#AddisAbaba : የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አዳዲስ ሹመቶችን ሰጥቷል።
አቶ ግርማ ሰይፉ ከኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ተነስተው የከተማ ውበትና አረንጏዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ ሆነው ተሹመዋል
ወ/ሮ ቆንጂት ደበለ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሆነዋል።
ከዚህ ባለፈ ወ/ሮ ኒዕመተላህ ከበደ የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ሆነዋል።
ወ/ሮ ይመኙሻል ታደሰ ከከተማ ውበትና አረንጏዴ ልማት ቢሮ ኃላፊነት ተነስተው የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ስራ አስኪያጅ ሆነው ተሹመዋል።
አቶ ሙባረክ ከማል የባህል ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ጽ/ቤት ኃላፊ ፤ አቶ ሁንዴ ከበደ - የባህል ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ የባህል ዘርፍ ምክትል ኃላፊ ሆነው መሾማቸው ታውቋል።
አቶ ታረቀኝ ገመቹ ደግሞ የንግድ ቢሮ ፅ/ቤት ኃላፊ ሆነዋል።
@tikvahethiopia
አቶ ግርማ ሰይፉ ከኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ተነስተው የከተማ ውበትና አረንጏዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ ሆነው ተሹመዋል
ወ/ሮ ቆንጂት ደበለ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሆነዋል።
ከዚህ ባለፈ ወ/ሮ ኒዕመተላህ ከበደ የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ሆነዋል።
ወ/ሮ ይመኙሻል ታደሰ ከከተማ ውበትና አረንጏዴ ልማት ቢሮ ኃላፊነት ተነስተው የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ስራ አስኪያጅ ሆነው ተሹመዋል።
አቶ ሙባረክ ከማል የባህል ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ጽ/ቤት ኃላፊ ፤ አቶ ሁንዴ ከበደ - የባህል ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ የባህል ዘርፍ ምክትል ኃላፊ ሆነው መሾማቸው ታውቋል።
አቶ ታረቀኝ ገመቹ ደግሞ የንግድ ቢሮ ፅ/ቤት ኃላፊ ሆነዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
" አየር መንገዱ ላደረገው ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ ማብራርያ እንዲሰጠን እንጠይቃለን " - የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር በክልሉ ትራንስፓርት እና መገናኛ ቢሮ በኩል ባወጣው መግለጫ ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አክሱም ህዳር ፅዮን ዓመታዊ ክብረ በዓል ለመሳተፍ በተጓዙ ወገኖች ላይ የተጋነነ የዋጋ ጭማሪ አድርጓል አለ።
ይኸው የተጋነነ ዋጋ ጭማሪ " ኢ-ፍትሃዊ እና አስደማሚ ነው " ብሎታል።
ቢሮ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ለፌደራል የትራንስፓርት ሚንስቴር በፃፈው ድብዳቤ እንደጠቆመው፤ " ተቋሙ የፈፀመው የተጋነነ የዋጋ ጭማሪ ታማኝነቱ ጥያቄ ውስጥ ከማስገባት ባለፈ ሌላ ፓለቲካዊ መልክ የሚያስይዝ ነው " ሲል አብራርተዋል።
ስለሆነም የበደላቸው ተጓዥ ደንበኞቹ እንዲክስ ፣ እንዲደግፍና ተግባሩ እንዲፈፅም ምክንያት የሆነውን በቂ ማብራርያ ለህዝብ እንዲሰጥ ቢሮው ጠይቋል።
ከአክሱም ህዳር ፅዮን በዓል ተጓዥ ተሳታፊዎች ጋር ተያይዞ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያደረገው የትኬት ጭማሪ የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ካቢኔ መወያያ አጀንዳ እንዳደረገው ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል መረጃ ማጋራቱ ይታወሳል።
#TikvahEthiopiaMekelle
@tikvahethiopia
" አየር መንገዱ ላደረገው ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ ማብራርያ እንዲሰጠን እንጠይቃለን " - የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር በክልሉ ትራንስፓርት እና መገናኛ ቢሮ በኩል ባወጣው መግለጫ ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አክሱም ህዳር ፅዮን ዓመታዊ ክብረ በዓል ለመሳተፍ በተጓዙ ወገኖች ላይ የተጋነነ የዋጋ ጭማሪ አድርጓል አለ።
ይኸው የተጋነነ ዋጋ ጭማሪ " ኢ-ፍትሃዊ እና አስደማሚ ነው " ብሎታል።
ቢሮ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ለፌደራል የትራንስፓርት ሚንስቴር በፃፈው ድብዳቤ እንደጠቆመው፤ " ተቋሙ የፈፀመው የተጋነነ የዋጋ ጭማሪ ታማኝነቱ ጥያቄ ውስጥ ከማስገባት ባለፈ ሌላ ፓለቲካዊ መልክ የሚያስይዝ ነው " ሲል አብራርተዋል።
ስለሆነም የበደላቸው ተጓዥ ደንበኞቹ እንዲክስ ፣ እንዲደግፍና ተግባሩ እንዲፈፅም ምክንያት የሆነውን በቂ ማብራርያ ለህዝብ እንዲሰጥ ቢሮው ጠይቋል።
ከአክሱም ህዳር ፅዮን በዓል ተጓዥ ተሳታፊዎች ጋር ተያይዞ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያደረገው የትኬት ጭማሪ የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ካቢኔ መወያያ አጀንዳ እንዳደረገው ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል መረጃ ማጋራቱ ይታወሳል።
#TikvahEthiopiaMekelle
@tikvahethiopia
#AddisAbaba
“ አንዳች ነገር ኮሽ ባላለበት ከተማ ‘ቦምብ ፈነዳ፣ ሰዎች ሞቱ ፣ የፓሊስ አባላት ሞቱ ’ እየተባለ ስለሚወራው ወሬ ራሱ ነዋሪው ነው የሚታዘባቸው ” - የአዲስ አበባ ፓሊስ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር “ ሰሚትና አያት አካባቢዎች የቦንብ ፍንዳታ ተከስቷል ” የሚሉ ወሬዎች ከትላንት ጀምሮ በX (ትዊተር) ላይ በስፋት ሲራወጡ ተስተውሏል።
ይህ መረጃ ዋና መነሻው የኢትዮጵያን ጉዳይ እየተከታተሉ ከሚፅፉ ገጾች ነው።
ጉዳዩን ግን በብዛት ሲያሰራጩት የተስተዋሉት ግብፃዊያን እና ሱማሊያዊያን ሲሆኑ፣ በቦምብ ፍንዳታው ሰዎች እደሞቱ ፣ የፓሊስ አባላት እንደተገደሉ ነው መረጃ ሲያሰራጩ የተስተዋሉት።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ በX (ቲዊተር) እየተራወጠ ያለውን መረጃ በተመለከተ የአዲስ አበባ ፓሊስ ኮሚሽንን መልዕክት እንዲያስተላልፍ ጠይቋል።
የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ፣ “ በከተማዋ ያለው ሰላም አስተማማኝ ነው ” ብዋል።
እንዲህ ያለ የሐሰተኛ መረጃ በሚነዙ አካላት ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ በአንክሮ ገልጸዋል።
ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ምን አሉ ?
“ ማንም በዬጫት ቤቱ ቁጭ ብሎ የሚያወራውን የመንግስት ተቋም ምላሽ የሚሰጥ ከሆነ በጣም አስቸጋሪ ነው የሚሆነው።
ማኀበራዊ ድረ ገጹ እንደሚታውቀው ነው።
በጣም ጥቂት ድረገጾች ናቸው ትክክለኛና ታማኝ መረጃ የሚዘግቡት እንጂ በአብዛኛው የከተማው ሰላም መሆን የሚያስጨንቃቸውም ስለሆኑ ዓይናቸው ደም ይለብሳል።
እንደዚህ ተወለደ ፣ እንደዚህ ተፈጠረ እያሉ ያልተፈጠረ ነገር እያወሩ ሰው በሰላም ገብቶ እንዳይወጣ ሽብር የመንዛት ሀሳብ ነው ያላቸው።
የከተማው ሰላም አስማማኝ መሆኑን 24 ሰዓት የነዋሪውን እንቅስቃሴ በማዬት ብቻ ማረጋገጥ ይቻላል። ምንም አይነት ጥናትም የሚያስፈልገው ጉዳይ አይደለም።
ከተማው 24 ሰዓት ክፍት ነው። አንዳች ነገር ኮሽ ባላለበት ከተማ ‘ቦምብ ፈነዳ፣ ሰዎች ሞቱ፣ የፓሊስ አባላት ሞቱ’ እየተባለ ስለሚወራው ወሬ ራሱ ነዋሪው ነው የሚታዘባቸው።
የተለመደ የበሬ ወለደ አይነት ወሬያቸው ነው። ዞሮ ዞሮ የከተማው ነዋሪ አሁን በጣም ገብቶታል። ለእነርሱ የሐሰት መረጃም ምንም ምላሽም አይሰጥም ትዝም አይለውም። መደበኛ ሥራውን ነው የሚምራው።
ከተማው አንዳችም የጸጥታ ችግር ያለበት ሁኔታ ላይ አይደለም። ሰላማዊ የሆነ እንቅስቃሴ ነው ያለው።
ምንም ነገር በሌለበት ሁኔታ እንደዚህ የሚሉ ግለሰቦችም ይሁኑ ቡድኖች ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ ነው መልዕክት ማስተላለፍ የምንፈልገው።
እንደ አዲስ አበባ ፓሊስ የከተማው የጸጥታ ጉዳይ በቀጥታ የሚመለከተው ነው። ኃላፊነትም ተቀብሎ እየተንቀሳቀሰበት ያለ ጉዳይ ነው። እንደዚህ አይነት ሥራ በሚሰሩ ሰዎች ላይ ሕጋዊ እርምጃ ይወስዳል። ” ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
“ አንዳች ነገር ኮሽ ባላለበት ከተማ ‘ቦምብ ፈነዳ፣ ሰዎች ሞቱ ፣ የፓሊስ አባላት ሞቱ ’ እየተባለ ስለሚወራው ወሬ ራሱ ነዋሪው ነው የሚታዘባቸው ” - የአዲስ አበባ ፓሊስ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር “ ሰሚትና አያት አካባቢዎች የቦንብ ፍንዳታ ተከስቷል ” የሚሉ ወሬዎች ከትላንት ጀምሮ በX (ትዊተር) ላይ በስፋት ሲራወጡ ተስተውሏል።
ይህ መረጃ ዋና መነሻው የኢትዮጵያን ጉዳይ እየተከታተሉ ከሚፅፉ ገጾች ነው።
ጉዳዩን ግን በብዛት ሲያሰራጩት የተስተዋሉት ግብፃዊያን እና ሱማሊያዊያን ሲሆኑ፣ በቦምብ ፍንዳታው ሰዎች እደሞቱ ፣ የፓሊስ አባላት እንደተገደሉ ነው መረጃ ሲያሰራጩ የተስተዋሉት።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ በX (ቲዊተር) እየተራወጠ ያለውን መረጃ በተመለከተ የአዲስ አበባ ፓሊስ ኮሚሽንን መልዕክት እንዲያስተላልፍ ጠይቋል።
የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ፣ “ በከተማዋ ያለው ሰላም አስተማማኝ ነው ” ብዋል።
እንዲህ ያለ የሐሰተኛ መረጃ በሚነዙ አካላት ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ በአንክሮ ገልጸዋል።
ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ምን አሉ ?
“ ማንም በዬጫት ቤቱ ቁጭ ብሎ የሚያወራውን የመንግስት ተቋም ምላሽ የሚሰጥ ከሆነ በጣም አስቸጋሪ ነው የሚሆነው።
ማኀበራዊ ድረ ገጹ እንደሚታውቀው ነው።
በጣም ጥቂት ድረገጾች ናቸው ትክክለኛና ታማኝ መረጃ የሚዘግቡት እንጂ በአብዛኛው የከተማው ሰላም መሆን የሚያስጨንቃቸውም ስለሆኑ ዓይናቸው ደም ይለብሳል።
እንደዚህ ተወለደ ፣ እንደዚህ ተፈጠረ እያሉ ያልተፈጠረ ነገር እያወሩ ሰው በሰላም ገብቶ እንዳይወጣ ሽብር የመንዛት ሀሳብ ነው ያላቸው።
የከተማው ሰላም አስማማኝ መሆኑን 24 ሰዓት የነዋሪውን እንቅስቃሴ በማዬት ብቻ ማረጋገጥ ይቻላል። ምንም አይነት ጥናትም የሚያስፈልገው ጉዳይ አይደለም።
ከተማው 24 ሰዓት ክፍት ነው። አንዳች ነገር ኮሽ ባላለበት ከተማ ‘ቦምብ ፈነዳ፣ ሰዎች ሞቱ፣ የፓሊስ አባላት ሞቱ’ እየተባለ ስለሚወራው ወሬ ራሱ ነዋሪው ነው የሚታዘባቸው።
የተለመደ የበሬ ወለደ አይነት ወሬያቸው ነው። ዞሮ ዞሮ የከተማው ነዋሪ አሁን በጣም ገብቶታል። ለእነርሱ የሐሰት መረጃም ምንም ምላሽም አይሰጥም ትዝም አይለውም። መደበኛ ሥራውን ነው የሚምራው።
ከተማው አንዳችም የጸጥታ ችግር ያለበት ሁኔታ ላይ አይደለም። ሰላማዊ የሆነ እንቅስቃሴ ነው ያለው።
ምንም ነገር በሌለበት ሁኔታ እንደዚህ የሚሉ ግለሰቦችም ይሁኑ ቡድኖች ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ ነው መልዕክት ማስተላለፍ የምንፈልገው።
እንደ አዲስ አበባ ፓሊስ የከተማው የጸጥታ ጉዳይ በቀጥታ የሚመለከተው ነው። ኃላፊነትም ተቀብሎ እየተንቀሳቀሰበት ያለ ጉዳይ ነው። እንደዚህ አይነት ሥራ በሚሰሩ ሰዎች ላይ ሕጋዊ እርምጃ ይወስዳል። ” ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
#DStvEthiopia
⚽️አዲስ ነገር ለኳስ አፍቃሪያን...
ሁሉንም ታላላቅ ሊጎች፣ ሁሉንም የቡድን ወኔ እንደ ምርጫችን በዲኤስቲቪ!
ℹ️ ሁሉንም የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታዎችን፣ የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ፣ ሎችም ዋና ዋና እግር ኳስ እና ምርጥ ምርጥ መዝናኛዎችን ያካተቱ ከ125 በላይ ቻናሎችን በወር በ1699 ብር ብቻ!
ደንብና ሁኔታዎች ተፈፀሚነት አላቸው! ለበለጠ መረጃ
👇
www.dstv.com/en-et
ዲኤስቲቪ ያስገቡ ፣ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇
https://bit.ly/3RFtEvh
#DStvEthiopia #ሁሉምያለውእኛጋርነው
⚽️አዲስ ነገር ለኳስ አፍቃሪያን...
ሁሉንም ታላላቅ ሊጎች፣ ሁሉንም የቡድን ወኔ እንደ ምርጫችን በዲኤስቲቪ!
ℹ️ ሁሉንም የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታዎችን፣ የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ፣ ሎችም ዋና ዋና እግር ኳስ እና ምርጥ ምርጥ መዝናኛዎችን ያካተቱ ከ125 በላይ ቻናሎችን በወር በ1699 ብር ብቻ!
ደንብና ሁኔታዎች ተፈፀሚነት አላቸው! ለበለጠ መረጃ
👇
www.dstv.com/en-et
ዲኤስቲቪ ያስገቡ ፣ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇
https://bit.ly/3RFtEvh
#DStvEthiopia #ሁሉምያለውእኛጋርነው
የኤርትራው ፕሬዝዳንት ምን አሉ ?
🔵 " ሕገ-መንግሥቱ ለውጥረት መንስዔ ከመሆኑም ባሻገር ሀገር ግንባታን የሚያስፋፋ አይደለም " - የኤርትራው ፕሬዝዳንት
የኤርትራው ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ ትላንት ምሽት በመንግሥታቸው የቴሌቪዥን ጣቢያ ቀርበው ስለወቅታዊ ጉዳዮች ቃለ-ምልልስ ሰጥተዋል።
ፕሬዝደንቱ ሶማሊያ፣ ግብፅ እና ሀገራቸው ኤርትራ ስለገቡት ስምምነት፣ በኢትዮጵያ በተለይ በትግራይ ክልል ስላለው ሁኔታ ተናግረዋል።
ምን አሉ ?
➡️ አሁን በኢትዮጵያ ያለው ግጭት እና ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያላት አለመስማማት የመነጨው በአውሮፓውያኑ 1994 ተግባራዊ በሆነው ሕገ-መንግሥት ነው (ብሔር ተኮር አሰራር የዘረጋ)። ሕገ-መንግሥቱ ለውጥረት መንስዔ ከመሆኑም ባሻገር ሀገር ግንባታን የሚያስፋፋ አይደለም።
➡️ ኢትዮጵያ ከራሷ ጋር ሰላም ካልፈጠረች ቀጣናው ለሚያስፈልገው መረጋጋት፣ ትብብር እና መቻቻል አዎንታዊ አስተዋፅዖ አይኖራትም።
➡️ የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት እንዲሁም ለ20 ዓመታት ያክል በባድመ ምክንያት በሁለቱ ሀገራት መካከል ሰፍኖ የቆየው ውጥረት የዚህ ፖሊሲ ውጤት ነው።
➡️ በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል ለነበረው የድንበር ግጭት የውጭ ኃይሎች ተጠያቂ ናቸው። በኢትዮጵያ አዲስ አስተዳደር [የዶ/ር ዐቢይ አሕመድ መንግሥት] ከመጣ በኋላ የተቀሰቀሰውም ጦርነት በዚህ አግባብ ሊታይ ይገባል።
(ፕሬዝደንቱ በቀጣናው እንዲሁም በመላው የአፍሪካ ቀንድ ግጭት እያስፋፉ ነው ያሏቸው የውጭ ኃይሎችን ማንነት በስም አልጠቀሱም)
➡️ ህወሓት በኢትዮጵያ የመጣውን ለውጥ ' አልቀበልም ' ብሎ ጦርነት ውስጥ በመግባት ኤርትራ ውስጥ ከ70 በላይ ዒላማዎችን በረዥም ርቀት ሮኬት መትቷል። የኤርትራ መንግሥት ህወሓት ከዚህ ድርጊቱ እንዲቆጠብ ያቀረበው ጥሪ ሰሚ አላገኘም።
➡️ ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በኋላ በአማራ ክልል ግጭት ተከስቷል። ከዚህ ጋር በተያያዘ በመንግሥታችን ላይ የሚነሳውን ወቀሳ አንቀበልም። ደም አፋሳሽ ጦርነት ውስጥ ከመግባት ሁሌም እንደሚቆጠቡ ነው የምናሳስበው።
➡️ ዓላማችን በቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት እንዲሰፍን ነው። የውጭ ኃይሎች ጣልቃ እንዲገቡ ክፍተት ላለመፈጠር እንሰራለን።
🔴 በትግራይ ክልል በተካሄደው ጦርነት የኤርትራ ሠራዊት መሳተፉ ይታወሳል። በዛም እጅግ በርካታ ግፍ እና የጦር ወንጀል በመፈጸም ይከሰሳል። ጦርነቱን ካስቆመው የፕሪቶሪያ ስምምነት በኋላ ግን የኤርትራ መንግሥት ከኢትዮጵያ ጋር ያለው ግንኙነት መቀዛቀዝ ተስተውሎበታል።
ከግብፅ እና ሶማሊያ ጋር ስላደረጉት ስምምነት ምን አሉ ?
ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር የባሕር በር የማግኘት የመግባቢያ ስምምነት ከተፈራረመች በኋላ ከሶማሊያ ጋር አለመግባባት ውስጥ እንደገባች ይወቃል።
ግብፅም በታላቁ የሕዳሴ ግድብ ምክንያት ከኢትዮጵያ ጋር አለመግባባት ውስጥ እንዳለች ይታወቃል።
ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር ላይ መተላለፊ እንዲሁም ሚና እንዲኖራት ያላትን ፍላጎት ይፋ ካደረገች በኋላ በቀጥታም ባይሆን ኤርትራ ደስተኛ አለመሆኗን ስታሳይ ነበር።
በዚህም የሶማሊያው ፕሬዝዳንት አንድ ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በኤርትራ ከሦስት ጊዜ በላይ ጉብኝት አድርገዋል።
በተጨማሪም ሶማሊያ ከግብፅ ጋር የወታደራዊ ስምምነት መፈራረሟን ተከትሎ አሥመራ ላይ የተፈረመው የጋራ ስምምነት ከኢትዮጵያ አንጻር መሆኑ በተደጋጋሚ ሲነገር ቆይቷል።
ነገር ግን የኤርትራው ፕሬዝዳንት ይህንን አስተባብለዋል።
ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ ፦
👉 የውጭ ኃይሎች እና አቀንቃኞች በመገናኛ ብዙኃን እና በማኅበራዊ ሚዲያ የሚያሠራጩት የተዛባ መረጃ እና ዘመቻ በቀጣናው ግጭት ያባብሳል።
👉 ይህ በመገናኛ ብዙኃን ላይ የሚሠራጨው የመነጨው ከልብ ለኢትየጵያ ከማሰብ አይደለም።
👉 በሦስቱ ሀገራት መካከል የተደረሰው ስምምነት ዋና ዓላማው በቀጣናዊ መረጋጋትን ማስፈን ነው።
👉 የኤርትራ ዋና ፍላጎት በመላው የአፍሪካ ቀንድ፣ በአባይ ተፋሰስ እና በቀይ ባሕር አጎራባች ሀገራት መረጋጋት እና ትብብር እንዲኖር ነው።
👉 ኤርትራ በፍፁም ኢትዮጵያ ያለመረጋጋት ውስጥ ገብታ የማየት ፍላጎት የላትም። በቀጣናው ሀገራት መካከል የሚደረሱ ስምምነቶች ያለመተማመንን ይቀርፋሉ፤ ፍሬያማም ናቸው።
... ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት ነው የወሰደው።
@tikvahethiopia
🔵 " ሕገ-መንግሥቱ ለውጥረት መንስዔ ከመሆኑም ባሻገር ሀገር ግንባታን የሚያስፋፋ አይደለም " - የኤርትራው ፕሬዝዳንት
የኤርትራው ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ ትላንት ምሽት በመንግሥታቸው የቴሌቪዥን ጣቢያ ቀርበው ስለወቅታዊ ጉዳዮች ቃለ-ምልልስ ሰጥተዋል።
ፕሬዝደንቱ ሶማሊያ፣ ግብፅ እና ሀገራቸው ኤርትራ ስለገቡት ስምምነት፣ በኢትዮጵያ በተለይ በትግራይ ክልል ስላለው ሁኔታ ተናግረዋል።
ምን አሉ ?
➡️ አሁን በኢትዮጵያ ያለው ግጭት እና ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያላት አለመስማማት የመነጨው በአውሮፓውያኑ 1994 ተግባራዊ በሆነው ሕገ-መንግሥት ነው (ብሔር ተኮር አሰራር የዘረጋ)። ሕገ-መንግሥቱ ለውጥረት መንስዔ ከመሆኑም ባሻገር ሀገር ግንባታን የሚያስፋፋ አይደለም።
➡️ ኢትዮጵያ ከራሷ ጋር ሰላም ካልፈጠረች ቀጣናው ለሚያስፈልገው መረጋጋት፣ ትብብር እና መቻቻል አዎንታዊ አስተዋፅዖ አይኖራትም።
➡️ የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት እንዲሁም ለ20 ዓመታት ያክል በባድመ ምክንያት በሁለቱ ሀገራት መካከል ሰፍኖ የቆየው ውጥረት የዚህ ፖሊሲ ውጤት ነው።
➡️ በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል ለነበረው የድንበር ግጭት የውጭ ኃይሎች ተጠያቂ ናቸው። በኢትዮጵያ አዲስ አስተዳደር [የዶ/ር ዐቢይ አሕመድ መንግሥት] ከመጣ በኋላ የተቀሰቀሰውም ጦርነት በዚህ አግባብ ሊታይ ይገባል።
(ፕሬዝደንቱ በቀጣናው እንዲሁም በመላው የአፍሪካ ቀንድ ግጭት እያስፋፉ ነው ያሏቸው የውጭ ኃይሎችን ማንነት በስም አልጠቀሱም)
➡️ ህወሓት በኢትዮጵያ የመጣውን ለውጥ ' አልቀበልም ' ብሎ ጦርነት ውስጥ በመግባት ኤርትራ ውስጥ ከ70 በላይ ዒላማዎችን በረዥም ርቀት ሮኬት መትቷል። የኤርትራ መንግሥት ህወሓት ከዚህ ድርጊቱ እንዲቆጠብ ያቀረበው ጥሪ ሰሚ አላገኘም።
➡️ ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በኋላ በአማራ ክልል ግጭት ተከስቷል። ከዚህ ጋር በተያያዘ በመንግሥታችን ላይ የሚነሳውን ወቀሳ አንቀበልም። ደም አፋሳሽ ጦርነት ውስጥ ከመግባት ሁሌም እንደሚቆጠቡ ነው የምናሳስበው።
➡️ ዓላማችን በቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት እንዲሰፍን ነው። የውጭ ኃይሎች ጣልቃ እንዲገቡ ክፍተት ላለመፈጠር እንሰራለን።
🔴 በትግራይ ክልል በተካሄደው ጦርነት የኤርትራ ሠራዊት መሳተፉ ይታወሳል። በዛም እጅግ በርካታ ግፍ እና የጦር ወንጀል በመፈጸም ይከሰሳል። ጦርነቱን ካስቆመው የፕሪቶሪያ ስምምነት በኋላ ግን የኤርትራ መንግሥት ከኢትዮጵያ ጋር ያለው ግንኙነት መቀዛቀዝ ተስተውሎበታል።
ከግብፅ እና ሶማሊያ ጋር ስላደረጉት ስምምነት ምን አሉ ?
ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር የባሕር በር የማግኘት የመግባቢያ ስምምነት ከተፈራረመች በኋላ ከሶማሊያ ጋር አለመግባባት ውስጥ እንደገባች ይወቃል።
ግብፅም በታላቁ የሕዳሴ ግድብ ምክንያት ከኢትዮጵያ ጋር አለመግባባት ውስጥ እንዳለች ይታወቃል።
ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር ላይ መተላለፊ እንዲሁም ሚና እንዲኖራት ያላትን ፍላጎት ይፋ ካደረገች በኋላ በቀጥታም ባይሆን ኤርትራ ደስተኛ አለመሆኗን ስታሳይ ነበር።
በዚህም የሶማሊያው ፕሬዝዳንት አንድ ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በኤርትራ ከሦስት ጊዜ በላይ ጉብኝት አድርገዋል።
በተጨማሪም ሶማሊያ ከግብፅ ጋር የወታደራዊ ስምምነት መፈራረሟን ተከትሎ አሥመራ ላይ የተፈረመው የጋራ ስምምነት ከኢትዮጵያ አንጻር መሆኑ በተደጋጋሚ ሲነገር ቆይቷል።
ነገር ግን የኤርትራው ፕሬዝዳንት ይህንን አስተባብለዋል።
ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ ፦
👉 የውጭ ኃይሎች እና አቀንቃኞች በመገናኛ ብዙኃን እና በማኅበራዊ ሚዲያ የሚያሠራጩት የተዛባ መረጃ እና ዘመቻ በቀጣናው ግጭት ያባብሳል።
👉 ይህ በመገናኛ ብዙኃን ላይ የሚሠራጨው የመነጨው ከልብ ለኢትየጵያ ከማሰብ አይደለም።
👉 በሦስቱ ሀገራት መካከል የተደረሰው ስምምነት ዋና ዓላማው በቀጣናዊ መረጋጋትን ማስፈን ነው።
👉 የኤርትራ ዋና ፍላጎት በመላው የአፍሪካ ቀንድ፣ በአባይ ተፋሰስ እና በቀይ ባሕር አጎራባች ሀገራት መረጋጋት እና ትብብር እንዲኖር ነው።
👉 ኤርትራ በፍፁም ኢትዮጵያ ያለመረጋጋት ውስጥ ገብታ የማየት ፍላጎት የላትም። በቀጣናው ሀገራት መካከል የሚደረሱ ስምምነቶች ያለመተማመንን ይቀርፋሉ፤ ፍሬያማም ናቸው።
... ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት ነው የወሰደው።
@tikvahethiopia
#ፍራንኮቫሉታ
የጉሙሩክ ኮሚሽን በፍራንኮ ቫሉታ ግዢ የተፈፀመባቸው ሽቀጦች ከአንድ ወር ባነሰ ጊዜ ዉስጥ ወደ ሃገር እንዲገቡ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
በፍራንኮ ቫሉታ ከውጭ የሚገቡ መሰረታዊ የፍጆታ ሸቀጦች በመደበኛ የንግድ ባንኮች የመተማመኛ ሰነድ /LC/ አማካኝነት እንዲገቡ መወሰኑን የገንዘብ ሚኒስትር ማስታወቁ ይታወሳል።
የጉምሩክ ኮሚሽን ህዳር 17 ቀን 2017 ዓ.ም. በፃፈዉ ደብዳቤ በፍራንኮ ቫሉታ ግዢ የተፈፀመባቸው ሸቀጦች በአንድ ወራት ባነሰ ጊዜ ዉስጥ ብቻ ወደ ሃገር ዉስጥ መግባት እንዳለባቸው አሳስቧል።
ኮሚሽኑ ይህን ያስተላለፈው የገንዘብ ሚኒስቴርን ዉሳኔ ተከትሎ መሆኑን ያስታወቀ ሲሆን ለሁሉም ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቶች እንዲያዉቁት አድርጓል።
መንግስት በመሰረታዊ የንግድ ሸቀጦች ላይ የምርት እጥረት እንዳይከሰት በማሰብ ለግል ባለሀብቶች ፍራንኮ ቫሉታ መፍቀዱ ይታወሳል፡፡
የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ህዳር 4 ቀን 2017 ዓ.ም. በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት ፍራንኮ ቫሉታ መሰረታዊ ሸቀጦችን ወደ ሀገር ውስጥ በማስገባት የምርት እጥረት እንዳይከሰት የተወሰነ እገዛ አድርጓል፡፡
ይሁን እንጂ የፍራንኮ ቫሉታ ባልተገባ መንገድ ለጥቁር ገበያ በመጋለጡ በውጭ ምንዛሬ ላይ ጫና በማሳደር ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ አመዝኗል ሲሉም ሚኒስትሩ ተናግረዋል ።
መሰረታዊ የፍጆታ ሸቀጦችን በፍራንኮ ቫሉታ ወደ ሀገር ውስጥ የማስገባት ውሳኔ ሙሉ በሙሉ እንዲቆም መደረጉንም የገለፁት አቶ አህመድ ሽዴ " በሂደት ላይ ያሉ ከውጭ የሚገቡ ሸቀጦች በሁለት ሳምንታት ውስጥ እንዲገቡ እንደሚደረግም " ተናግረው ነበር።
የጉምሩክ ኮሚሽን ከ ከጥቅም 28 ቀን 2017 ዓ.ም. በፊት የንግድ ሸቀጦች በፍራንኮቫሉታ ግዢ የተፈፀመባቸውን ሰነዶች በቅርንጫፍ ጽ/ቤት ያስመዘገቡ እና በዋና መስሪያቤት በኩል የተረጋገጡ አስመጪዎች በአንድ ወር ዉስጥ የንግድ ሸቀጣቸዉን አጠቃለዉ ወደ አገር ዉስጥ እንዲያስገቡ ነዉ ማሳሰቢያ የሰጠዉ።
መረጃው የካፒታል ጋዜጣ ነው።
@tikvahethiopia
የጉሙሩክ ኮሚሽን በፍራንኮ ቫሉታ ግዢ የተፈፀመባቸው ሽቀጦች ከአንድ ወር ባነሰ ጊዜ ዉስጥ ወደ ሃገር እንዲገቡ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
በፍራንኮ ቫሉታ ከውጭ የሚገቡ መሰረታዊ የፍጆታ ሸቀጦች በመደበኛ የንግድ ባንኮች የመተማመኛ ሰነድ /LC/ አማካኝነት እንዲገቡ መወሰኑን የገንዘብ ሚኒስትር ማስታወቁ ይታወሳል።
የጉምሩክ ኮሚሽን ህዳር 17 ቀን 2017 ዓ.ም. በፃፈዉ ደብዳቤ በፍራንኮ ቫሉታ ግዢ የተፈፀመባቸው ሸቀጦች በአንድ ወራት ባነሰ ጊዜ ዉስጥ ብቻ ወደ ሃገር ዉስጥ መግባት እንዳለባቸው አሳስቧል።
ኮሚሽኑ ይህን ያስተላለፈው የገንዘብ ሚኒስቴርን ዉሳኔ ተከትሎ መሆኑን ያስታወቀ ሲሆን ለሁሉም ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቶች እንዲያዉቁት አድርጓል።
መንግስት በመሰረታዊ የንግድ ሸቀጦች ላይ የምርት እጥረት እንዳይከሰት በማሰብ ለግል ባለሀብቶች ፍራንኮ ቫሉታ መፍቀዱ ይታወሳል፡፡
የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ህዳር 4 ቀን 2017 ዓ.ም. በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት ፍራንኮ ቫሉታ መሰረታዊ ሸቀጦችን ወደ ሀገር ውስጥ በማስገባት የምርት እጥረት እንዳይከሰት የተወሰነ እገዛ አድርጓል፡፡
ይሁን እንጂ የፍራንኮ ቫሉታ ባልተገባ መንገድ ለጥቁር ገበያ በመጋለጡ በውጭ ምንዛሬ ላይ ጫና በማሳደር ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ አመዝኗል ሲሉም ሚኒስትሩ ተናግረዋል ።
መሰረታዊ የፍጆታ ሸቀጦችን በፍራንኮ ቫሉታ ወደ ሀገር ውስጥ የማስገባት ውሳኔ ሙሉ በሙሉ እንዲቆም መደረጉንም የገለፁት አቶ አህመድ ሽዴ " በሂደት ላይ ያሉ ከውጭ የሚገቡ ሸቀጦች በሁለት ሳምንታት ውስጥ እንዲገቡ እንደሚደረግም " ተናግረው ነበር።
የጉምሩክ ኮሚሽን ከ ከጥቅም 28 ቀን 2017 ዓ.ም. በፊት የንግድ ሸቀጦች በፍራንኮቫሉታ ግዢ የተፈፀመባቸውን ሰነዶች በቅርንጫፍ ጽ/ቤት ያስመዘገቡ እና በዋና መስሪያቤት በኩል የተረጋገጡ አስመጪዎች በአንድ ወር ዉስጥ የንግድ ሸቀጣቸዉን አጠቃለዉ ወደ አገር ዉስጥ እንዲያስገቡ ነዉ ማሳሰቢያ የሰጠዉ።
መረጃው የካፒታል ጋዜጣ ነው።
@tikvahethiopia
#SavetheChildren #MoH
የህፃናት አድን ደርጅት (Save the children) በኢትዮጵያ በ3 ክልሎችበ16 ወረዳዎች የክትባት ተደራሽነትን ለማስፋፋት የሚረዳ “ቡስት” የተሰኘ ፕሮጀክት ይፋ አድርጓል።
ድርጅቱ ፕሮጀክቱን ይፋ ያደደረገው ከጂኤስኬ ተገኘ በተባለ የገንዘብ ድጋፍ ፣ ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ነው።
ፕሮጀክቱ በአማራ፣ ኦሮሚያና ሶማሌ ክልሎች በሚገኙ 16 ወረዳዎች ተግባራዊ ይደረጋል ተብሏል።
ክትባት በሚስጥበት ወቅት ገጠራማ በሆኑ ቦታዎች ለትራንስፓርት አገልግሎት የሚረዱ 50 ታብሌቶች የተገጠሙላቸው 52 ሞተር ሳይክሎችን ድርጅቱ አበርክቷል።
ድርጅቱ ፥ “ በዚህ ፕሮጀክት ከ200 ሺሕ በላይ ልጆች እንዲከተቡ ይደረጋል ” ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።
ቲክቫህ ለህጻናቱ የሚሰጡት ክትባት የምን በሽታ መከላከያ ነው ? ሲል ላቀገበው ጥያቄ “ በጤና ሚኒስቴር የተቀመጡትን 13ቱንም ክትባቶች ሳፓርት እናደርጋለን ” የሚል መልስ ከድርጅቱ ተሰጥቷል።
ክትባቱ ፦
- ሚዝልስ፣
- ፓሊዮ፣
- ዲያሪያ፣
- ኒሞኒያና ከመሳሰሉ ህመሞች የሚከላከል ነው ተብሏል።
የጤና ሚኒስቴር ሚኒስቴር ዴዔታ ዶ/ር ደረጄ ድጉማ “ በኢትዮጵያ ውስጥ ክትባት በአግባቡ ያልወሰዱና ጭራሽም ያልወሰዱ በርከት ያሉ ህፃናት አሉ ” ሲሉ ጠቁመዋል።
እኚህም ከ1 ሚሊዮን በላይ እንደሚሆኑ ገልጸዋል።
እነዚህም ራቅ ያሉ ቦታዎች ላይ የሚገኙ ናቸው።
ምንም ክትባት ያላገኙና ጀምረው ያቋረጡ ህፃናት በአብዛኛው በአማራ፣ ኦሮሚያና በሶማሌ ክልሎች እንደሚገኙ በጥናት መረጋገጡን ገልጸዋል።
ያንብቡ : https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-12-01
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የህፃናት አድን ደርጅት (Save the children) በኢትዮጵያ በ3 ክልሎችበ16 ወረዳዎች የክትባት ተደራሽነትን ለማስፋፋት የሚረዳ “ቡስት” የተሰኘ ፕሮጀክት ይፋ አድርጓል።
ድርጅቱ ፕሮጀክቱን ይፋ ያደደረገው ከጂኤስኬ ተገኘ በተባለ የገንዘብ ድጋፍ ፣ ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ነው።
ፕሮጀክቱ በአማራ፣ ኦሮሚያና ሶማሌ ክልሎች በሚገኙ 16 ወረዳዎች ተግባራዊ ይደረጋል ተብሏል።
ክትባት በሚስጥበት ወቅት ገጠራማ በሆኑ ቦታዎች ለትራንስፓርት አገልግሎት የሚረዱ 50 ታብሌቶች የተገጠሙላቸው 52 ሞተር ሳይክሎችን ድርጅቱ አበርክቷል።
ድርጅቱ ፥ “ በዚህ ፕሮጀክት ከ200 ሺሕ በላይ ልጆች እንዲከተቡ ይደረጋል ” ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።
ቲክቫህ ለህጻናቱ የሚሰጡት ክትባት የምን በሽታ መከላከያ ነው ? ሲል ላቀገበው ጥያቄ “ በጤና ሚኒስቴር የተቀመጡትን 13ቱንም ክትባቶች ሳፓርት እናደርጋለን ” የሚል መልስ ከድርጅቱ ተሰጥቷል።
ክትባቱ ፦
- ሚዝልስ፣
- ፓሊዮ፣
- ዲያሪያ፣
- ኒሞኒያና ከመሳሰሉ ህመሞች የሚከላከል ነው ተብሏል።
የጤና ሚኒስቴር ሚኒስቴር ዴዔታ ዶ/ር ደረጄ ድጉማ “ በኢትዮጵያ ውስጥ ክትባት በአግባቡ ያልወሰዱና ጭራሽም ያልወሰዱ በርከት ያሉ ህፃናት አሉ ” ሲሉ ጠቁመዋል።
እኚህም ከ1 ሚሊዮን በላይ እንደሚሆኑ ገልጸዋል።
እነዚህም ራቅ ያሉ ቦታዎች ላይ የሚገኙ ናቸው።
ምንም ክትባት ያላገኙና ጀምረው ያቋረጡ ህፃናት በአብዛኛው በአማራ፣ ኦሮሚያና በሶማሌ ክልሎች እንደሚገኙ በጥናት መረጋገጡን ገልጸዋል።
ያንብቡ : https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-12-01
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
#መቄዶንያ❤️
🔵 “ የጎዳና ኑሮ ከባድ ነው፣ የ85 ዓመት እናቶች ተደፍረው የመጡበት አጋጣሚዎች አሉ። ጎዳና ላይ ሰዎች በብርድ ምክንያት ይሞታሉ” - የክብር ዶክተር ቢኒያም በለጠ
🔴 “ ኢትዮጵያዊያን እባካችሁ ወደ ቀልባችን እንመለስ። ሰውን በመግደል፣ በማፈናቀል የምናገኘው ጥቅም የለም። ሰውን በመርዳት ግን ጥቅም ይገኛል ” - ቀሲስ ታጋይ ታደለ
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ ከመቄዶንያ በጎ አድራጎት ማኀበር ጋር በመተባበር ለመጀመሪያ ጊዜ በመቄዶንያን ቅጥር ግቢ ውስጥ አረጋዊያን በተገኙበት ዛሬ የጸሎት መርሀ ግብር አዘጋጅቶ ነበር።
ጸሎቱን የሰባቱም የሃይማኖት ተቋማት አባቶች ሁሉም በዬእምነታቸው መርሀ ግብሩን በጸሎት አስጀምረው፣ የጸሎት መርሀ ግብሩ ተከናውኗል።
የጸሎት ፕሮግራሙ ዓላማ አረጋዊያንን ጋር ተኩኖ ቢጸለይ ፈጣሪ ሰላሙን፣ ፍቅሩን እንደሚሰጥ በማሰብ እንዲሁም የካቲት 1 ቀን 2017 ዓ/ም በሚደረገው ለመቄዶንያ ርዳታ የማሰባሰብ መርሃ ግብር ሁሉም ኢትዮጵያውያን ርብርብ ያደርጉ ጥሪ ለማቅረብ ነው።
የመቄዶንያ መስራች የክብር ዶክተር ቢኒያም በለጠ ምን አሉ?
“ እንደሚታወቀው መቄዶኒያ የዘር፣ የሃይማኖት፣ የጾታ ልዩነት ሳያደርግ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች ነው የሚረዳው።
ሁሉም የእምነት ተከታዮች በመቄዶንያ አሉ። መቄዶንያ ውስጥ ፕሮቴስታንቶች፣ ሙስሊሞች፣ ኦሮቶዶክሶች፣ ካቶሊኮች አሉ።
እንዲያውም የሚጠበቅብን ምግብ፣ ልብስ መጠለያ ማሟላት ነው። ነገር ግን ከሚጠበቅበት በላይ ድርጅቱ መንፈሳዊ ፍላጎቶችንም ጭምር እያሟላ ይገኛል።
ዛሬ ስለመጣችሁ በጣም ደስ ብሎናል ምክንያቱም ሁሉም የሃይማኖት ተከታዮች እዚህ ስላሉ እናንተን ሲያዩ በጣም ደስ ይላቸዋል። ወደፊትም በሚመቻችሁ ጊዜ እንደዚሁ እየመጣችሁ ብትጎበኙን በጣም ደስ ይለናል።
በአሁኑ ወቅት በጣም በርካታ ሰዎች እየረዳን እንገኛለን። 5 ወለል ያለው ህንጻ እየገነባን እንገኛለን። በክልሎችም እንደዚሁ በተለያዩ ቦታዎች ግንባታዎች እየተፋጠኑ ይገኛሉ።
ደሴ፣ ድሬዳዋ፣ ጋምቤላ፣ ኮንሶ፣ ሞያሌ፣ ያቤሎ፣ ጅማ፣ አምቦ፣ ዓዲግራት፣ ዓድዋና ሌሎችም ቦታዎች መቄዶንያ አለ። በተለይ ደግሞ እኛ የምንረዳቸው የአልጋ ቁራኛ፣ የጎዳና ነዋሪ የሆኑ ሰዎችን ነው።
የጎዳና ኑሮ በጣም ከባድ ነው፣ የሚገርማችሁ የ85 ዓመት እናቶች ተደፍረው እዚህ የመጡበት አጋጣሚዎች አሉ። ጎዳና ላይ ሰዎች በብርድ ምክንያት ይሞታሉ። ብርድ የመታቸው ሰዎች ወደ ህክምና የሚወስዳቸው የለም ” ብለዋል።
በመሆኑም የካቲት 1 ቀን 2017 ዓ/ም በሚደረገው ዓለም አቀፍ ገቢ የማሰባሰብ መርሀ ግብር፣ ሁሉም አካላት ከወዲሁ ዝግጅት እንዲያደርጉ በ8,000 አረጋዊያን ስም ጥሪ አቅርበዋል።
በመርሀ ግብሩ የተገኙት የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ የበላይ ፀሐፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ በበኩላቸው፣ መርሀ ግብሩ የተዘጋጀው ከአረጋዊያኑ ጋር ቢጸለይ ፈጣሪ ጸሎት ይሰማን ተብሎ ታስቦ መሆኑን አስረድተዋል።
ቀሲስ ታጋይ ምን አሉ ?
“ ዛሬ በመቄዶንያ የተገኘነው ሁለት ጉዳዮችን መሠረት አድርገን ነው። አንደኛው ጸሎት ለማድረግ ነው።
በአገር ሰላም ላይ ሁሉም ኢትዮጵያዊያን የድርሻቸውን እንዲወጡ በማሰብ ጸሎት ማድረግና የሰላም ጥሪ የቀረበላቸው ወገኖች ወደ ሰላም እንዲመለሱ አስቸኳይ ሁኔታ ለመፍጠር የተደረገ ነው።
ሁለተኛው በመቄዶንያ የተገኘንበት ምክንያት በመቄዶንያ ከ8,000 የሚልቁ ለችግር የተጋለጡ፣ ጎዳና ላይ የወደቁ ኢትዮጵያዊያን ምዕመናን፣ ሙስሊሞች ክርስቲያኖች በኀብረት አሉ።
ስለዚህ ከእነርሱ ጋር ሆነን ብንጸልይ፣ ወደ ፈጣሪ ብናነባ ፈጣሪ ምህረት፣ ቸርነት ያደርግልናል በሚል እሳቤና መቄዶንያም መደገፍ ስላለበት ድጋፍ እንዲደረግለት በዚሁ አጋጣሚ ጥሪ ለማቅረብ ነው።
ስለዚህ ኢትዮጵያዊያን እባካችሁ ወደ ቀልባችን እንመለስ። ሰውን በመግደል፣ በማፈናቀል የምናገኘው ጥቅም የለም። ሰውን በመርዳት ግን ጥቅም ይገኛል። ሰላምን በማረጋገጥ ግን ጥቅም ይገኛል ” ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
🔵 “ የጎዳና ኑሮ ከባድ ነው፣ የ85 ዓመት እናቶች ተደፍረው የመጡበት አጋጣሚዎች አሉ። ጎዳና ላይ ሰዎች በብርድ ምክንያት ይሞታሉ” - የክብር ዶክተር ቢኒያም በለጠ
🔴 “ ኢትዮጵያዊያን እባካችሁ ወደ ቀልባችን እንመለስ። ሰውን በመግደል፣ በማፈናቀል የምናገኘው ጥቅም የለም። ሰውን በመርዳት ግን ጥቅም ይገኛል ” - ቀሲስ ታጋይ ታደለ
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ ከመቄዶንያ በጎ አድራጎት ማኀበር ጋር በመተባበር ለመጀመሪያ ጊዜ በመቄዶንያን ቅጥር ግቢ ውስጥ አረጋዊያን በተገኙበት ዛሬ የጸሎት መርሀ ግብር አዘጋጅቶ ነበር።
ጸሎቱን የሰባቱም የሃይማኖት ተቋማት አባቶች ሁሉም በዬእምነታቸው መርሀ ግብሩን በጸሎት አስጀምረው፣ የጸሎት መርሀ ግብሩ ተከናውኗል።
የጸሎት ፕሮግራሙ ዓላማ አረጋዊያንን ጋር ተኩኖ ቢጸለይ ፈጣሪ ሰላሙን፣ ፍቅሩን እንደሚሰጥ በማሰብ እንዲሁም የካቲት 1 ቀን 2017 ዓ/ም በሚደረገው ለመቄዶንያ ርዳታ የማሰባሰብ መርሃ ግብር ሁሉም ኢትዮጵያውያን ርብርብ ያደርጉ ጥሪ ለማቅረብ ነው።
የመቄዶንያ መስራች የክብር ዶክተር ቢኒያም በለጠ ምን አሉ?
“ እንደሚታወቀው መቄዶኒያ የዘር፣ የሃይማኖት፣ የጾታ ልዩነት ሳያደርግ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች ነው የሚረዳው።
ሁሉም የእምነት ተከታዮች በመቄዶንያ አሉ። መቄዶንያ ውስጥ ፕሮቴስታንቶች፣ ሙስሊሞች፣ ኦሮቶዶክሶች፣ ካቶሊኮች አሉ።
እንዲያውም የሚጠበቅብን ምግብ፣ ልብስ መጠለያ ማሟላት ነው። ነገር ግን ከሚጠበቅበት በላይ ድርጅቱ መንፈሳዊ ፍላጎቶችንም ጭምር እያሟላ ይገኛል።
ዛሬ ስለመጣችሁ በጣም ደስ ብሎናል ምክንያቱም ሁሉም የሃይማኖት ተከታዮች እዚህ ስላሉ እናንተን ሲያዩ በጣም ደስ ይላቸዋል። ወደፊትም በሚመቻችሁ ጊዜ እንደዚሁ እየመጣችሁ ብትጎበኙን በጣም ደስ ይለናል።
በአሁኑ ወቅት በጣም በርካታ ሰዎች እየረዳን እንገኛለን። 5 ወለል ያለው ህንጻ እየገነባን እንገኛለን። በክልሎችም እንደዚሁ በተለያዩ ቦታዎች ግንባታዎች እየተፋጠኑ ይገኛሉ።
ደሴ፣ ድሬዳዋ፣ ጋምቤላ፣ ኮንሶ፣ ሞያሌ፣ ያቤሎ፣ ጅማ፣ አምቦ፣ ዓዲግራት፣ ዓድዋና ሌሎችም ቦታዎች መቄዶንያ አለ። በተለይ ደግሞ እኛ የምንረዳቸው የአልጋ ቁራኛ፣ የጎዳና ነዋሪ የሆኑ ሰዎችን ነው።
የጎዳና ኑሮ በጣም ከባድ ነው፣ የሚገርማችሁ የ85 ዓመት እናቶች ተደፍረው እዚህ የመጡበት አጋጣሚዎች አሉ። ጎዳና ላይ ሰዎች በብርድ ምክንያት ይሞታሉ። ብርድ የመታቸው ሰዎች ወደ ህክምና የሚወስዳቸው የለም ” ብለዋል።
በመሆኑም የካቲት 1 ቀን 2017 ዓ/ም በሚደረገው ዓለም አቀፍ ገቢ የማሰባሰብ መርሀ ግብር፣ ሁሉም አካላት ከወዲሁ ዝግጅት እንዲያደርጉ በ8,000 አረጋዊያን ስም ጥሪ አቅርበዋል።
በመርሀ ግብሩ የተገኙት የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ የበላይ ፀሐፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ በበኩላቸው፣ መርሀ ግብሩ የተዘጋጀው ከአረጋዊያኑ ጋር ቢጸለይ ፈጣሪ ጸሎት ይሰማን ተብሎ ታስቦ መሆኑን አስረድተዋል።
ቀሲስ ታጋይ ምን አሉ ?
“ ዛሬ በመቄዶንያ የተገኘነው ሁለት ጉዳዮችን መሠረት አድርገን ነው። አንደኛው ጸሎት ለማድረግ ነው።
በአገር ሰላም ላይ ሁሉም ኢትዮጵያዊያን የድርሻቸውን እንዲወጡ በማሰብ ጸሎት ማድረግና የሰላም ጥሪ የቀረበላቸው ወገኖች ወደ ሰላም እንዲመለሱ አስቸኳይ ሁኔታ ለመፍጠር የተደረገ ነው።
ሁለተኛው በመቄዶንያ የተገኘንበት ምክንያት በመቄዶንያ ከ8,000 የሚልቁ ለችግር የተጋለጡ፣ ጎዳና ላይ የወደቁ ኢትዮጵያዊያን ምዕመናን፣ ሙስሊሞች ክርስቲያኖች በኀብረት አሉ።
ስለዚህ ከእነርሱ ጋር ሆነን ብንጸልይ፣ ወደ ፈጣሪ ብናነባ ፈጣሪ ምህረት፣ ቸርነት ያደርግልናል በሚል እሳቤና መቄዶንያም መደገፍ ስላለበት ድጋፍ እንዲደረግለት በዚሁ አጋጣሚ ጥሪ ለማቅረብ ነው።
ስለዚህ ኢትዮጵያዊያን እባካችሁ ወደ ቀልባችን እንመለስ። ሰውን በመግደል፣ በማፈናቀል የምናገኘው ጥቅም የለም። ሰውን በመርዳት ግን ጥቅም ይገኛል። ሰላምን በማረጋገጥ ግን ጥቅም ይገኛል ” ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia