ዜጎች 9,372,085 ደርሰዋል።
@tikvahethiopia
የ24 ሰዓት የኮቪድ-19 ሪፖርት ፦
• የተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ 👉 7,696
• ቫይረሱ የተገኘባቸው 👉 319
• ህይወታቸው ያለፈ 👉 6
• ከበሽታው ያገገሙ 👉 576
• ፅኑ ታማሚዎች 👉 252
በኢትዮጵያ ውስጥ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ከተከሰተ ጊዜ አንስቶ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች 465,477 የደረሰ ሲሆን ከነዚህ መካከል 7,343 ህይወታቸው አልፏል፤ 399,021 ከበሽታው አገግመዋል።
በአሁን ሰዓት ቫይረሱ ያለባቸው 59,111 ሰዎች ናቸው።
በኢትዮጵያ ክትባት መሰጠት ከጀመረ አንስቶ የተከተቡ ዜጎች 9,372,085 ደርሰዋል።
@tikvahethiopia