TIKVAH-ETHIOPIA
ፍትህ ! ፍትህ ! ፍትህ ! " ሀኪም ህይወት እያተረፈ ፣ህይወቱን መነጠቅ የለበትም! " - ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ዶ/ር አንዷለም ዳኜ ከስራ ወደ መኖሪያ ቤቱ ሲመለስ በጥይት ተደብድቦ በመገደሉ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ እና መላው የሃገራችን ህዝቦች በተለያዩ የሚዲያ አውታሮች ፍትህን በመጠየቅ ላይ ናቸው። " ፍትህን እንሻለን ! " በሚል የፍትህ ጥያቄ ዘመቻ እየተካሄደ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል። …
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሴኔት የዶ/ር አንዱአለም ዳኘን ህልፈትን ተከትሎ ምን ውሳኔ አሳለፈ ?
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራር ከዩኒቨርሲቲው የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ አመራር አካላት ጋር የዶ/ር አንዱአለም ዳኘን ህልፈት ተከትሎ መሰራት ባለባቸው ስራዎች ዙሪያ ውይይት ማካሄዱን ገልጿል።
ውይይቱ በተለይ ቤተሰቦቹ ሊደገፉ በሚችሉባቸውና ሃኪሙ በህይዎት ዘመኑ ያከናወናቸው ልዩ ሙያዊ አስተዋጽኦችን መዘከር በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ትኩረት ያደረገ ነው።
ዶ/ር አንዱአለም ምንም እንኳን የተሰጠውን ጸጋ ሳይሰስት በመጠቀም ለበርካቶች የዘርፉ ባለሙያዎችና በሙያው ላገለገላቸው በርካታ ህሙማን የቅን አገልጋይነት ተምሳሌት የነበረ እንቁ ባለሙያ ቢሆንም ገና በ37 ዓመቱ የተቀጠፈ በመሆኑ ለህጻናት ልጆቹና ቤተሰቡ ትቶ ያለፈው ቤትም ሆነ ሌላ ንብረት የሌለው መሆኑ ተገልጿል።
የቀረቡለትን በርካታ ዓለምአቀፍ የስራ ቅጥር ግብዣዎች ባለመቀበል ወገኑን ለማገልገል ቆርጦ የነበረ ባለሙያ ከመሆኑም በላይ በጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በቀዶ ጥገና ክፍል የነበረውን ልዩ አበርክቶና የቀዶ ጥገና ክፍሉን ደረጃውን በጠበቀ መልኩ ለማሻሻል እየጣረ የነበረ እና እውን ለማድረግ ጫፍ ላይ ደርሶ ያለፈ መሆኑ በውይይቱ ተነስቷል።
ከሁሉም በላይ ደግሞ የነበረውን ሞያዊ አቅም ተጠቅሞ ራሱን ለተገልጋዮች በቅንነት ሰጥቶ ያለፈ ታላቅ ባለሙያ እንደነበረ የስራ ባልደረቦቹ ፣ተማሪዎቹ እና አገልግሎቱን ያገኙ ደምበኞቹ የሚመሰክሩለት ድንቅ ሃኪም የነበረ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አመልክቷል።
በመሆኑም ፦
➡ የዶ/ር አንዱአለም ልጆች ለከፍተኛ ትምህርት ሲደርሱ በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ በነጻ እንዲማሩ፤
➡ ባለቤቱ ከትምህርት ዝግጅት አንጻር በሲቪል ምህንድስና 2ኛ ዲግሪ ያላት እና ጥሩ አቅም ያላት በመሆኑ በዩኒቨርሲቲው የባሕር ዳር ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በሲቪል ምህንድስና ትምህርት ክፍል የምትቀጠርበት ሁኔታ እንዲመቻች፤
➡ ዶ/ር እንዱአለም በጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ታሪክ የመጀመሪያውን ቀዶ ጥገና የሰራው እሱ በመሆኑና ክፍሉን እስከ ህልፈቱ ድረስ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ ለማሳደግ ከፍተኛ ጥረት ሲያደርግ የነበረ በመሆኑ የጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የቀዶ ጥገና ዋርድ በስሙ ዶ/ር አንዱአለም ዳኘ ቀዶ ጥገና ዋርድ ተብሎ እንዲሰየም፤
➡ የዶ/ር አንዱአለምን የአገልጋይነት ጥግ እንዲሁም ለሙያው የተሰጠ ተምሳሌታዊነቱን በቋሚነት ለመዘከርና ማስተማሪያ እንዲሆን በጥበበ ጊዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ግቢ ሃውልት እንዲቆምለት፤
➡ በህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጁ School of Medicine ውስጥ በስሙ BDU Talent Scholarship እንዲቋቋም፤
➡ ለ40ኛ ቀኑ መታሰቢያ የሚደርስ ስለ ዶ/ር አንዱአለም የህይዎት ታሪክ የሚዳስስ መጣጥፍ እንዲዘጋጅ ዩኒቨርሲቲው ወስኗል።
ውሳኔው ለዩኒቨርሲቲው ሴኔት ቀርቦ በሙሉ ድምጽ ጸድቋል፡፡
#BDU
@tikvahethiopia
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራር ከዩኒቨርሲቲው የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ አመራር አካላት ጋር የዶ/ር አንዱአለም ዳኘን ህልፈት ተከትሎ መሰራት ባለባቸው ስራዎች ዙሪያ ውይይት ማካሄዱን ገልጿል።
ውይይቱ በተለይ ቤተሰቦቹ ሊደገፉ በሚችሉባቸውና ሃኪሙ በህይዎት ዘመኑ ያከናወናቸው ልዩ ሙያዊ አስተዋጽኦችን መዘከር በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ትኩረት ያደረገ ነው።
ዶ/ር አንዱአለም ምንም እንኳን የተሰጠውን ጸጋ ሳይሰስት በመጠቀም ለበርካቶች የዘርፉ ባለሙያዎችና በሙያው ላገለገላቸው በርካታ ህሙማን የቅን አገልጋይነት ተምሳሌት የነበረ እንቁ ባለሙያ ቢሆንም ገና በ37 ዓመቱ የተቀጠፈ በመሆኑ ለህጻናት ልጆቹና ቤተሰቡ ትቶ ያለፈው ቤትም ሆነ ሌላ ንብረት የሌለው መሆኑ ተገልጿል።
የቀረቡለትን በርካታ ዓለምአቀፍ የስራ ቅጥር ግብዣዎች ባለመቀበል ወገኑን ለማገልገል ቆርጦ የነበረ ባለሙያ ከመሆኑም በላይ በጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በቀዶ ጥገና ክፍል የነበረውን ልዩ አበርክቶና የቀዶ ጥገና ክፍሉን ደረጃውን በጠበቀ መልኩ ለማሻሻል እየጣረ የነበረ እና እውን ለማድረግ ጫፍ ላይ ደርሶ ያለፈ መሆኑ በውይይቱ ተነስቷል።
ከሁሉም በላይ ደግሞ የነበረውን ሞያዊ አቅም ተጠቅሞ ራሱን ለተገልጋዮች በቅንነት ሰጥቶ ያለፈ ታላቅ ባለሙያ እንደነበረ የስራ ባልደረቦቹ ፣ተማሪዎቹ እና አገልግሎቱን ያገኙ ደምበኞቹ የሚመሰክሩለት ድንቅ ሃኪም የነበረ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አመልክቷል።
በመሆኑም ፦
➡ የዶ/ር አንዱአለም ልጆች ለከፍተኛ ትምህርት ሲደርሱ በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ በነጻ እንዲማሩ፤
➡ ባለቤቱ ከትምህርት ዝግጅት አንጻር በሲቪል ምህንድስና 2ኛ ዲግሪ ያላት እና ጥሩ አቅም ያላት በመሆኑ በዩኒቨርሲቲው የባሕር ዳር ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በሲቪል ምህንድስና ትምህርት ክፍል የምትቀጠርበት ሁኔታ እንዲመቻች፤
➡ ዶ/ር እንዱአለም በጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ታሪክ የመጀመሪያውን ቀዶ ጥገና የሰራው እሱ በመሆኑና ክፍሉን እስከ ህልፈቱ ድረስ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ ለማሳደግ ከፍተኛ ጥረት ሲያደርግ የነበረ በመሆኑ የጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የቀዶ ጥገና ዋርድ በስሙ ዶ/ር አንዱአለም ዳኘ ቀዶ ጥገና ዋርድ ተብሎ እንዲሰየም፤
➡ የዶ/ር አንዱአለምን የአገልጋይነት ጥግ እንዲሁም ለሙያው የተሰጠ ተምሳሌታዊነቱን በቋሚነት ለመዘከርና ማስተማሪያ እንዲሆን በጥበበ ጊዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ግቢ ሃውልት እንዲቆምለት፤
➡ በህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጁ School of Medicine ውስጥ በስሙ BDU Talent Scholarship እንዲቋቋም፤
➡ ለ40ኛ ቀኑ መታሰቢያ የሚደርስ ስለ ዶ/ር አንዱአለም የህይዎት ታሪክ የሚዳስስ መጣጥፍ እንዲዘጋጅ ዩኒቨርሲቲው ወስኗል።
ውሳኔው ለዩኒቨርሲቲው ሴኔት ቀርቦ በሙሉ ድምጽ ጸድቋል፡፡
#BDU
@tikvahethiopia
📣 የ Jasiri Talent Investor Fully-Funded Program ተመልሷል
ባለሽበት የስራ መስክ በቂ የሆነ ችሎታ ካለሽ፣ አዲስ እና በፍጥነት የማደግ አቅም ያለው ተቋም የመመስረት ፍላጎት ካለሽ፣ እንዲሁም ችግር የመፍታትና ተጽዕኖ የመፍጠር ብቃት ካለሽ ይህ ዕድል ላንቺ ነው።
ሙሉ ወጪሽ ተሸፍኖ በሩዋንዳ የ 3 ወር ስልጠና፤ የቢዝነስ መነሻ፤ ቢዝነሱ እስኪቋቋም ለተወሰኑ ወራት የሚያቆይ የኪስ ገንዘብ የሚታገኚበት፤ ስልጠናሽን ጨርሰሽ ወደ ኢትዮጵያ ስትመለሺ ለተወሰነ ግዜ የምትጠቀሚበት የጋራ ቢሮ (co-working space) ተመቻችቷል።
8ኛው ዙር ለመቀላቀል፣ ዛሬውኑ ተመዝገቢ!
👉 https://bit.ly/40Ai4oR
ለበልጠ መረጃ @jasiri4Africa
ባለሽበት የስራ መስክ በቂ የሆነ ችሎታ ካለሽ፣ አዲስ እና በፍጥነት የማደግ አቅም ያለው ተቋም የመመስረት ፍላጎት ካለሽ፣ እንዲሁም ችግር የመፍታትና ተጽዕኖ የመፍጠር ብቃት ካለሽ ይህ ዕድል ላንቺ ነው።
ሙሉ ወጪሽ ተሸፍኖ በሩዋንዳ የ 3 ወር ስልጠና፤ የቢዝነስ መነሻ፤ ቢዝነሱ እስኪቋቋም ለተወሰኑ ወራት የሚያቆይ የኪስ ገንዘብ የሚታገኚበት፤ ስልጠናሽን ጨርሰሽ ወደ ኢትዮጵያ ስትመለሺ ለተወሰነ ግዜ የምትጠቀሚበት የጋራ ቢሮ (co-working space) ተመቻችቷል።
8ኛው ዙር ለመቀላቀል፣ ዛሬውኑ ተመዝገቢ!
👉 https://bit.ly/40Ai4oR
ለበልጠ መረጃ @jasiri4Africa
TIKVAH-ETHIOPIA
#መቄዶንያ “ ህንፃው ለማጠናቀቅ ገንዘብ ተቸግረናል። ለማጠናቀቅ ወደ 5 ቢሊዮን ብር ያስፈልገናል ” - መቄዶንያ መቄዶንያ የአረጋዊያንና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል በሚያስገነባው ሆስፒታል ጭምር ያለው ህንፃ ለማጠናቀቅ የገንዘብ እጥረት ስለገጠመው እርዳታ እንዲያደርግ ጥሪ አቀረበ። ከየካቲት 1 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ “ በሰይፉ ኢቢኤስ የዩቱብ ቻነል ” ድጋፍ ማድረጊያ መርሀ ግብር ስለሚጀመር…
“ ለአእምሮ ህሙማን ብቻ በየወሩ እስከ 5 ሚሊዮን ብር መድኃኒት እንገዛለን። የህክምና ባለሙዎች እጥረት አለብን ” - የመቄዶኒያ ህክምና ክፍል
የመቄዶንያ አረጋዊያንና የአእምሮ ህሙማን መረጃ ማዕከል ህክምና ክፍል የመድኃኒት መወደድና የስፔሻሊት ሀኪሞች እጥረት እንደፈተነው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።
የማዕከሉ የህክምና ክፍል አስተባባሪ አቶ ዮናስ ሙሉጌታ በሰጡን ቃል፤ ገንዘብ ያለው በገንዘቡ፣ እውቀት ያለው በእውቀቱ፣ ጳጳሳቱ በጸሎታቸው እርዳታ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።
የማዕከሉ ህክምና ክፍል በዝርዝር ምን አለ?
“በመቄዶንያ ካሉት 8,000 ሰዎች ወደ 2000 የሚሆኑት የአእምሮ ህሙማን ናቸው። የአእምሮ ህሙማኑ መድኃኒቶች ደግሞ ብዙ ጊዜ አገር ውስጥ አይገኙም።
ቢኖሩም ውስን ፋብሪካዎች ናቸው የሚያመርቷቸው ጥሬ እቃ ከውጪ አገር እያስመጡ። የተወሰኑ መድኃኒቶችም በቀጥታ ከውጪ አገር ነው የሚመጡት።
ከገበያ የሚጠፉ መድኃኒቶችም አሉ ከምንዛሪ እጥረት ጋር በተያያዘ። መድኃኒቶቹ መጥፋታቸው ህሙማኑ ህመሙ እንዲያርሽባቸው ይዳርጋቸዋል። ወደ ጤንነታቸው ለመመለስም ጊዜ ይወዳል።
አዲስ አበባ፣ ሰንዳፋ፣ ፃድቃኔ፣ ሶማሌ ክልል ጎዴ፣ አማራ ክልል ደሴ፣ ሀረር፣ ድሴዳዋ በብዛት የአእምሮ ህሙማን የሚገኙባቸው ቦታዎች ናቸው።
በመቄዶንያ ደግሞ የአእምሮ ህሙማንና አረጋዊያን ብቻ ሳይሆኑ ያሉት የደም ግፊት፣ ስኳር፣ አስም፣ ካንሰር፣ የኩላሊት (ዲያሌሲስ የሚያደርጉ) ህሙማንም አሉ።
የአእምሮ ህሙማን መድኃኒቶች በጣም ውድ ናቸው። የምንገዛው ከኢትዮጵያ መድኃኒት አቅርቦት አገልግሎት ነው። ለአእምሮ ህሙማን ብቻ በየወሩ እስከ 5 ሚሊዮን ብር እንገዛለን። የህክምና ባለሙያዎች እጥረት አለብን” ብሏል።
“ካለው ቁጥር አንጻር የባለሙያዎች ቁጥር በቂ አይደለም። ሳይካትሪ እንኳ ወደ 18 ነው የሚሆኑት። ግን ስፔሻሊስቶች ያስፈልጉናል። ባለሙያዎች በበጎ ፈቃደኝነት እንዲያገለግሉ እንፈልጋለን” ሲልም ጥሪ አቅርቧል።
“በወር ለአንድ እንኳ ሰዓት የህክምና አገልግሎት ቢሰጡ ለህሙማኑ ቀላል አይደለም” ያሉት የህክምና ክፍሉ፣ “የአእምሮ ስፔሻሊቲ፣ የዓይን፣ የጥርስ፣ የፊዚዮትራፒ፣ የሳይኮሎጁ ባለሙያዎች እጥረት አለብን” ብለዋል።
በሙያቸው ወደ ውጪ አገር ሂደው በትላልቅ የህክምና ተቋማት፣ ፋብሪካዎች የሚሰሩ ወገኖች መድኃኒት ቢልኩላቸው መቄዶንያ በህጋዊ መንገድ ፕሮሰስ አድርጎ መቀበል እንደሚችል፣ ድጋፉ ቢገኝ ህሙማን ሳያቋርጡ ህክምናቸውን መከታተል እንደሚችሉ ተመልክቷል።
#ማስታወሻ : የካቲት 1 ቀን 2017 ዓ/ም በSiefu Show Tube ላይ ድጋፍ ለማድረግ ይዘጋጁ።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የመቄዶንያ አረጋዊያንና የአእምሮ ህሙማን መረጃ ማዕከል ህክምና ክፍል የመድኃኒት መወደድና የስፔሻሊት ሀኪሞች እጥረት እንደፈተነው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።
የማዕከሉ የህክምና ክፍል አስተባባሪ አቶ ዮናስ ሙሉጌታ በሰጡን ቃል፤ ገንዘብ ያለው በገንዘቡ፣ እውቀት ያለው በእውቀቱ፣ ጳጳሳቱ በጸሎታቸው እርዳታ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።
የማዕከሉ ህክምና ክፍል በዝርዝር ምን አለ?
“በመቄዶንያ ካሉት 8,000 ሰዎች ወደ 2000 የሚሆኑት የአእምሮ ህሙማን ናቸው። የአእምሮ ህሙማኑ መድኃኒቶች ደግሞ ብዙ ጊዜ አገር ውስጥ አይገኙም።
ቢኖሩም ውስን ፋብሪካዎች ናቸው የሚያመርቷቸው ጥሬ እቃ ከውጪ አገር እያስመጡ። የተወሰኑ መድኃኒቶችም በቀጥታ ከውጪ አገር ነው የሚመጡት።
ከገበያ የሚጠፉ መድኃኒቶችም አሉ ከምንዛሪ እጥረት ጋር በተያያዘ። መድኃኒቶቹ መጥፋታቸው ህሙማኑ ህመሙ እንዲያርሽባቸው ይዳርጋቸዋል። ወደ ጤንነታቸው ለመመለስም ጊዜ ይወዳል።
አዲስ አበባ፣ ሰንዳፋ፣ ፃድቃኔ፣ ሶማሌ ክልል ጎዴ፣ አማራ ክልል ደሴ፣ ሀረር፣ ድሴዳዋ በብዛት የአእምሮ ህሙማን የሚገኙባቸው ቦታዎች ናቸው።
በመቄዶንያ ደግሞ የአእምሮ ህሙማንና አረጋዊያን ብቻ ሳይሆኑ ያሉት የደም ግፊት፣ ስኳር፣ አስም፣ ካንሰር፣ የኩላሊት (ዲያሌሲስ የሚያደርጉ) ህሙማንም አሉ።
የአእምሮ ህሙማን መድኃኒቶች በጣም ውድ ናቸው። የምንገዛው ከኢትዮጵያ መድኃኒት አቅርቦት አገልግሎት ነው። ለአእምሮ ህሙማን ብቻ በየወሩ እስከ 5 ሚሊዮን ብር እንገዛለን። የህክምና ባለሙያዎች እጥረት አለብን” ብሏል።
“ካለው ቁጥር አንጻር የባለሙያዎች ቁጥር በቂ አይደለም። ሳይካትሪ እንኳ ወደ 18 ነው የሚሆኑት። ግን ስፔሻሊስቶች ያስፈልጉናል። ባለሙያዎች በበጎ ፈቃደኝነት እንዲያገለግሉ እንፈልጋለን” ሲልም ጥሪ አቅርቧል።
“በወር ለአንድ እንኳ ሰዓት የህክምና አገልግሎት ቢሰጡ ለህሙማኑ ቀላል አይደለም” ያሉት የህክምና ክፍሉ፣ “የአእምሮ ስፔሻሊቲ፣ የዓይን፣ የጥርስ፣ የፊዚዮትራፒ፣ የሳይኮሎጁ ባለሙያዎች እጥረት አለብን” ብለዋል።
በሙያቸው ወደ ውጪ አገር ሂደው በትላልቅ የህክምና ተቋማት፣ ፋብሪካዎች የሚሰሩ ወገኖች መድኃኒት ቢልኩላቸው መቄዶንያ በህጋዊ መንገድ ፕሮሰስ አድርጎ መቀበል እንደሚችል፣ ድጋፉ ቢገኝ ህሙማን ሳያቋርጡ ህክምናቸውን መከታተል እንደሚችሉ ተመልክቷል።
#ማስታወሻ : የካቲት 1 ቀን 2017 ዓ/ም በSiefu Show Tube ላይ ድጋፍ ለማድረግ ይዘጋጁ።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
“ ‘እስካሁን የተፋጠነ ምላሽ አላገኘንም' እያሉ ያሉ በችሎት ሁሌ ነው የሚያነሱት፤ በኛ እምነትም የተፋጠነ ፍትህ እያገኙ አይደለም ” - የእነ አቶ ክርስቲያን ጠበቃ እነ አቶ ክርስቲያን ታደለ እና አቶ ዮሐንስ ቧያለድ ትላንት የችሎት ቀጠሮ ነበራቸው። ጉዳዩን የሚከታተሉ የቅርብ ሰዎች፣ “የእምነት ክህደት ቃል ለመስጠት ነበር ትላንት ተዘጋጅተው የሄዱት ግን ያ ሳይሆን ቀርቷል” ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ…
" ፍትህ የለም እንጂ ፍትህ ካለ እኔ ነጻ ሰው ነኝ። ፍርድ ቤት በነጻ ለቆ ለደረሰብኝ በደል ሁሉ ካሳ ሊያሰጠኝ በቻለ ነበር " - አቶ ዮሐንስ ቧያለው
እነ አቶ ዮሐንስ ቧያለው እና አቶ ክርስቲያን ታደለ ዛሬ ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ህገ መንግስትና የሽብር ወንጀል ችሎት በረበባቸው ክስ የእምነት ክህደት ቃል መስጠታቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከደረሰው የሰነድ ማስረጃ ለማወቅ ችሏል።
አቶ ዮሐንስ ቧያለው በሰጡት የእምነት ክህደት ቃል፣ " የቀረበብኝን ውንጀላና አሉባልታ አልቀበልም። ወንጀልም አልፈጸምኩም " ማለታቸውን ሰነዱ ያወሳል።
አክለው፣ " ፍትህ የለም እንጂ ፍትህ ካለ እኔ ነጻ ሰው ነኝ። ፍርድ ቤት በነጻ ለቆ ለደረሰብኝ በደል ሁሉ ካሳ ሊያሰጠኝ በቻለ ነበር። ግን እንዴት ሆኖ/ ራሱ ነጻ ያልሆነ ማንን ሊያደርግ ይችላል " ነው ያሉት።
የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ በ18/07/2016 ዓ/ም በስማቸው በሚጠራው መዝገብ ላይ ያቀረበውን ክስ " ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት የለውም " ሲሉ ውድቅ አድርገውታል።
የተቃውሟቸውን ምክንያት የገለጹበት ሰነድ፣ " ሁሉም የክስ ጭብጦች በፈጠራ ተሞሉ ናቸው " ይላል።
የክስ ጭብጡ፣ " ‘የሽብር ቡድን አመራር በመሆን፣ አባል በመሆን፣ ራሱን በመሰየም፣ በማደረጃት፣ የሰራተኛ ሰነድ በማዘጋጀትና ጽንፈኛ ፋኖን በመምራት የሽብር ወንጀል ፈፅሟል’ ይላል " ሲሉ አስረድተዋል በሰነዳቸው።
ዮሐንስ በሰጡት የእምነት ክህደት ቃል፣ " የተጠቀሰው ሀሳብ በአንድ በኩል መረጃ አልባና ከእውነት የራቀ ሲሆን፣ በሌላ መልኩ ደግሞ የአንድን የህዝብ ባህላዊ ተቋም ለመክሰስ የሞከረ ሆኖ አግኝቼዋለሁ " ሲሉ ወንጅለዋል።
" መረጃ አልባነቱን " ጭምር በገለጹበት ሰነድ አቶ ዮሐንስ ምን አሉ ?
“ በኢፌድሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተሰየመ አሸባሪ ቡድን ማን እንደሆነ፣ በዚህ ቡድን ላይ የእኔ ኃላፊነትና የፈጸምኩት ወንጀል ምን እንደሆነ ከመግለጽ ይልቅ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ራሱ በጭንቅላቱ የፈጠረው ‘አሸባሪና ጽንፈኛ ቡድን አመራርና አባል ነው’ የሚል የፈጠራ ድርሰት መቅረቡ ነው።
በአንጻሩ አንድን የህዝብ ባህላዊ ተቋም ፍትህ ሚኒስቴር (ጠቅላይ አቃቢ ህግ) በአዋጅ ከተሰጠው ስልጣን በመተላለፍና በደመኝነት መንፈስ ‘አሸባሪ’ ብሎ መሰየሙ ነው።
ፋኖ የአማራ ህዝብ ተቋም ሆኖ እያለ የፋኖ አመራርና አባል የሆኑ ሰዎች አሸባሪ ናቸው ብሎ መክሰስ ህዝቡን እንደ ህዝብ ከመክሰሱም በላይ ለአማራ ህዝብ ተቋሙ ያሳየውን ንቀት የሚያረጋግጥ ሆኖ አግኝቼዋለሁ።
የአማራ ጠላት የሆነው ዘረኛው ስርዓትም ይሁን በመሳሪያነት እያገለገለ ያለው ጠቅላይ አቅቢ ህግ ሊያውቁት የሚገባ ጉዳይ ቢኖር ሁሉም አማራ ፋኖ መሆኑን ነው። የእኔ ‘ፋኖ’ መሆንም በቀጥታ ከአማራነቴ ጋር የተያያዘ ነው።
ሲወርድ ሲዋረድ የመጣው መላው የአማራ ህዝብ እስካሁን ድረስ ምናአልባትም በጉዲፈቻና በሞጋሳ ከተሸጡት ጥቂት የአብይ አህመድ ቡድን የሆኑ የካቢኔ አባላት ውጪ ሁሉም አማራ ፋኖ እንደሆነ ሁሉ እኔም በፋኖነቴ አላፍርም። እኮራለሁ እንጂ !
ቄሮነትና አባገዳነት ወንጀል እንዳልሆነው ሁሉ ፋኖነትን መንካት በአንድ ህዝብ ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ከመሆኑም በላይ ምንጊዜም ቢሆን በማንነቴ ላይ የሚመጣን ጥቃት እንደ ባንዳዎችና በጉዲፈቻ እንደተሸጡ የስራዓቱ (የብልጽግና ቡድን) አባላት ዝም ብዩ ልቀበለው እንደማልችል በድጋሚ ላረጋግጥ እወዳለሁ።
ፋኖነት ወንጀል ሳይሆይን በክብር የሚሰውለት አማራዊነት ነው " ብለዋል።
አቶ ዮሐንስ ቧያለው ሙሉ የእምነት ክህደት ቃል ገለጻ የያዘው ሰነድ ከላይ የተያያዘ ሲሆን የአቶ ክርስቲያን ታደለ የእምነት ክህደት ቃል ደግሞ በቀጣይ ይቀርባል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
እነ አቶ ዮሐንስ ቧያለው እና አቶ ክርስቲያን ታደለ ዛሬ ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ህገ መንግስትና የሽብር ወንጀል ችሎት በረበባቸው ክስ የእምነት ክህደት ቃል መስጠታቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከደረሰው የሰነድ ማስረጃ ለማወቅ ችሏል።
አቶ ዮሐንስ ቧያለው በሰጡት የእምነት ክህደት ቃል፣ " የቀረበብኝን ውንጀላና አሉባልታ አልቀበልም። ወንጀልም አልፈጸምኩም " ማለታቸውን ሰነዱ ያወሳል።
አክለው፣ " ፍትህ የለም እንጂ ፍትህ ካለ እኔ ነጻ ሰው ነኝ። ፍርድ ቤት በነጻ ለቆ ለደረሰብኝ በደል ሁሉ ካሳ ሊያሰጠኝ በቻለ ነበር። ግን እንዴት ሆኖ/ ራሱ ነጻ ያልሆነ ማንን ሊያደርግ ይችላል " ነው ያሉት።
የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ በ18/07/2016 ዓ/ም በስማቸው በሚጠራው መዝገብ ላይ ያቀረበውን ክስ " ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት የለውም " ሲሉ ውድቅ አድርገውታል።
የተቃውሟቸውን ምክንያት የገለጹበት ሰነድ፣ " ሁሉም የክስ ጭብጦች በፈጠራ ተሞሉ ናቸው " ይላል።
የክስ ጭብጡ፣ " ‘የሽብር ቡድን አመራር በመሆን፣ አባል በመሆን፣ ራሱን በመሰየም፣ በማደረጃት፣ የሰራተኛ ሰነድ በማዘጋጀትና ጽንፈኛ ፋኖን በመምራት የሽብር ወንጀል ፈፅሟል’ ይላል " ሲሉ አስረድተዋል በሰነዳቸው።
ዮሐንስ በሰጡት የእምነት ክህደት ቃል፣ " የተጠቀሰው ሀሳብ በአንድ በኩል መረጃ አልባና ከእውነት የራቀ ሲሆን፣ በሌላ መልኩ ደግሞ የአንድን የህዝብ ባህላዊ ተቋም ለመክሰስ የሞከረ ሆኖ አግኝቼዋለሁ " ሲሉ ወንጅለዋል።
" መረጃ አልባነቱን " ጭምር በገለጹበት ሰነድ አቶ ዮሐንስ ምን አሉ ?
“ በኢፌድሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተሰየመ አሸባሪ ቡድን ማን እንደሆነ፣ በዚህ ቡድን ላይ የእኔ ኃላፊነትና የፈጸምኩት ወንጀል ምን እንደሆነ ከመግለጽ ይልቅ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ራሱ በጭንቅላቱ የፈጠረው ‘አሸባሪና ጽንፈኛ ቡድን አመራርና አባል ነው’ የሚል የፈጠራ ድርሰት መቅረቡ ነው።
በአንጻሩ አንድን የህዝብ ባህላዊ ተቋም ፍትህ ሚኒስቴር (ጠቅላይ አቃቢ ህግ) በአዋጅ ከተሰጠው ስልጣን በመተላለፍና በደመኝነት መንፈስ ‘አሸባሪ’ ብሎ መሰየሙ ነው።
ፋኖ የአማራ ህዝብ ተቋም ሆኖ እያለ የፋኖ አመራርና አባል የሆኑ ሰዎች አሸባሪ ናቸው ብሎ መክሰስ ህዝቡን እንደ ህዝብ ከመክሰሱም በላይ ለአማራ ህዝብ ተቋሙ ያሳየውን ንቀት የሚያረጋግጥ ሆኖ አግኝቼዋለሁ።
የአማራ ጠላት የሆነው ዘረኛው ስርዓትም ይሁን በመሳሪያነት እያገለገለ ያለው ጠቅላይ አቅቢ ህግ ሊያውቁት የሚገባ ጉዳይ ቢኖር ሁሉም አማራ ፋኖ መሆኑን ነው። የእኔ ‘ፋኖ’ መሆንም በቀጥታ ከአማራነቴ ጋር የተያያዘ ነው።
ሲወርድ ሲዋረድ የመጣው መላው የአማራ ህዝብ እስካሁን ድረስ ምናአልባትም በጉዲፈቻና በሞጋሳ ከተሸጡት ጥቂት የአብይ አህመድ ቡድን የሆኑ የካቢኔ አባላት ውጪ ሁሉም አማራ ፋኖ እንደሆነ ሁሉ እኔም በፋኖነቴ አላፍርም። እኮራለሁ እንጂ !
ቄሮነትና አባገዳነት ወንጀል እንዳልሆነው ሁሉ ፋኖነትን መንካት በአንድ ህዝብ ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ከመሆኑም በላይ ምንጊዜም ቢሆን በማንነቴ ላይ የሚመጣን ጥቃት እንደ ባንዳዎችና በጉዲፈቻ እንደተሸጡ የስራዓቱ (የብልጽግና ቡድን) አባላት ዝም ብዩ ልቀበለው እንደማልችል በድጋሚ ላረጋግጥ እወዳለሁ።
ፋኖነት ወንጀል ሳይሆይን በክብር የሚሰውለት አማራዊነት ነው " ብለዋል።
አቶ ዮሐንስ ቧያለው ሙሉ የእምነት ክህደት ቃል ገለጻ የያዘው ሰነድ ከላይ የተያያዘ ሲሆን የአቶ ክርስቲያን ታደለ የእምነት ክህደት ቃል ደግሞ በቀጣይ ይቀርባል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
“ በአጠቃላይ አቃቢ ህግ በእኔ ላይ መስርቶ ባቀረበው ክስ ላይ የተገለጸውን ወንጀል አልፈጸምኩም” - አቶ ክርስቲያን ታደለ
እነአቶ ክርስቲያን ታደለ ዛሬ ችሎት ቀርበው የእምነት ክህደት ቃል መስጠታቸውን ጉዳዩን ከሚከታተሉ ሰዎችና ቃላቸውን ካቀረበበት ሰነድ መረዳት ትችሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው አቶ ክርስቲያን የእምነት ክህደት ቃል የሰጡበት ሰነድ፣ “በአጠቃላይ አቃቢ ህግ በእኔ ላይ መስርቶ ባቀረበው ክስ ላይ የተገለጸውን ወንጀል አልፈጸምኩም። ጥፋተኛም አይደለሁም” ይላል።
አቶ ክርስቲያን በሰጡት የእምነት ክህደት ቃል ምን አሉ?
“ለ550 ቀናትም በግፍና ጭካኔ እገታ ውስጥ የምገኘው ለአንዲት ደቂቃ እንኳን በጥፋተኝነት የሚያስቀጣ አንዳችም የወንጀል ድርጊት የሚያቋቁም የህግ መተላለፍ ስለፈጸምኩ አይደለም። የአማራ ሕዝብ የሚያነሳቸውን የህልውና ጥያቄዎች በይፋ በማቅረቤ፣ በሕዝቤ የሚደርሰውን ግፍ፣ በደል በማስረጃ በመሞገቴ፣ የገዢውን ፓርቲ አፈናና የመንግስት አሰራሮችንና አመራሮችን ብልሹነትና ዘረፋ በመታገሌ ነው ” ብለዋል።
“ ተደጋጋሚ የአመራር ብልሹነት ባሳዩ አካላትም የወንጀልና የፍትሃብሔር ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ ክስ እንዲመሰረት ፍትህ ሚኒስቴር አዝዥለው ” የሚሉና ሌሎች ድርጊቶችን በአደባባይ እንደታገሉ ገልጸዋል።
“ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ ሌሎች የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች በአሰራራቸው የፋይናንስ ገልጸኝነትና ህጋዊነት እንዲከተሉና እንዲረጋገጡ እንዲሁም ኦዲት ለመደረግ ፈቃደኝነታቸውን እንዲያረጋግጡ ጠይቄከለሁ ” ነው ያሉት።
እነዚህን ጥያቄዎች እንዳልጠይቅ አንዳንድ አመራሮች ለማግባባት እንደሞከሩ ገልጸው፣ “ አንዳንዶቹም ሊገድሉኝ፣ ሊያስሩኝና አንዳች ነገር ሊያደርሱብኝ እንደሚችሉ ጭምር ነግረውኛል፤ መልዕክትም አድርሰውኛል ” ብለዋል።
“ አንዳች ወንጀል አልፈጸምኩም ” ያሉት ክርስቲያን፣ “ ይህን በተመለከተ ከክሱ ይዘት ብቻ ሳይሆን በራሴ መንገድ ይህን ክስ ተዘጋጅቶ እንዲቀርብብኝ ካደረገው አካል ዘንድም አረጋግጫለሁ ” ሲሉ አስረድተዋል።
“ እኔ አማራ የሆንኩት አማራ ሆኘ ስለተወለድኩ ነው። የከማራ ብሔርተኝነት አቀንቃኝ የሆንኩትም ፈቅጄ፣ መርጨና ወድጄ ነው። በየትኛውም ቦታና ሁኔታ ለአማራነቴ ጥብቅና መቆምም ተፈጥሯዊ ግዴታዬ ነው ” ብለዋል።
“ አማራዊ እሴቶታችን ለኛ ቅዱስ ነው ” ብለው፣ “ ይሁንና አቃቢ ህግ ባቀረበው የፓለቲካ ውንጀላ ሰነድ ላይ፣ ‘አማራ ርስቱን ተቀምቷል፤ አገሪቱ በአማራ እሴት መመራት አለባት’ የሚል የርዕዮተዓለማዊ አቋም መያዛችን ክስ ሆኖ ቀርቧል” ብለዋል።
“ ይህ የአቃቢ ህግ ክስ ግን መንግስት ከአማራና ከአማራነት የጸዳች ኢትዮጵያ ነው ወይ የሚፈልገው ? የሚል ሙግት ያስነሳል። ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት ከአማራና ከአማራነት በስተቀር እንዲሆኑ የሚደነግግ ህግስ አለ ወይ? ” ሲሉ ጠይቀዋል።
በሌላ በኩል “ በአቃቢ ህግ ክስ ላይ ‘ቋሪትና ደጋ ዳሞት ላሉ የሽብር ቡድን አስተባባዎች በስልክ ሐምሌ 25/2015 ዓ/ም በመደወል መከላከያን ማጥቃት ህገ መንግስታዊ መብት መሆኑን በማሳወቅ እንዲመቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል’ ” ማለቱን ጠቅሰል።
“ አቃቢ ህግ ለዚህ ክስ አስረጅ የሆነ አንዳችም ማስረጃ አላቀረበም ” ብለዋል።
(ሙሉ የእምነት ቃላቸውን የሰጡበት ሰነድ ከላይ ተያይዟል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
እነአቶ ክርስቲያን ታደለ ዛሬ ችሎት ቀርበው የእምነት ክህደት ቃል መስጠታቸውን ጉዳዩን ከሚከታተሉ ሰዎችና ቃላቸውን ካቀረበበት ሰነድ መረዳት ትችሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው አቶ ክርስቲያን የእምነት ክህደት ቃል የሰጡበት ሰነድ፣ “በአጠቃላይ አቃቢ ህግ በእኔ ላይ መስርቶ ባቀረበው ክስ ላይ የተገለጸውን ወንጀል አልፈጸምኩም። ጥፋተኛም አይደለሁም” ይላል።
አቶ ክርስቲያን በሰጡት የእምነት ክህደት ቃል ምን አሉ?
“ለ550 ቀናትም በግፍና ጭካኔ እገታ ውስጥ የምገኘው ለአንዲት ደቂቃ እንኳን በጥፋተኝነት የሚያስቀጣ አንዳችም የወንጀል ድርጊት የሚያቋቁም የህግ መተላለፍ ስለፈጸምኩ አይደለም። የአማራ ሕዝብ የሚያነሳቸውን የህልውና ጥያቄዎች በይፋ በማቅረቤ፣ በሕዝቤ የሚደርሰውን ግፍ፣ በደል በማስረጃ በመሞገቴ፣ የገዢውን ፓርቲ አፈናና የመንግስት አሰራሮችንና አመራሮችን ብልሹነትና ዘረፋ በመታገሌ ነው ” ብለዋል።
“ ተደጋጋሚ የአመራር ብልሹነት ባሳዩ አካላትም የወንጀልና የፍትሃብሔር ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ ክስ እንዲመሰረት ፍትህ ሚኒስቴር አዝዥለው ” የሚሉና ሌሎች ድርጊቶችን በአደባባይ እንደታገሉ ገልጸዋል።
“ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ ሌሎች የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች በአሰራራቸው የፋይናንስ ገልጸኝነትና ህጋዊነት እንዲከተሉና እንዲረጋገጡ እንዲሁም ኦዲት ለመደረግ ፈቃደኝነታቸውን እንዲያረጋግጡ ጠይቄከለሁ ” ነው ያሉት።
እነዚህን ጥያቄዎች እንዳልጠይቅ አንዳንድ አመራሮች ለማግባባት እንደሞከሩ ገልጸው፣ “ አንዳንዶቹም ሊገድሉኝ፣ ሊያስሩኝና አንዳች ነገር ሊያደርሱብኝ እንደሚችሉ ጭምር ነግረውኛል፤ መልዕክትም አድርሰውኛል ” ብለዋል።
“ አንዳች ወንጀል አልፈጸምኩም ” ያሉት ክርስቲያን፣ “ ይህን በተመለከተ ከክሱ ይዘት ብቻ ሳይሆን በራሴ መንገድ ይህን ክስ ተዘጋጅቶ እንዲቀርብብኝ ካደረገው አካል ዘንድም አረጋግጫለሁ ” ሲሉ አስረድተዋል።
“ እኔ አማራ የሆንኩት አማራ ሆኘ ስለተወለድኩ ነው። የከማራ ብሔርተኝነት አቀንቃኝ የሆንኩትም ፈቅጄ፣ መርጨና ወድጄ ነው። በየትኛውም ቦታና ሁኔታ ለአማራነቴ ጥብቅና መቆምም ተፈጥሯዊ ግዴታዬ ነው ” ብለዋል።
“ አማራዊ እሴቶታችን ለኛ ቅዱስ ነው ” ብለው፣ “ ይሁንና አቃቢ ህግ ባቀረበው የፓለቲካ ውንጀላ ሰነድ ላይ፣ ‘አማራ ርስቱን ተቀምቷል፤ አገሪቱ በአማራ እሴት መመራት አለባት’ የሚል የርዕዮተዓለማዊ አቋም መያዛችን ክስ ሆኖ ቀርቧል” ብለዋል።
“ ይህ የአቃቢ ህግ ክስ ግን መንግስት ከአማራና ከአማራነት የጸዳች ኢትዮጵያ ነው ወይ የሚፈልገው ? የሚል ሙግት ያስነሳል። ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት ከአማራና ከአማራነት በስተቀር እንዲሆኑ የሚደነግግ ህግስ አለ ወይ? ” ሲሉ ጠይቀዋል።
በሌላ በኩል “ በአቃቢ ህግ ክስ ላይ ‘ቋሪትና ደጋ ዳሞት ላሉ የሽብር ቡድን አስተባባዎች በስልክ ሐምሌ 25/2015 ዓ/ም በመደወል መከላከያን ማጥቃት ህገ መንግስታዊ መብት መሆኑን በማሳወቅ እንዲመቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል’ ” ማለቱን ጠቅሰል።
“ አቃቢ ህግ ለዚህ ክስ አስረጅ የሆነ አንዳችም ማስረጃ አላቀረበም ” ብለዋል።
(ሙሉ የእምነት ቃላቸውን የሰጡበት ሰነድ ከላይ ተያይዟል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ካቢኔ ምን ውሳኔዎች አሳለፈ ?
የአዲስ አበ ባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ባካሄደው 4ተኛ አመት 7ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል።
የመጀመሪያው በከተማዉ አስተዳደር በጀት ተመድቦላቸዉ የተገነቡ እና በመጠናቀቅ ያሉትን አዳዲስ ሆስፒታሎችን የሚመለከት ነው።
በዚህም ሆስፒታሎቹ ዘመኑን በዋጀ ህክምና መሳሪያ ለማሟላት እና አለም አቀፍ ደረጃን የሚያሟላ አገልግሎት መስጠት ያስችላቸው ዘንድ በዘርፉ ትልቅ ልምድ ካከበቱ #የግል_ሴክተር ጋር በአጋርነት ለመስራት ዉሳኔ አሳልፏል።
ሁለተኛ አንዳንድ የመንግስት አገልግሎቶችን በውል #ለ3ተኛ_ወገን ለማስራት የወጣውን ረቂቅ ደንብ መርምሮ በማየት ካቢኔዉ አፅድቋል።
በሶስተኛ ደረጀ የተለያዩ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ላላቸው እና ተኪ ምርቶችን ለሚያመርቱ ኢንዲስትሪዎች ባቀረቡት #የማስፋፊያ_ቦታ ጥያቄዎች ላይ በመወያየት እና የአተገባበር አቅጣጫ በማስቀመጥ ካቢኔው በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።
አራተኛ የኮሪደር ልማት ውጤት ከሆኑት ሥራዎች አንዱ የብዙሀን ትራንስፖርት መሠረተ ልማት ችግሮች የሚያቃልል እና የትራፊክ ፍስቱን የሚያሻሽለው የብስክሌት መጋራት አገልግሎት እና የብስክሌት መስመር አጠቃቀም ደንብን በመመርመር ማፅደቁን ከከተማ አስተዳደሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
@tikvahethiopia
የአዲስ አበ ባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ባካሄደው 4ተኛ አመት 7ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል።
የመጀመሪያው በከተማዉ አስተዳደር በጀት ተመድቦላቸዉ የተገነቡ እና በመጠናቀቅ ያሉትን አዳዲስ ሆስፒታሎችን የሚመለከት ነው።
በዚህም ሆስፒታሎቹ ዘመኑን በዋጀ ህክምና መሳሪያ ለማሟላት እና አለም አቀፍ ደረጃን የሚያሟላ አገልግሎት መስጠት ያስችላቸው ዘንድ በዘርፉ ትልቅ ልምድ ካከበቱ #የግል_ሴክተር ጋር በአጋርነት ለመስራት ዉሳኔ አሳልፏል።
ሁለተኛ አንዳንድ የመንግስት አገልግሎቶችን በውል #ለ3ተኛ_ወገን ለማስራት የወጣውን ረቂቅ ደንብ መርምሮ በማየት ካቢኔዉ አፅድቋል።
በሶስተኛ ደረጀ የተለያዩ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ላላቸው እና ተኪ ምርቶችን ለሚያመርቱ ኢንዲስትሪዎች ባቀረቡት #የማስፋፊያ_ቦታ ጥያቄዎች ላይ በመወያየት እና የአተገባበር አቅጣጫ በማስቀመጥ ካቢኔው በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።
አራተኛ የኮሪደር ልማት ውጤት ከሆኑት ሥራዎች አንዱ የብዙሀን ትራንስፖርት መሠረተ ልማት ችግሮች የሚያቃልል እና የትራፊክ ፍስቱን የሚያሻሽለው የብስክሌት መጋራት አገልግሎት እና የብስክሌት መስመር አጠቃቀም ደንብን በመመርመር ማፅደቁን ከከተማ አስተዳደሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Kenya
በUSAID እርዳታ ስራ የተቀጠሩ ብዙሃኑ በጤናው ዘርፍ ላይ ያሉ ከ40 ሺህ በላይ ኬንያውን ስራ አጥ ሊሆኑ ነው።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራንፕ አስተዳደር ከUSAID ጋር በተገናኘ እርዳታ እንዲቆም ውሳኔ ማሳላፋቸውን ተከትሎ በተለይ በአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በአሜሪካ እርዳታ የተቀጠሩ ሰራተኞች ስራ አጥ ይሆናሉ።
ከነዚህ ሀገራት መካከል ጎረቤታችን ኬንያ አንዷ ናት።
በሀገሪቱ በአሜሪካ መንግሥት እርዳታ ስራቸውን የሚሰሩ ከ40,000 በላይ ሰራተኞች ስራ አጥ ይሆናሉ ከነዚህ ውስጥ አብዛኞቹ በጤናው ዘርፍ ላይ ያሉ መሆናቸውን ከሲቲዝን ቴሌቪዥን የተገኘው መረጃ ያሳያል።
በኢትዮጵያ ከUSAID እና CDC ጋር በተገናኘ ድጋፍ በጤና ዘርፍ ስራ እየሰሩ ያሉ ከ5,000 በላይ ሰራተኞች ውላቸው እንዲቋረጥ ጤና ሚኒስቴር ትዕዛዝ መሰጠቱን ነግረናችሁ ነበር። ይህ በጤና ሚኒስቴር ብቻ የታዘዘው ነው። ሌሎች በUSAID እርዳታ የሚሰሩ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፤ ፕሮጀክቶች መኖራቸውን ልብ በሉ።
@tikvahethiopia
በUSAID እርዳታ ስራ የተቀጠሩ ብዙሃኑ በጤናው ዘርፍ ላይ ያሉ ከ40 ሺህ በላይ ኬንያውን ስራ አጥ ሊሆኑ ነው።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራንፕ አስተዳደር ከUSAID ጋር በተገናኘ እርዳታ እንዲቆም ውሳኔ ማሳላፋቸውን ተከትሎ በተለይ በአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በአሜሪካ እርዳታ የተቀጠሩ ሰራተኞች ስራ አጥ ይሆናሉ።
ከነዚህ ሀገራት መካከል ጎረቤታችን ኬንያ አንዷ ናት።
በሀገሪቱ በአሜሪካ መንግሥት እርዳታ ስራቸውን የሚሰሩ ከ40,000 በላይ ሰራተኞች ስራ አጥ ይሆናሉ ከነዚህ ውስጥ አብዛኞቹ በጤናው ዘርፍ ላይ ያሉ መሆናቸውን ከሲቲዝን ቴሌቪዥን የተገኘው መረጃ ያሳያል።
በኢትዮጵያ ከUSAID እና CDC ጋር በተገናኘ ድጋፍ በጤና ዘርፍ ስራ እየሰሩ ያሉ ከ5,000 በላይ ሰራተኞች ውላቸው እንዲቋረጥ ጤና ሚኒስቴር ትዕዛዝ መሰጠቱን ነግረናችሁ ነበር። ይህ በጤና ሚኒስቴር ብቻ የታዘዘው ነው። ሌሎች በUSAID እርዳታ የሚሰሩ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፤ ፕሮጀክቶች መኖራቸውን ልብ በሉ።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ህዝቡ ያለፈው አልበቃ ብሎት የትናንት ቁስሉ ሳይሽር አሁንም በሽብር እና በጦርነት ወሬ ስሜት ወስጥ ይገኛል ! " - የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚንስትር የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) ለትግራይ ህዝብ በተለይ ደግሞ ለልሂቃን መልእክት እና ምክር አስተላልፈዋል። ጠቅላይ ሚንስትሩ ጥር 26/2017 ዓ.ም በፅሁፍ ባስተላለፉት ጠንካራ መልእክት እና ምክር ትግራይን እና ህዝብዋን " የጥንታዊ…
ትግራይ ?
🔴 " በትግራይ በማንኛውም መመዘኛ ጦርነት የሚጋብዝ አንዳች ሁኔታ የለም " - በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት
🚨" በአሁኑ ወቅት በትግራይ በማንኛውም ደቂቃ በሆነ ሰው በሚፈጠር ስህተት ለግጭት የሚዳርግ ሁኔታ ሰፍቷል " - አቶ ጌታቸው ረዳ
ከቀናት በፊት የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በትግራይ ክልል ያለውን ሁኔታ ተንተርሶ ለትግራይ ህዝብ በተለይም ለትግራይ ሊህቃን ጠንካራ መልዕክት እና ምክር ማስተላለፋቸው ይታወሳል።
ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) በመልዕክታቸው ፥ " ህዝቡ ያለፈው አልበቃ ብሎት የትናንት ቁስሉ ሳይሽር አሁንም በሽብር እና በጦርነት ወሬ ስሜት ወስጥ ይገኛል " ብለዋል።
በፓለቲካ ፣ በንግድ ፣ ፀጥታ ፣ አካዳሚ እና ሚድያ እና በሌሎች የስራ ዘርፎች ለተሰማሩ የትግራይ ልሂቃን ወገኖች ባስተላለፉት መልዕክት " የትግራይ ህዝብ እስከ ዛሬ የተሰቃየው የከፈለው ዋጋ ይብቃው ፤ ልዩነትን በመነጋገር እና በውይይት የመፍታት ባህልንና ልምድ ታጠቁ " ብለዋል።
ልሂቃኑ ከፌደራል መንግስት እና ሌሎች ሃይሎች ያላቸው ልዩነት በአገሪቱ ህገ-መንግስት በዴሞክራሲያዊ መንገድ በመግባባት ለመፍታት ዝግጁ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።
ለዚህ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥሪ በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) በሚመራው ህወሓት የፓለቲካዊ ጉዳዮች ሃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገ/ሄር ምላሽ ያሉትን ሰጥተዋል።
ምላሹን የሰጡት 50ኛው ዓመት የትግራይ ህዝብ ትግል የጀመረበት የካቲት 11 አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ ነው።
በደብረፅዮን (ዶ/ር) ህወሓት የፓለቲካዊ ጉዳዮች ሃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገ/ሄር ምን አሉ ?
➡️ " ጠቅላይ ሚንስትሩ የትግራይ ህዝብ በኢትዮጵያ ህልውና የነበረው ተሳትፎ አስመልክተው የተጠቀሙበት አገላለፅ ልክ ነው። የትግራይ ህዝብ ሚና ባሉት ደረጃ ነው መገለፅ ያለበት ብለን እናምናለን። የትግራይ ህዝብ ለኢትዮጵያ ነፃነት ፣ ልማት እና ዴሞክራሲ የከፈለው ዋጋ እጅግ ውድ ነው። እሳቸው በፅሁፋዊ መልእክታቸው የተጠቀሙበት አገላለፅ የምንጋራው እና ክብር የምንሰጠው ነው " ብለዋል።
➡️ " የመልእክታቸው አንኳር ነጥብ ህዝቡ ጦርነት ስለማያስፈልገው የትግራይ መሪዎች እና ልሂቃን ልብ ግዙ ተመካከሩ የሚል ነው። የትግራይ ህዝብ ብቻ ሳይሆን ማንኛውም ህዝብ ጦርነት አይወድም ፤ አይገባውም። በተለይ ደግሞ የትግራይ ህዝብም ጦርነት አያስፈልገውም። ይሁን እንጂ የትግራይ ህዝብ ባለፉት 100 ዓመታት ከማእከላዊ መንግስቱ ያደረጋቸው ጦርነቶች ከመሬት ተነስቶ ያደረጋቸው ተንኳሽ እንደሆነ በሚያደምጥ መልኩ በደብዳቤው የቀረበ አገላለፅ ልክ ነው ብለን አንወስድም " ሲሉ ተናግረዋል።
➡️ " የትግራይ ህዝብ ላለፉት 100 ዓመታት እና ከዛ በላይ የተዋጋው የሚወሩትን ፣ መብቱን የሚነፍጉትን እና ድምፁን የሚያፍኑትን ለመከላከል ሲባል መሆኑ ልብ ማለት ይገባል። ስለሆነም የትግራይ ህዝብ ጦረኛ እና ተንኳሽ በሚመስል መልኩ የቀረበ አገላለፅ ልክ አይደለም። የትግራይ ህዝብ ትናንት ፣ ዛሬ ይሁን ነገ አይገዛም አይምበረከክም። ልግዛህ ላምበረክክህ ለሚለው ወራሪ መልሱ እምቢ ነው። ከዚህ ውጭ ጦርነት ጀማሪ ሆኖ አያውቅም ፤ ማንንም ሄዶ አይወርም ልግዛህ አይልም ፤ ስለሆነም ጦርነት ጀማሪ በሚመስል የቀረበው አገላለፅ ልክ አይደለም " ብለዋል።
➡️ " እኛ እንወረራለን እንጂ አንወርም ፤ ጦርነት ይከፈትብናል እንጂ በማንኛውም ህዝብ ላይ ጦርነት አንከፍትም " ሲሉ ገልጸዋል።
➡️ " ማንኛውም የትግራይ ፓለቲካዊ ፓርቲ ፣ ስቪክ ማህበር እና ህዝቡ ከማንኛውም ህዝብ በላይ በጦርነት የወደመ የተጠቃ ፣ ጦርነት እጅግ አፍራሽ መሆኑ ስለሚያውቅ አሁንም የጦርነት ፍላጎት የለውም " ብለዋል።
➡️ " በትግራይ በኩል ለጦርነት የሚጋብዝ አንድም ምክንያት የለም ። እርግጥ ነው በህወሓት ከፍተኛ አመራሮች መካከል ልዩነት እና መሳሳብ አለ። ይህንንም በሰለጠነ የፓለቲካ አግባብ ይፈታ እንደሆነ እንጂ ወደ ጦርነት የሚመራ ምክንያት ሊሆን አይችልም " ሲሉ ተናግረዋል።
➡️ " ያለንን የፓለቲካ ልዩነት በውይይት እና በሰለጠነ የፓለቲካ አግባብ እንፈታዋለን እንጂ ወደ ጦርነት የሚያስገባን አይሆንም " ብለዋል።
➡️ " ከፌደራል መንግስት ጋር የሚያገናኘን የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ነው። ስምምነቱ ማእከል በማድረግ የጎደለን ነገር በውይይት ለሞምላት ነው 'እንወያይ ' የሚል ጥሪ እያቀረብን ያለነው። እንወያይ የፕሪቶሪያ ስምምነት ተፈፃሚ ይሁን ፣ ወራሪዎች በሃይል ከያዙት ግዛታችን ይውጡ ፣ የግዛት አንደነታችን ይከበር ፣ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው ይመለሱ ፣ የሁለትዮሽ ፓለቲካዊ ውይይት ይጀመር ወደ መደበኛው ህገ-መንግስታዊ ስርዓት የምንመለስበት ሁኔታ ይፍጠን ብሎ መጠየቅ የጦርነት መንስኤ ሊሆን አይችልም " ብለዋል።
➡️ " የ2013 ዓ.ም ጦርነት ከመጀመሩ ጥቂት ሳምታት ቀደም ብሎ በጠቅላይ ሚንስትሩ የአሁኑ አይነት ተመሳሳይ የፅሁፍ መግለጫ ተሰጥቶ ነበር። ያኔም ' ወደ ትግራይ ማሰክ እንጂ የጥይት ቁምቡላ አንልክም ' ተብሎ ነበር። ቅኔ ነው የነበረው። አሁንም በውጭ ሲታይ ለስላሳ እና ጣፋጭ ውስጡ ሲታይ ግን ' ተጠንቀቁ ወደ ጦርነት የሚያስገባ ሁኔታ ነው ያለው ' የሚል እንድምታ ያለው ደብዳቤ ነው የተሰራጨው " ብለዋል።
➡️ " ደብዳቤው ሆን ተብሎ ህዝብ ለማሸበር የተደረገ ነው። ይህ በትግራይ ህዝብ ላይ እየቀጠለ ያለውን በደል አካል አድርገን ነው የምንቆጥረው። የትግራይ ህዝብ ማስፈራራት አይገባም። አሁንም ' መጣሁብህ ገደልኩህ ' ማለት ለትግራይ ህዝብ ተገቢ አይደለም። የትግራይ ህዝብ አሁን የሚያስፈልገው የበደል ካሳ ፣ ሰላም ፣ ልማት እና ውይይት ነው በመሪዎች መካከል የተፈጠረው የፓለቲካ ልዩነት በሰለጠነ ውይይት መፍታት ያስፈልጋል " ብለዋል።
➡️ " በአሁኑ ወቅት ህወሓትም ሆነ የትግራይ ህዝብ የጦርነት ፍላጎት የላቸውም። በመላው ትግራይ ጦርነት የሚጋብዝ እንዳች ምልክት የለም። መብታችን ፣ ማንነታችን ይከበርልን ፣ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መሰረት ሁሉም ነገር ይፈፀም የሚል ግን ጥያቄያችን አስኪመለስ ድረስ የምናቆመው አይደለም ይህ ዓይነት ጥያቄ በፍፁም የጦርነት መንስኤ ሊሆን አይችልም " ብለዋል።
➡️ " በትግራይ ለጦርነት የሚጋብዝን አንዳች ነገር የለም " ሲሉ ተደምጠዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ትላንት 50ኛው ዓመት የትግራይ ህዝብ ትግል የጀመረበት የካቲት 11 በጊዚያዊ አስተዳደሩ ለማክበር እየተደረገ ያለው ቅድመ ዝግጅት በማስመልከት የክልሉ ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ መግለጫ ሰጥተው ነበር።
አቶ ጌታቸው በዚሁ ወቅት በህወሓት አመራሮች መካከላል ባለው ክፍፍል የግጭት ስጋት ስለመኖሩ ጠቋሚ ቃል ሰጥተዋል።
" በአሁኑ ወቅት በትግራይ በማንኛውም ደቂቃ በሆነ ሰው በሚፈጠር ስህተት ለግጭት የሚዳርግ ሁኔታ ሰፍቷል " በማለት ነው ስጋታቸው የገለጹት።
ትግራይ ክልል ከአስከፊው ጦርነት ገና በቅጡ ያላገገመ ሲሆን አሁን ደግሞ ህዝብን በከፍተኛ ስጋት ላይ በጣለ የአመራሮች ክፍፍል እየታመሰ ነው።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
🔴 " በትግራይ በማንኛውም መመዘኛ ጦርነት የሚጋብዝ አንዳች ሁኔታ የለም " - በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት
🚨" በአሁኑ ወቅት በትግራይ በማንኛውም ደቂቃ በሆነ ሰው በሚፈጠር ስህተት ለግጭት የሚዳርግ ሁኔታ ሰፍቷል " - አቶ ጌታቸው ረዳ
ከቀናት በፊት የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በትግራይ ክልል ያለውን ሁኔታ ተንተርሶ ለትግራይ ህዝብ በተለይም ለትግራይ ሊህቃን ጠንካራ መልዕክት እና ምክር ማስተላለፋቸው ይታወሳል።
ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) በመልዕክታቸው ፥ " ህዝቡ ያለፈው አልበቃ ብሎት የትናንት ቁስሉ ሳይሽር አሁንም በሽብር እና በጦርነት ወሬ ስሜት ወስጥ ይገኛል " ብለዋል።
በፓለቲካ ፣ በንግድ ፣ ፀጥታ ፣ አካዳሚ እና ሚድያ እና በሌሎች የስራ ዘርፎች ለተሰማሩ የትግራይ ልሂቃን ወገኖች ባስተላለፉት መልዕክት " የትግራይ ህዝብ እስከ ዛሬ የተሰቃየው የከፈለው ዋጋ ይብቃው ፤ ልዩነትን በመነጋገር እና በውይይት የመፍታት ባህልንና ልምድ ታጠቁ " ብለዋል።
ልሂቃኑ ከፌደራል መንግስት እና ሌሎች ሃይሎች ያላቸው ልዩነት በአገሪቱ ህገ-መንግስት በዴሞክራሲያዊ መንገድ በመግባባት ለመፍታት ዝግጁ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።
ለዚህ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥሪ በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) በሚመራው ህወሓት የፓለቲካዊ ጉዳዮች ሃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገ/ሄር ምላሽ ያሉትን ሰጥተዋል።
ምላሹን የሰጡት 50ኛው ዓመት የትግራይ ህዝብ ትግል የጀመረበት የካቲት 11 አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ ነው።
በደብረፅዮን (ዶ/ር) ህወሓት የፓለቲካዊ ጉዳዮች ሃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገ/ሄር ምን አሉ ?
➡️ " ጠቅላይ ሚንስትሩ የትግራይ ህዝብ በኢትዮጵያ ህልውና የነበረው ተሳትፎ አስመልክተው የተጠቀሙበት አገላለፅ ልክ ነው። የትግራይ ህዝብ ሚና ባሉት ደረጃ ነው መገለፅ ያለበት ብለን እናምናለን። የትግራይ ህዝብ ለኢትዮጵያ ነፃነት ፣ ልማት እና ዴሞክራሲ የከፈለው ዋጋ እጅግ ውድ ነው። እሳቸው በፅሁፋዊ መልእክታቸው የተጠቀሙበት አገላለፅ የምንጋራው እና ክብር የምንሰጠው ነው " ብለዋል።
➡️ " የመልእክታቸው አንኳር ነጥብ ህዝቡ ጦርነት ስለማያስፈልገው የትግራይ መሪዎች እና ልሂቃን ልብ ግዙ ተመካከሩ የሚል ነው። የትግራይ ህዝብ ብቻ ሳይሆን ማንኛውም ህዝብ ጦርነት አይወድም ፤ አይገባውም። በተለይ ደግሞ የትግራይ ህዝብም ጦርነት አያስፈልገውም። ይሁን እንጂ የትግራይ ህዝብ ባለፉት 100 ዓመታት ከማእከላዊ መንግስቱ ያደረጋቸው ጦርነቶች ከመሬት ተነስቶ ያደረጋቸው ተንኳሽ እንደሆነ በሚያደምጥ መልኩ በደብዳቤው የቀረበ አገላለፅ ልክ ነው ብለን አንወስድም " ሲሉ ተናግረዋል።
➡️ " የትግራይ ህዝብ ላለፉት 100 ዓመታት እና ከዛ በላይ የተዋጋው የሚወሩትን ፣ መብቱን የሚነፍጉትን እና ድምፁን የሚያፍኑትን ለመከላከል ሲባል መሆኑ ልብ ማለት ይገባል። ስለሆነም የትግራይ ህዝብ ጦረኛ እና ተንኳሽ በሚመስል መልኩ የቀረበ አገላለፅ ልክ አይደለም። የትግራይ ህዝብ ትናንት ፣ ዛሬ ይሁን ነገ አይገዛም አይምበረከክም። ልግዛህ ላምበረክክህ ለሚለው ወራሪ መልሱ እምቢ ነው። ከዚህ ውጭ ጦርነት ጀማሪ ሆኖ አያውቅም ፤ ማንንም ሄዶ አይወርም ልግዛህ አይልም ፤ ስለሆነም ጦርነት ጀማሪ በሚመስል የቀረበው አገላለፅ ልክ አይደለም " ብለዋል።
➡️ " እኛ እንወረራለን እንጂ አንወርም ፤ ጦርነት ይከፈትብናል እንጂ በማንኛውም ህዝብ ላይ ጦርነት አንከፍትም " ሲሉ ገልጸዋል።
➡️ " ማንኛውም የትግራይ ፓለቲካዊ ፓርቲ ፣ ስቪክ ማህበር እና ህዝቡ ከማንኛውም ህዝብ በላይ በጦርነት የወደመ የተጠቃ ፣ ጦርነት እጅግ አፍራሽ መሆኑ ስለሚያውቅ አሁንም የጦርነት ፍላጎት የለውም " ብለዋል።
➡️ " በትግራይ በኩል ለጦርነት የሚጋብዝ አንድም ምክንያት የለም ። እርግጥ ነው በህወሓት ከፍተኛ አመራሮች መካከል ልዩነት እና መሳሳብ አለ። ይህንንም በሰለጠነ የፓለቲካ አግባብ ይፈታ እንደሆነ እንጂ ወደ ጦርነት የሚመራ ምክንያት ሊሆን አይችልም " ሲሉ ተናግረዋል።
➡️ " ያለንን የፓለቲካ ልዩነት በውይይት እና በሰለጠነ የፓለቲካ አግባብ እንፈታዋለን እንጂ ወደ ጦርነት የሚያስገባን አይሆንም " ብለዋል።
➡️ " ከፌደራል መንግስት ጋር የሚያገናኘን የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ነው። ስምምነቱ ማእከል በማድረግ የጎደለን ነገር በውይይት ለሞምላት ነው 'እንወያይ ' የሚል ጥሪ እያቀረብን ያለነው። እንወያይ የፕሪቶሪያ ስምምነት ተፈፃሚ ይሁን ፣ ወራሪዎች በሃይል ከያዙት ግዛታችን ይውጡ ፣ የግዛት አንደነታችን ይከበር ፣ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው ይመለሱ ፣ የሁለትዮሽ ፓለቲካዊ ውይይት ይጀመር ወደ መደበኛው ህገ-መንግስታዊ ስርዓት የምንመለስበት ሁኔታ ይፍጠን ብሎ መጠየቅ የጦርነት መንስኤ ሊሆን አይችልም " ብለዋል።
➡️ " የ2013 ዓ.ም ጦርነት ከመጀመሩ ጥቂት ሳምታት ቀደም ብሎ በጠቅላይ ሚንስትሩ የአሁኑ አይነት ተመሳሳይ የፅሁፍ መግለጫ ተሰጥቶ ነበር። ያኔም ' ወደ ትግራይ ማሰክ እንጂ የጥይት ቁምቡላ አንልክም ' ተብሎ ነበር። ቅኔ ነው የነበረው። አሁንም በውጭ ሲታይ ለስላሳ እና ጣፋጭ ውስጡ ሲታይ ግን ' ተጠንቀቁ ወደ ጦርነት የሚያስገባ ሁኔታ ነው ያለው ' የሚል እንድምታ ያለው ደብዳቤ ነው የተሰራጨው " ብለዋል።
➡️ " ደብዳቤው ሆን ተብሎ ህዝብ ለማሸበር የተደረገ ነው። ይህ በትግራይ ህዝብ ላይ እየቀጠለ ያለውን በደል አካል አድርገን ነው የምንቆጥረው። የትግራይ ህዝብ ማስፈራራት አይገባም። አሁንም ' መጣሁብህ ገደልኩህ ' ማለት ለትግራይ ህዝብ ተገቢ አይደለም። የትግራይ ህዝብ አሁን የሚያስፈልገው የበደል ካሳ ፣ ሰላም ፣ ልማት እና ውይይት ነው በመሪዎች መካከል የተፈጠረው የፓለቲካ ልዩነት በሰለጠነ ውይይት መፍታት ያስፈልጋል " ብለዋል።
➡️ " በአሁኑ ወቅት ህወሓትም ሆነ የትግራይ ህዝብ የጦርነት ፍላጎት የላቸውም። በመላው ትግራይ ጦርነት የሚጋብዝ እንዳች ምልክት የለም። መብታችን ፣ ማንነታችን ይከበርልን ፣ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መሰረት ሁሉም ነገር ይፈፀም የሚል ግን ጥያቄያችን አስኪመለስ ድረስ የምናቆመው አይደለም ይህ ዓይነት ጥያቄ በፍፁም የጦርነት መንስኤ ሊሆን አይችልም " ብለዋል።
➡️ " በትግራይ ለጦርነት የሚጋብዝን አንዳች ነገር የለም " ሲሉ ተደምጠዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ትላንት 50ኛው ዓመት የትግራይ ህዝብ ትግል የጀመረበት የካቲት 11 በጊዚያዊ አስተዳደሩ ለማክበር እየተደረገ ያለው ቅድመ ዝግጅት በማስመልከት የክልሉ ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ መግለጫ ሰጥተው ነበር።
አቶ ጌታቸው በዚሁ ወቅት በህወሓት አመራሮች መካከላል ባለው ክፍፍል የግጭት ስጋት ስለመኖሩ ጠቋሚ ቃል ሰጥተዋል።
" በአሁኑ ወቅት በትግራይ በማንኛውም ደቂቃ በሆነ ሰው በሚፈጠር ስህተት ለግጭት የሚዳርግ ሁኔታ ሰፍቷል " በማለት ነው ስጋታቸው የገለጹት።
ትግራይ ክልል ከአስከፊው ጦርነት ገና በቅጡ ያላገገመ ሲሆን አሁን ደግሞ ህዝብን በከፍተኛ ስጋት ላይ በጣለ የአመራሮች ክፍፍል እየታመሰ ነው።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ
ሀገራዊ የጾም ፀሎት ጥሪ ከመሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን !
መሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ከየካቲት 1 እስከ የካቲት 15 ድረስ የሚዘልቅ ሀገራዊ የጾም ፀሎት አውጃለች።
ቤተክርስቲያኗ በልመና / ምልጃ ጸሎት ወቅት ፦
➡️ " በሀገሪቱ በተለያዩ ሥፍራዎች ያሉ የፖለቲካ ኃይሎች በኃላፊነት መንፈስ በጋራ ለሀገር እና ለህዝብ በአንድነት መስራት የሚችሉበትን ጥበብ፤ እውቀትና ማስተዋል እግዚአብሔር እንዲሰጣቸው እንለምን። "
➡️ " በሀገራችን በሚገኙት የኦሮሚያ፤ የአማራ እና የትግራይ ክልሎች ያለው አፍተኛ የጸጥታ ችግር ጌታ እንዲያቆመው እንጸልይ። "
➡️ " በምድሪቱ ላይ ፍትህ እንዲሰፍን እንዲሁም በተለያዩ የሥልጣን ደረጃዎች ያሉ የመንግስት አካላት ሕዝቡን በከፍተኛ ኃላፊነት፤ አክብሮትና ቅንነት ማገልገል የሚችሉበትን ጥበብ፣ ማስተዋልና የልብ ስፋት እግዚአብሔር እንዲሰጣቸው እንለምን። "
➡️ " የሀገራችን ኢኮኖሚ ስርዐት ድሃው ማህበረሰብ ሰርቶና በልቶ እንዲያድር ፍትሐዊ እንዲሆን እንጸልይ፡፡ "
... ብላለች።
(የቤተክርስቲያኒቱ ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
ሀገራዊ የጾም ፀሎት ጥሪ ከመሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን !
መሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ከየካቲት 1 እስከ የካቲት 15 ድረስ የሚዘልቅ ሀገራዊ የጾም ፀሎት አውጃለች።
ቤተክርስቲያኗ በልመና / ምልጃ ጸሎት ወቅት ፦
➡️ " በሀገሪቱ በተለያዩ ሥፍራዎች ያሉ የፖለቲካ ኃይሎች በኃላፊነት መንፈስ በጋራ ለሀገር እና ለህዝብ በአንድነት መስራት የሚችሉበትን ጥበብ፤ እውቀትና ማስተዋል እግዚአብሔር እንዲሰጣቸው እንለምን። "
➡️ " በሀገራችን በሚገኙት የኦሮሚያ፤ የአማራ እና የትግራይ ክልሎች ያለው አፍተኛ የጸጥታ ችግር ጌታ እንዲያቆመው እንጸልይ። "
➡️ " በምድሪቱ ላይ ፍትህ እንዲሰፍን እንዲሁም በተለያዩ የሥልጣን ደረጃዎች ያሉ የመንግስት አካላት ሕዝቡን በከፍተኛ ኃላፊነት፤ አክብሮትና ቅንነት ማገልገል የሚችሉበትን ጥበብ፣ ማስተዋልና የልብ ስፋት እግዚአብሔር እንዲሰጣቸው እንለምን። "
➡️ " የሀገራችን ኢኮኖሚ ስርዐት ድሃው ማህበረሰብ ሰርቶና በልቶ እንዲያድር ፍትሐዊ እንዲሆን እንጸልይ፡፡ "
... ብላለች።
(የቤተክርስቲያኒቱ ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia