#Bitcoin
" በፍጹም ቢትኮይናችሁን አንዳትሸጡ " - ትራምፕ (በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት የተናገሩት)
የዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ ፕሬዜዳንት ሆኖ መመረጥ ለክሪፕቶ ማህበረሰቡ ትልቅ ብስራት ነው የሆነው።
ትራምፕ መመረጣቸው ከተሰማ በኃላ ቢትኮይን ታይቶ ባይታወቅ እና በማይታመን ሁኔታ ጨምሯል።
ዛሬ ላይ አንድ ቢትኮይን ከ91,000 ዶላር በላይ ገብቷል።
ልክ ትራምፕ ሲመረጡ በክሪፕቶ ማህበረሰቡ ዘንድ ትልቅ ደስታ የተፈጠረ ሲሆን " የመጀመሪያው የክሪፕቶ ፕሬዝዳንት ተመረጠ " ነው የተባለው።
ትራምፕ የመጀመሪያው በይፋ ቢትኮይን እና ክሪፕቶከረንሲ የሚደግፉ ተመራጭ ፕሬዚዳንት ናቸው።
ተመራጩ ፕሬዝደንት በምርጫ ቅስቀሳቸው ወቅት " አሜሪካን የፕላኔታችን የክሪፕቶከረንሲ መዲና አደርጋታለሁ " ሲሉ ቃል ገብተዋል።
ለዲጂታል መገበያያዎች የተመቻቸ ሁኔታ እንደሚፈጥሩም ተናግረዋል። ይህን ተከትሎ በክሪፕቶ ኢንዱስትሪ ላይ የተጣለው ቁጥጥር ይላላል የሚል እምነት አለ።
ትራምፕ በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት " በፍጹም ቢትኮይናችሁን አንዳትሸጡ " ሲሉ ተናግረው ነበር።
የዓለማችን ትልቁ ክሪፕቶከረንሲ የሆነው ቢትኮይት ከትራምፕ መመረጥ በኃላ በማይታመን ሁኔታ ጨምሮ ዛሬ ላይ ከ91,000 (ዘጠና አንድ ሺህ) ዶላር በላይ ሆኗል።
ሌሎች እንደ ዶጅኮይን ያሉ ክሪፕቶከረንሲዎችም ዋጋቸው ከፍ እያለ ነው። የዶናልድ ትራምፕ ቀኝ እጅ የሆነው ኢላን መስክ ዶጅኮይን በስፋት ያስተዋውቃል።
ክሪፕቶከረንሲ ምንድን ነው ?
ኦክስፎርድ መዝገበ ቃላት ክሪፕቶከረንሲን " የገንዘብ ልውውጦችን ደኅንነት የሚያረጋግጥ፣ የተጨማሪ አሃዶችን መፈጠርን የሚቆጣጠር እና ገንዘብ መተላለፉን የሚያረጋግጥ ጠንካራ ክራፕቶግራፊ የሚጠቀም መገበያያ እንዲሆን ተደርጎ የተቀረጸ ዲጂታል ገንዘብ " ይለዋል።
ከላይ የተጠቀሰውን መስፈርት የሚያሟሉ በርካታ ዓይነት ክሪፕቶካረንሲዎች አሉ።
በስፋት ከሚታወቁት መካከል ፦
- ቢትኮይን፣
- ኤቴሪያም፣
- ሪፕል እና ቢትኮይን ካሽ የሚባሉት ከበርካታ ክሪፕቶካረንሲዎች መካከል ሊጠቀሱ ይችላሉ።
ቢትኮይን ማለት በቀላል ቋንቋ፤ ዲጂታል + ገንዘብ + መገበያያ በማለት ማጠቃለል ይቻላል።
ይህ መገበያያ በኪሳችን ተሸክመን እንደምንዞረው የወረቀት ገንዘብ ወይም ሳንቲም ሳይሆን በበይነ መረብ ላይ የሚቀመጥ ዲጂታል ገንዘብ ነው።
ሌላው የቢትኮይንና የተቀሩት የክሪፕቶከረንሲዎች ልዩ ባህሪ በመንግሥታት እና በባንኮች አለመታተማቸው እንዲሁም ቁጥጥር አለመደረጉ ነው።
ቢትኮይን የሚፈጠረው 'ማይኒንግ' በሚባል ሂደት ነው። በመላው ዓለም በኔትወርክ በተሳሰሩ ኮምፒውተሮች አማካኝነት ቁጥጥር ይደረግበታል።
ቢትኮይንን የፈጠረው ግለሰብ/ቡድን በዓለም ላይ 21 ሚሊዮን ቢትኮይኖች ብቻ እንዲፈጠሩ ገደብ እንዳስቀመጠ/ጡ ይታመናል።
የብሎክቼይን መረጃዎች እንደሚያሳዩት እስካሁን ከ17 ሚሊዮን ያህል ቢትኮይኖች ማይን ተደርገዋል ተብሎ ይታመናል ሲል ቢቢሲ አስነብቧል።
#USA #Bitcoin #BBC #Mario #Crypto
@tikvahethiopia
" በፍጹም ቢትኮይናችሁን አንዳትሸጡ " - ትራምፕ (በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት የተናገሩት)
የዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ ፕሬዜዳንት ሆኖ መመረጥ ለክሪፕቶ ማህበረሰቡ ትልቅ ብስራት ነው የሆነው።
ትራምፕ መመረጣቸው ከተሰማ በኃላ ቢትኮይን ታይቶ ባይታወቅ እና በማይታመን ሁኔታ ጨምሯል።
ዛሬ ላይ አንድ ቢትኮይን ከ91,000 ዶላር በላይ ገብቷል።
ልክ ትራምፕ ሲመረጡ በክሪፕቶ ማህበረሰቡ ዘንድ ትልቅ ደስታ የተፈጠረ ሲሆን " የመጀመሪያው የክሪፕቶ ፕሬዝዳንት ተመረጠ " ነው የተባለው።
ትራምፕ የመጀመሪያው በይፋ ቢትኮይን እና ክሪፕቶከረንሲ የሚደግፉ ተመራጭ ፕሬዚዳንት ናቸው።
ተመራጩ ፕሬዝደንት በምርጫ ቅስቀሳቸው ወቅት " አሜሪካን የፕላኔታችን የክሪፕቶከረንሲ መዲና አደርጋታለሁ " ሲሉ ቃል ገብተዋል።
ለዲጂታል መገበያያዎች የተመቻቸ ሁኔታ እንደሚፈጥሩም ተናግረዋል። ይህን ተከትሎ በክሪፕቶ ኢንዱስትሪ ላይ የተጣለው ቁጥጥር ይላላል የሚል እምነት አለ።
ትራምፕ በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት " በፍጹም ቢትኮይናችሁን አንዳትሸጡ " ሲሉ ተናግረው ነበር።
የዓለማችን ትልቁ ክሪፕቶከረንሲ የሆነው ቢትኮይት ከትራምፕ መመረጥ በኃላ በማይታመን ሁኔታ ጨምሮ ዛሬ ላይ ከ91,000 (ዘጠና አንድ ሺህ) ዶላር በላይ ሆኗል።
ሌሎች እንደ ዶጅኮይን ያሉ ክሪፕቶከረንሲዎችም ዋጋቸው ከፍ እያለ ነው። የዶናልድ ትራምፕ ቀኝ እጅ የሆነው ኢላን መስክ ዶጅኮይን በስፋት ያስተዋውቃል።
ክሪፕቶከረንሲ ምንድን ነው ?
ኦክስፎርድ መዝገበ ቃላት ክሪፕቶከረንሲን " የገንዘብ ልውውጦችን ደኅንነት የሚያረጋግጥ፣ የተጨማሪ አሃዶችን መፈጠርን የሚቆጣጠር እና ገንዘብ መተላለፉን የሚያረጋግጥ ጠንካራ ክራፕቶግራፊ የሚጠቀም መገበያያ እንዲሆን ተደርጎ የተቀረጸ ዲጂታል ገንዘብ " ይለዋል።
ከላይ የተጠቀሰውን መስፈርት የሚያሟሉ በርካታ ዓይነት ክሪፕቶካረንሲዎች አሉ።
በስፋት ከሚታወቁት መካከል ፦
- ቢትኮይን፣
- ኤቴሪያም፣
- ሪፕል እና ቢትኮይን ካሽ የሚባሉት ከበርካታ ክሪፕቶካረንሲዎች መካከል ሊጠቀሱ ይችላሉ።
ቢትኮይን ማለት በቀላል ቋንቋ፤ ዲጂታል + ገንዘብ + መገበያያ በማለት ማጠቃለል ይቻላል።
ይህ መገበያያ በኪሳችን ተሸክመን እንደምንዞረው የወረቀት ገንዘብ ወይም ሳንቲም ሳይሆን በበይነ መረብ ላይ የሚቀመጥ ዲጂታል ገንዘብ ነው።
ሌላው የቢትኮይንና የተቀሩት የክሪፕቶከረንሲዎች ልዩ ባህሪ በመንግሥታት እና በባንኮች አለመታተማቸው እንዲሁም ቁጥጥር አለመደረጉ ነው።
ቢትኮይን የሚፈጠረው 'ማይኒንግ' በሚባል ሂደት ነው። በመላው ዓለም በኔትወርክ በተሳሰሩ ኮምፒውተሮች አማካኝነት ቁጥጥር ይደረግበታል።
ቢትኮይንን የፈጠረው ግለሰብ/ቡድን በዓለም ላይ 21 ሚሊዮን ቢትኮይኖች ብቻ እንዲፈጠሩ ገደብ እንዳስቀመጠ/ጡ ይታመናል።
የብሎክቼይን መረጃዎች እንደሚያሳዩት እስካሁን ከ17 ሚሊዮን ያህል ቢትኮይኖች ማይን ተደርገዋል ተብሎ ይታመናል ሲል ቢቢሲ አስነብቧል።
#USA #Bitcoin #BBC #Mario #Crypto
@tikvahethiopia
#Ethiopia #USA
የአሜሪካ ከፍተኛ ባለስልጣናት ኢትዮጵያ ይገኛሉ።
በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ማሲንጋን ጨምሮ፣ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምክትል ረዳት ሚኒስትር ስፔራ፣ የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስቴር ምክትል ረዳት ፀሀፊ ፋሬል እና ሌሎችም የተካተቱበት ልዑክ ከሀገር መከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሐመድ ጋር መክረዋል።
በወቅቱም ኢንጂነር አይሻ ፤ ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ጋር ላላት የረዥም ጊዜ ወታደራዊ ግንኙነት ትልቅ ዋጋ እንደምትሰጥ እንደገለጹና ይህንኑ ትብብር የበለጠ ለማጠናከር ኢትዮጵያ ፍላጎት እንዳለት መናገራቸውን ሀገር መከላከያ ሰራዊት ገልጿል።
የአሜሪካ ኤምባሲ እንዳለው ከሆነ ደግሞ በምክክሩ ላይ #በአማራ እና #ኦሮሚያ ያለው ግጭት ጉዳይ ተነስቷል።
ሌላው የቀድሞ ተዋጊዎችን ዲሞብላይዝ በማድረግ ወደ ማህበረሰቡ መልሶ ለመቀላቀልና ለማቋቋም ስለሚደረገው ስራ (DDR) ውይይት ተደርጓል።
በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ መካከል ያለውን ወታደራዊ ትብብር በማጠናከር ላይም ትኩርት ያደረገ ምክክር መደረጉን ከኤምባሲው የተገኘ መረጃ ያሳያል።
#USA #USEmbassy
@tikvahethiopia
የአሜሪካ ከፍተኛ ባለስልጣናት ኢትዮጵያ ይገኛሉ።
በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ማሲንጋን ጨምሮ፣ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምክትል ረዳት ሚኒስትር ስፔራ፣ የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስቴር ምክትል ረዳት ፀሀፊ ፋሬል እና ሌሎችም የተካተቱበት ልዑክ ከሀገር መከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሐመድ ጋር መክረዋል።
በወቅቱም ኢንጂነር አይሻ ፤ ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ጋር ላላት የረዥም ጊዜ ወታደራዊ ግንኙነት ትልቅ ዋጋ እንደምትሰጥ እንደገለጹና ይህንኑ ትብብር የበለጠ ለማጠናከር ኢትዮጵያ ፍላጎት እንዳለት መናገራቸውን ሀገር መከላከያ ሰራዊት ገልጿል።
የአሜሪካ ኤምባሲ እንዳለው ከሆነ ደግሞ በምክክሩ ላይ #በአማራ እና #ኦሮሚያ ያለው ግጭት ጉዳይ ተነስቷል።
ሌላው የቀድሞ ተዋጊዎችን ዲሞብላይዝ በማድረግ ወደ ማህበረሰቡ መልሶ ለመቀላቀልና ለማቋቋም ስለሚደረገው ስራ (DDR) ውይይት ተደርጓል።
በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ መካከል ያለውን ወታደራዊ ትብብር በማጠናከር ላይም ትኩርት ያደረገ ምክክር መደረጉን ከኤምባሲው የተገኘ መረጃ ያሳያል።
#USA #USEmbassy
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#USA
" እውነት ነው " - ትራምፕ
ዶናልድ ትራምፕ ሰነድ አልባ ስደተኞችን በገፍ በጅምላ ከሀገር ለማባረር ጦሩን (መከላከያውን) ሊጠቀሙ ይችላሉ ተብሏል።
ተመራጩ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ትራምፕ ፤ በምርጫ ዘመቻ ወቅት ለደጋፊዎቻቸው በገቡት ቃል መሰረት ሰነድ የሌላቸውን በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ስደተኞች ወደየመጡበት ሀገር ያባርራሉ።
ለዚህም በመላ ሀገሪቱ አስቸኳይ የአደጋ ጊዜ አዋጅ ሊያውጁ እንደሚችሉ እንዲሁም ስደተኞቹን ለማባረር የአሜሪካን ጦር ሃብት ሊጠቀሙ እንደሚችሉ ተነግሯል።
የጁዲሻል ዋች ፕሬዜዳንት የሆኑት ቶም ፊቶን ፥ ከዛሬ 10 ቀናት በፊት ትሩዝ በተሰኘው የትራንፕ የማህበራዊ ሚዲያው ላይ ቀጣዩ አስታዳደር በገፍ ስደተኞችን ከሀገር ለማባረር ብሄራዊ የአደጋ ጊዜ ሊያውጅ እና ወታደራዊ ንብረቶችንም ሊጠቀም እንደሚችል ፅፏል።
ትራምፕ ዛሬ " እውነት ነው !!! " ሲሉ የፊቶንን መረጃ አጋርተዋል።
ተመራጩ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቢሮ እንደገቡ የመጀመሪያ ስራቸው ስድተኞችን ከሀገር ማባረር እንደሆነ እየተነገረ ነው። በዚህም በርካታ ስድተኞች " ከአሜሪካ ልንባበረር ነው " በሚል ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ ወድቀዋል።
አንዳንድ ሰነድ የሌላቸው ስደተኞች የትራምፕ በጅምላ ስደተኞችን ማባረር የሚያተኩረው በ ' ወንጀለኞች ላይ ብቻ ነው ' የሚል ተስፋ አድርገዋል።
#USA #deportation
@tikvahethiopia
" እውነት ነው " - ትራምፕ
ዶናልድ ትራምፕ ሰነድ አልባ ስደተኞችን በገፍ በጅምላ ከሀገር ለማባረር ጦሩን (መከላከያውን) ሊጠቀሙ ይችላሉ ተብሏል።
ተመራጩ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ትራምፕ ፤ በምርጫ ዘመቻ ወቅት ለደጋፊዎቻቸው በገቡት ቃል መሰረት ሰነድ የሌላቸውን በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ስደተኞች ወደየመጡበት ሀገር ያባርራሉ።
ለዚህም በመላ ሀገሪቱ አስቸኳይ የአደጋ ጊዜ አዋጅ ሊያውጁ እንደሚችሉ እንዲሁም ስደተኞቹን ለማባረር የአሜሪካን ጦር ሃብት ሊጠቀሙ እንደሚችሉ ተነግሯል።
የጁዲሻል ዋች ፕሬዜዳንት የሆኑት ቶም ፊቶን ፥ ከዛሬ 10 ቀናት በፊት ትሩዝ በተሰኘው የትራንፕ የማህበራዊ ሚዲያው ላይ ቀጣዩ አስታዳደር በገፍ ስደተኞችን ከሀገር ለማባረር ብሄራዊ የአደጋ ጊዜ ሊያውጅ እና ወታደራዊ ንብረቶችንም ሊጠቀም እንደሚችል ፅፏል።
ትራምፕ ዛሬ " እውነት ነው !!! " ሲሉ የፊቶንን መረጃ አጋርተዋል።
ተመራጩ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቢሮ እንደገቡ የመጀመሪያ ስራቸው ስድተኞችን ከሀገር ማባረር እንደሆነ እየተነገረ ነው። በዚህም በርካታ ስድተኞች " ከአሜሪካ ልንባበረር ነው " በሚል ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ ወድቀዋል።
አንዳንድ ሰነድ የሌላቸው ስደተኞች የትራምፕ በጅምላ ስደተኞችን ማባረር የሚያተኩረው በ ' ወንጀለኞች ላይ ብቻ ነው ' የሚል ተስፋ አድርገዋል።
#USA #deportation
@tikvahethiopia
#USA
ተመራጩ የአሜሪካ ፕሬዜዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጾታቸውን የቀየሩ የሀገሪቱ ጦር አባላት ወታደሮችን እንደሚያግዱ ተነገረ።
ትራምፕ ሰዎች ተፈጥሯዊ ጾታዎችን መቀየር የለባቸውም ብለው ያምናሉ።
ይህን ተከትሎም ጾታቸውን የቀየሩ እና የሀገሪቱ ጦር አባላት የሆኑ ወታደሮችን ከስራ እንደሚያግዱ ዘ ታየምስ ዘግቧል።
እንደዘገባው ከሆነ 15 ሺህ ጾታቸውን የቀየሩ ወታደሮችን የማባረር እቅድ አላቸው።
ከዚህ በተጨማሪም ተፈጥሯዊ ጾታቸውን የቀየሩ አሜሪካዊያን የሀገሪቱን ጦር መቀላቀል እንዳይችሉ እገዳ እንደሚጥሉም ተገልጿል።
ዶኔልድ ትራምፕ በከ2016-2020 ድረስ በስልጣን ላይ በነበሩባቸው ዓመታት ውስጥ ተፈጥሯዊ ጾታቸውን የቀየሩ ዜጎች የአሜሪካ ጦርን እንዳይቀላቀሉ እገዳ ጥለው የነበረ ቢሆንም ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ይህንን እገዳ አንስተውታል።
ይህን መረጃ ዘ ታይምስን ዋቢ በማድረግ ያጋራው አል አይን ኒውስ ነው።
@tikvahethiopia
ተመራጩ የአሜሪካ ፕሬዜዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጾታቸውን የቀየሩ የሀገሪቱ ጦር አባላት ወታደሮችን እንደሚያግዱ ተነገረ።
ትራምፕ ሰዎች ተፈጥሯዊ ጾታዎችን መቀየር የለባቸውም ብለው ያምናሉ።
ይህን ተከትሎም ጾታቸውን የቀየሩ እና የሀገሪቱ ጦር አባላት የሆኑ ወታደሮችን ከስራ እንደሚያግዱ ዘ ታየምስ ዘግቧል።
እንደዘገባው ከሆነ 15 ሺህ ጾታቸውን የቀየሩ ወታደሮችን የማባረር እቅድ አላቸው።
ከዚህ በተጨማሪም ተፈጥሯዊ ጾታቸውን የቀየሩ አሜሪካዊያን የሀገሪቱን ጦር መቀላቀል እንዳይችሉ እገዳ እንደሚጥሉም ተገልጿል።
ዶኔልድ ትራምፕ በከ2016-2020 ድረስ በስልጣን ላይ በነበሩባቸው ዓመታት ውስጥ ተፈጥሯዊ ጾታቸውን የቀየሩ ዜጎች የአሜሪካ ጦርን እንዳይቀላቀሉ እገዳ ጥለው የነበረ ቢሆንም ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ይህንን እገዳ አንስተውታል።
ይህን መረጃ ዘ ታይምስን ዋቢ በማድረግ ያጋራው አል አይን ኒውስ ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#USA " እውነት ነው " - ትራምፕ ዶናልድ ትራምፕ ሰነድ አልባ ስደተኞችን በገፍ በጅምላ ከሀገር ለማባረር ጦሩን (መከላከያውን) ሊጠቀሙ ይችላሉ ተብሏል። ተመራጩ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ትራምፕ ፤ በምርጫ ዘመቻ ወቅት ለደጋፊዎቻቸው በገቡት ቃል መሰረት ሰነድ የሌላቸውን በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ስደተኞች ወደየመጡበት ሀገር ያባርራሉ። ለዚህም በመላ ሀገሪቱ አስቸኳይ የአደጋ ጊዜ አዋጅ ሊያውጁ እንደሚችሉ…
" ቤተሰብ መበታተን አልፈልግም ፤ ቤተሰቦች የማይለያዩበት ብቸኛው መንገድ ሁሉንም አንድ ላይ ከአገር ማባረር ነው " - ትራምፕ
ተመራጩ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከNBC ጋር ቆይታ አድርገው ነበር።
በዚህም ቆይታቸው ከስድተኞች ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን አንስተዋል።
ምን አሉ ?
ትራምፕ ወላጆቻቸው በውጭ አገራት ቢወለዱም በአሜሪካ የተወለዱ ልጆቻቸው ዜግነት የሚያገኙበትን መብት እሽራለሁ ብለዋል።
ወላጆቻቸው ሌላ ቦታ ቢወለዱም በአሜሪካ የሚወልዷቸው ልጆች የአሜሪካ ፓስፖርት የማግኘት መብት የሚሰጠውን በመወለድ የሚገኝ የዜግነት መብት ለማስቆም ፕሬዚዳንታዊ ትዕዛዝ እንደሚያስተላልፉ አሳውቀዋል።
በተለያዩ ምክንያቶች ተሰደው ወደ አሜሪካ የሄዱ ሰዎች የመኖሪያም ሆነ የዜግነት መብት ባያገኙም አሜሪካ ውስጥ የወለዷቸው ልጆች ዜግነትን ማግኘት ይችላሉ ታዲያ ትራምፕ ስራ ሲጀምሩ ይህንን ነው የሚሽሩት።
ሆኖም በልጅነታቸው ወደ አሜሪካ የመጡ ሰነድ የሌላቸው ስደተኞች ለመርዳት ከዴሞክራቶች ጋር እንደሚሰሩ ገልጸዋል።
🇺🇸 በመወለድ የሚገኝ የዜግነት መብት የአሜሪካ ህገ መንግሥት አንቀጽ 14ን መሰረት ያደረገ ነው። '' ማንኛውም አሜሪካ ውስጥ የተወለደ ወይም ተገቢውን ግዴታዎች የተወጣ ሰው የአሜሪካ ዜጋ የመሆን ሙሉ መብት አለው '' ይላል።
በሌላ በኩል ፤ ትራምፕ በምርጫ ቅስቀሳቸው ወቅት የአሜሪካ ዜግነት ያላቸው የቤተሰብ አባላት ያላቸውን ጨምሮ ህጋዊ ሰነዶች ያላሟሉ ስደተኞችን ከአገር ለማባረር የገቡትን ቃል ተግባራዊ እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል።
" ቤተሰብ መበተታተን አልፈልግም " ያሉት ትራምፕ " ስለዚህ ቤተሰቦች የማይለያዩበት ብቸኛው መንገድ ሁሉንም አንድ ላይ ከአገር ማባረር ነው " ብለዋል።
ትራምፕ በአንድ ወቅት ለመሰረዝ ሞክረው የነበረውን ወደ አሜሪካ ብቻቸውን ለሚመጡ ህጻናት ከለላ የሰጠውን የኦባማ 'ዲፈርድ አክሽን ፎር ቻይልድ ሁድ አራይቫልስ' በተሰኘው ፕሮግራም የታቀፉትን በተመለከተ ከምክር ቤቱ ጋር አብሬ እሰራለሁ ብለዋል።
" ከዴሞክራቶች ጋር በአንድ ዕቅድ ላይ እሰራለሁ " ያሉት ትራምፕ ከነዚህ ስደተኞች መካከል ጥቂቶች ጥሩ ስራ የያዙ በንግድ ላይ የተሰማሩም አሉ ሲሉ አክለዋል።
መረጃውን ኤንቢሲን ዋቢ በማድረግ ያጋራው ቢቢሲ ነው።
#USA #MASSDEPORTATION
@tikvahethiopia
ተመራጩ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከNBC ጋር ቆይታ አድርገው ነበር።
በዚህም ቆይታቸው ከስድተኞች ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን አንስተዋል።
ምን አሉ ?
ትራምፕ ወላጆቻቸው በውጭ አገራት ቢወለዱም በአሜሪካ የተወለዱ ልጆቻቸው ዜግነት የሚያገኙበትን መብት እሽራለሁ ብለዋል።
ወላጆቻቸው ሌላ ቦታ ቢወለዱም በአሜሪካ የሚወልዷቸው ልጆች የአሜሪካ ፓስፖርት የማግኘት መብት የሚሰጠውን በመወለድ የሚገኝ የዜግነት መብት ለማስቆም ፕሬዚዳንታዊ ትዕዛዝ እንደሚያስተላልፉ አሳውቀዋል።
በተለያዩ ምክንያቶች ተሰደው ወደ አሜሪካ የሄዱ ሰዎች የመኖሪያም ሆነ የዜግነት መብት ባያገኙም አሜሪካ ውስጥ የወለዷቸው ልጆች ዜግነትን ማግኘት ይችላሉ ታዲያ ትራምፕ ስራ ሲጀምሩ ይህንን ነው የሚሽሩት።
ሆኖም በልጅነታቸው ወደ አሜሪካ የመጡ ሰነድ የሌላቸው ስደተኞች ለመርዳት ከዴሞክራቶች ጋር እንደሚሰሩ ገልጸዋል።
🇺🇸 በመወለድ የሚገኝ የዜግነት መብት የአሜሪካ ህገ መንግሥት አንቀጽ 14ን መሰረት ያደረገ ነው። '' ማንኛውም አሜሪካ ውስጥ የተወለደ ወይም ተገቢውን ግዴታዎች የተወጣ ሰው የአሜሪካ ዜጋ የመሆን ሙሉ መብት አለው '' ይላል።
በሌላ በኩል ፤ ትራምፕ በምርጫ ቅስቀሳቸው ወቅት የአሜሪካ ዜግነት ያላቸው የቤተሰብ አባላት ያላቸውን ጨምሮ ህጋዊ ሰነዶች ያላሟሉ ስደተኞችን ከአገር ለማባረር የገቡትን ቃል ተግባራዊ እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል።
" ቤተሰብ መበተታተን አልፈልግም " ያሉት ትራምፕ " ስለዚህ ቤተሰቦች የማይለያዩበት ብቸኛው መንገድ ሁሉንም አንድ ላይ ከአገር ማባረር ነው " ብለዋል።
ትራምፕ በአንድ ወቅት ለመሰረዝ ሞክረው የነበረውን ወደ አሜሪካ ብቻቸውን ለሚመጡ ህጻናት ከለላ የሰጠውን የኦባማ 'ዲፈርድ አክሽን ፎር ቻይልድ ሁድ አራይቫልስ' በተሰኘው ፕሮግራም የታቀፉትን በተመለከተ ከምክር ቤቱ ጋር አብሬ እሰራለሁ ብለዋል።
" ከዴሞክራቶች ጋር በአንድ ዕቅድ ላይ እሰራለሁ " ያሉት ትራምፕ ከነዚህ ስደተኞች መካከል ጥቂቶች ጥሩ ስራ የያዙ በንግድ ላይ የተሰማሩም አሉ ሲሉ አክለዋል።
መረጃውን ኤንቢሲን ዋቢ በማድረግ ያጋራው ቢቢሲ ነው።
#USA #MASSDEPORTATION
@tikvahethiopia
#Ethiopia #USA #Starbucks
የአሜሪካው ' ስታርባክስ / Starbucks ' ኤክስኪዩቲቭ ቫይስ ፕሬዝዳንት ሚሼል በርን ኢትዮጵያ፣ አዲስ አበባ ይገኛሉ።
በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ማሲንጋ እና የUSAID ዳይሬክተር ሆክላንደር ለበርን አቀባበል አድርገውላቸዋል።
አሜሪካ በኤምባሲዋ በኩል የስታርባክስን አመራር " እንኳን ወደ ኢትዮጵያ፤ ወደ ቡና መገኛዋ ሀገር በደህና መጡ " ብላለች።
የስታር ባክስ አመራር ሚሼል በርን በኢትዮጵያ ቆይታቸው በኢንዱስትሪው ውስጥ ስላለው አስደናቂ እድገት፣ በምርታማነት ላይ ስላሉ ኢንቨስትመንቶች ይመክራሉ ተብሏል።
በተጨማሪም በኢትዮጵያ ላሉ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች የንፁህ ውሃ አቅርቦትን ማሳደግ በተመለከተ ይወያያሉ።
ስታር ባክስ (starbucks) በቡና አቅርቦቱ በመላው ዓለም የሚታወቅ ከፍተኛ ሃብት ያለው ኩባንያ ነው።
@tikvahethiopia
የአሜሪካው ' ስታርባክስ / Starbucks ' ኤክስኪዩቲቭ ቫይስ ፕሬዝዳንት ሚሼል በርን ኢትዮጵያ፣ አዲስ አበባ ይገኛሉ።
በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ማሲንጋ እና የUSAID ዳይሬክተር ሆክላንደር ለበርን አቀባበል አድርገውላቸዋል።
አሜሪካ በኤምባሲዋ በኩል የስታርባክስን አመራር " እንኳን ወደ ኢትዮጵያ፤ ወደ ቡና መገኛዋ ሀገር በደህና መጡ " ብላለች።
የስታር ባክስ አመራር ሚሼል በርን በኢትዮጵያ ቆይታቸው በኢንዱስትሪው ውስጥ ስላለው አስደናቂ እድገት፣ በምርታማነት ላይ ስላሉ ኢንቨስትመንቶች ይመክራሉ ተብሏል።
በተጨማሪም በኢትዮጵያ ላሉ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች የንፁህ ውሃ አቅርቦትን ማሳደግ በተመለከተ ይወያያሉ።
ስታር ባክስ (starbucks) በቡና አቅርቦቱ በመላው ዓለም የሚታወቅ ከፍተኛ ሃብት ያለው ኩባንያ ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#USA
በአሜሪካ ሀገር በደቡባዊ ካሊፎርኒያ አንድ አነስተኛ አውሮፕላን ተከስክሶ ሁለት ሰዎች መሞታቸው ተነግሯል።
19 ሰዎችም ተጎድተዋል።
አውሮፕላኑ የተከሰከሰው ፉለርተን በተሰኘ ከተማ በአንድ የፈርኒቸር ውጤቶች ማምረቻ ህንጻ አናት ላይ ነው።
በህንጻው ውስጥ 200 የሚደርሱ ሰራተኞች ስራ ላይ ነበሩም ተብሏል።
የሞቱት ሰዎች አውሮፕላኑ ውስጥ ከነበሩት መካካል እንደሆነ የሚታመን ሲሆን ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ደግሞ በህንጻው ውስጥ ስራ ላይ የነበሩት ናቸው።
አውሮፕላኑ ፉለርተን ከተባለ ኤርፖርት በተነሳ ከሁለት ደቂቃ ባነሰ ጊዜ ውስጥ ነው በህንጻው አናት ላይ የተከሰከሰው።
መንስኤው እየተጣራ መሆኑን የኤፒ መረጃ ያሳያል።
ሰሞኑን በዓለም አቀፍ ደረጃ ከአውሮፕላን ጋር የተያያዙ አደጋዎች ተደጋግመው ተሰምተዋል።
በደቡብ ኮሪያ ሙዋን ሲያርፍ የነበረ አውሮፕላን ላይ አደጋ ደርሶ አውሮፕላኑ ውስጥ ከነበሩት 181 ሰዎች 179 ሰዎች መሞታቸው ይታወሳል።
ሌላው ምንም እንኳን የተመዘገበ እጅግ የከፋ ጉዳት ባይኖርም በካናዳ፣ ሀሊፋክስ ኤርፖርት ሲያርፍ የነበረ 71 መንገደኞችን የጫነ አውሮፕላን በእሳት መያያዙና በሚያስደነግጥ ሁኔታ መቆሙ ሰሞኑን ከተሰሙት ክስተቶች መካከል ነው።
@tikvahethiopia
በአሜሪካ ሀገር በደቡባዊ ካሊፎርኒያ አንድ አነስተኛ አውሮፕላን ተከስክሶ ሁለት ሰዎች መሞታቸው ተነግሯል።
19 ሰዎችም ተጎድተዋል።
አውሮፕላኑ የተከሰከሰው ፉለርተን በተሰኘ ከተማ በአንድ የፈርኒቸር ውጤቶች ማምረቻ ህንጻ አናት ላይ ነው።
በህንጻው ውስጥ 200 የሚደርሱ ሰራተኞች ስራ ላይ ነበሩም ተብሏል።
የሞቱት ሰዎች አውሮፕላኑ ውስጥ ከነበሩት መካካል እንደሆነ የሚታመን ሲሆን ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ደግሞ በህንጻው ውስጥ ስራ ላይ የነበሩት ናቸው።
አውሮፕላኑ ፉለርተን ከተባለ ኤርፖርት በተነሳ ከሁለት ደቂቃ ባነሰ ጊዜ ውስጥ ነው በህንጻው አናት ላይ የተከሰከሰው።
መንስኤው እየተጣራ መሆኑን የኤፒ መረጃ ያሳያል።
ሰሞኑን በዓለም አቀፍ ደረጃ ከአውሮፕላን ጋር የተያያዙ አደጋዎች ተደጋግመው ተሰምተዋል።
በደቡብ ኮሪያ ሙዋን ሲያርፍ የነበረ አውሮፕላን ላይ አደጋ ደርሶ አውሮፕላኑ ውስጥ ከነበሩት 181 ሰዎች 179 ሰዎች መሞታቸው ይታወሳል።
ሌላው ምንም እንኳን የተመዘገበ እጅግ የከፋ ጉዳት ባይኖርም በካናዳ፣ ሀሊፋክስ ኤርፖርት ሲያርፍ የነበረ 71 መንገደኞችን የጫነ አውሮፕላን በእሳት መያያዙና በሚያስደነግጥ ሁኔታ መቆሙ ሰሞኑን ከተሰሙት ክስተቶች መካከል ነው።
@tikvahethiopia
#USA 🔥 በአሜሪካ ፤ በሎስ አንጀለስ ታሪክ አውዳሚ ነው በተባለ የሰደድ እሳት እስካሁን በውል ያልታወቁ ሰዎች ሲሞቱ ፤ በርካቶችም ተፈናቅለዋል።
እሳቱ በሎስ አንጀለስ ከተማ በብዙ ስፍራ እየተዛመተ ነው ተብሏል።
የሰደድ እሳቱ የሆሊውድ ምልክት በሚገኝበት የሆሊውድ ኮረብታማ ስፍራዎች ላይ እየተያያዘ መሆኑ ተነግሯል።
በሎስ አንጀለስ እና በአጎራባች ግዛቶች ቢያንስ 5 ሰደድ እሳቶች የተያያዙ ሲሆን ሶስቱን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር አልተቻለም።
1. ፓሊሳድስ
ፓሊሳድስ የተሰኘ መጠሪያ የተሰጠው ሰደድ እሳት በሎስ አንጀለስ የተቀሰቀሰው ማክሰኞ እለት ሲሆን በግዛቲቷ ትልቁ ነው። የፓስፊክ ፓሊሳድስ አካባቢን ጨምሮ ከ17 ሺህ 200 ሄክታር በላይ የሚሸፍን ሰፊ ግዛት አውድሟል።
2. ኢቶን
ኢቶን የተሰኘው ደግሞ በሰሜናዊ የሎስ አንጀለስ እን አልታዴና ባሉ ከተሞች እየተዛመተ የሚገኝ ሲሆን 10 ሺህ 600 ሄክታርን መሬት በመሸፈን በግዛቲቷ ሁለተኛው ትልቁ እሳት ሆኗል።
3. ኸረስት
ኸረትስ የተሰኘው ሰደድ እሳት ማክሰኞ እለት ተከስቶ ከሳን ፈርናንዶ በስተሰሜን በኩል እየተዛመተ ይገኛል። ይህም እሳት 855 ሄክታርን ይሸፍናል።
4. ሊዲያ
ይህ ደግሞ ረቡዕ ከሰዓት በኋላ በሎስ አንጀለስ በስተሰሜን ተራራማዋ አክቶን አካባቢ ተቀስቅሶ ወደ 350 ሄክታርን መሬት በመሸፈን ተዛምቷል።
5. ሰንሴት
ይህ ሰደድ እሳት ረቡዕ ምሽት ላይ በሆሊውድ ኮረብታማ ስፍራዎች የተከሰተው ሰደድ እሳት ሲሆን ከሰዓት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ወደ 20 ሄክታር እያደገ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት ወደ 43 ሄክታር ተዛምቷል።
ውድሌይ እና ኦሊቫስ የተሰኙት ሰደድ እሳቶች በአሁኑ ወቅት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የአካባቢው የእሳት አደጋ ባስልጣናት ገልጸዋል።
የመረጃው ምንጮች ፦ ቢቢሲ እና ሲኤንኤን ናቸው።
ቪድዮ ፦ ከማህበራዊ ሚዲያ
@tikvahethiopia
እሳቱ በሎስ አንጀለስ ከተማ በብዙ ስፍራ እየተዛመተ ነው ተብሏል።
የሰደድ እሳቱ የሆሊውድ ምልክት በሚገኝበት የሆሊውድ ኮረብታማ ስፍራዎች ላይ እየተያያዘ መሆኑ ተነግሯል።
በሎስ አንጀለስ እና በአጎራባች ግዛቶች ቢያንስ 5 ሰደድ እሳቶች የተያያዙ ሲሆን ሶስቱን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር አልተቻለም።
1. ፓሊሳድስ
ፓሊሳድስ የተሰኘ መጠሪያ የተሰጠው ሰደድ እሳት በሎስ አንጀለስ የተቀሰቀሰው ማክሰኞ እለት ሲሆን በግዛቲቷ ትልቁ ነው። የፓስፊክ ፓሊሳድስ አካባቢን ጨምሮ ከ17 ሺህ 200 ሄክታር በላይ የሚሸፍን ሰፊ ግዛት አውድሟል።
2. ኢቶን
ኢቶን የተሰኘው ደግሞ በሰሜናዊ የሎስ አንጀለስ እን አልታዴና ባሉ ከተሞች እየተዛመተ የሚገኝ ሲሆን 10 ሺህ 600 ሄክታርን መሬት በመሸፈን በግዛቲቷ ሁለተኛው ትልቁ እሳት ሆኗል።
3. ኸረስት
ኸረትስ የተሰኘው ሰደድ እሳት ማክሰኞ እለት ተከስቶ ከሳን ፈርናንዶ በስተሰሜን በኩል እየተዛመተ ይገኛል። ይህም እሳት 855 ሄክታርን ይሸፍናል።
4. ሊዲያ
ይህ ደግሞ ረቡዕ ከሰዓት በኋላ በሎስ አንጀለስ በስተሰሜን ተራራማዋ አክቶን አካባቢ ተቀስቅሶ ወደ 350 ሄክታርን መሬት በመሸፈን ተዛምቷል።
5. ሰንሴት
ይህ ሰደድ እሳት ረቡዕ ምሽት ላይ በሆሊውድ ኮረብታማ ስፍራዎች የተከሰተው ሰደድ እሳት ሲሆን ከሰዓት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ወደ 20 ሄክታር እያደገ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት ወደ 43 ሄክታር ተዛምቷል።
ውድሌይ እና ኦሊቫስ የተሰኙት ሰደድ እሳቶች በአሁኑ ወቅት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የአካባቢው የእሳት አደጋ ባስልጣናት ገልጸዋል።
የመረጃው ምንጮች ፦ ቢቢሲ እና ሲኤንኤን ናቸው።
ቪድዮ ፦ ከማህበራዊ ሚዲያ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#USA ዶናልድ ትራምፕ 47ኛው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ሆነው ቃለመሀላ ፈጸሙ።
ፕሬዚዳንቱ ወደ ቢሮ እንደገቡ 200 ገደማ ትዕዛዞች ላይ ፊርማቸውን እንደሚያኖሩ ተናግረዋል።
ፕሬዜዳንቱ ፊርማቸውን ከሚያኖሩባቸው ትዕዛዞች መካከል ፦
- በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰነድ አልባ ስደተኞችን ከአሜሪካ ማባረር ፤
- ጾታቸውን የቀየሩ (ትራንስጀንደር) ሰዎች በሴቶች ስፖርት ላይ እንዳይሳተፉ ማድረግ ፤
- ብዝሀነት፣ እኩልነትና አካታችነት የሚባሉ ፖሊሲዎችን ከጦር ሠራዊቱ ማስወገድ ዋነኞቹ ናቸው።
ትዕዛዞቻቸው በፍ/ቤት ሙግት ሊቀርብባቸው ይችላል ተብሎ ይጠበቃል።
@tikvahethiopia
ፕሬዚዳንቱ ወደ ቢሮ እንደገቡ 200 ገደማ ትዕዛዞች ላይ ፊርማቸውን እንደሚያኖሩ ተናግረዋል።
ፕሬዜዳንቱ ፊርማቸውን ከሚያኖሩባቸው ትዕዛዞች መካከል ፦
- በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰነድ አልባ ስደተኞችን ከአሜሪካ ማባረር ፤
- ጾታቸውን የቀየሩ (ትራንስጀንደር) ሰዎች በሴቶች ስፖርት ላይ እንዳይሳተፉ ማድረግ ፤
- ብዝሀነት፣ እኩልነትና አካታችነት የሚባሉ ፖሊሲዎችን ከጦር ሠራዊቱ ማስወገድ ዋነኞቹ ናቸው።
ትዕዛዞቻቸው በፍ/ቤት ሙግት ሊቀርብባቸው ይችላል ተብሎ ይጠበቃል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#USA ዶናልድ ትራምፕ 47ኛው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ሆነው ቃለመሀላ ፈጸሙ። ፕሬዚዳንቱ ወደ ቢሮ እንደገቡ 200 ገደማ ትዕዛዞች ላይ ፊርማቸውን እንደሚያኖሩ ተናግረዋል። ፕሬዜዳንቱ ፊርማቸውን ከሚያኖሩባቸው ትዕዛዞች መካከል ፦ - በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰነድ አልባ ስደተኞችን ከአሜሪካ ማባረር ፤ - ጾታቸውን የቀየሩ (ትራንስጀንደር) ሰዎች በሴቶች ስፖርት ላይ እንዳይሳተፉ ማድረግ ፤ - ብዝሀነት፣ እኩልነትና…
" ሁለት ፆታዎች ብቻ ነው ያሉት እነሱም #ወንድ እና #ሴት ናቸው " - ፕሬዝዳንት ትራምፕ
47ኛው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቢሮ እንደገቡ ከሚሰሯቸው ዋነኛ ስራዎች አንዱ በሀገሪቱ ለወንድ እና ሴት ፆታ ብቻ እውቅና መስጠት ነው።
ይህም በቀድሞው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ስልጣን የመልቀቂያ ጊዜ ለትራንስጀንደር / ፆታቸውን ለሚቀይሩ ሰዎች የሚሰጠውን ከለላና ጥበቃ የሚሽር ነው።
ለወንድ እና ለሴት ብቻ እውቅና መስጠት ትራፕም ከሚያስተላልፏቸው ትዕዛዛት አንዱና ዋነኛው እንደሆነ ታውቋል።
ትራምፕ ቃለ መሀላ ሲፈጽሙ ፥ " ከዛሬ ጀምሮ / ከእንግዲህ ወዲህ / የአሜሪካ መንግሥት ፖሊሲ እውቅና የሚሰጠው ለሁለት ፆታ ብቻ ነው እነሱም ወንድ እና ሴት " ሲሉ አስረግጠው ተናግረዋል።
የአሜሪካ መንግሥት ከአሁን በኃላ እውቅና የሚሰጠው ለወንድ እና ሴት ፆታ ብቻ እንዳሆነ የገለጹት ትራፕም ፤ ስልጣናቸውን ተጠቅመው ብዝሀነት፣ እኩልነትና አካታችነት የሚባሉ ፖሊሲዎችን ለማስወገድ የአፈጻሚ ትዕዛዝ እንደሚያስተላልፉ ተነግሯል።
ከዚህ ባለፈ ፕሬዚዳንት ትራምፕ ፤ ፆታቸውን የቀየሩ (ትራንስጀንደር) ሰዎች በሴቶች ስፖርት ላይ እንዳይሳተፉ የሚያደርግ ትዕዛዝም ያስተላልፋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ትራምፕ " ሰዎች ተፈጥሯዊ ፃታቸውን መቀየር የለባቸውም " ብለው የሚያምኑ ሲሆን ከዚህ ቀደም ፆታቸውን የቀየሩ የሀገሪቱ ጦር አባላት ወታደሮችን ከስራ እንደሚያግዱ መነገሩ ይታወሳል።
15 ሺህ ፆታቸውን የቀየሩ ወታደሮችን የማባረር እቅድ አላቸው።
ከዚህ በተጨማሪም ተፈጥሯዊ ጾታቸውን የቀየሩ አሜሪካዊያን የሀገሪቱን ጦር መቀላቀል እንዳይችሉ እገዳ እንደሚጥሉ መገለጹ የሚዘነጋ አይደለም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቪድዮው የፎክስ ኒውስ መሆኑን ይገልጻል።
#USA #PresidentDonaldTrump
@tikvahethiopia
47ኛው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቢሮ እንደገቡ ከሚሰሯቸው ዋነኛ ስራዎች አንዱ በሀገሪቱ ለወንድ እና ሴት ፆታ ብቻ እውቅና መስጠት ነው።
ይህም በቀድሞው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ስልጣን የመልቀቂያ ጊዜ ለትራንስጀንደር / ፆታቸውን ለሚቀይሩ ሰዎች የሚሰጠውን ከለላና ጥበቃ የሚሽር ነው።
ለወንድ እና ለሴት ብቻ እውቅና መስጠት ትራፕም ከሚያስተላልፏቸው ትዕዛዛት አንዱና ዋነኛው እንደሆነ ታውቋል።
ትራምፕ ቃለ መሀላ ሲፈጽሙ ፥ " ከዛሬ ጀምሮ / ከእንግዲህ ወዲህ / የአሜሪካ መንግሥት ፖሊሲ እውቅና የሚሰጠው ለሁለት ፆታ ብቻ ነው እነሱም ወንድ እና ሴት " ሲሉ አስረግጠው ተናግረዋል።
የአሜሪካ መንግሥት ከአሁን በኃላ እውቅና የሚሰጠው ለወንድ እና ሴት ፆታ ብቻ እንዳሆነ የገለጹት ትራፕም ፤ ስልጣናቸውን ተጠቅመው ብዝሀነት፣ እኩልነትና አካታችነት የሚባሉ ፖሊሲዎችን ለማስወገድ የአፈጻሚ ትዕዛዝ እንደሚያስተላልፉ ተነግሯል።
ከዚህ ባለፈ ፕሬዚዳንት ትራምፕ ፤ ፆታቸውን የቀየሩ (ትራንስጀንደር) ሰዎች በሴቶች ስፖርት ላይ እንዳይሳተፉ የሚያደርግ ትዕዛዝም ያስተላልፋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ትራምፕ " ሰዎች ተፈጥሯዊ ፃታቸውን መቀየር የለባቸውም " ብለው የሚያምኑ ሲሆን ከዚህ ቀደም ፆታቸውን የቀየሩ የሀገሪቱ ጦር አባላት ወታደሮችን ከስራ እንደሚያግዱ መነገሩ ይታወሳል።
15 ሺህ ፆታቸውን የቀየሩ ወታደሮችን የማባረር እቅድ አላቸው።
ከዚህ በተጨማሪም ተፈጥሯዊ ጾታቸውን የቀየሩ አሜሪካዊያን የሀገሪቱን ጦር መቀላቀል እንዳይችሉ እገዳ እንደሚጥሉ መገለጹ የሚዘነጋ አይደለም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቪድዮው የፎክስ ኒውስ መሆኑን ይገልጻል።
#USA #PresidentDonaldTrump
@tikvahethiopia
#USA
" ሥራችሁን በፈቃዳቸው ከለቀቃችሁ የ8 ወር ደመወዝ ጉርሻ እንሰጣችኋለን " - የትራምፕ አስተዳደር
አዲሱ የአሜሪካ ፕሬዜዳንት ዶናልድ ትረምፕ አስተዳደር፣ ፍላጎት ያላቸው የመንግሥት ሠራተኞች በመጪው መስከረም መጨረሻ ሥራቸውን በፈቃዳቸው የሚለቁ ከሆነ የ8 ወር ደመወዝ ጉርሻ እንደሚሰጥ ትላንት ለመንግሥት ሠራተኞች በላከው ኢሜይል አስታውቋል።
ፕሮግራሙ የዶናልድ ትረምፕ አስተዳደር የመንግሥት መሥሪያ ቤቶችንና ሠራተኞችን ለመቀነስ የያዘው ዕቅድ አካል መሆኑ ተመልክቷል።
ሠራተኞች ፍላጎታቸውን እስከ መጪው ሐሙስ ማለትም እአአ የካቲት 6 ቀን ድረስ ማሳወቅ እንዳለባቸው ተመልክቷል። ይህን የሚያደርጉ ሠራተኞች፣ የመንግሥት ሠራተኞች ሙሉ ለሙሉ ከቢሮ እንዲሠሩ የሚያዘው ደንብ ላይመለከታቸው እንደሚችል ታውቋል።
በስደተኞችና በብሔራዊ ፀጥታ ጉዳይ ላይ የሚሠሩ እንዲሁም የፖስታ ቤት ሠራተኞች ፕሮግራሙ እንደማይመለከታቸው ተመልክቷል።
የመንግሥት ሠራተኞችን የሚወክሉ የሠራተኛ ማኅበራት የአስተዳደሩን ሐሳብ ተቃውመዋል። ሠራተኞች እንዳይስማሙም መክረዋል።
“ የፌዴራል ሠራተኞች ታማኝ፣ አስተማማኝና በየቀኑ ለመሻሻል የሚጥሩ መሆን አለባቸው ” ብሏል ከትራምፕ አስተዳደር የተላከው መልዕክት፡፡
የአሜሪካ መንግሥት ሠራተኞች ፌዴሬሽን “ ሠራተኞች አዲሱ ፕሮግራም በፈቃደኝነት የሚያደርጉት ጉዳይ አድርገው እንዳያዩት” አሳስቧል።
የአስተዳደሩ ተግባር የሚያሳየው በመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ውስጥ ጤናማ ያልሆነ አካባቢን መፍጠርና ሠራተኞች መቆየት ቢሹ እንኳ ሥራቸውን መቀጠል እንዳይችሉ ለማድረግ ነው ብሏል።
#VOA
@tikvahethiopia
" ሥራችሁን በፈቃዳቸው ከለቀቃችሁ የ8 ወር ደመወዝ ጉርሻ እንሰጣችኋለን " - የትራምፕ አስተዳደር
አዲሱ የአሜሪካ ፕሬዜዳንት ዶናልድ ትረምፕ አስተዳደር፣ ፍላጎት ያላቸው የመንግሥት ሠራተኞች በመጪው መስከረም መጨረሻ ሥራቸውን በፈቃዳቸው የሚለቁ ከሆነ የ8 ወር ደመወዝ ጉርሻ እንደሚሰጥ ትላንት ለመንግሥት ሠራተኞች በላከው ኢሜይል አስታውቋል።
ፕሮግራሙ የዶናልድ ትረምፕ አስተዳደር የመንግሥት መሥሪያ ቤቶችንና ሠራተኞችን ለመቀነስ የያዘው ዕቅድ አካል መሆኑ ተመልክቷል።
ሠራተኞች ፍላጎታቸውን እስከ መጪው ሐሙስ ማለትም እአአ የካቲት 6 ቀን ድረስ ማሳወቅ እንዳለባቸው ተመልክቷል። ይህን የሚያደርጉ ሠራተኞች፣ የመንግሥት ሠራተኞች ሙሉ ለሙሉ ከቢሮ እንዲሠሩ የሚያዘው ደንብ ላይመለከታቸው እንደሚችል ታውቋል።
በስደተኞችና በብሔራዊ ፀጥታ ጉዳይ ላይ የሚሠሩ እንዲሁም የፖስታ ቤት ሠራተኞች ፕሮግራሙ እንደማይመለከታቸው ተመልክቷል።
የመንግሥት ሠራተኞችን የሚወክሉ የሠራተኛ ማኅበራት የአስተዳደሩን ሐሳብ ተቃውመዋል። ሠራተኞች እንዳይስማሙም መክረዋል።
“ የፌዴራል ሠራተኞች ታማኝ፣ አስተማማኝና በየቀኑ ለመሻሻል የሚጥሩ መሆን አለባቸው ” ብሏል ከትራምፕ አስተዳደር የተላከው መልዕክት፡፡
የአሜሪካ መንግሥት ሠራተኞች ፌዴሬሽን “ ሠራተኞች አዲሱ ፕሮግራም በፈቃደኝነት የሚያደርጉት ጉዳይ አድርገው እንዳያዩት” አሳስቧል።
የአስተዳደሩ ተግባር የሚያሳየው በመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ውስጥ ጤናማ ያልሆነ አካባቢን መፍጠርና ሠራተኞች መቆየት ቢሹ እንኳ ሥራቸውን መቀጠል እንዳይችሉ ለማድረግ ነው ብሏል።
#VOA
@tikvahethiopia
#USA
በአሜሪካ የመንገደኞች አውሮፕላን እና የወታደራዊ ሂሊኮፕተር በአየር ላይ ተላትመው ተከሰከሱ።
አደጋው ያጋጠመው በዋሽንግቶን ዲሲ በሀገሪቱ ሰዓት አቆጣጠር ምሽት 3:00 ላይ ነው።
የፒኤስኤ ንብረት የሆነው የበረራ ቁጥሩ 5342 የሆነና 60 መንገደኞችን እና 4 የበረራ ሰራተኞችን የያዘው አውሮፕላን ሬገን ዋሽንግተን ብሔራዊ ኤርፖርት ለማረፍ በተቃረበበት ሰዓት ነው 3 የአሜሪካ ጦር አባላትን ከያዘ ወታደራዊ ሂሊኮፕተር (ብላክ ሀውክ) ጋር የተላተመው።
አውሮፕላኑ እና ሂሊኮፕተሩ ' ፖቶማክ ወንዝ ' ላይ ነው የተከሰከሱት።
አደጋውን ተከትሎ የነፍስ አንድ ስራ እየተሰራ ሲሆን የሬገን ኤርፖርት ለጊዜው የአውሮፕላን በረራ ማድተናገድ አቁሟል።
የዲሲ ፖሊስ እስካሁን ስለ ሞቱ ሰዎች የተረጋገጠ መረጃ እንደሌለና የነፍስ አድን ስራ ላይ ርብርብ እየተደረገ እንደሆነ ገልጿል።
የአይን እማኞች ግጭቱ ሲፈጠር ከፍተኛ ብርሃን በአካባቢያቸው ታይቶ እነበር ጠቁመዋል።
የሀገሪቱ ፕሬዜዳንት ዶናልድ ትራምፕ " አሰቃቂ አደጋ " ሲሉ ገልጸው የተሰማቸውን ሀዘን አካፍለዋል።
ምክትል ፕሬዜዳንት ጄዲ ቫንስ ከአሰቃቂው አደጋ ሰዎች እንዲተርፉ ሁሉም በፀሎት እንዲተጋ ጥሪ አቅርበዋል።
የዋይት ሀውስ የፕሬስ ሴክሬታሪ ካሮሊን ሌቪት በኤክስ ገጻቸው ላይ " እግዚአብሔር ነፍሳቸውን ይማር " ብለዋል።
መረጃው ከኤስቢኤስ፣ ኒውስኤክስ፣ ቢቢሲ የተሰባሰበ ነው።
ቪድዮ ፦ avgeekjake
@tikvahethiopia
በአሜሪካ የመንገደኞች አውሮፕላን እና የወታደራዊ ሂሊኮፕተር በአየር ላይ ተላትመው ተከሰከሱ።
አደጋው ያጋጠመው በዋሽንግቶን ዲሲ በሀገሪቱ ሰዓት አቆጣጠር ምሽት 3:00 ላይ ነው።
የፒኤስኤ ንብረት የሆነው የበረራ ቁጥሩ 5342 የሆነና 60 መንገደኞችን እና 4 የበረራ ሰራተኞችን የያዘው አውሮፕላን ሬገን ዋሽንግተን ብሔራዊ ኤርፖርት ለማረፍ በተቃረበበት ሰዓት ነው 3 የአሜሪካ ጦር አባላትን ከያዘ ወታደራዊ ሂሊኮፕተር (ብላክ ሀውክ) ጋር የተላተመው።
አውሮፕላኑ እና ሂሊኮፕተሩ ' ፖቶማክ ወንዝ ' ላይ ነው የተከሰከሱት።
አደጋውን ተከትሎ የነፍስ አንድ ስራ እየተሰራ ሲሆን የሬገን ኤርፖርት ለጊዜው የአውሮፕላን በረራ ማድተናገድ አቁሟል።
የዲሲ ፖሊስ እስካሁን ስለ ሞቱ ሰዎች የተረጋገጠ መረጃ እንደሌለና የነፍስ አድን ስራ ላይ ርብርብ እየተደረገ እንደሆነ ገልጿል።
የአይን እማኞች ግጭቱ ሲፈጠር ከፍተኛ ብርሃን በአካባቢያቸው ታይቶ እነበር ጠቁመዋል።
የሀገሪቱ ፕሬዜዳንት ዶናልድ ትራምፕ " አሰቃቂ አደጋ " ሲሉ ገልጸው የተሰማቸውን ሀዘን አካፍለዋል።
ምክትል ፕሬዜዳንት ጄዲ ቫንስ ከአሰቃቂው አደጋ ሰዎች እንዲተርፉ ሁሉም በፀሎት እንዲተጋ ጥሪ አቅርበዋል።
የዋይት ሀውስ የፕሬስ ሴክሬታሪ ካሮሊን ሌቪት በኤክስ ገጻቸው ላይ " እግዚአብሔር ነፍሳቸውን ይማር " ብለዋል።
መረጃው ከኤስቢኤስ፣ ኒውስኤክስ፣ ቢቢሲ የተሰባሰበ ነው።
ቪድዮ ፦ avgeekjake
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " እስካሁን በህይወት የተገኘ የለም " በአሜሪካ ፤ ዋሽንግቶን ዲሲ የመንገደኞች አውሮፕላን ከጦር ሄሊኮፕተር ጋር ተላትሞ በ " ፖቶማክ ወንዝ " ውስጥ ከተከሰከሰበት አደጋ የነፍስ አድን ሰራተኞች እስካሁን አንድም ሰው በህይወት አላገኙም። የነፍስ አድን ስራው ግን መቀጠሉ ተነግሯል። አውሮፕላኑ 60 መንገደኞችን እና 4 የበረራ ሰራተኞችን ይዞ ነው 3 ሰው ከያዘው የጦር ሂሊኮፕተር ጋር…
#USA
" ታዳጊዋ በሕይወት ለመትረፍ ብዙ ታግላለች፤ በሚያሳዝን ሁኔታ ወደ ቤቷ ስትሄድ ነው ይህ ገጠማት " - ሬስኪዩ ኤር አምቡላንስ
በአሜሪካ፣ ፔንሲልቫኒያ ግዛት፣ በፊላደልፊያ ከተማ ሰሜን ምሥራቅ ክፍል አንድ አነስተኛ የሕክምና ማጓጓዣ አገልግሎት የሚሰጥ ጄት በርካታ ሕንጻዎች በሚገኙበት ሰፈር ውስጥ ተከሰከሰ።
የሕክምና አውሮፕላኑ ድርጅት-ሬስኪዩ ኤር አምቡላንስ በሰጠው መግለጫ ፤ ጄቱ አርብ ምሽት አንድ ታማሚ ሕፃንና አስታማሚዋን እናቷን እንዲሁም 4 የበረራ አስተናጋጆችን አሳፍሮ እየተጓዘ ነበር ።
በአውሮፕላኑ ላይ ተሳፍራ የነበረችው ሕፃን ሕይወቷን አደጋ ላይ በሚጥል የጤና እክል የነበረባት ሲሆን በአሜሪካ ሕክምና አድርጋ ወደ ሜክሲኮ ቲጁዋና እየተጓዘች እንደነበር የአየር አምቡላንስ ድርጅቱ ለኤንቢሲ ኒውስ ተናግረዋል።
ከእናት እና ልጅ በተጨማሪም አብራሪው ፣ረዳት አብራሪው ፣ ዶክተር እና የመድሃኒት ባለሙያ በአውሮፕላኑ ውስጥ ነበሩ።
ድርጅቱ " ታዳጊዋ በሕይወት ለመትረፍ ብዙ ታግላለች፤ በሚያሳዝን ሁኔታ ወደ ቤቷ ስትሄድ ነው ይህ ገጠማት " ብሏል።
አውሮፕላኑ በተከሰከሰበት አካባቢም ቤቶች እና ተሽከርካሪዎች በእሳት የተያያዙ ሲሆን መሬት ላይ የነበሩ ሰዎችም ለጉዳት መዳረጋቸው ተገልጿል።
የግዛቷ አስተዳዳር " የሕይወት መጥፋት እንደሚኖር እናውቃለን፤ አደጋው አሳዛኝ ነው " ብሏል።
የፊላደልፊያ ከንቲባ ቺርል ፓርከር የከተማዋ ባለስልጣናት በአደጋው የደረሰው ጉዳት መጠን ምን ያህል እንደሆነ አለማወቃቸውን ገልጸው ፤ በአደጋው የተጎዱ ወገኖችን በፀሎት እንዲታሰቡ ጠይቀዋል።
እስካሁን በህይወት ያለ ሰው ስለመኖሩ ማረጋገጥ አልተቻለም።
ከቀናት በፊት በዋሽንግቶን ዲሲ የመንገደኞች አውሮፕላን ከጦር ሄሊኮፕተር ጋር ተላትሞ ወንዝ ላይ ከተከሰከሰ በኃላ በህይወት የተረፈ ሰው አልተገኘም።
መረጃው ከቢቢሲ እና ኤንቢሲ ኒውስ የተውጣጣ ነው።
ቪድዮ ፦ ፌርበክ
@tikvahethiopia
" ታዳጊዋ በሕይወት ለመትረፍ ብዙ ታግላለች፤ በሚያሳዝን ሁኔታ ወደ ቤቷ ስትሄድ ነው ይህ ገጠማት " - ሬስኪዩ ኤር አምቡላንስ
በአሜሪካ፣ ፔንሲልቫኒያ ግዛት፣ በፊላደልፊያ ከተማ ሰሜን ምሥራቅ ክፍል አንድ አነስተኛ የሕክምና ማጓጓዣ አገልግሎት የሚሰጥ ጄት በርካታ ሕንጻዎች በሚገኙበት ሰፈር ውስጥ ተከሰከሰ።
የሕክምና አውሮፕላኑ ድርጅት-ሬስኪዩ ኤር አምቡላንስ በሰጠው መግለጫ ፤ ጄቱ አርብ ምሽት አንድ ታማሚ ሕፃንና አስታማሚዋን እናቷን እንዲሁም 4 የበረራ አስተናጋጆችን አሳፍሮ እየተጓዘ ነበር ።
በአውሮፕላኑ ላይ ተሳፍራ የነበረችው ሕፃን ሕይወቷን አደጋ ላይ በሚጥል የጤና እክል የነበረባት ሲሆን በአሜሪካ ሕክምና አድርጋ ወደ ሜክሲኮ ቲጁዋና እየተጓዘች እንደነበር የአየር አምቡላንስ ድርጅቱ ለኤንቢሲ ኒውስ ተናግረዋል።
ከእናት እና ልጅ በተጨማሪም አብራሪው ፣ረዳት አብራሪው ፣ ዶክተር እና የመድሃኒት ባለሙያ በአውሮፕላኑ ውስጥ ነበሩ።
ድርጅቱ " ታዳጊዋ በሕይወት ለመትረፍ ብዙ ታግላለች፤ በሚያሳዝን ሁኔታ ወደ ቤቷ ስትሄድ ነው ይህ ገጠማት " ብሏል።
አውሮፕላኑ በተከሰከሰበት አካባቢም ቤቶች እና ተሽከርካሪዎች በእሳት የተያያዙ ሲሆን መሬት ላይ የነበሩ ሰዎችም ለጉዳት መዳረጋቸው ተገልጿል።
የግዛቷ አስተዳዳር " የሕይወት መጥፋት እንደሚኖር እናውቃለን፤ አደጋው አሳዛኝ ነው " ብሏል።
የፊላደልፊያ ከንቲባ ቺርል ፓርከር የከተማዋ ባለስልጣናት በአደጋው የደረሰው ጉዳት መጠን ምን ያህል እንደሆነ አለማወቃቸውን ገልጸው ፤ በአደጋው የተጎዱ ወገኖችን በፀሎት እንዲታሰቡ ጠይቀዋል።
እስካሁን በህይወት ያለ ሰው ስለመኖሩ ማረጋገጥ አልተቻለም።
ከቀናት በፊት በዋሽንግቶን ዲሲ የመንገደኞች አውሮፕላን ከጦር ሄሊኮፕተር ጋር ተላትሞ ወንዝ ላይ ከተከሰከሰ በኃላ በህይወት የተረፈ ሰው አልተገኘም።
መረጃው ከቢቢሲ እና ኤንቢሲ ኒውስ የተውጣጣ ነው።
ቪድዮ ፦ ፌርበክ
@tikvahethiopia
#USA
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዓለም አቀፉ የጦር ወንጀለኞች ፍርድ ቤት (ICC) ላይ ማዕቀብ ጥለዋል።
ትራምፕ " በአሜሪካ እና የቅርብ አጋሯ እስራኤል ላይ ቅቡለነት እና መሠረት የሌለው ተግባር እየፈጸመ ነው " ሲሉ የከሰሱትን የዓለም አቀፉ የጦር የወንጀለኞች ፍርድ ቤት (ICC) ላይ ማዕቀብ የጣሉበት ፕሬዝዳንታዊ ትዕዛዝ ላይ ፈርመዋል።
ትራምፕ ICC ላይ የጣሉት ዕቀባ እና ቪዛን የሚያጠቃልል ነው።
የቪዛ ዕቀባው የአሜሪካ ወይም የአጋሯቿ ዜጎች ላይ ምርመራ የሚያደረጉትንና የሚረዱ ግለሰቦች እና ቤተሰቦቻችን ዒላማ ያደረገ ነው።
ታራምፕ ይህንን ፕሬዝዳንታዊ ትዕዛዝ የፈረሙት የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታኒያሁ ዋሽንግተንን እየጎበኙ ባሉበት ወቅት ነው።
ባለፈው ጥቅምት ዓለም አቀፉ የጦር ወንጀለኞች ፍርድ ኔታኒያሁ በጋዛ ፈጽመውታል ባለው የጦር ወንጀል ምክንያት የእስር ትዕዛዝ አውጥቶባቸው እንደነበር ይታወሳል።
አሜሪካ የዚህ ዓለም አቀፍ ተቋም አባል አይደለችም። በተደጋጋሚም በአሜሪካ ዜጎች ላይ በፍርድ ቤቱ የሚተላለፍ ውሳኔዎችን ውድቅ ማድረጓን ቢቢሲ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዓለም አቀፉ የጦር ወንጀለኞች ፍርድ ቤት (ICC) ላይ ማዕቀብ ጥለዋል።
ትራምፕ " በአሜሪካ እና የቅርብ አጋሯ እስራኤል ላይ ቅቡለነት እና መሠረት የሌለው ተግባር እየፈጸመ ነው " ሲሉ የከሰሱትን የዓለም አቀፉ የጦር የወንጀለኞች ፍርድ ቤት (ICC) ላይ ማዕቀብ የጣሉበት ፕሬዝዳንታዊ ትዕዛዝ ላይ ፈርመዋል።
ትራምፕ ICC ላይ የጣሉት ዕቀባ እና ቪዛን የሚያጠቃልል ነው።
የቪዛ ዕቀባው የአሜሪካ ወይም የአጋሯቿ ዜጎች ላይ ምርመራ የሚያደረጉትንና የሚረዱ ግለሰቦች እና ቤተሰቦቻችን ዒላማ ያደረገ ነው።
ታራምፕ ይህንን ፕሬዝዳንታዊ ትዕዛዝ የፈረሙት የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታኒያሁ ዋሽንግተንን እየጎበኙ ባሉበት ወቅት ነው።
ባለፈው ጥቅምት ዓለም አቀፉ የጦር ወንጀለኞች ፍርድ ኔታኒያሁ በጋዛ ፈጽመውታል ባለው የጦር ወንጀል ምክንያት የእስር ትዕዛዝ አውጥቶባቸው እንደነበር ይታወሳል።
አሜሪካ የዚህ ዓለም አቀፍ ተቋም አባል አይደለችም። በተደጋጋሚም በአሜሪካ ዜጎች ላይ በፍርድ ቤቱ የሚተላለፍ ውሳኔዎችን ውድቅ ማድረጓን ቢቢሲ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
#USA
አሜሪካ በአስገድዶ መድፈር ወንጀል ጥፋተኛ የተባለ ዜጋዋን አፍና ገደለች።
አሜሪካዊው የ52 ዓመቱ ድሜትሪስ ፍሬዘር በአስገድዶ መድፈር እና ግድያ ወንጀሎች ጥፋተኛ ሆኖ ተገኝቷል።
ግለሰቡ በአላባማ በርሚንግሀም ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ፓውሊን ብራውን የተባለች የ2 ልጆች እናትን በመኖሪያ ቤቷ ገብቶ አስገድዶ ከደፈረ በኋላ #እንደገደላት ተገልጿል።
በሌላ ጊዜ የ14 ታዳጊ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል መፈጸሙ መረጋገጡን ተከትሎ በተደራራቢ ወንጀሎች ክስ ተመስርቶበት ነበር።
ይህንንም ተከትሎ ተከሳሽ ድሚትሪስ ፍሬዘር በሞት ፍርድ እንዲቀጣ የተላለፈበት ሲሆን የፍርድ ሂደቱ የተካሄደው የሞት ፍርድ የማይተላለፍበት ሚቺጋን ግዛት ውስጥ በመሆኑ ፍርዱ ወደ እድሜ ልክ እስራት ተቀይሮለት ነበር።
በአላባማ ወንጀል መፈጸሙ በፍርድ ቤት መረጋገጡን ተከትሎ ወደ አላባማ እስር ቤት ተላልፎ ሊሰጥ ችሏል።
አላባማ ግዛት የሞት ፍርድ የተላለፈባቸው ፍርደኞችን አየር አጥሯቸው እንዲሞቱ የሚያደርግ ህግ ስላላት ይህም ወንጀለኛ በናይትሮጅን ጋዝ ታፍኖ ህይወቱ እንዲያልፍ መደረጉን ሮይተርስን ዋቢ በማድረግ አል አይን ኒውስ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
አሜሪካ በአስገድዶ መድፈር ወንጀል ጥፋተኛ የተባለ ዜጋዋን አፍና ገደለች።
አሜሪካዊው የ52 ዓመቱ ድሜትሪስ ፍሬዘር በአስገድዶ መድፈር እና ግድያ ወንጀሎች ጥፋተኛ ሆኖ ተገኝቷል።
ግለሰቡ በአላባማ በርሚንግሀም ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ፓውሊን ብራውን የተባለች የ2 ልጆች እናትን በመኖሪያ ቤቷ ገብቶ አስገድዶ ከደፈረ በኋላ #እንደገደላት ተገልጿል።
በሌላ ጊዜ የ14 ታዳጊ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል መፈጸሙ መረጋገጡን ተከትሎ በተደራራቢ ወንጀሎች ክስ ተመስርቶበት ነበር።
ይህንንም ተከትሎ ተከሳሽ ድሚትሪስ ፍሬዘር በሞት ፍርድ እንዲቀጣ የተላለፈበት ሲሆን የፍርድ ሂደቱ የተካሄደው የሞት ፍርድ የማይተላለፍበት ሚቺጋን ግዛት ውስጥ በመሆኑ ፍርዱ ወደ እድሜ ልክ እስራት ተቀይሮለት ነበር።
በአላባማ ወንጀል መፈጸሙ በፍርድ ቤት መረጋገጡን ተከትሎ ወደ አላባማ እስር ቤት ተላልፎ ሊሰጥ ችሏል።
አላባማ ግዛት የሞት ፍርድ የተላለፈባቸው ፍርደኞችን አየር አጥሯቸው እንዲሞቱ የሚያደርግ ህግ ስላላት ይህም ወንጀለኛ በናይትሮጅን ጋዝ ታፍኖ ህይወቱ እንዲያልፍ መደረጉን ሮይተርስን ዋቢ በማድረግ አል አይን ኒውስ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#USA " ታዳጊዋ በሕይወት ለመትረፍ ብዙ ታግላለች፤ በሚያሳዝን ሁኔታ ወደ ቤቷ ስትሄድ ነው ይህ ገጠማት " - ሬስኪዩ ኤር አምቡላንስ በአሜሪካ፣ ፔንሲልቫኒያ ግዛት፣ በፊላደልፊያ ከተማ ሰሜን ምሥራቅ ክፍል አንድ አነስተኛ የሕክምና ማጓጓዣ አገልግሎት የሚሰጥ ጄት በርካታ ሕንጻዎች በሚገኙበት ሰፈር ውስጥ ተከሰከሰ። የሕክምና አውሮፕላኑ ድርጅት-ሬስኪዩ ኤር አምቡላንስ በሰጠው መግለጫ ፤ ጄቱ አርብ…
#USA : ከቀናት በፊት በአሜሪካ አላስካ ግዛት 9 መንገደኞችን እና 1 አብራሪን ይዞ ሲጓዝ የነበረ አነስተኛ አውሮፕላን ደብዛው ጠፍቶ ከቆየ በኃላ በአየር እና ምድር በተደረገ አሰሳ ስብርባሪው ተገኝቷል።
በአደጋው በሕይወት የተረፈ ሰው የለም።
የ3 ሰዎች አስክሬን በነፍስ አድን ሰራተኞች ተገኝቷል።
ይህ አደጋ በአሜሪካ ከ1 ሳምንት ባነሰ ጊዜ የደረሰ 3ኛው የአቬዬይሽን አደጋ መሆኑን የቪኦኤ ዘገባ ያሳያል።
በአሜሪካ፣ ፔንሲልቫኒያ ግዛት፣ አንድ አነስተኛ የሕክምና ማጓጓዣ አገልግሎት የሚሰጥ ጄት በርካታ ሕንጻዎች በሚገኙበት ሰፈር ውስጥ ተከስክሶ በህይወት የተገኘ እንደሌለ ይታወቃል።
ከዚህ አደጋ በፊት ደግሞ በዋሽንግቶን ዲሲ 60 መንገደኞች እና 4 የበረራ ሰራተኞችን የያዘ የመንገደኞች አውሮፕላን 3 ሰዎች ከያዘ የጦር ሄሊኮፕተር ጋር ተላትሞ አንድም ሰው በህይወት አለመገኘቱ መገለጹ ይታወሳል።
@tikvahethiopia
በአደጋው በሕይወት የተረፈ ሰው የለም።
የ3 ሰዎች አስክሬን በነፍስ አድን ሰራተኞች ተገኝቷል።
ይህ አደጋ በአሜሪካ ከ1 ሳምንት ባነሰ ጊዜ የደረሰ 3ኛው የአቬዬይሽን አደጋ መሆኑን የቪኦኤ ዘገባ ያሳያል።
በአሜሪካ፣ ፔንሲልቫኒያ ግዛት፣ አንድ አነስተኛ የሕክምና ማጓጓዣ አገልግሎት የሚሰጥ ጄት በርካታ ሕንጻዎች በሚገኙበት ሰፈር ውስጥ ተከስክሶ በህይወት የተገኘ እንደሌለ ይታወቃል።
ከዚህ አደጋ በፊት ደግሞ በዋሽንግቶን ዲሲ 60 መንገደኞች እና 4 የበረራ ሰራተኞችን የያዘ የመንገደኞች አውሮፕላን 3 ሰዎች ከያዘ የጦር ሄሊኮፕተር ጋር ተላትሞ አንድም ሰው በህይወት አለመገኘቱ መገለጹ ይታወሳል።
@tikvahethiopia