#Somalia
የሶማሊያ መንግስት ቃል አቀባይ በአጥፍቶ ጠፊ የቦንብ ጥቃት ጉዳት ደርሶባቸው ሆስፒታል ገቡ።
ዛሬ ጥዋት በሞቃዲሾ የአጥፍቶ ጠፊ የቦንብ ፍንዳታ መድረሱን ፖሊስ ሪፖርት አድርጓል።
በአጥፍቶ ጠፊ ጥቃቱ የቀድሞው ጋዜጠኛ እና የአሁን የሶማሊያ መንግስት ቃል አቀባይ መሀመድ ኢብራሂም ሙአሊሙ ተሽከርካሪ ኢላማ እንደተደረገ እና እሳቸው ላይም ጉዳት እንደደረሰባቸው ተሰምቷል።
ቃልአቀባዩ በጥቃቱ ቆስለው ሞቃዲሾ በሚገኝ አንድ ሆስፒታል ውስጥ ህክምና እየተደረገላቸው መሆኑን የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
ለጥቃቱ ኃላፊነት የወሰደ አካል እስካሁን የለም።
@tikvahethiopia
የሶማሊያ መንግስት ቃል አቀባይ በአጥፍቶ ጠፊ የቦንብ ጥቃት ጉዳት ደርሶባቸው ሆስፒታል ገቡ።
ዛሬ ጥዋት በሞቃዲሾ የአጥፍቶ ጠፊ የቦንብ ፍንዳታ መድረሱን ፖሊስ ሪፖርት አድርጓል።
በአጥፍቶ ጠፊ ጥቃቱ የቀድሞው ጋዜጠኛ እና የአሁን የሶማሊያ መንግስት ቃል አቀባይ መሀመድ ኢብራሂም ሙአሊሙ ተሽከርካሪ ኢላማ እንደተደረገ እና እሳቸው ላይም ጉዳት እንደደረሰባቸው ተሰምቷል።
ቃልአቀባዩ በጥቃቱ ቆስለው ሞቃዲሾ በሚገኝ አንድ ሆስፒታል ውስጥ ህክምና እየተደረገላቸው መሆኑን የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
ለጥቃቱ ኃላፊነት የወሰደ አካል እስካሁን የለም።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Timket የጥምቀት በዓል ሊከበር ቀናቶች ቀርተዋል። በአዲስ አበባ ከተማ የጥምቀት በዓል በድምቀት የሚከበርበት የጃንሜዳ ባህረ ጥምቀት ሥራ በመፋጠን ላይ መሆኑ ተገልጿል። ወቅታዊ የግንባታ ይዘቱ ከላይ በፎቶ ተያይዟል። Photo Credit : EOTCTV @tikvahethiopia
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
#Update
የጃንሜዳ ባህረ ጥምቀት የምዕራፍ አንድ የግንባታ ሥራ ተጠናቆ ለበዓል አከባበር ሥርዓቱ ዝግጁ ሆነ።
ከአንድ ወር በፊት የግንባታ ሥራው የተጀመረው የጃንሜዳ ባህረ ጥምቀት የምዕራፍ አንድ የግንባታ ሥራ መጠናቀቁና ለጥምቀት በዓል ዝግጁ መሆኑ ተገልጿል።
በምዕራፍ አንድ የግንባታ ሥራ ከተከናወኑት ተግባራት መካከል የባህረ ጥምቀቱን ገንዳ በአዲስና ዘመናዊ መንገድ የመገንባት ፣ የኤሌክትሪክና የውኃ መስመር ዝርጋታ ሥራዎች እንዲሁም ቅጽረ ጊቢውን የማስዋብና ቡራኬ ማከናወኛ ስፍራዎችን የማስጌጥ ሥራዎች ተከናውነዋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ የጸበል መርጫ መስመሮች የተገጠሙ ሲሆን ብቃት ያላቸው የውኃ መሳቢያ ሞተሮች ገጠማም ተከናውኖ ዝግጁ መሆኑን የማረጋገጥ ሥራም ተከናውኗል።
በአጠቃላይ የዘንድሮን የጥምቀት በዓልን በጥሩ ሁኔታ ለማክበር የሚያስችሉ የግንባታሥራዎች፣ የታቦታት ማረፊይያ ቦታዎች፣ የክብር እኝግዶች የሚስተናገዱባቸው ስቴጆችና የድምጽ ማጉያ መስመር ዝርጋታዎች ተከናውኗል።
ቀሪ የግንባታ ሥራዎችና ይዞታውን የማስከበር ተግባራትም በዓሉ ከተከበረ በኋላ ተጠናክረው መቀጠል ይችሉ ዘንድ አስፈላጊው የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መከናወናቸውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ህዝብ ግንኙነት መምሪያ አሳውቋል።
ቪድዮ : 25 MB (Wi-Fi ተጠቀሙ)
@tikvahethiopia
የጃንሜዳ ባህረ ጥምቀት የምዕራፍ አንድ የግንባታ ሥራ ተጠናቆ ለበዓል አከባበር ሥርዓቱ ዝግጁ ሆነ።
ከአንድ ወር በፊት የግንባታ ሥራው የተጀመረው የጃንሜዳ ባህረ ጥምቀት የምዕራፍ አንድ የግንባታ ሥራ መጠናቀቁና ለጥምቀት በዓል ዝግጁ መሆኑ ተገልጿል።
በምዕራፍ አንድ የግንባታ ሥራ ከተከናወኑት ተግባራት መካከል የባህረ ጥምቀቱን ገንዳ በአዲስና ዘመናዊ መንገድ የመገንባት ፣ የኤሌክትሪክና የውኃ መስመር ዝርጋታ ሥራዎች እንዲሁም ቅጽረ ጊቢውን የማስዋብና ቡራኬ ማከናወኛ ስፍራዎችን የማስጌጥ ሥራዎች ተከናውነዋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ የጸበል መርጫ መስመሮች የተገጠሙ ሲሆን ብቃት ያላቸው የውኃ መሳቢያ ሞተሮች ገጠማም ተከናውኖ ዝግጁ መሆኑን የማረጋገጥ ሥራም ተከናውኗል።
በአጠቃላይ የዘንድሮን የጥምቀት በዓልን በጥሩ ሁኔታ ለማክበር የሚያስችሉ የግንባታሥራዎች፣ የታቦታት ማረፊይያ ቦታዎች፣ የክብር እኝግዶች የሚስተናገዱባቸው ስቴጆችና የድምጽ ማጉያ መስመር ዝርጋታዎች ተከናውኗል።
ቀሪ የግንባታ ሥራዎችና ይዞታውን የማስከበር ተግባራትም በዓሉ ከተከበረ በኋላ ተጠናክረው መቀጠል ይችሉ ዘንድ አስፈላጊው የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መከናወናቸውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ህዝብ ግንኙነት መምሪያ አሳውቋል።
ቪድዮ : 25 MB (Wi-Fi ተጠቀሙ)
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Abala በአፋር ክልል ፣ አብአላ ከተማ በሚሰነዘር የከባድ መሳሪያ ድብደባ የከተማው ነዋሪ ከቄዬው እየተሰደደ መሆኑን የከተማው ከንቲባ ተናገሩ። ከንቲባው ይህን የተገሩት ለቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ ነው። ከመቐለ ከተማ 40 ኪ/ሜ ርቀት ላይ የምትገኘው የአፋር የንግድ ከተማ አብአላ ከንቲባ አቶ ጣሂር ሀሰን ህወሓት ተቆጣጥሯቸው ከነበሩት የአፋር እና አማራ ክልሎች እንዲወጣ ከተደረገ በኃላ አብአላ ላይ ተደጋጋሚ…
" በአፋር በኩል ጦርነቱ አልቆመም "- አፋር ክልል
የአፋር ክልል መንግስት ፥ ህወሓት በሰላም ወዳዱ የአፋር ህዝብ ላይ በድጋሚ እያካሄደ ያለውን የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ በአስቸኳይ ማቆም አለበት ሲል አስጠንቅቋል።
ክልሉ ፥ " አሸባሪው ህወሓት በኪልበቲ ረሱ / ዞን ሁለት / በአብአላ በኩል ከታህሳስ 10/2014 ጀምሮ በከፈተው አዲስ ግንባር በተከታታይ እየተኮሰ ባለው ከባድ መሳሪያ ንፁሀን ዜጎችን መጨፍጨፉን ቀጥሏል" ብሏል።
አክሎ ፥ "የትግራይን ህዝብ ከሁሉም ኢትዮጵያውያን ጋር ለማናከስ ቆርጦ የተነሳው አሸባሪው ህወሀት በትግራይ ክልል አዋሳኝ በሆነው በዚሁ አካባቢ የትግራይን ህዝብ ከጎረቤቱ ጋር በማናከስ፣ ጉርብትና እንዲሻክርና ጎረቤቶችን በማጣላት የራሳቸውን እድሜ ለማራዘም አፋር እና ትግራይ ጎረቤት ህዝቦችን እያናከሰ ይገኛል" ሲል አሳውቋል።
ክልሉ፥ "ጎረቤታሞች በሰላም ውሎ እንዳያድር ትልቅ ጥረት በማድረግ ላይ ነው" የሚለው የአፋር ክልል" የትግራይ ህዝብም ይሄንን የጀንታውን እብደት ሊቃወም ይገባል፤ በቃቹህ ሊሉ ይገባል" ሲል አስገንዝቧል። ቡድኑ በንፁሀን የአፋር ህዝብ ላይ በተለይም በኪልበቲ ረሲ ዞን አብአላና መጋሌ በኩል የከፈተውን በጥብቅ ሊያወግዝ ይባልም ብሏል።
የአፋር ክልሉ መንግስት " ህወሓት በከባድ መሳሪያ ንፁሀንን የመግደል የመጨፍጨፍ ተግባሩን አሁንም አላቆመም፣በአፋር በኩል ጦርነቱ አልቆመም፣ ንፁሀን ሴት፣ ህፃናት እና አዛውንት አሁንም ሰለባ እየሆኑ ነው" ብሏል።
የዓለም ህብረተሰብ የህወሓትን ድርጊት እንዲያወግዝ ጥሪ አቅርቧል።
ህወሓት ፥ በሚቆጣጠረው የትግራይ ቲቪ በኩል ባወጣው መግለጫ የአፋር ልዩ ኃይል በህዝባችን ላይ ተከታታይ ግፎችና ጭፍጨፋዎች እየፈፀመ ሰንብቷል ሲል ከሷል።
ያንብቡ : telegra.ph/Afar-Tigray-01-16
@tikvahethiopia
የአፋር ክልል መንግስት ፥ ህወሓት በሰላም ወዳዱ የአፋር ህዝብ ላይ በድጋሚ እያካሄደ ያለውን የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ በአስቸኳይ ማቆም አለበት ሲል አስጠንቅቋል።
ክልሉ ፥ " አሸባሪው ህወሓት በኪልበቲ ረሱ / ዞን ሁለት / በአብአላ በኩል ከታህሳስ 10/2014 ጀምሮ በከፈተው አዲስ ግንባር በተከታታይ እየተኮሰ ባለው ከባድ መሳሪያ ንፁሀን ዜጎችን መጨፍጨፉን ቀጥሏል" ብሏል።
አክሎ ፥ "የትግራይን ህዝብ ከሁሉም ኢትዮጵያውያን ጋር ለማናከስ ቆርጦ የተነሳው አሸባሪው ህወሀት በትግራይ ክልል አዋሳኝ በሆነው በዚሁ አካባቢ የትግራይን ህዝብ ከጎረቤቱ ጋር በማናከስ፣ ጉርብትና እንዲሻክርና ጎረቤቶችን በማጣላት የራሳቸውን እድሜ ለማራዘም አፋር እና ትግራይ ጎረቤት ህዝቦችን እያናከሰ ይገኛል" ሲል አሳውቋል።
ክልሉ፥ "ጎረቤታሞች በሰላም ውሎ እንዳያድር ትልቅ ጥረት በማድረግ ላይ ነው" የሚለው የአፋር ክልል" የትግራይ ህዝብም ይሄንን የጀንታውን እብደት ሊቃወም ይገባል፤ በቃቹህ ሊሉ ይገባል" ሲል አስገንዝቧል። ቡድኑ በንፁሀን የአፋር ህዝብ ላይ በተለይም በኪልበቲ ረሲ ዞን አብአላና መጋሌ በኩል የከፈተውን በጥብቅ ሊያወግዝ ይባልም ብሏል።
የአፋር ክልሉ መንግስት " ህወሓት በከባድ መሳሪያ ንፁሀንን የመግደል የመጨፍጨፍ ተግባሩን አሁንም አላቆመም፣በአፋር በኩል ጦርነቱ አልቆመም፣ ንፁሀን ሴት፣ ህፃናት እና አዛውንት አሁንም ሰለባ እየሆኑ ነው" ብሏል።
የዓለም ህብረተሰብ የህወሓትን ድርጊት እንዲያወግዝ ጥሪ አቅርቧል።
ህወሓት ፥ በሚቆጣጠረው የትግራይ ቲቪ በኩል ባወጣው መግለጫ የአፋር ልዩ ኃይል በህዝባችን ላይ ተከታታይ ግፎችና ጭፍጨፋዎች እየፈፀመ ሰንብቷል ሲል ከሷል።
ያንብቡ : telegra.ph/Afar-Tigray-01-16
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
የሶማሊያ ጠቅላይ ሚንስትር መሀመድ ሁሴን ሮቤል በሀገሪቱ መንግስት ቃል አቀባይ መሀመድ ኢብራሂም ሙአሊሙ ላይ ያነጣጠረውን አሰቃቂ ያሉትን የሽብር ጥቃት አወገዙ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሽብር ጥቃቱ ጉዳት የደረሰባቸው ቃል አቀባዩ በመልካም ሁኔታ ላይ ይገኛሉ ብለዋል።
ጠ/ሚ መሀመድ ሁሴን ሮብሌ ፥ ለመሀመድ ኢብራሂም ሙአሊሙ ፈጣን ማገገምን ተመኝተዋል።
እስካሁን ለአጥፍቶ ጠፊ ጥቃቱ ኃላፊነት የወሰደ አካል የለም።
@tikvahethiopia
የሶማሊያ ጠቅላይ ሚንስትር መሀመድ ሁሴን ሮቤል በሀገሪቱ መንግስት ቃል አቀባይ መሀመድ ኢብራሂም ሙአሊሙ ላይ ያነጣጠረውን አሰቃቂ ያሉትን የሽብር ጥቃት አወገዙ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሽብር ጥቃቱ ጉዳት የደረሰባቸው ቃል አቀባዩ በመልካም ሁኔታ ላይ ይገኛሉ ብለዋል።
ጠ/ሚ መሀመድ ሁሴን ሮብሌ ፥ ለመሀመድ ኢብራሂም ሙአሊሙ ፈጣን ማገገምን ተመኝተዋል።
እስካሁን ለአጥፍቶ ጠፊ ጥቃቱ ኃላፊነት የወሰደ አካል የለም።
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ድጋፍ ፦
አዲስ አበባ ከተማ ዛሬ እና ትላንት ለሶማሌና ኦሮሚያ ክልሎች በድርቅ ለተጎዱ ወገኖቻችን በድምሩ የ150 ሚሊዮን ብር የአይነት ድጋፍ አድርጋለች።
ዛሬ በኦሮሚያ ክልል በቦረና ዞን በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች የ50 ሚሊዮን ብር የአይነት ድጋፍ ተደርጓል።
በመጀመርያ ዙር 51 ሚሊዮን ብር የሚገመት ድጋፍ የተደረገ ሲሆን በሁለት ዙር በአጠቃላይ 101 ሚሊዮን ብር የሚሆን ድጋፍ ማድረስ ተችሏል።
ትላንት ደግሞ በሶማሌ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች በድርቅ ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የ100 ሚሊዮን ብር የምግብ ቁሳቁሶች ድጋፍ ተደርጓል።
ምንጭ፦ የአ/አ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፅ
@tikvahethiopia
አዲስ አበባ ከተማ ዛሬ እና ትላንት ለሶማሌና ኦሮሚያ ክልሎች በድርቅ ለተጎዱ ወገኖቻችን በድምሩ የ150 ሚሊዮን ብር የአይነት ድጋፍ አድርጋለች።
ዛሬ በኦሮሚያ ክልል በቦረና ዞን በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች የ50 ሚሊዮን ብር የአይነት ድጋፍ ተደርጓል።
በመጀመርያ ዙር 51 ሚሊዮን ብር የሚገመት ድጋፍ የተደረገ ሲሆን በሁለት ዙር በአጠቃላይ 101 ሚሊዮን ብር የሚሆን ድጋፍ ማድረስ ተችሏል።
ትላንት ደግሞ በሶማሌ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች በድርቅ ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የ100 ሚሊዮን ብር የምግብ ቁሳቁሶች ድጋፍ ተደርጓል።
ምንጭ፦ የአ/አ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፅ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ItsMyDam🇪🇹 ሀገራችን ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. ከ2022 ጀምሮ ከታላቁ የኅዳሴ ግድብ በዓመት 700 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት እንደምትጀምር የኢትዮጵያ የኢኖቬስን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የአይሲቲ እና ዲጂታል ኢኮኖሚ ሚኒስትር ደኤታ ሁሪያ አሊ ማህዲ አስታወቁ። ኢትዮጵያ በዚሁ ከመጀመሪያ ዙር እንደምታመነጭ ከሚጠበቀው የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት አጠቃላይ የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት…
#GERD🇪🇹
አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ስለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በዚህ ሳምንት በሰጡት መግለጫ ከተናገሩት ፦
(ከሪፖርተር)
" ... የታላቁ ህዳሴ ግድብ ኤሌክተሪክ ማመንጨት የሚጀምርበትን ቀን ይህ ነው ብሎ መነገር ባይቻልም፣ በጣም በቅርብ ጊዜ ይጀምራል።
የግድቡ ጉዳይ ሊለወጥ የማይችልና ያለቀ ነገር በመሆኑ፣ የታችኛው ተፋሰስ አገሮች ከዚህ ካለቀ ጉዳይ ጋር አብረው መቆም አለባቸው።
ከዚህ በኋላ ግድቡ ሲያመነጭ ለግብፆችም ሆነ ለሱዳኖች ጠቃሚ ከመሆኑም በላይ ፣ በሚመነጨው ኃይል ሌሎችም አገሮች ተጠቃሚ እንዲሆኑ እነዚህ አገሮች ቢሠሩ መልካም ነው። ነገር ግን የሦስትዮሽ ድርድሩ ይቁም ማለት አይደለም።
ሱዳን እና ግብፅ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ከጀመራቸሁ ችግር ይፈጠራል፣ ሰማዩ ይገለባበጣል የሚሉት ነገር አዲስ አይደለም፡፡
ቀድሞውንም ሙሌት ከጀመራችሁ አደጋ ይፈጠራል፣ ጉድ ይፈላል ሲሉ ነበር ይህ ፉከራ የተለመደ ቢሆንም አሁን ግን ያረጀና ጊዜው ያለፈበት ሆኗል።
በህዳሴ ግድቡ ውኃው ተርባይኑን አንቀሳቅሶ አልፎ ስለሚሄድ መጠኑ ስለማይቀንስ፣ ሱዳኖች የግድቡ ኃይል ማመንጨት መጀመር ሊያስደስታቸው እና ሊያከብሩት ይገባል። "
@tikvahethiopia
አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ስለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በዚህ ሳምንት በሰጡት መግለጫ ከተናገሩት ፦
(ከሪፖርተር)
" ... የታላቁ ህዳሴ ግድብ ኤሌክተሪክ ማመንጨት የሚጀምርበትን ቀን ይህ ነው ብሎ መነገር ባይቻልም፣ በጣም በቅርብ ጊዜ ይጀምራል።
የግድቡ ጉዳይ ሊለወጥ የማይችልና ያለቀ ነገር በመሆኑ፣ የታችኛው ተፋሰስ አገሮች ከዚህ ካለቀ ጉዳይ ጋር አብረው መቆም አለባቸው።
ከዚህ በኋላ ግድቡ ሲያመነጭ ለግብፆችም ሆነ ለሱዳኖች ጠቃሚ ከመሆኑም በላይ ፣ በሚመነጨው ኃይል ሌሎችም አገሮች ተጠቃሚ እንዲሆኑ እነዚህ አገሮች ቢሠሩ መልካም ነው። ነገር ግን የሦስትዮሽ ድርድሩ ይቁም ማለት አይደለም።
ሱዳን እና ግብፅ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ከጀመራቸሁ ችግር ይፈጠራል፣ ሰማዩ ይገለባበጣል የሚሉት ነገር አዲስ አይደለም፡፡
ቀድሞውንም ሙሌት ከጀመራችሁ አደጋ ይፈጠራል፣ ጉድ ይፈላል ሲሉ ነበር ይህ ፉከራ የተለመደ ቢሆንም አሁን ግን ያረጀና ጊዜው ያለፈበት ሆኗል።
በህዳሴ ግድቡ ውኃው ተርባይኑን አንቀሳቅሶ አልፎ ስለሚሄድ መጠኑ ስለማይቀንስ፣ ሱዳኖች የግድቡ ኃይል ማመንጨት መጀመር ሊያስደስታቸው እና ሊያከብሩት ይገባል። "
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ዶ/ር ቴድሮስ ምን አሉ ? የአፋር እና የአማራ ክልል ባለስጣናት ምን መለሱ ? የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ፦ " 7 ሚሊዮን ህዝብ የሚኖርበት ክልል ከአንድ አመት በላይ ሙሉ በሙሉ ከበባ ውስጥ ሆናል። በዚህ ምክንያት ህዝቡ ምንም አይነት የምግብ አቅርቦት፣ የህክምና ፣ ኤሌክትሪክ፣ የቴሌፎን ፣ የመገናኛ አገልግሎት አያገኝም። በመድሃኒት አቅርቦት እጥረት ምክንያት ሰዎች…
#Update
የዓለም ጤና ድርጅት በዋና ዳይሬክተሩ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ላይ ከኢትዮጵያ መንግስት በኩል ቅሬታ እና ክስ ቢቀርብም በጦርነት ለተጎዳው የትግራይ ክልል ህዝብ እርዳታ መጠየቁን እንደሚቀጥል አስታውቋል።
ባለፈው ዓርብ የኢትዮጵያ መንግስት ዶክተር ቴድሮስ ጎጂ እንዲሁም የተሳሳተ መረጃ በማሰራጨት እና TPLFን በመደገፍ የተሳሳተ ተግባር ላይ መሳተፋቸውን በመግለፅ ከሶ ድርጅቱ ምርመራ እንዲያከናውን መጠየቁ ይታወሳል።
ዛሬ የዓለም ጤና ድርጅት የኢትዮጵያ መንግስት በይፋ ክስ ማቅረቡን አረጋግጧል።
ድርጅቱ ግን 7 ሚሊዮን ለሚደርሰው የትግራይ ክልል ህዝብ መሰረታዊ አገልግሎት እንዲደርስ የኢትዮጵያ መንግስት እንዲፈቅድ መጠየቁን እንደሚቀጥል አሳውቋል።
ባለፈው ዓርብ ዕለት የኢትዮጵያ መንግስት ቅሬታውን ያቀረበው ባለፈው ሳምንት ዶ/ር ቴድሮስ መንግስት ወደትግራይ ክልል መድሃኒትና የነፍስ አድን እርዳታዎች እንዳይገባ እየከለከለ ነው በማለት በክልሉ ያለው ሁኔታ ሲኦል ነው ብለው ከገለፁ በኃላ ነው።
መንግስት ፥ ዶ/ር ቴድሮስ የሰጡት አሰተያየት የዓለም የጤና ድርጅትን ተአማኒነት ጥያቄ ውስጥ እንደሚጥል ፤ የተጣለባቸውን ህጋዊ እና ሞያዊ ኃላፊነት ጥሰው በመገኘታቸው ምርመራ እንዲደረግ ጠይቆ ነበር።
በተመድ የኢትዮጵያ ልዑክም ዶ/ር ቴድሮስ የፖለቲካ ውግንና እንዳላቸው በመግለፅ ኢትዮጵያን ከሚመለከቱ ጉዳዮች እራሳቸው እዲያርቁ ጠይቆ እንደነበር የፈረሳይ ዜና አገልግሎትን ዋቢ አድርጎ ዶቼ ቨለ ሬድዮ ዘግቧል።
ዶ/ር ቴድሮስ ከሰጡት አስተያየት ጋር በተያያዘ የአማራ እና አፋር ክልል ባለስልጣናት ጠንካራ ትችት ሰንዝረው ዶ/ር ቴድሮስ የተናገሩት ለህወሓት ፕሮፖጋንዳ መሆኑንና በአፋር እና አማራ ክልል ህወሓት ስላደረሰው ጥፋት ተናግረው እንደማያውቁ መግለፃቸው አይዘነጋም።
@tikvahethiopia
የዓለም ጤና ድርጅት በዋና ዳይሬክተሩ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ላይ ከኢትዮጵያ መንግስት በኩል ቅሬታ እና ክስ ቢቀርብም በጦርነት ለተጎዳው የትግራይ ክልል ህዝብ እርዳታ መጠየቁን እንደሚቀጥል አስታውቋል።
ባለፈው ዓርብ የኢትዮጵያ መንግስት ዶክተር ቴድሮስ ጎጂ እንዲሁም የተሳሳተ መረጃ በማሰራጨት እና TPLFን በመደገፍ የተሳሳተ ተግባር ላይ መሳተፋቸውን በመግለፅ ከሶ ድርጅቱ ምርመራ እንዲያከናውን መጠየቁ ይታወሳል።
ዛሬ የዓለም ጤና ድርጅት የኢትዮጵያ መንግስት በይፋ ክስ ማቅረቡን አረጋግጧል።
ድርጅቱ ግን 7 ሚሊዮን ለሚደርሰው የትግራይ ክልል ህዝብ መሰረታዊ አገልግሎት እንዲደርስ የኢትዮጵያ መንግስት እንዲፈቅድ መጠየቁን እንደሚቀጥል አሳውቋል።
ባለፈው ዓርብ ዕለት የኢትዮጵያ መንግስት ቅሬታውን ያቀረበው ባለፈው ሳምንት ዶ/ር ቴድሮስ መንግስት ወደትግራይ ክልል መድሃኒትና የነፍስ አድን እርዳታዎች እንዳይገባ እየከለከለ ነው በማለት በክልሉ ያለው ሁኔታ ሲኦል ነው ብለው ከገለፁ በኃላ ነው።
መንግስት ፥ ዶ/ር ቴድሮስ የሰጡት አሰተያየት የዓለም የጤና ድርጅትን ተአማኒነት ጥያቄ ውስጥ እንደሚጥል ፤ የተጣለባቸውን ህጋዊ እና ሞያዊ ኃላፊነት ጥሰው በመገኘታቸው ምርመራ እንዲደረግ ጠይቆ ነበር።
በተመድ የኢትዮጵያ ልዑክም ዶ/ር ቴድሮስ የፖለቲካ ውግንና እንዳላቸው በመግለፅ ኢትዮጵያን ከሚመለከቱ ጉዳዮች እራሳቸው እዲያርቁ ጠይቆ እንደነበር የፈረሳይ ዜና አገልግሎትን ዋቢ አድርጎ ዶቼ ቨለ ሬድዮ ዘግቧል።
ዶ/ር ቴድሮስ ከሰጡት አስተያየት ጋር በተያያዘ የአማራ እና አፋር ክልል ባለስልጣናት ጠንካራ ትችት ሰንዝረው ዶ/ር ቴድሮስ የተናገሩት ለህወሓት ፕሮፖጋንዳ መሆኑንና በአፋር እና አማራ ክልል ህወሓት ስላደረሰው ጥፋት ተናግረው እንደማያውቁ መግለፃቸው አይዘነጋም።
@tikvahethiopia
#ነፃ_ዋይፋይ
ኢትዮ ቴሌኮም በአዲስ አበባ ከተማ በመስቀል አደባባይ ፣ እንጦጦ ፣ አንድነት ፓርክ እና የወዳጅነት አደባባዮች በከፍተኛ ወጪ የዋይፋይ (WiFi) አገልግሎት ገንብቶ በነጻ ማቅረቡን ዛሬ ገልጿል።
@tikvahethiopia
ኢትዮ ቴሌኮም በአዲስ አበባ ከተማ በመስቀል አደባባይ ፣ እንጦጦ ፣ አንድነት ፓርክ እና የወዳጅነት አደባባዮች በከፍተኛ ወጪ የዋይፋይ (WiFi) አገልግሎት ገንብቶ በነጻ ማቅረቡን ዛሬ ገልጿል።
@tikvahethiopia
ሀገራችን ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ ምድቧን የማለፍ እድል አላት ?
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በምድብ ሀ ሦስተኛ የጨዋታ መርሐ ግብር ከቡርኪና ፋሶ አቻው ጋር ዛሬ ምሸት 1 ሰዓት ላይ በባፎሳም ስታዲየም ያካሂዳል።
ለመሆኑ ሀገራችን ኢትዮጵያ ምድቧን የማለፍ እድል አላት ? ትላንት መግለጫ የሰጡት አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ተከታዩን ተናግረዋል ፦
" ሁለት ቡድኖች በቀጥታ ከምድቡ ያልፋሉ። ጥሩ ሶስተኛ ሆኖ የሚያልፍም ይኖራል።
ጨዋታውን ማሸነፍ በሌሎች ውጤት ላይ የሚወሰን ቢሆንም የመጀመርያው ነገር ጨዋታውን ማሸነፍ ነው።
የማለፍ ጉዳይ በቀጣይ የሌሎች ውጤትን ተመርኩዞ ነው የሚወሰነው።
ከዚህ ባሻገር በቡድናችን ላይ ችግሮች ተመልክተናል ፤ በተለይ በአእምሮው ረገድ። በዛ ላይ ከሰራን ፣ ባለን ነገር ላይ እምነት ካለን እና እህንንም ወደ ተጫዋቾቹ ማስረፅ ከቻልን ማድረግ እንደምንችል አምናለሁ። እድሉ አለን ፤ እንደምናሳካም አምናለሁ። "
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በምድብ ሀ ሦስተኛ የጨዋታ መርሐ ግብር ከቡርኪና ፋሶ አቻው ጋር ዛሬ ምሸት 1 ሰዓት ላይ በባፎሳም ስታዲየም ያካሂዳል።
ለመሆኑ ሀገራችን ኢትዮጵያ ምድቧን የማለፍ እድል አላት ? ትላንት መግለጫ የሰጡት አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ተከታዩን ተናግረዋል ፦
" ሁለት ቡድኖች በቀጥታ ከምድቡ ያልፋሉ። ጥሩ ሶስተኛ ሆኖ የሚያልፍም ይኖራል።
ጨዋታውን ማሸነፍ በሌሎች ውጤት ላይ የሚወሰን ቢሆንም የመጀመርያው ነገር ጨዋታውን ማሸነፍ ነው።
የማለፍ ጉዳይ በቀጣይ የሌሎች ውጤትን ተመርኩዞ ነው የሚወሰነው።
ከዚህ ባሻገር በቡድናችን ላይ ችግሮች ተመልክተናል ፤ በተለይ በአእምሮው ረገድ። በዛ ላይ ከሰራን ፣ ባለን ነገር ላይ እምነት ካለን እና እህንንም ወደ ተጫዋቾቹ ማስረፅ ከቻልን ማድረግ እንደምንችል አምናለሁ። እድሉ አለን ፤ እንደምናሳካም አምናለሁ። "
@tikvahethiopia
#DireDawa
የቀድሞ የድሬዳዋ ከተማ ከንቲባ 3.9 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ የመኪና ስጦታ ተበረከተላቸው።
ለቀድሞ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አህመድ መሀመድ ቡህ አስተዳደሩ በአመራርነት ዘመናቸው ላበረከቱት መልካም ስራዎች የምስጋና ኘሮግራም ተካሄዶል።
በዚሁ ፕሮግራም ላይ 3.9 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ ዘመናዊ የመኪና ስጦታ ተበርክቶላቸዋል።
የአስተዳደሩ ከንቲባ ከድር ጆሀር በምስጋና ፕሮግራሙ ላይ " ጥቂት ብንዘገይም፤ እጅግ ለምንወዳቸው የቀድሞ ከንቲባችን እና ወንድማችን አቶ አህመድ መሀመድ ቡህ ዛሬ ያደረግነው ሽኝትና የሰጠነው ስጦታ፤ በአመራርነት ዘመኑ ካደረጉት አሰተወፅኦ አንፃር ለሳቸው ያንስባቸዋል እንጂ አይበዛም " ሲሉ ተናግረዋል።
ስጦታው በባለሀብቶች ተሳትፎ የተበረከተ መሆኑ ተገልጿል።
የቀድሞው ከንቲባ ለሶስት ዓመት ሙሉ ከተማዋ የነበረባትን የፀጥታ ችግር የፀጥታ አካላትን በማሰባሰብ ፣ አመራሮችን በማቀናጀት የከተማዋ ሰላም በአስተማማኝነት እንዲረጋገጥ እና ተጨባጭ ለውጥ እንዲመጣ አመራር የሰጡ ጠንካራ መሪ እንደነበሩ ተገልጿል።
በትላንትናው ዕለት ከቀድሞ ከንቲባው በተጨማሪ የድሬዳዋ ፀጥታ አካላት ፣ የፀጥታ ምክር ቤት አባላት ከ25 ሺህ ብር እስከ 100 ሺህ ብር በየደረጃው ተሸልመዋል። አጠቃላይ ሽልማቱ ከ700 ሺህ ብር በላይ እንደሆነ ተመላክቷል።
ብሩ የተገኘው ከባለሀብቶች ሲሆን የመንግስት በጀት እንዳልተነካ ተገልጿል። የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ተጠይቀው ቀና ምላሽ ለሰጡ የከተማው ባለሀብቶች ምስጋና አቅርቧል።
@tikvahethiopia
የቀድሞ የድሬዳዋ ከተማ ከንቲባ 3.9 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ የመኪና ስጦታ ተበረከተላቸው።
ለቀድሞ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አህመድ መሀመድ ቡህ አስተዳደሩ በአመራርነት ዘመናቸው ላበረከቱት መልካም ስራዎች የምስጋና ኘሮግራም ተካሄዶል።
በዚሁ ፕሮግራም ላይ 3.9 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ ዘመናዊ የመኪና ስጦታ ተበርክቶላቸዋል።
የአስተዳደሩ ከንቲባ ከድር ጆሀር በምስጋና ፕሮግራሙ ላይ " ጥቂት ብንዘገይም፤ እጅግ ለምንወዳቸው የቀድሞ ከንቲባችን እና ወንድማችን አቶ አህመድ መሀመድ ቡህ ዛሬ ያደረግነው ሽኝትና የሰጠነው ስጦታ፤ በአመራርነት ዘመኑ ካደረጉት አሰተወፅኦ አንፃር ለሳቸው ያንስባቸዋል እንጂ አይበዛም " ሲሉ ተናግረዋል።
ስጦታው በባለሀብቶች ተሳትፎ የተበረከተ መሆኑ ተገልጿል።
የቀድሞው ከንቲባ ለሶስት ዓመት ሙሉ ከተማዋ የነበረባትን የፀጥታ ችግር የፀጥታ አካላትን በማሰባሰብ ፣ አመራሮችን በማቀናጀት የከተማዋ ሰላም በአስተማማኝነት እንዲረጋገጥ እና ተጨባጭ ለውጥ እንዲመጣ አመራር የሰጡ ጠንካራ መሪ እንደነበሩ ተገልጿል።
በትላንትናው ዕለት ከቀድሞ ከንቲባው በተጨማሪ የድሬዳዋ ፀጥታ አካላት ፣ የፀጥታ ምክር ቤት አባላት ከ25 ሺህ ብር እስከ 100 ሺህ ብር በየደረጃው ተሸልመዋል። አጠቃላይ ሽልማቱ ከ700 ሺህ ብር በላይ እንደሆነ ተመላክቷል።
ብሩ የተገኘው ከባለሀብቶች ሲሆን የመንግስት በጀት እንዳልተነካ ተገልጿል። የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ተጠይቀው ቀና ምላሽ ለሰጡ የከተማው ባለሀብቶች ምስጋና አቅርቧል።
@tikvahethiopia