TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update የመከላከያ ሠራዊት መዋቅር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ዛሬ ጸድቋል፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሪቂቅ አዋጁን ያጸደቀው በ1 ድምጸ ተዓቅቦ ነው፡፡ በአዋጁ የባህር ሃይል እና የስፔስ እና ሳይበር ዘርፎች ተካተዋል፡፡ የሠራዊቱ መኮንኖች ምልመላም ከሠራዊቱ ውጭ ጭምር እንዲሆን ይፈቅዳል፡፡ የሠራዊቱን የአገልግሎት ዘመንም አሻሽሏል፡፡ በጠቅላላው በነባሩ አዋጅ ላይ 28 አንቀጾች ማሻሻያ ተደርጎባቸዋል፡፡

Via~wazemaradio
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Fake News Alert‼️

"የመከላከያ ሰራዊት ይህንን መግለጫ #አያውቀውም።" ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ግዙፍ የመንግስት የልማት ድርጅቶችን በከፊል ወደ ግል ለማዛወር ጥናት ተጀመረ። በገንዘብ ሚኒስቴር ስር ከፍተኛ ባለሙያዎች የተካተቱበት የቴክኒካልና የስትሪንግ ኮሚቴ እንዲሁም በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የሚመራ የማክሮ ኢኮኖሚ ኮሚቴ ተቋቁሞ ወደ ስራ መገባቱም ነው የተነገረው።

@tsegabwolde
#update በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ቤተክህነት የሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት “እርቅ ይቀድማል #ሰላም ይከተላል” በሚል መርህ የአሰልጣኞች ስልጠና እየሰጠ ነው፡፡ የስልጠናው ዓላማ በህዝቦች መካከል እርቅ ለማምጣትና ሰላምን ለመጠበቅ ነው ተብሏል፡፡

Via~etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Alert‼️የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በግቢው ውስጥ ከትላንት ምሽት ጀምሮ አለመግባባት እደተፈጠረ እየገለፁ ናቸው። የሚመለከተው አካል አፋጣኝ መፍትሄ እንዲፈልግ ተማሪዎች ጥሪ እያቀረቡ ይገኛሉ።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
አዲስ አበባ‼️

በጉለሌ ክ/ከተማ በህገወጥ መንገድ ተይዘው የነበሩ 120 የቀበሌ ቤቶችና 64 ሼዶች #ለችግረኞች ተሰጡ።

ከህብረተሰቡ የተወጣጡ ከ200 በላይ አባላት ያሉት ኮሚቴ የሚደርሰውን ጥቆማ በማጥራት በህገ ወጥ መንገድ የተያዙ ቤቶችን ለማስለቀቅ እየሰራ መሆኑን የክፍለከተማው የስራ ሀላፊዎች ገልፀዋል።

የማህበረሰቡን ተጠቃሚነትና ፍትሀዊነትን ለማረጋገጥ በክፍለከተማው ከተገኙት 120 ቤቶች 53 ቤቶች በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ ነዋሪዎች የተላለፉ ሲሆን ቀሪዎቹ ቤቶች ለልማት ተነሺዎች ተሰጥተዋል።

በተመሳሳይ በክፍለ ከተማው ያላግባብ ተይዘው የነበሩ የጥቃቅንና አነስተኛ መስሪያ ቦታዎችን በማስለቀቅ ከ2009 ዓ.ም ጀምሮ ተደራጅተው በመስሪያ ቦታ እጦት ወደ ስራ ላልገቡ ወጣቶችና ሴቶች ተሰጥተዋል፡፡

በተጨማሪም ኢ-መደበኛ ነጋዴዎችን ወደ ህጋዊነት በማምጣት ለ1046 ነዋሪዎች በክፍለከተማው ባሉ 5 ሳይቶች ቦታ በማመቻቸት ወደ ስራ የሚገቡበት ሁኔታም ተመቻችቷል፡፡

ምንጭ፡- የከንቲባ ጽ/ቤት

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ሱዳን ውስጥ የዳቦና የነዳጅ ዋጋ ንሮብናል ብለው #ተቃውሞ የወጡ ዜጎች ከፖሊስ ጋር ተጋጩ። ፖሊስ ሰልፈኞቹን ለመበተን አስለቃሽ ጭስ የተጠቀመ ሲሆን፤ መንግስት አፋጣኝ ምላሽ እንደሚሰጥ ይጠበቃል።

©BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ገና!!

መሠረት የበጎ አድራጎት ድርጅት ሴቶችና ህፃናት የህይወት መሠረት ለማስያዝ የተቋቋመ ሀገር በቀል ህጋዊ ድርጅት ነው፡፡ የሞራል ስብራት የደረሰባቸው እና የኢኮኖሚ ድቀት የደረሰባቸው እናቶች ከሞራል ስብራታቸው ተላቀው እራሳቸውንና ልጆቻቸው መደገፍ እንዲችሉ ወላጅ አጥና ለችግር የተጋለጡ ህፃናት ጤናቸው ተጠብቆ ከትምህርት ገበታቸው እንዳይስተጓገሉ ለማድረግ ከፍተኛ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡

የገናን በዓል ምክንያት በማድረግ ለ 1079 ቤተሰቦች አንድ ዶሮና 6 እንቁላል በመለገስ እንደ እምነታቸዉና ፍላጎታቸው በቤታቸው እንዲያከብሩ በምናደርገው ጥረት እንድትተባበሩን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡ በኢትዮጵያ ብር 250 በአሜሪካ $10 አንድ ቤተሰብን በዓል ማዋል ይችላል፡፡

መሠረት የበጎ አድራጎት ድርጅት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000024879363 ለበለጠ መረጃ በዌብሳይት ፦www.meserethumanitarian.org
Facebook ፦ Meseret Humanitarian Organization
+251 974 43 43 43
ከተባበርን ለሌላ እንተርፋለን!!
አሳዛኝ ዜና!!!!!

ጋዜጠኛ፤ ተርጓሚ እና ደራሲ #ግርማ_ለማ ደሳለኝ ህይወታቸው አለፈ፡፡

★የቅርብ ዘመድ፤ ወገን ስለሌላቸው በማዘጋጃ ቤት ሊቀበሩ ነበር ተብሏል፡፡

በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ “እንዲህ ቢሆንስ” “ድሮና ዘንድሮ” “ሃሳብ አለኝ” የተባሉ አምዶች አዘጋጅ ነበሩ፤ የዘመን መፅሄት መስራች እና የአምድ አዘጋጅ ነበሩ፤ ከ1983 በኋላ መፅሄቶች በብዛት ለገበያ መውጣት በጀመሩበት ወቅት “አፍሮዳይት” እና “ዛቬራ” በተሰኙ መፅሄቶች ላይ በ ዋና አዘጋጅነት ሰርተዋል፡፡

በሬዲዮ ፋና በአስተዳዳሪነት ና በ አዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ ተወዳጅ የነበረውን “ታቦት ፍለጋ” በሚል ርዕስ በተከታታይ ይወጡ የነበሩ የግርሃም ኩክ ስራዎችም የእሳቸው ትርጉሞች ነበሩ፡፡

እንዲሁም አሁን ከህትመት በወጣችው ኢትዮ ቻናል ጋዜጣ ላይ በ “ማህደር” አምድ ተወዳጅ የነበረውን እና በኋላም በመፅሃፍ ታትሞ ለአንባቢ የቀረበውን “የንጉሱ ገመና” የተሰኘ ፅሁፍ እና ሌሎች ስራዎችንም ያስነበቡት አንጋፋው ጋዜጠኛ ፣ጸሃፊ፣ ደራሲና አማካሪ የነበሩት ግርማ ለማ ደሳለኝ በዛሬው እለት ህይወታቸው አልፏል፡፡

ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በህዝብ አስተዳደር በከፍተኛ ማዕረግ በዲግሪ የተመረቁት ጋሽ ግርማ “ የንጉሱ ገመና” ከተሰኘው መፅሀፍ በተጨማሪ “የካህሊል ጅብራን ምርጥ ስራዎች” የተሰኘ ትርጉም ስራ ለአንባቢ ያቀረቡ እና ለህትመት ያልበቁ አምስት ያህል የትርጉምና የራሳቸው ወጥ ስራዎች ነበሯቸው፡፡ባለሙያው ከላይ የተዘረዘሩት ሁሉ የትርፍ ሰዓትስራዎቻቸው ሲሆኑ በመደበኛነት የሂውማን ሪሶርስ ማኔጅመንት አማካሪ ነበሩ፡፡

በህይወታቸው መጨረሻ በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ሲሰሩ የነበሩ ሲሆን በጠና ታመው አልጋ ላይ ከዋሉ መቆየታቸውን የገለጹልን ምንጮቻችን በዛሬው እለት በተከራዩበት ቤት ህይወታቸው ማለፉን ተከትሎ የቅርብ ዘመድም ሆነ ወገን ስለሌላቸው አስክሬናቸው በመንግስት( ማዘጋጃ ቤት) ሊቀበር እንደነበርም ታውቋል፡፡

ጉዳዩን ከሰሙት መካከል የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ባልደረባ የሆነው ጋዜጠኛ ጌታቸው ለማ እና ባለሙያውን የሚያውቁ ጥቂት ወዳጆቹ ሁኔታውን ለፕሬስ ድርጅት እና ለ ቀድሞ ባልደረቦቹ በማሳወቅ እና በማስተባበር በመንግስት እንዳይቀበር ያደረጉ ሲሆን በነገው እለትም በ6፡00 አዲሱ ገበያ በሚገኘው እግዚአብሄር አብ ቤተክርስትያን የቀብር ስነ ስርዓቱ የሚፈጸም መሆኑን ገልጸው በሙያው ላይ ያሉ ሁሉ ለአንጋፋው ባለሙያ ሽኝት እንዲያደርግ ጠይቀዋል፡፡

ምንጭ፦ ሸገር ታይምስ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#update በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ሞያሌ ከተማ ሰሞኑን ተቀስቅሶ የነበረው ግጭት ቆሞ አሁን በአካባቢው አንፃራዊ #ሰላም መስፈኑ ተነግሯል፡፡

Via~ሸገር 102.1
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሆሳዕና‼️

በሆሳዕና ከተማ በአንድ ግለሰብ ሱቅ ውስጥ 10 ቱርክ ሰራሽ #ሽጉጦች ከ358 #ጥይቶች ጋር ተደብቀው መገኘታቸውን የሃዲያ ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።

የመምሪያው አዛዥ ኮማንደር #ደሳለኝ_ሽጉጤ ለኢዜአ እንደገለፁት ፖሊስ ህገ-ወጥ የጦር መሳሪያውን ሊይዝ የቻለው ከህብረተሰቡ በተደረገ ጥቆማ አማካኝነት ነው።

በከተማው ሴች ዱና ቀበሌ ከተያዘው የጦር መሳሪያ ጋር ባለ ሱቁን ጨምሮ እጃቸው አለበት በሚል የተጠረጠሩ አራት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ማዋላቸውንም ኮማንደሩ ተናግረዋል፡፡

ህብረተሰቡ ላከናወነው ተግባር ያመሰገኑት ኮማንደር ደሳለኝ ሰላምን የሚያደፈርስና የሚያጠራጥር መሰል ድርጊት ሲያጋጥም ለፖሊስ መጠቆሙን አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጠይቀዋል።

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia 
አሳዛኝ ዜና‼️

በደቡብ ወሎ ዞን ኮምቦልቻ ከተማ በቅርብ ርቀት በምትገኝ #ቁልቁለታማ ቦታ ላይ በደረሰ የመኪና አደጋ የሰዎች ህይወት አልፏል፡፡

50 የሚሆኑ የራማ ኮንስትራክሽን ሰራተኞች በአይስዙ መኪና ተጭነው በመጓዝ ላይ እያሉ ነው አደጋው የደረሰው፡፡

የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደርና ጸጥታ ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ኃላፊ ኮሎኔል ጌታወይ ዘገየ አደጋው አስከፊ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ከአደጋው የተረፉትን ከባድና ቀላል ጉዳት የደረሰባቸውን ሰዎች ደሴ ሪፈራል ሆስፒታል ማድረሳቸውንም ገልጸዋል፡፡

ፖሊስና የጸጥታ አካላት ስለአደጋው #አስከፊነት እንጂ ስለሟቾች ቁጥር ትክክለኛ መረጃ መስጠት እንዳልቻሉ ነው ለአብመድ የተናገሩት።

ሰራተኞቹ መደበኛ የስራ ሰርቪስ መኪና ቢኖራቸውም ዛሬ ምሽት ከስራ ገበታቸው በአይዝሱ ተጭነው ወደየቤታቸው በሚመለሱበት ወቅት አደጋ ደርሶባቸዋል፡፡ የአደጋው መንስኤ እየተጣራ ነው፡፡

ምንጭ፦ አብመድ

🔹አደጋው በደረሰበት አካባቢ የሚኖር የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባል በአደጋው እስካሁን የ20 ሰው ህይወት ሳያልፍ እንዳልቀረ ገልጿል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኮምቦልቻ‼️

በኮምቦልቻ ከተማ በትናንትናው ዕለት በደረሰ የትራፊክ አደጋ የሰባት ሰዎች ህይወት ማለፉን ፖሊስ አስታወቀ፡፡

የኮምቦልቻ ከተማ የመንገድ ደህንነት የስራ ሂደት ባለቤት ምክትል ኮማንደር ወሰን አሰፋ ለfbc እንደተናገሩት፥ በአደጋው ከሞቱት በተጨማሪ ቁጥራቸው ያልታወቁ ሰዎች ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል።

በአደጋው የሟቾቹ ቁጥር ሊጨምር እንደሚችልም ምክትል ኮማንደር ወሰን ተናግረዋል።

አደጋው ትናንት ምሽት አንድ ሰዓት ላይ ኮምቦልቻ ከተማ በተለምዶ ማርያም ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የደረሰ መሆኑንም ገልጸዋል።

አደጋው የደረሰው የቀን ሰራተኞችን አሳፍሮ ይጓዝ የነበረ የጭነት አይሱዙ መኪና በመገልበጡ መሆኑን ጠቅሰው፥ በፍጥነት ማሽከርከር የአደጋው መንስኤ መሆኑንም አስታውቀዋል።

ተሸከርካሪው በአጠቃላይ 50 ሰዎችን አሳፍሮ ይጓዝ እንደነበርም ምክትል ኮማንደሩ ጠቅሰዋል።

ምንጭ፦ fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የODP ማዕከላዊ ኮሚቴ‼️

የህዝቡን ደህንነት ለማስከበር አስፈላጊውን እርምጃ ለመውሰድ መወሰኑን የODP ማዕከላዊ ኮሚቴ ገለጸ።
.
.

የኦሮሞ ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ODP) ማዕከላዊ ኮሚቴ በወቅታዊ የጸጥታ ጉዳዮች ላይ በስፋት ከተወያየ በኋላ ውሳኔዎችን አስተላልፏል፡፡

ማንኛውም ዓይነት የፓለቲካ ፉክክሮች በጠመንጃ አፈሙዝ ሳይሆን ሰላማዊ ትግል እንዲደረግ በር ተከፍቷል፣ አገርን የዘረፉና ወንጀል የፈጸሙ ደግሞ በሕግ እንዲጠየቁ ሰፊ ስራ እየተሰራ መሆኑን የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ ገልጿል፡፡

ፓርቲው ለሰላም ቅድሚያ ሰጥቶ በትዕግስት መስራቱን እንደ ፍርሃት የቆጠሩ አካላት ኦሮሚያን የጦር አውድማ ለማድረግ እየሰሩ መሆናቸውን የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ አስታውቋል፡፡

ፓርቲው ከህዝብ ጋር በመሆን የህዝቡን ደህንነት በማረጋገጥ የተገኘውን ድል ያለ ምንም እንቅፋት እንዲቀጥል ለማድረግ ወስኗል፡፡

የሕግ የበላይነትን ለማስከበር የመንግስት ኃላፊነት ነው ያለው ማዕከላዊ ኮሚቴው፣ በህዝብ ላይ ወንጀል የፈጸሙ፣ ያስፈጸሙና ወንጀል እንዲፈጸም ሁኔታዎችን ያመቻቹ አካላት ለፍርድ የማቅረብ ስራ በፓርቲው የሚመራ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በፍጥነት እንዲያስፈጽም አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡

አሁን በአገሪቱ ውስጥ እየተወሰዱ ያሉት የለውጥ እርምጃዎችን ለማደናቀፍ እየተሰራ ያለውን ሴራ ከመሰረቱ ለመንቀል ፣ ፓርቲው የሚወስደውን እርምጃ ህዝቡ፣ ምሁራን፣ ቄሮዎችና ቀሬዎች፣ አባገዳዎችና የአገር ሽማግሌዎች እንዲደግፉት ጥሪ አቅርቧል፡፡

ምንጭ፦ etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
6 ፓርቲዎች ወደሀገር ውስጥ ገቡ‼️

ስድስት የፖለቲካ ፓርቲዎች በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ወደ ሀገር ውስጥ ገቡ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ለተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች ባደረጉት በሰላማዊ መንገድ የመታገል ጥሪ መሰረት ስድስት የተፎካካሪ ፓርቲ ወደ ሃገር ውስጥ ገብተዋል፡፡

ከውጭ ሃገር ከሰሜን አሜሪካና ከእንግሊዝ ስድስት ድርጅቶች በዛሬው ዕለት ወደ ሃገር ውስጥ ተጠቃለው መግባታቸው የኢትዮጵያ ራዕይ ፓርቲ ፕሬዝዳንት አቶ ተሻለ ሰብሮ ተናግረዋል፡፡

አክለውም ከውጭ ሃገር ከሰሜን አሜሪካና ከእንግሊዝ ስድስት ድርጅቶች በመሆን እንዲሁም ከሃገር ውስጥ አንድ ሃገር አቀፍና አንድ ክልል አቀፍ ፓርቲዎች በመሆን እስከ ውህደት የሚደርስ አብሮ ተባብሮ ለመስራት የጋራ የመግባቢያ ሰነድ ህዳር 15 ቀን 2011 ዓ.ም መፈራረማቸውን ገልጸዋል፡፡

ውህደት ለመፈጸም የተፈራረሙ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንደሚከተሉት ቀርበዋል፡፡
መድህን ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ፣ ቱሳ የኢትዮጵያ ትንሣኤ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ፣ኢትዮጵያ ህዝባዊ ንቅናቄ ፣ብሩህ ኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ ፣ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ሽግግር ምክር ቤት እና ደቡብ ኢትዮጵያ አረንጓዴ ኮኮብ ቅንጅት ወደ ሃገር ውስጥ መግባታቸውን አስተባባሪው አቶ ተሻለ ሰብሮ ገልጸዋል፡፡

ምንጭ፦ ena
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በደቡብ ክልል አማሮ ወረዳ ማንነታቸው #ያልታወቁ ታጣቂዎች በሰላማዊ ዜጎች ላይ ጥቃት ፈጽመዋል፡፡ DW እንደዘገበው በጥቃቱ 3 ሰዎች ተገድለዋል፡፡ ጥቃት አድራሾቹ በርካታ መኖሪያ ቤቶችን አቃጥለዋል፤ የእርሻ ማሳዎችን አውድመዋል፡፡ ጥቃቱ የተፈጸመው አማሮ ወረዳ ከኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ጉጅ ዞን ጋር በሚዋሰንበት አካባቢ ነው፡፡

Via~DW
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጋዜጠኛ ፍፁም‼️

በሙስና ወንጀል የተጠረጠሩት #ፍፁም_የሺጥላ በ50 ሺ ብር ዋስትና ከእስር እንዲወጡ ተወሰነ፡፡

ፖሊስ ቅሬታ አለኝ ብሎ ይግባኝ ጠይቋል፡፡ የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 10ኛ ወንጀል ችሎት ከቀድሞ የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን የስራ ሀላፊዎች ጋር በመመሳጠር 11 ሺ የአሜሪካን ዶላር እና ከአንድ ሚሊየን ብር በላይ አለአግባብ በመቀበል የተጠረጠሩትን ፍፁም የሺጥላን የዋስ መብታቸው ተከብሮ ጉዳያቸውን በውጭ ሆነው እንዲከታሉ ወስኗል፡፡

ፖሊስ በተጠርጣሪዋ ጉዳይ የሁለት ምስክሮች ቃል መቀበሉን አስረድቶ ተጨማሪ የኦዲት ስራዎችን ለማሰራት የ14 ቀናት ተጨማሪ ጊዜ እንዲሰጠው አመልክቶ ነበር፡፡

የተጠርጣሪዋ ጠበቆችም ፖሊስ ለችሎት ያቀረባቸው መርጃዎች የምርመራ ስራው መጠናቀቁን የሚያመላክቱ በመሆናቸው ተጨማሪ ቀን ሊሰጠው አይገባም ብለው ተከራክረዋል፡፡

ፍርድ ቤቱም ግራና ቀኙን አዳምጦ በ50 ሺህ ብር ዋስትና ከእስር ወጥተው በውጭ ሆነው ይከታተላሉ ብሏል፡፡

መርማሪ ፖሊስ ለተጠርጣሪዋ የዋስትና መብት መፈቃዱ ተገቢ አይደለም ብሎ ይግባኝ ጠይቋል፡፡

ምንጭ፦ ሸገር 102.1
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኦነግ‼️

የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በክልሉ ሰላም እንዲኖር ቁርጠኛ አቋም ካለው ለመነጋገር ዝግጁ መሆናቸውን የኦሮሞ ነፃነት ግንባር ሊቀመንበር አቶ #ዳውድ_ኢብሳ ተናገሩ።

የኦሮሞ ነፃነት ግንባር ሊቀመንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ በዛሬው እለት በሰጡት መግለጫ፥ ኦነግ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ስምምነት ላይ ደርሶ በህጋዊ መንገድ ለመንቀሳቀስ ወደ ሀገር ከገባ 4 ወራት መቆጠራቸውን አንስተዋል።

አቶ ዳውድ በመግለጫቸው፥ በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ ለውጥ የመጣው የኦነግ አባላት፣ የኦሮሞ ህዝብ በተለይም ደግሞ ወጣቱ በከፈለው መስዋእትነት ነው ብሎ እንደሚያምን ገልፀዋል።

ለውጡ ወደ ትክክለኛ ዴሞክራሲ እንዲሸጋገር እና ስልጣን የህዝቡ ሆኖ ህዝቡ በምርጫ ተወካዩን እንዲመርጥ እና ህዝባዊ መንግስት እንዲመሰረትም ሁሉም የበኩሉን ድርሻ ወስዶ እየሰራ መሆኑንም አንስተዋል።

ባለፉት 27 ዓመታት በኢትዮጵያ መንግስት እና በኦነግ መካከል ጦርነት ነው የነበረው፤ አሁን ግን ኢህአዴግ ለውጡን ወደ ራሱ ተቀብሎ መንቀሳቀስ በመጀመሩ ጦርነት ለማቆም ተስማምተናል ይላሉ።

የመከላከያ ሰራዊት፣ የደህንነት አገልግሎት፣ የፌደራል ፖሊስ እና የክልል ፖሊሶች ፓርቲን ሲያገለግሉ ነበር ያሉት አቶ ዳውድ፤ ከመንግስት ጋር በተደረሰው ስምምነት የፀጥታ ሀይሉ ገለልተኛ እንዲሆን የመንግስት እንጅ የፓርቲ እንዳይሆን በሚል መስማማታቸውንም ገልጸዋል።

የኦነግ ሰራዊት በፀጥታ መዋቅር እንዲካተት እና ይህንን የሚስራ ኮሚቴ እንዲቋቋም ከስምምነት እንደተደረሰም ነው አቶ ዳውድ ኢብሳ በመግለጫቸው ያነሱት።

በአሁኑ ወቅት ግን ከመንግስት ጋር የተገባው ስምምነት እየተጣሰ ነው ያሉት አቶ ዳውድ፥ በስልጠና ላይ ያሉ የኦነግ ሰራዊት በአመራር አባላት እንዲጎበኙ አለመፍቀድ አንዱ መሆኑን ጠቅሰዋል።

አቶ ዳውድ በመግለጫቸው የመከላከያ ሰራዊት የኦነግ ታጣቂዎች ባሉበት አካባቢ መስፈሩ ግጭት እንዲከሰት ምክንያት መሆኑን ጠቅሰው፥ ሰሞኑንም በምዕራብ ወለጋ በመከላከያ ሀይል እና በኦነግ ታጣቂዎች መካከል ግጭት መፈጠሩንም አንስተዋል።

አሁንም መንግስት በክልሉ ሰላም እንዲኖር ቁርጠኛ አቋም ካለው የኦሮሞ ነፃነት ግንባር ከመንግስት ጋር ለመነጋገር ዝግጁ መሆኑንም ነው ሊቀ መንበሩ አቶ ዳውድ የገለጹት።

ምርጫን በተመለከተም አቶ ዳውድ ኢብሳ፥ የቀጣዩ ምርጫ በተቀመጠለት ጊዜ እንዲካሄድ እንፈልጋለን ብለዋል።

ምንጭ፦ fbc
@tsegabwolde @tikvahethioia