TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#አሳዛኝ_የትራፊክ_አደጋ

ዛሬ በባንጃ ወረዳ " ዚቅ ጎመርታ " ቀበሌ በተከሰተ የትራፊክ አደጋ የሠው ህይወት አለፈ።

ዛሬ መጋቢት 22/2015 ዓ.ም በባንጃ ወረዳ ዚቅ ጎመርታ ቀበሌ 2:00 ሰአት አካባቢ የ " ዳሳሽ አካዳሚ ት/ት ቤት " ተማሪዎችን ወደቻግኒ ታሪካዊ ቦታዎችን ለማስጎብኘት ይዞ እየሔደ እያለ በደረሠ የትራፊክ አደጋ 3 የህፃናት ወዲያውኑ ህይወታቸው አልፏል።

አንድ ህፃን እና አንዲት መምህር ደግሞ ወደ ህከምና እንደደረሱ ህይወታቸው አልፏል።

ሌሎች ከባድና ቀላል ጉዳት የደረሰባቸው ህፃናት ወደ እንጅባራ ጠቅላላ ሆስፒታል ገብተው ህክምና እየተደረገላቸው ይገኛል። ወደ ህክምና ከገቡት መካከል 4ቱ አገግመው ወደ ቤተሠቦቻቸው ተቀላቅለዋል።

ወረዳው ተጨማሪ ዝርዝር መረጃዎችን እንደሚሰጥ ገልጿል።

@tikvahethiopia
😢1.8K👍15674🕊48🙏36😱21🥰11👎1