Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
የቺክቭ ምልክቶች ምንድናቸው? አንድ ሰው በተለከፈ ትንኝ ከተነከሰ በኋላ ከ 3 እስከ 7 ቀናቶች ውስጥ ምልክቶች ይታዩበታል። የቺክቭ ምልክቶች ከሰው ወደ ሰው የሚለያዩ ሲሆን፣ የሚከተሉትን ያጠቃልላሉ፦
በድንገት የሚከሰት ከፍተኛ ትኩሳት (>102°F)
ከባድ የሆነ የመገጣጠሚያ ህመም በተለይ በክንዶች ወይም እግሮች ላይ
ራስ ምታት
የጡንቻ ህመም
የጀርባ ህመም
ሽፍታ (~50% ተጠቂዎች ላይ የሚያጋጥም)
በብዛት በሚከተሉት ሰዎች ላይ ይስተዋላሉ፦
ህጻናት (<1 ዓመት)
አረጋውያን (>65 ዓመት)
እንደ ስኳር በሽታ፣ ከፍተኛ የደም ግፊት ወዘተ በመሳሰሉ ስር የሰደዱ በሽታዎች የተጠቁ ሰዎች።
*ከላይ የተጠቀሱት ሰዎች በትንኝ እንዳይነከሱ ከሌሎች የበለጠ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል።*
ቺክቭ እንዴት ነው የሚታከመው? ቺክቭ ለማከም የሚውል ተለይቶ የታወቀ መድሀኒትም ይሁን ክትባት #የለም።
#DCSSH
#share #ሼር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በድንገት የሚከሰት ከፍተኛ ትኩሳት (>102°F)
ከባድ የሆነ የመገጣጠሚያ ህመም በተለይ በክንዶች ወይም እግሮች ላይ
ራስ ምታት
የጡንቻ ህመም
የጀርባ ህመም
ሽፍታ (~50% ተጠቂዎች ላይ የሚያጋጥም)
በብዛት በሚከተሉት ሰዎች ላይ ይስተዋላሉ፦
ህጻናት (<1 ዓመት)
አረጋውያን (>65 ዓመት)
እንደ ስኳር በሽታ፣ ከፍተኛ የደም ግፊት ወዘተ በመሳሰሉ ስር የሰደዱ በሽታዎች የተጠቁ ሰዎች።
*ከላይ የተጠቀሱት ሰዎች በትንኝ እንዳይነከሱ ከሌሎች የበለጠ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል።*
ቺክቭ እንዴት ነው የሚታከመው? ቺክቭ ለማከም የሚውል ተለይቶ የታወቀ መድሀኒትም ይሁን ክትባት #የለም።
#DCSSH
#share #ሼር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
በቺክቭ ተጠቂቻለሁ የሚል ጥርጣሬ ካደረብኝ ምን ማድረግ አለብኝ? ትኩሳት እና የመገጣጠሚያ ህመም ለመቀነስ መድሀኒቶችን መጠቀም ጥቅም ሊኖረው ይችላል። ሐኪም ያማክሩ።
ቺክቭ ይዞኝ ሉሆን ይችላል የሚል ጥርጣሬ ካደረብዎ፦
የታይብዎ ምልክቶችን መዝግበው በመያዝ ወደ ሐኪም ይሂዱ።
ራስዎን ተጨማሪ በትንኝ ከመነከስ ይከላከሉ።
በቺክቭ ከተያዙ በሽታው ወደ ሌሎች ሰዎች ላለማስተላለፍ እራስዎን ከትንኝ ንክሻ መከላከል ይኖርብዎታል።
ምን ማድረግ አለብኝ?
#ይልበሱ
ረዥም፣ ቀለል ያለ እና ቀላል ቀለም ያለው ልብስ ይልበሱ።
#ፈሳሽ_ማድረቅ
እቤት ውስጥም ከቤት ውጪም ያለ ማንኛውም ያቆረ ውሃ ያስወግዱ።
#ማታ እና #ጠዋት
ማታና ጠዋት ትንኞች በብዛት የሚንቀሳቅሱበት ጊዜ በመሆኑ በተቻለ መጠን ከቤት አይውጡ።
#DCSSH
#share #ሼር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ቺክቭ ይዞኝ ሉሆን ይችላል የሚል ጥርጣሬ ካደረብዎ፦
የታይብዎ ምልክቶችን መዝግበው በመያዝ ወደ ሐኪም ይሂዱ።
ራስዎን ተጨማሪ በትንኝ ከመነከስ ይከላከሉ።
በቺክቭ ከተያዙ በሽታው ወደ ሌሎች ሰዎች ላለማስተላለፍ እራስዎን ከትንኝ ንክሻ መከላከል ይኖርብዎታል።
ምን ማድረግ አለብኝ?
#ይልበሱ
ረዥም፣ ቀለል ያለ እና ቀላል ቀለም ያለው ልብስ ይልበሱ።
#ፈሳሽ_ማድረቅ
እቤት ውስጥም ከቤት ውጪም ያለ ማንኛውም ያቆረ ውሃ ያስወግዱ።
#ማታ እና #ጠዋት
ማታና ጠዋት ትንኞች በብዛት የሚንቀሳቅሱበት ጊዜ በመሆኑ በተቻለ መጠን ከቤት አይውጡ።
#DCSSH
#share #ሼር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ስለ ፓልም ዘይት በሚዲያ የተሰራጨው መረጃ ተገቢ አይደለም ተባለ!
የፓልም ዘይት በህብረተሰቡ ላይ ጤና ላይ ጉዳት ያመጣል በሚል በሚዲያዎች የተሰራጨው መረጃ ተገቢ ያልሆነና በህዝቡ ዘንድ ውዥንብር እየፈጠረ መሆኑን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ገለፀ፡፡
የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከንግዱ ማህበራት ጋር እያካሄደው ባለው የውይይት መድረክ የሚኒስቴሩ ሚኒስትር ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገ/እግዚያብሄር እንደተናገሩት የፓልም ዘይት በተገቢው ደረጃ እየተፈተሸ ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገባ የሚደረግ፤ ህብረተሰቡም እንደ ልቡ ገዝቶ እንዲጠቀም የሚደረግ ነው ብለዋል፡፡
ሚኒስተሯ እንዳሉት ዘይቱ ወደ ሀገር ውስጥ ሲገባ ተገቢው ቁጥጥር ስለሚደረግበት እንደተባለው በሰው ላይ ጉዳት አያደርስም፡፡ እንደ ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገለፃ የትኛውም ዘይት እኩል ደረጃ የለውም፤እኩል ለጤናም ጠቃሚም አይደለም፡፡
የፓልም ዘይትም የራሱ ደረጃዎች ያሉትና ህብረተሰቡም እንደ አቅሙ ገዝቶ ሊጠቀመው የሚችል ነው፡፡በመሆኑም የተሰራጨው መረጃ ተገቢ ያልሆነና ህብረተሰቡን ውዥንብር ውስጥ የከተተና ወደ አላስፈላጊ ነገር ውስጥ የሚያስገባም ነው ሲሉ ሚኒስትሯ ተናግረዋል፡፡
ምንጭ፦ ኢፕድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የፓልም ዘይት በህብረተሰቡ ላይ ጤና ላይ ጉዳት ያመጣል በሚል በሚዲያዎች የተሰራጨው መረጃ ተገቢ ያልሆነና በህዝቡ ዘንድ ውዥንብር እየፈጠረ መሆኑን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ገለፀ፡፡
የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከንግዱ ማህበራት ጋር እያካሄደው ባለው የውይይት መድረክ የሚኒስቴሩ ሚኒስትር ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገ/እግዚያብሄር እንደተናገሩት የፓልም ዘይት በተገቢው ደረጃ እየተፈተሸ ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገባ የሚደረግ፤ ህብረተሰቡም እንደ ልቡ ገዝቶ እንዲጠቀም የሚደረግ ነው ብለዋል፡፡
ሚኒስተሯ እንዳሉት ዘይቱ ወደ ሀገር ውስጥ ሲገባ ተገቢው ቁጥጥር ስለሚደረግበት እንደተባለው በሰው ላይ ጉዳት አያደርስም፡፡ እንደ ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገለፃ የትኛውም ዘይት እኩል ደረጃ የለውም፤እኩል ለጤናም ጠቃሚም አይደለም፡፡
የፓልም ዘይትም የራሱ ደረጃዎች ያሉትና ህብረተሰቡም እንደ አቅሙ ገዝቶ ሊጠቀመው የሚችል ነው፡፡በመሆኑም የተሰራጨው መረጃ ተገቢ ያልሆነና ህብረተሰቡን ውዥንብር ውስጥ የከተተና ወደ አላስፈላጊ ነገር ውስጥ የሚያስገባም ነው ሲሉ ሚኒስትሯ ተናግረዋል፡፡
ምንጭ፦ ኢፕድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኮሌራ በሽታ በሶስት ክልሎች ላይ በድጋሚ ተከስቷል ተባለ!
በሀገሪቱ ተከስቶ የነበረውን የኮሌራ ወረርሽኝ በአብዛኛው ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር የተቻለ ቢሆንም በአሁኑ ሰዓት በሶስት ክልሎች ላይ በሽታው ተከስቷል ተባለ፡፡ በአሁን ወቅት ወረርሽኙ በኦሮሚያ ክልል በሻሸመኔ ወረዳ 15 ሰዎች በፈዲስ ወረዳ 20 ሰዎች፣ ሀረሪ ክልል በ6 ወረዳዎች 15 ሰዎች ተይዘዋል ተብሏል።
እንዲሁም በደቡብ ክልል በሃዋሳ ከተማ 14 ሰዎች በበሽታው መያዛቸው ተገልጿል። በወረርሽኙ የተያዙ ሰዎች የህክምና አገልግሎት እያገኙ እንደሆነ የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ለኢትዮ ኤፍ ኤም አስታውቋል፡፡
በኢትዮጵያ ከወራት በፊት በተከሰተው የኮሌራ ወረርሽኝ 19 ሰዎች መሞታቸው ይታወሳል። የበሽታው ስርጭት በከፍተኛ ሁኔታ የቀነሰ ቢሆንም ማህበረሰቡ በዚህ ሳይዘናጋ አሁንም አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ ኢንስቲትዩቱ አስጠንቅቋል፡፡
ምንጭ፦ ኢትዮ ኤፍ ኤም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በሀገሪቱ ተከስቶ የነበረውን የኮሌራ ወረርሽኝ በአብዛኛው ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር የተቻለ ቢሆንም በአሁኑ ሰዓት በሶስት ክልሎች ላይ በሽታው ተከስቷል ተባለ፡፡ በአሁን ወቅት ወረርሽኙ በኦሮሚያ ክልል በሻሸመኔ ወረዳ 15 ሰዎች በፈዲስ ወረዳ 20 ሰዎች፣ ሀረሪ ክልል በ6 ወረዳዎች 15 ሰዎች ተይዘዋል ተብሏል።
እንዲሁም በደቡብ ክልል በሃዋሳ ከተማ 14 ሰዎች በበሽታው መያዛቸው ተገልጿል። በወረርሽኙ የተያዙ ሰዎች የህክምና አገልግሎት እያገኙ እንደሆነ የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ለኢትዮ ኤፍ ኤም አስታውቋል፡፡
በኢትዮጵያ ከወራት በፊት በተከሰተው የኮሌራ ወረርሽኝ 19 ሰዎች መሞታቸው ይታወሳል። የበሽታው ስርጭት በከፍተኛ ሁኔታ የቀነሰ ቢሆንም ማህበረሰቡ በዚህ ሳይዘናጋ አሁንም አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ ኢንስቲትዩቱ አስጠንቅቋል፡፡
ምንጭ፦ ኢትዮ ኤፍ ኤም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በፋሲል ከነማ ደጋፊዎች እና በነቂያ የበጎ አድራጎት ማህበር ትብብር የተዘጋጀት የበጎት ዘመቻ እየተካሄደ ይገኛል። "ህፃናት ይማሩ፤ ሀገር ይረከቡ!" በሚል መሪቃል በዛሬው ዕለት 40 ደርዘን ደብተር ለህፃናት አበርክተዋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ኖርዌይ አዲስ አበባ የሚጓዙ ዜጎቿን በመርካቶ፣ ጊዮን ሆቴል፣ ብሔራዊና ቦሌ አካባቢዎች ኪስ አውላቂዎች እንደሚያሰጉ አስጠነቀቀች። የአገሪቱ መንግሥት ከ2017 ጀምሮ በከተማዋ ኪስ ማውለቅና ዘረፋን የመሰሉ አነስተኛ ወንጀሎች መጨመራቸውን ገልጿል። ጋምቤላና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ አካባቢዎች ውጥረት ይታያል፤ በደቡብ ክልል የጸጥታ ሁኔታው ፈታኝ ነው ያለው የኖርዌይ መንግሥት ኢትዮጵያ አሁንም ለአገር ጎብኚዎች አስተማማኝ አይደለችም፤ የትራፊክ አደጋም ያሰጋቸዋል ብሏል።
Via #EsheteBekele
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via #EsheteBekele
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የተለያዩ 17 የዓለም አገራት ዜግነት ያላቸው 80 የአደንዛዥ ዕፅ አዘዋዋሪዎች በ2011 በጀት ዓመት በኢትዮጵያ በቁጥጥር ሥር መያዛቸውን የፌደራል ፖሊስ የፀረ አደንዛዥ ዕፅ ዝውውር ግብረ ኃይል አስታውቋል።
Via #ADDISMALEDA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via #ADDISMALEDA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ማር ሲል ቴሌቪዥን በ2012 መስከረም ወር ላይ ትምህርት ለሚጀምሩ ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ። ድጋፉ የተደረገው ለምዕራብ አርሲ ዞን አርሲ ነገሌ ወረዳ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ሲሆን አገልጋይ ዮናታን አክሊሉ፣ የአዲስ ኪዳን ካህናት ቤተክርስቲያን አገልጋዮች እና የማር ሲል ቴሌቪዥን የሚዲያ አባላት ትናንት በአርሲ ነገሌ ከተማ አርሲ ነገሌ ወረዳ አስተዳደር ጽህፈት ቤት በመገኘት የመማሪያ ቁሳቁሱን አበርክተዋል። የመማሪያ ቁሳቁሱም የተሰበሰበው በመልካም ወጣት 2011 በሰባቱም ዙር ከተሳተፉ መልካም ወጣቶች ነው። ማር ሲል ቴሌቪዥን በ2012 ዓ.ም ትምህርት ለሚጀምሩ ተማሪዎችም መልካም የትምህርት ዘመን እንዲሆን ተመኝቷል።
Via #MarcilTV
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via #MarcilTV
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በሽብር ወንጀል በተጠረጠሩ ሰባት ሰዎች ላይ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ተፈቀደ!
የፌዴራሉ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ከባለስልጣናት ግድያ ጋር በተያያዘ ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩን ጨምሮ በሽብር ወንጀል የተጠረጠሩ ሰባት ሰዎች ላይ ፖሊስ የጠየቀውን ተጨማሪ የ28 ቀናት የምርመራ ጊዜ ፈቀደ።
በአዲስ አበባና ባሕርዳር ከተሞች ሰኔ 15 ቀን 2011 ዓ.ም ከተፈፀመው የባለስልጣናት ግድያ ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር የዋሉት ተጠርጣሪዎች ዛሬ በፌዴራሉ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 2ኛ ወንጀል ችሎት ቀርበዋል።
ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/eth-09-02-4
የፌዴራሉ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ከባለስልጣናት ግድያ ጋር በተያያዘ ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩን ጨምሮ በሽብር ወንጀል የተጠረጠሩ ሰባት ሰዎች ላይ ፖሊስ የጠየቀውን ተጨማሪ የ28 ቀናት የምርመራ ጊዜ ፈቀደ።
በአዲስ አበባና ባሕርዳር ከተሞች ሰኔ 15 ቀን 2011 ዓ.ም ከተፈፀመው የባለስልጣናት ግድያ ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር የዋሉት ተጠርጣሪዎች ዛሬ በፌዴራሉ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 2ኛ ወንጀል ችሎት ቀርበዋል።
ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/eth-09-02-4
ከቴፒ...
"በቴፒ በ2010 ነሀሴ ውስጥ በአከባቢው በተነሳ ግጭት የተፈናቀሉ የ3 ቀበሌ ነዋሪዎች 12 ወራት አስቆጥረው ይገኛሉ፡፡ እስካሁን በቴፒ ከተማ ህዝብ ድጋፍ ነው ህይወታቸው የቆየው፤ እነዚህ ከ10ሺ በላይ የሚሆኑ ተፈናቃዮች ቤቶቻቸው መሉ በመሉ ተቃጥሎ ሰለሚገኝ ወደ ቄያቸው ለመመለስ በተደጋጋሚ ቢገልፁም የትኛውም የመንግስት አካል ለመደገፍ ዝግጁ አይደለም ፍላጎትም የለውም፡፡ እነዚህ ተፈናቃዮች የሸራ ቤት እንኳ ተሰርቶላቸው ወደ ቄያቸው የሚገቡበትን መንገድ ቢፈለግ ወቅቱ የግብርና ስራ የሚሰራበት በመሆኑ ተፈናቃዮቹ ወደ አከባቢያቸው መመለስ ይፈልጋሉ፡፡"
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"በቴፒ በ2010 ነሀሴ ውስጥ በአከባቢው በተነሳ ግጭት የተፈናቀሉ የ3 ቀበሌ ነዋሪዎች 12 ወራት አስቆጥረው ይገኛሉ፡፡ እስካሁን በቴፒ ከተማ ህዝብ ድጋፍ ነው ህይወታቸው የቆየው፤ እነዚህ ከ10ሺ በላይ የሚሆኑ ተፈናቃዮች ቤቶቻቸው መሉ በመሉ ተቃጥሎ ሰለሚገኝ ወደ ቄያቸው ለመመለስ በተደጋጋሚ ቢገልፁም የትኛውም የመንግስት አካል ለመደገፍ ዝግጁ አይደለም ፍላጎትም የለውም፡፡ እነዚህ ተፈናቃዮች የሸራ ቤት እንኳ ተሰርቶላቸው ወደ ቄያቸው የሚገቡበትን መንገድ ቢፈለግ ወቅቱ የግብርና ስራ የሚሰራበት በመሆኑ ተፈናቃዮቹ ወደ አከባቢያቸው መመለስ ይፈልጋሉ፡፡"
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የደቡብ ክልል ምክር ቤት ለዎላይታ ዞን የክልልነት ጥያቄ ባስቸኳይ ምላሽ ይስጥ ሲል የዎላይታ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ግንባር (ዎሕዴግ) ዛሬ በሰጠው መግለጫ በድጋሚ ጠይቋል፡፡ የክልሉ መንግሥት እና ደኢሕዴን ሕገ መንግሥታዊውን ጥያቄችን ለማዳፈን እየሠሩ ነው በማለትም ከሷል፡፡ አስቸኳይ ጊዜ አዋጁም ከዎላይታ ዞንና አካባቢው እንዲይነሳ አሳስቧል፡፡ የክልሉ ምክር ቤት ሰሞኑን ባካሄደው ጉባዔ ለየትኛውም የክልልነት ጥያቄ ምላሽ አልሰጠም፡፡
Via #DW/wazema
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via #DW/wazema
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ የ10 ሰው እና የ10 ዝሆኖች ህይወት አለፈ!
በባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ በህገ-ወጥ እርሻና ሰፈራ መስፋፋት እንዲሁም ህገ ወጥ አደን ሳቢያ የተቆጡ ዝሆኖች በ2011 14 ሰዎችን ያጠቁ ሲሆን ስድስቱ ወዲያውኑ ህይወታቸው አልፏል። ሌሎች አራት ሰዎችም በተለያየ ጊዜ በደረሰባቸው ጥቃት ህይወታቸው ሲያልፍ በተመሳሳይም አራት ግለሰቦች ከባድ የመቁሰል አደጋ ደርሶባቸዋል።
አስር ዝሆኖች በአንድ ዓመት ውስጥ ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን ከእነዚህ መካከል ሦስቱ ግልገሎች መሆናቸውን የመጠለያው ኃላፊ አደም ሞሐመድ ለአዲስ ማለዳ ጋዜጣ ገልጸዋል። ሰባቱ አዋቂ ዝሆኖችም በህገወጥ አደን ምክንያት ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን፣ ግልገሎቹ በአካባቢው በሰፈሩት ሰዎች በመረበሻቸውና ለጭንቀት በመዳረጋቸው መሞታቸውን ገልጸዋል።
Via #አዲስማለዳ_ጋዜጣ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ በህገ-ወጥ እርሻና ሰፈራ መስፋፋት እንዲሁም ህገ ወጥ አደን ሳቢያ የተቆጡ ዝሆኖች በ2011 14 ሰዎችን ያጠቁ ሲሆን ስድስቱ ወዲያውኑ ህይወታቸው አልፏል። ሌሎች አራት ሰዎችም በተለያየ ጊዜ በደረሰባቸው ጥቃት ህይወታቸው ሲያልፍ በተመሳሳይም አራት ግለሰቦች ከባድ የመቁሰል አደጋ ደርሶባቸዋል።
አስር ዝሆኖች በአንድ ዓመት ውስጥ ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን ከእነዚህ መካከል ሦስቱ ግልገሎች መሆናቸውን የመጠለያው ኃላፊ አደም ሞሐመድ ለአዲስ ማለዳ ጋዜጣ ገልጸዋል። ሰባቱ አዋቂ ዝሆኖችም በህገወጥ አደን ምክንያት ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን፣ ግልገሎቹ በአካባቢው በሰፈሩት ሰዎች በመረበሻቸውና ለጭንቀት በመዳረጋቸው መሞታቸውን ገልጸዋል።
Via #አዲስማለዳ_ጋዜጣ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"በ2012 በኦሮሚያ ክልል በህግ ከተፈቀደለት አካል ውጪ የታጠቀ ኃይል እንዳይኖር እንሰራለን" – አቶ አድማሱ
”በ2012 በኦሮሚያ ክልል በህግ ከተፈቀደለት አካል ውጪ የታጠቀ ኃይል እንዳይኖር እንሰራለን” ሲሉ የክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሃላፊ አቶ አድማሱ ዳምጠው ገለጹ። በአዲሱ አመት በሁሉም መስክ ያልተጠናቀቁ ስራዎችን ማጠናቀቅ እና የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እንደሚሰራም ጠቁመዋል።
ላለፉት አምስት ቀናት በአዳማ ከተማ ሲካሄድ የነበረው የኦሮሚያ ክልል መንግስትና የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኦዴፓ) የ2012 ዓ.ም እቅድና የምክክር መድረክ በትናንትናው እለት ተጠናቋል። ሁለት ሺህ ሰዎች የተሳተፉበትን የምክክር መድረክ በማስመልከት የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ዛሬ መግለጫ ሰጥቷል።
Via #ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
”በ2012 በኦሮሚያ ክልል በህግ ከተፈቀደለት አካል ውጪ የታጠቀ ኃይል እንዳይኖር እንሰራለን” ሲሉ የክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሃላፊ አቶ አድማሱ ዳምጠው ገለጹ። በአዲሱ አመት በሁሉም መስክ ያልተጠናቀቁ ስራዎችን ማጠናቀቅ እና የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እንደሚሰራም ጠቁመዋል።
ላለፉት አምስት ቀናት በአዳማ ከተማ ሲካሄድ የነበረው የኦሮሚያ ክልል መንግስትና የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኦዴፓ) የ2012 ዓ.ም እቅድና የምክክር መድረክ በትናንትናው እለት ተጠናቋል። ሁለት ሺህ ሰዎች የተሳተፉበትን የምክክር መድረክ በማስመልከት የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ዛሬ መግለጫ ሰጥቷል።
Via #ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በህገወጦች ላይ ተገቢውን እርምጃ ባለመውሰዱ የኑሮ ውድነት እንዲባባስ ምክንያት ሆኗል!
መንግስት በህገወጦች ላይ ተገቢውን እርምጃ በየጊዜው ባለመውሰዱ የኑሮ ውድነት እንዲባባስ ምክንያት እንደሆነ የንግድና ኢንደስትሪ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ የኑሮ ንረትን በተመለከተ ሚኒስቴር መስርያቤቱ ዛሬ ባዘጋጀው የንቅናቄ ውይይት መድረክ ላይ እንደተባለው ምንም እንኳን በመንግስት በተለያየ ጊዜ የኑሮ ውድነትን የሚያባብሱ ሰዎች ቢያዙም ተገቢ እርምጃ ባለመወሰዱ ምክንያት የኑሮ ንረቱ ገደብ አጥቷል፡፡
በመድረኩ ጥናታዊ ፅሁፍ ያቀረቡት የንግድና ኢንደስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ እሸቴ አስፋው እንዳሉት ህገ ወጦች ላይ መቀጣጫ የሚሆን እርምጃ አለመውሰዱ እንዲሁም ጠንካራ የሆነ የክትትልና ቁጥጥር ስርአት ዝርጋታባለመበጀቱ ህገወጦች እንደልባቸው እንዲሆኑ አድርጓቸዋል፡፡ እንደ ሚኒስቴር ዴኤታው ገለፃ የደላላ ጣልቃ ገብነት፣ ምርትን በክምችት መያዝ፣ ፍትሀዊ ያልሆነ የዋጋ ውድድር (የዋጋ ወሰን)፣ ያለ ደረሰኝ ግብይት ማካሄድና ፎርጅድ ደረሰኝ እንዲሁም የመግዣ ዋጋ አለማየትና የመሸጫ ዋጋ አለመለጠፍ በሀገራችን ለሚታየው ኑሮ ውድነት እንደ አብይ ምክንያት ናቸው፡፡
በሚኒስቴር ዴኤታው የዋጋ ንረቱን ለማረጋጋት በመንግስት በኩል የተለያዩ የመፍትሄ ሀሳብ ተብለው የቀረቡ ሲሆን ስንዴን ለማሰራጨት መዘጋጀቱን፣ የህብረት ስራ ማህበራት ብድር እንዲያገኙና ስራቸውን ማከናወን እንዲችሉ መደረጉን ለአብነት ጠቅሰዋል፡፡
Via #EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
መንግስት በህገወጦች ላይ ተገቢውን እርምጃ በየጊዜው ባለመውሰዱ የኑሮ ውድነት እንዲባባስ ምክንያት እንደሆነ የንግድና ኢንደስትሪ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ የኑሮ ንረትን በተመለከተ ሚኒስቴር መስርያቤቱ ዛሬ ባዘጋጀው የንቅናቄ ውይይት መድረክ ላይ እንደተባለው ምንም እንኳን በመንግስት በተለያየ ጊዜ የኑሮ ውድነትን የሚያባብሱ ሰዎች ቢያዙም ተገቢ እርምጃ ባለመወሰዱ ምክንያት የኑሮ ንረቱ ገደብ አጥቷል፡፡
በመድረኩ ጥናታዊ ፅሁፍ ያቀረቡት የንግድና ኢንደስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ እሸቴ አስፋው እንዳሉት ህገ ወጦች ላይ መቀጣጫ የሚሆን እርምጃ አለመውሰዱ እንዲሁም ጠንካራ የሆነ የክትትልና ቁጥጥር ስርአት ዝርጋታባለመበጀቱ ህገወጦች እንደልባቸው እንዲሆኑ አድርጓቸዋል፡፡ እንደ ሚኒስቴር ዴኤታው ገለፃ የደላላ ጣልቃ ገብነት፣ ምርትን በክምችት መያዝ፣ ፍትሀዊ ያልሆነ የዋጋ ውድድር (የዋጋ ወሰን)፣ ያለ ደረሰኝ ግብይት ማካሄድና ፎርጅድ ደረሰኝ እንዲሁም የመግዣ ዋጋ አለማየትና የመሸጫ ዋጋ አለመለጠፍ በሀገራችን ለሚታየው ኑሮ ውድነት እንደ አብይ ምክንያት ናቸው፡፡
በሚኒስቴር ዴኤታው የዋጋ ንረቱን ለማረጋጋት በመንግስት በኩል የተለያዩ የመፍትሄ ሀሳብ ተብለው የቀረቡ ሲሆን ስንዴን ለማሰራጨት መዘጋጀቱን፣ የህብረት ስራ ማህበራት ብድር እንዲያገኙና ስራቸውን ማከናወን እንዲችሉ መደረጉን ለአብነት ጠቅሰዋል፡፡
Via #EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#SayNoToRacism
ሮሜሎ ሉካኩ ከትላንት ምሽት የዘረኝነት ጥቃት በኋላ ያስተላለፈው መልዕክት!
"ባሳለፍነው ወር በርካታ ተጫዋቾች የዘረኝነት ጥቃት ደርሶባቸዋል። እኔም በትላንትናው ዕለት የጥቃቱ ገፈጥ ቀማሽ ሆኛለው። እግር ኳስ ሁሉም የሰው ዘር በእኩል የሚዝናናበት ጨዋታ ነው አንዱን ከሌላው ማግለል የምንወደውን ጨዋታ ዝቅ ያደርገዋል።
በሁሉም ሀገራት የሚገኙ የእግርኳስ ፌዴሬሽኖች ለእንደዚህ አይነት ማግለል ጠንከር ያለ እርምጃ ይወስዳሉ ብዬ ተስፋ አደርጋለው። የማህበራዊ ትስስር አውታሮች (ኢንስታግራም ትዊተር ፌስቡክ እና ሌሎችም ) ከእግር ኳስ ክለቦች ጋር እጅ እና ጓንት ሆነው መስራት ይጠበቅባቸዋል ምክንያቱም አብዛኛው የሚለጠፉ መልእክቶች ስር ቀለምን መሰረት ያደረገ ጥቃት ስለማይጠፋ ነው።
ክቡራት እና ክቡራን አሁን 2019 ላይ ነው የምንገኘው በዚህ የሰለጠነ ወቅት ላይ ወደፊት መሄድ ሲገባን የኋልዮሽ ጉዞውን ተያይዘነዋል ስለዚህ እኛ ኳስ ተጫዋቾች ህብረታችንን አጠንክረን የምንወደውን እግር ኳስ ንፁህ ለማድረግ አንድ አቋም ላይ መድረስ አለብን" ሮሜሎ ሉካኩ ክለቡ ኢንተርሚላንን አሸናፊ ያደረግችዋን ግብ ካስቆጠረ በኋላ በ ካግላሪ ደጋፊዋች የዘረኝነት ጥቃት ከደረሰበት በኋላ ያስተላለፈው መልዕክት።
ቲኪቫህ ኢትዮጵያ እና ቲኪቫህ ኢትዮጵያ ስፖርት ዘረኝነትን ያወግዛል።
#SayNoToRacism #TikvahEthiopiaAgainstRacism
#TikvahEthiopiaSportAgainstRacism
#RomeluLukaku
@tikvahethsport @kidusyoftahe @yidaaa
ሮሜሎ ሉካኩ ከትላንት ምሽት የዘረኝነት ጥቃት በኋላ ያስተላለፈው መልዕክት!
"ባሳለፍነው ወር በርካታ ተጫዋቾች የዘረኝነት ጥቃት ደርሶባቸዋል። እኔም በትላንትናው ዕለት የጥቃቱ ገፈጥ ቀማሽ ሆኛለው። እግር ኳስ ሁሉም የሰው ዘር በእኩል የሚዝናናበት ጨዋታ ነው አንዱን ከሌላው ማግለል የምንወደውን ጨዋታ ዝቅ ያደርገዋል።
በሁሉም ሀገራት የሚገኙ የእግርኳስ ፌዴሬሽኖች ለእንደዚህ አይነት ማግለል ጠንከር ያለ እርምጃ ይወስዳሉ ብዬ ተስፋ አደርጋለው። የማህበራዊ ትስስር አውታሮች (ኢንስታግራም ትዊተር ፌስቡክ እና ሌሎችም ) ከእግር ኳስ ክለቦች ጋር እጅ እና ጓንት ሆነው መስራት ይጠበቅባቸዋል ምክንያቱም አብዛኛው የሚለጠፉ መልእክቶች ስር ቀለምን መሰረት ያደረገ ጥቃት ስለማይጠፋ ነው።
ክቡራት እና ክቡራን አሁን 2019 ላይ ነው የምንገኘው በዚህ የሰለጠነ ወቅት ላይ ወደፊት መሄድ ሲገባን የኋልዮሽ ጉዞውን ተያይዘነዋል ስለዚህ እኛ ኳስ ተጫዋቾች ህብረታችንን አጠንክረን የምንወደውን እግር ኳስ ንፁህ ለማድረግ አንድ አቋም ላይ መድረስ አለብን" ሮሜሎ ሉካኩ ክለቡ ኢንተርሚላንን አሸናፊ ያደረግችዋን ግብ ካስቆጠረ በኋላ በ ካግላሪ ደጋፊዋች የዘረኝነት ጥቃት ከደረሰበት በኋላ ያስተላለፈው መልዕክት።
ቲኪቫህ ኢትዮጵያ እና ቲኪቫህ ኢትዮጵያ ስፖርት ዘረኝነትን ያወግዛል።
#SayNoToRacism #TikvahEthiopiaAgainstRacism
#TikvahEthiopiaSportAgainstRacism
#RomeluLukaku
@tikvahethsport @kidusyoftahe @yidaaa