TIKVAH-ETHIOPIA
የአቶ በቴ ኡርጌሳ ምርመራ ከምን ደረሰ ? “ ... ምርመራው ተጀምሯል ፤ እየቀጠለ ነው ” - ኢሰመኮ በኦሮሚያ ክልል፣ መቂ ከተማ ተገደሉትን የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ከፍተኛ አመራር አቶ በቴ ኡርጌሳን ጉዳይ በተመለከተ በርካታ መረጃዎች አድርሰናችሁ ነበር። ሰሞኑን ደግሞ ፦ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በአቶ በቴ ኡርጌሳ ግድያ ላይ የጀመረውን ምርመራ በደረሰበት ጫና ማቆሙን…
" በቴ ምን ያህል ለህዝቡ አስፈላጊ እንደነበር በህዝቡ ሁኔታ፣ በህዝቡ ለቅሶ ተመልክቻለሁ ! " - የፖለቲከኛ አቶ በቴ ኡርጌሳ ባለቤት
ከወራት በፊት መቂ ላይ በግፍ የተገደሉት የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ከፍተኛ አመራር ፖለቲከኛው አቶ በቴ ኡርጌሳ ባለቤት ከልጆቻቸው ጋር ከሀገር ወጥተው አሜሪካ መግባታቸው ተሰምቷል።
ባለቤታቸው ወ/ሮ ስንታየሁ አንበሴ በአጭር ቪድዮ ባሰራጩት ቃላቸው ፥ አሁን ላይ ከልጆቻቸው ጋር አሜሪካ ሀገር እንደሚገኙ ገልጸዋል።
" ባለቤቴ በቴ ኡርጌሳ ከሞተ 7ኛ ወር ሊሞላ ነው። " ብለዋል።
" በዓለም ላይ ያላችሁ ሃዘናችንን የተካፈላችሁ ፣ የኦሮሞ ኮሚውኒቲ ፤ በቴ ምን ያህል ለህዝቡ አስፈላጊ እንዳሆነ በሃዘናችሁ ፤ ባለው ነገር ሁሉ አይተናል " ሲሉ ገልጸዋል።
" እሱ ካረፈበት ቀን ጀምሮ በሀዘናችን ያለቀሳችሁ፣ ከኛ ጋር ያዘናችሁ ፣ በገንዘባችሁ በሃሳባችሁ በጸሎታችሁ የረዳችሁን እግዚአብሔር ይስጥልን ፤ እናመሰግናለን " ብለዋል።
" የኛን ሰላም መሆን ለተጨነቃችሁ ፤ ድምጻችን ሲጠፋ ለተጨነቃችሁ ' ምን ሆናችሁ ነው ? ' ላላችሁን ያለንበትን ለመግለፅ ነው ፤ አሁን ያለነው አሜሪካ ነው ፤ በሰላም ደርሰናል " ሲሉ ገልጸዋል።
" ኤምባሲዎች በጣም እናመሰግናለን ፤ ያለንበት ቦታ ድምጻችን የጠፋባችሁ ስልካችን እንቢ ያላችሁ ፣ ቤታችን ድረስ ሄዳችሁ ያጣችሁን ምን ሆናችሁ ነው ? ላለችሁን ላደረጋችሁልን ነገር ሁሉ እናመሰግናለን " ብለዋል።
" በቴ ምን ያህል ለህዝቡ አስፈላጊ እንደነበር በህዝቡ ሁኔታ፣ ለቅሶ ተመልክቻለሁ " ያሉት ወ/ሮ ስንታየሁ " እኔ እውነት ለመናገር በቴ ከሞተ በኃላ ነው ህዝቡ እንዴት በቴን ያውቅ እንደነበር የተረዳሁት ምክንያቱም በቴን እንደዚህ አላውቀውም ነበር እውነቱን ለመናገር ከጫፍ ጫፍ ነው ህዝቡ ያዘነው " ሲሉ በእምባ ታጅበው ስሜታቸውን ገልጸዋል።
እምባቸውን 😭 እያፈሰሱ የተናገሩት የበቴ ባለቤት " እሱ የኢትዮጵያ ብቻ አይደለም የዓለም ሰው እንደሆነ አውቃለሁ " ብለዋል።
አሁንም ከጎናቸው ሆነው በብዙ ነገር እየረዷቸው ላሉ በተለይ ለኦሮሞ ኮሚውኒቲ ፣ በውጭ ሆነው በስልክ እየደወሉ እያፅናኗቸው ያሉ፣ በፀሎታቸው ፣ በገንዘብ እየደገፏቸው ላሉ ሁሉ " እግዚአብሔር ይስጥልን " ሲሉ አመስግነዋል።
ወ/ሮ ስንታየው አንበሴ ፤ ልጆቻቸው ደህንነታቸው የተጠበቀ ቦታ ላይ እንዳሉና ትምህርትም እንደጀመሩ ገልጸዋል።
ወደፊት ጊዜው ሲደርስ ደግሞ ስላሳለፉት ነገር እንደሚገልጹ ቃል ገብተዋል።
ለተደረገላቸው ነገር ሁሉ እያነቡ በልጆቻቸው ስም ምስጋና አቅርበዋል።
የአምስት ልጆች አባቱ ፖለቲከኛው በቴ ኡርጌሳ ከወራት በፊት መቂ ላይ በግፍ መገደላቸው ይታወሳል። ከዛ በኃላ " ማጣራት ተደርጎ ስለ ግድያው ዝርዝር ማብራሪያ ለህዝቡ ይሰጣል " ተብሎ ቃል ቢገባም እስከ ዛሬ ስለ ግድያው ሁኔታ ፣ ከግድያው ጋር በተያያዘ ተጠያቂ ስለሆነ አካል በይፋ አንድም የተባለ ነገር የለም።
የፖለቲከኛ አቶ በቴ ኡርጌሳ ጉዳይ " ቄሱም ዝም መፅሃፉም ዝም " እንዲሉ ሆኖ ቀጥሏል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
ከወራት በፊት መቂ ላይ በግፍ የተገደሉት የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ከፍተኛ አመራር ፖለቲከኛው አቶ በቴ ኡርጌሳ ባለቤት ከልጆቻቸው ጋር ከሀገር ወጥተው አሜሪካ መግባታቸው ተሰምቷል።
ባለቤታቸው ወ/ሮ ስንታየሁ አንበሴ በአጭር ቪድዮ ባሰራጩት ቃላቸው ፥ አሁን ላይ ከልጆቻቸው ጋር አሜሪካ ሀገር እንደሚገኙ ገልጸዋል።
" ባለቤቴ በቴ ኡርጌሳ ከሞተ 7ኛ ወር ሊሞላ ነው። " ብለዋል።
" በዓለም ላይ ያላችሁ ሃዘናችንን የተካፈላችሁ ፣ የኦሮሞ ኮሚውኒቲ ፤ በቴ ምን ያህል ለህዝቡ አስፈላጊ እንዳሆነ በሃዘናችሁ ፤ ባለው ነገር ሁሉ አይተናል " ሲሉ ገልጸዋል።
" እሱ ካረፈበት ቀን ጀምሮ በሀዘናችን ያለቀሳችሁ፣ ከኛ ጋር ያዘናችሁ ፣ በገንዘባችሁ በሃሳባችሁ በጸሎታችሁ የረዳችሁን እግዚአብሔር ይስጥልን ፤ እናመሰግናለን " ብለዋል።
" የኛን ሰላም መሆን ለተጨነቃችሁ ፤ ድምጻችን ሲጠፋ ለተጨነቃችሁ ' ምን ሆናችሁ ነው ? ' ላላችሁን ያለንበትን ለመግለፅ ነው ፤ አሁን ያለነው አሜሪካ ነው ፤ በሰላም ደርሰናል " ሲሉ ገልጸዋል።
" ኤምባሲዎች በጣም እናመሰግናለን ፤ ያለንበት ቦታ ድምጻችን የጠፋባችሁ ስልካችን እንቢ ያላችሁ ፣ ቤታችን ድረስ ሄዳችሁ ያጣችሁን ምን ሆናችሁ ነው ? ላለችሁን ላደረጋችሁልን ነገር ሁሉ እናመሰግናለን " ብለዋል።
" በቴ ምን ያህል ለህዝቡ አስፈላጊ እንደነበር በህዝቡ ሁኔታ፣ ለቅሶ ተመልክቻለሁ " ያሉት ወ/ሮ ስንታየሁ " እኔ እውነት ለመናገር በቴ ከሞተ በኃላ ነው ህዝቡ እንዴት በቴን ያውቅ እንደነበር የተረዳሁት ምክንያቱም በቴን እንደዚህ አላውቀውም ነበር እውነቱን ለመናገር ከጫፍ ጫፍ ነው ህዝቡ ያዘነው " ሲሉ በእምባ ታጅበው ስሜታቸውን ገልጸዋል።
እምባቸውን 😭 እያፈሰሱ የተናገሩት የበቴ ባለቤት " እሱ የኢትዮጵያ ብቻ አይደለም የዓለም ሰው እንደሆነ አውቃለሁ " ብለዋል።
አሁንም ከጎናቸው ሆነው በብዙ ነገር እየረዷቸው ላሉ በተለይ ለኦሮሞ ኮሚውኒቲ ፣ በውጭ ሆነው በስልክ እየደወሉ እያፅናኗቸው ያሉ፣ በፀሎታቸው ፣ በገንዘብ እየደገፏቸው ላሉ ሁሉ " እግዚአብሔር ይስጥልን " ሲሉ አመስግነዋል።
ወ/ሮ ስንታየው አንበሴ ፤ ልጆቻቸው ደህንነታቸው የተጠበቀ ቦታ ላይ እንዳሉና ትምህርትም እንደጀመሩ ገልጸዋል።
ወደፊት ጊዜው ሲደርስ ደግሞ ስላሳለፉት ነገር እንደሚገልጹ ቃል ገብተዋል።
ለተደረገላቸው ነገር ሁሉ እያነቡ በልጆቻቸው ስም ምስጋና አቅርበዋል።
የአምስት ልጆች አባቱ ፖለቲከኛው በቴ ኡርጌሳ ከወራት በፊት መቂ ላይ በግፍ መገደላቸው ይታወሳል። ከዛ በኃላ " ማጣራት ተደርጎ ስለ ግድያው ዝርዝር ማብራሪያ ለህዝቡ ይሰጣል " ተብሎ ቃል ቢገባም እስከ ዛሬ ስለ ግድያው ሁኔታ ፣ ከግድያው ጋር በተያያዘ ተጠያቂ ስለሆነ አካል በይፋ አንድም የተባለ ነገር የለም።
የፖለቲከኛ አቶ በቴ ኡርጌሳ ጉዳይ " ቄሱም ዝም መፅሃፉም ዝም " እንዲሉ ሆኖ ቀጥሏል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
#InfinixEthiopia
የዛንዚባር የቢዝነስ ክላስ ደርሶ መልስ የአውሮፕላን ቲኬት፣ የኢንፊኒክስ ስማርት ቲቪ፣ የኢንፊኒክስ ላፕቶፕ እንዲሁም ሌሎች አጓጊ ሽልማቶችን ኢንፊኒክስ ስማርት ስልኮች የሆኑትን ሆት 40 ፣ ኖት 40 ፣ ዜሮ 40 እና የኢንፊኒክስ ስማርት TVን ሲገበያዩ ኩፖን በመውሰድ አብሮት ካለ ወዳጅ ዘመድ ወይም ጓደኛ ጋር በመረጡት ስፍራ ፎቶ በመነሳት #InfinixEthiopia የሚለውን ሃሽ ታግ በመጠቀም እና ማህበራዊ ሚዲያ ላይ በመለጠፍ ማሸነፍ ይችላሉ ይፍጠኑ የዚህ ልዩ የሽልማት ፕሮግራም አካል ይሁኑ፡፡
መመሪያ
1. የኢንፊኒክስ ኢትዮጵያን ፌስ ቡክ ፣ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ገጾችን ፎሎው ያድርጉ፡፡
2. የተነሱትን ፎቶ በመረጡት ማህበራዊ ሚዲያ ሲለጥፉ የኢንፊኒክስ ኢትዮጵያን ገፅ ከፖስቶት ጋር ታግ ያድርጉ፡፡
3. #InfinixEthiopia የሚለውን ሃሽታግ መጠቀሞን አይርሱ፡፡
Tag ሲያደርጉ ለ Facebook @InfinixMobileEthiopia ፣ ለ Instagram @infinixethiopia ለ TikTok @Infinixet እና ለ Telegram @Infinixeth ሜንሽን ማድረግ እንዳይረሱ።
የዛንዚባር የቢዝነስ ክላስ ደርሶ መልስ የአውሮፕላን ቲኬት፣ የኢንፊኒክስ ስማርት ቲቪ፣ የኢንፊኒክስ ላፕቶፕ እንዲሁም ሌሎች አጓጊ ሽልማቶችን ኢንፊኒክስ ስማርት ስልኮች የሆኑትን ሆት 40 ፣ ኖት 40 ፣ ዜሮ 40 እና የኢንፊኒክስ ስማርት TVን ሲገበያዩ ኩፖን በመውሰድ አብሮት ካለ ወዳጅ ዘመድ ወይም ጓደኛ ጋር በመረጡት ስፍራ ፎቶ በመነሳት #InfinixEthiopia የሚለውን ሃሽ ታግ በመጠቀም እና ማህበራዊ ሚዲያ ላይ በመለጠፍ ማሸነፍ ይችላሉ ይፍጠኑ የዚህ ልዩ የሽልማት ፕሮግራም አካል ይሁኑ፡፡
መመሪያ
1. የኢንፊኒክስ ኢትዮጵያን ፌስ ቡክ ፣ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ገጾችን ፎሎው ያድርጉ፡፡
2. የተነሱትን ፎቶ በመረጡት ማህበራዊ ሚዲያ ሲለጥፉ የኢንፊኒክስ ኢትዮጵያን ገፅ ከፖስቶት ጋር ታግ ያድርጉ፡፡
3. #InfinixEthiopia የሚለውን ሃሽታግ መጠቀሞን አይርሱ፡፡
Tag ሲያደርጉ ለ Facebook @InfinixMobileEthiopia ፣ ለ Instagram @infinixethiopia ለ TikTok @Infinixet እና ለ Telegram @Infinixeth ሜንሽን ማድረግ እንዳይረሱ።
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ንጉስማልት
ደስስስስስስ ደስስስስስስ የሚለዉን የንጉስ ጠርሙስን ያሽከርክሩ ፈገግታን ይላበሱ !! ምን ደረስዎ ? ይሄ 🥰 ? ይሄኛው 🤩 ? ወይስ ሌላ ? ደስ የሚል ግዜ ይሁንልዎ !!
#ደስደስበንጉስ #nonalcoholic #ከአልኮልነፃ
ደስስስስስስ ደስስስስስስ የሚለዉን የንጉስ ጠርሙስን ያሽከርክሩ ፈገግታን ይላበሱ !! ምን ደረስዎ ? ይሄ 🥰 ? ይሄኛው 🤩 ? ወይስ ሌላ ? ደስ የሚል ግዜ ይሁንልዎ !!
#ደስደስበንጉስ #nonalcoholic #ከአልኮልነፃ
#MPESASafaricom
የሀገር ዉስጥ በረራ ትኬታችንን በM-PESA እንቁረጥ ፤ 5% ተመላሽ አሁኑኑ እናግኝ !
የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያን በዚህ ሊንክ እናውርድ ፡ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle
የቴሌግራም ቻናላችንን እዚህ እንቀላቀል 👉https://t.iss.one/Safaricom_Ethiopia_PLC
ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን https://t.iss.one/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!
#FurtherAheadTogether
የሀገር ዉስጥ በረራ ትኬታችንን በM-PESA እንቁረጥ ፤ 5% ተመላሽ አሁኑኑ እናግኝ !
የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያን በዚህ ሊንክ እናውርድ ፡ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle
የቴሌግራም ቻናላችንን እዚህ እንቀላቀል 👉https://t.iss.one/Safaricom_Ethiopia_PLC
ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን https://t.iss.one/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!
#FurtherAheadTogether
በአማራ ክልል፣ ደቡብ ወሎ ዞን ቃሉ ወረዳ በዘጠኝ ጤና ጣቢያ ውስጥ የሚሰሩ የጤና ባለሞያዎች ከግንቦት 2016 ዓ/ም ጀምሮ ያልተከፈላቸው የተጠራቀመ የትርፍ ሰዓት ስራ (ዲዩቲ) ክፍያቸው ሳይከፈላቸው እንደቆየ ተናግረዋል።
ክፍያቸው እንዲፈጸምላቸው ተደጋጋሚ የሆነ ጥያቄ ለወረዳው እና ለጤና ጽ/ቤቱ ሲጠይቁ የቆዩ ሲሆን የወረዳው ጤና ጽ/ቤት ከ6 ወር ክፍያው ውስጥ የ2 ወሩን እንደከፈላቸው ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ያቀረቡ የጤና ባለሞያዎች ተናግረዋል።
ቅሬታ አቅራቢዎች የቀረውን የ4 ወር ክፍያ ለመፈጸም ግን ከወረዳው " በጀት የለንም " የሚል ምላሽ እንደተሰጣቸው ተናግረዋል።
ያነጋገርናቸው የጤና ባለሞያዎች " ወረዳው በክልሉ ካሉ የሰላም ወረዳ (ቀጠና) አንዱ ነው የመንግስት ስራ በሁሉም ሴክተር እየተሰራ ነው ያለው የግብር እና የታክስ መሰብሰብ ስራም በአግባቡ እየተሰራ ነው የበጀት እጥረት አጋጠመን የሚባለው በጭራሽ ከእውነት የራቀ ነው " ብለዋል።
" በዞኑ የሚገኙ አጎራባች ወረዳዎችን፣ ኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር፣ ባቲ ወረዳ፣ አርጎባ ልዩ ወረዳ እና ሌሎችም ወረዳዎች ለባለሙያዎቻቸው የሰሩበትን የትርፍ ሰዓት ክፍያ ከፍለዋል የእኛ በምን ተለይቶ ዘገየ " የሚል ጥያቄን አንስተዋል።
በወረዳው ከሚገኙ ጤና ጣቢያዎች አንዱ ከሆነው " ደጋን " ጤና ጣቢያ ሁለት የጤና ባለሞያዎች ማክሰኞ 03/03/17 ዓም በጸጥታ አካላት ተወስደዋል።
የጤና ባለሞያዎች ለእስር የተዳረጉት ካልተከፈላቸው ክፍያ ጋር በተገናኘ የሰሩበትን የትርፍ ሰዓት ክፍያ እንዲከፈላቸው የሚጠይቅ ጽሁፍ " በሶሻል ሚዲያ አጋርታቹሃል " በሚል ሳይሆን እንዳልቀረ ተነግሯል።
ባለሞያዎቹ ከ4 ቀናት እስር በኋላ ትላንት ምሽት ተፈተዋል።
የቃሉ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ሙህዲን አህመድ ለጤና ባለሞያዎቹ ክፍያው በእርግጥም አለመፈጸሙን አረጋግጠው ያልተከፈላቸው ግን በበጀት እጥረት ምክንያት አለመሆኑን ተናግረዋል።
" ክፍያው የዘገየው በየጤና ጣቢያዎቹ የሚሰጠው አገልግሎት እና የሥራ ጫና የሚለያይ በመሆኑ የሚያድረው የጤና ባለሞያ ቁጥርም ይለያያል በዛ ምክንያት ደረጃ ይውጣለትና በሚሰጡት አገልግሎት እና ባለባቸው የስራ ጫና ልክ ይከፈላቸው ተብሎ ይህንን የሚያጣራ ኮሚቴ ተቋቁሞ በወረዳው በሚገኙ በዘጠኙም ጤና ጣቢያዎች እያጣራ ነው ሪፖርቱን እንዳቀረበ ይከፈላቸዋል " ብለዋል።
በሌሎች ትይዩ ወረዳዎች ላይ ከክፍያ ጋር በተያያዘ ተመሳሳይ ችግር የለም ይህ በቃሉ ወረዳ ለምን ተፈጠረ ለሚለው የቲክቫህ ጥያቄ " የእኛ ወረዳ ከሌሎች የጎንዮሽ ወረዳዎች ጋር ለማነጻጸሪያ ቢቀርብ የተሻለ ከፋይ ነው " ብለዋል።
ታሰሩ ስለተባሉት ባለሞያዎች መረጃው እንደሌላቸው ተናግረው በሌላ ጉዳይ ተጠርጥረው ካልታሰሩ በቀር በክፍያው ጉዳይ አይታሰሩም ብለዋል።
" ከተያዙም ሌላ የጸጥታ ስራ ስላለ በዛ ምክንያት ተጠርጥረው ነው የሚሆነው በተባለው ምክንያት ከሆነ ግን አጣርቼ ልጆቹን ትሪት አደርጋለው " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ችግሩ ቢነገር ቢነገር መፍትሄ ያልተገኘለት በክልሎች ያለው የቤንዚን ጉዳይ !
በክልል ከተሞች ነዳጅ በተለይም ቤንዚን ማግኘት ፈተና እንደሆነ ቀጥሏል።
በርካታ በትራንስፖርት ስራ ላይ የተሰማሩ ወጣቶች ባለው ችግር ምክንያት ሰርቶ መግባት ቤተሰብ ማስተዳደር ከባድ ሆኖባቸዋል።
ከክልል ከተሞች አንዷ የሲዳማ መዲናዋ ሀዋሳ ናት።
በዚህች ከተማ ነዳጅ እንደልብ ማግኘት ከቆመ ዓመታት አልፈዋል።
ያለው ችግር በተደጋጋሚ ቢነገርም በክልል መዲናይቱ ምንም የተቀየረ ነገር የለም። አሁንም ችግሩ እንደቀጠለ ነው። እንደልብ ነዳጅ ማግኘት አይቻልም።
አሽከርካሪዎች " ነዳጅ ማግኘት ከፍተኛ መከራ ሆኖብናል " ሲሉ ድምጻቸውን በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አሰምተዋል።
" ብላክ በኃይላድ እየተሞላ እንደሸቀጥ ዕቃ በየሱቁ አንድ ሊትር ከ160 እስከ 180 ከዛም በላይ እየተሸጠ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
በከተማው በርካታ ማደያዎች ቢኖሩም ነዳጅ ማግኘት ስቃይ ነው።
ነዳጅ በፕሮግራም ማሸጥ ከተጀመረም በርካታ ወራት አልፈዋል።
ምንም እንኳን በየማደያው ቤንዚን የለም ይባል እንጂ ባጥቁር ገቢያ ነጋዴዎች በከፍተኛ ብር እንደጉድ ይቸበቸባል።
ቤንዚን ከከተማ እስከ ገጠር ድረስ ከጥቁር ገበያው ጠፍቶ አያውቅም።
ጉዳዩ ይመለከታቸዋል የሚባሉት የሥራ ኃላፊዎች " ችግሩ ይቀረፋል እየሰራን ነው " እያሉ ተደጋጋሚ ቃል ከመስጠት ውጪ ያመጡት መሬት ላይ የሚታይ ለውጥ እንደሌለ ነዋሪዎቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ባለው ሁኔታ ምክንያት " ሰርቶ መኖር በጣም ችግር ሆኖብናል " ብለዋል።
ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ እና ሌሎች ክልሎችም ብንመለከት የቤንዚን ችግር እንደዚሁ ነው።
በየማደያው የለም የሚባለው ቤንዚን ከጥቁር ከገበያ እንደልብ ሲገኝ ይታያል።
ቃላቸውን የሰጡን ነዋሪዎች " ቤንዚን በየሱቁ ፤ በየመንደሩ እንደጉድ ይቸበቸሻል ነዳጅ ማደያ ሲኬድ የለም ነው መልሳቸው " ብለዋል።
" ህዝብ እየተሰቃየ ነው። በተለይ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ዜጎች መከራቸውን እያዩ ነው። ችግሩ በርካታ ጊዜ ቢያልፈውም ለምን ማስተካከል እንዳልተቻለ ሊገባን አልቻለም " ሲሉ አክለዋል።
ከነዳጅ ማደያዎች ሌሊት በሲኖትራክ ሳይቀር ነዳጅ ተጭኖ እንደሚወጣ ፤ በዚህ የጥቁር ገበያና የነዳጅ ሽያጭ ሰንሰለት እጃቸው የረዘመ በመዋቅር ውስጥ ያሉ አካላት ሊኖሩ እንደሚችላ ጠቁመዋል።
በየመዋቅሩ ተጠቃሚ ሰዎች ባይኖሩ እንዴት ይሄን ያህል ጊዜ ችግሩ ይቀጥላል ? ሲሉም ጠይቀዋል።
ለአብነት ወላይታ ሶዶ ከተማ ውስጥ ቤንዚን ማግኘት አይታሰብም።
በጥቁር ገበያ እስከ 200 ብር ድረስ ይቸበቸድረስ
ከዚህ ባለፈ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከነዋሪዎች እንደሰማው አንዳንድ ከከተማ የወጡ ማደያዎች ሳይቀሩ ነዳጅ በድብቅ ይሸጣሉ።
አንድ ሊትር ቤንዚን 92 ብር መሸጥ ሲገባው ከጀርባ በትውውቅ እስከ 220 ብር ድረስ ለመሸጥ የሚደራደሩ አሉ።
ይህ ሁሉ ሲሆን ግን የመፍትሄ እርምጃ ሲወሰድ እና ማስተካከያ ሲደረግ አይታይም።
በአጠቃላይ በክልል ከተሞች በቤንዚን ምክንያት ስራ መስራት ፈተና እንደሆነ ነው። ከከተማ ወጥቶ ለመስራትም እየተቻለ አይደለም።
የዚህ ሁሉ ችግር መጨረሻ የሚወርደው ህዝብ ላይ ነው። " ነዳጅ የለም ተወዷል " በሚል በትራንስፖርት ተገልጋዩ ዜጋ ላይ የሚጨመረው ዋጋ ከፍተኛ ነው ፤ ካለው የኑሮ ውድነት ጋር ይሄ ተጨምሮ የሚያሳድረው ተፅእኖ እንዲሁ በቃላት የሚገለጽ አይደለም።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#እንድታውቁት
ነገ እሁድ በአዲስ አበባ ከተማ ለ24ኛ ጊዜ የተዘጋጀው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ አዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።
መነሻና መድረሻውን መስቀል አደባባይ ነው።
ውድድሩ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ለተሽከርካሪ የሚዘጉት መንገዶች ፦
- ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ (ኦሎምፒያ አደባባይ )
- ከጥላሁን አደባባይ ወደ ሳንጆሴፍ መብራት (ጥላሁን አደባባይ ) ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ
- ከአፍሪካ ህብረት መብራት ወደ ሜክሲኮ አደባባይ (ጥይት ቤት መስቀለኛ )
- ከፓርላማ መብራት ወደ ኮንሰን መታጠፊያ (ፓርላማ መብራት )
- ከኮንሰን መታጠፊያ ወደ ገብርኤል (ኮንሰን መታጠፊያ )
- ከጥይት ቤት ወደ ገብርኤል በጀርባው (ጥይት ቤት መታጠፊያ )
- ከሴቶች አደባባይ ወደ ካዛንቺስ (ሴቶች አደባባይ )
- ከሴቶች አደባባይ ወደ ካዛንቺስ ቶታል (ሴቶች አደባባይ )
- ከ22 አደባባይ ወይም ዘሪሁን ህንፃ ወደ ዑራኤል አደባባይ (ዘሪሁን ህንፃ መስቀለኛ )
- ከፒኮክ አዲሱ መንገድ ወደ ዑራኤል አደባባይ (ፒኮክ መብራት)
- ከጋዜቦ አደባባይ ወደ ደንበል (ጋዜቦ አደባባይ)
- ከቂርቆስ ቤ/ክርስቲያን መስቀለኛ ወደ ለገሃር መብራት (ቂርቆስ ቤ/ክርሰቲያን ነርክ ተራ )
- ከላንድ ማርክ ሆስፒታል መታጠፊያ ገነት ሆቴል ወይም ወደ ገነት መብራት (ላንድ ማርክ ሆስፒታል መስቀለኛ )
- ከጠማማ ፎቅ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ (ጠማማ ፎቅ መስቀለኛ )
- ከአፍሪካ ህብረት መብራት ወደ ሜክሲኮ አደባባይ (ሜክሲኮ ጥይት ፋብሪካ መስቀለኛ )
- ከፈረሰኛ መብራት ወደ ጨፌ ሜዳ (ፈረሰኛ መብራት )
- ከሞላ ማሩ መስቀለኛ ወደ ጌጃ ሰፈር (ጌጃ ሰፈር መስቀለኛ )
- ከከፍተኛ ፍ/ቤት አደባባይ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ (ከፍተኛ ፍ/ቤት አደባባይ)
- ከሠንጋ ተራ 40/60 ወደ ሠንጋ ተራ መብራት (ሠንጋ ተራ 40/60 መታጠፊያ)
- ከጎማ ቁጠባ መብራት ወደ ብ/ቲያትር (ጎማ ቁጠባ መብራት)
- ከሜትሮሎጂ መታጠፊያ ወደ ፖስታ ቤት መብራት (ሜትሮዎሎጂ መታጠፊያ )
- ከጥቁር አንበሳ ሼል ወደ ኢምግሬሽን (ጥቁር አንበሳ ሼል)
- ከጎላ ሚካኤል መስቀለኛ ወደ ኢምግሬሽን (ጎላ ሚካኤል መስቀለኛ)
- ከቴዎድሮስ አደባባይ ወደ አገር አስተዳደር መብራት (ቴዎድሮስ አደባባይ) ከንጋቱ 11:30 - ሰዓት ጀምሮ ውድድሩ እስከሚጠናቀቅ ይዘጋሉ።
ፖሊስ " ለጋራ ደህንነት ሲባል ፍተሻ ይኖራል " ብሏል።
" ከውድድሩ ዓላማ ውጪ ህገ-ወጥ ተግባራትንና መልእክቶችን ማስተላለፍ የውድድሩን መንፈስ የሚረብሽ ስለሆነ አዘጋጅ ተቋሙ እና ተሳታፊዎች ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው " ሲልም አሳስቧል።
@tikvahethiopia
ነገ እሁድ በአዲስ አበባ ከተማ ለ24ኛ ጊዜ የተዘጋጀው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ አዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።
መነሻና መድረሻውን መስቀል አደባባይ ነው።
ውድድሩ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ለተሽከርካሪ የሚዘጉት መንገዶች ፦
- ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ (ኦሎምፒያ አደባባይ )
- ከጥላሁን አደባባይ ወደ ሳንጆሴፍ መብራት (ጥላሁን አደባባይ ) ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ
- ከአፍሪካ ህብረት መብራት ወደ ሜክሲኮ አደባባይ (ጥይት ቤት መስቀለኛ )
- ከፓርላማ መብራት ወደ ኮንሰን መታጠፊያ (ፓርላማ መብራት )
- ከኮንሰን መታጠፊያ ወደ ገብርኤል (ኮንሰን መታጠፊያ )
- ከጥይት ቤት ወደ ገብርኤል በጀርባው (ጥይት ቤት መታጠፊያ )
- ከሴቶች አደባባይ ወደ ካዛንቺስ (ሴቶች አደባባይ )
- ከሴቶች አደባባይ ወደ ካዛንቺስ ቶታል (ሴቶች አደባባይ )
- ከ22 አደባባይ ወይም ዘሪሁን ህንፃ ወደ ዑራኤል አደባባይ (ዘሪሁን ህንፃ መስቀለኛ )
- ከፒኮክ አዲሱ መንገድ ወደ ዑራኤል አደባባይ (ፒኮክ መብራት)
- ከጋዜቦ አደባባይ ወደ ደንበል (ጋዜቦ አደባባይ)
- ከቂርቆስ ቤ/ክርስቲያን መስቀለኛ ወደ ለገሃር መብራት (ቂርቆስ ቤ/ክርሰቲያን ነርክ ተራ )
- ከላንድ ማርክ ሆስፒታል መታጠፊያ ገነት ሆቴል ወይም ወደ ገነት መብራት (ላንድ ማርክ ሆስፒታል መስቀለኛ )
- ከጠማማ ፎቅ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ (ጠማማ ፎቅ መስቀለኛ )
- ከአፍሪካ ህብረት መብራት ወደ ሜክሲኮ አደባባይ (ሜክሲኮ ጥይት ፋብሪካ መስቀለኛ )
- ከፈረሰኛ መብራት ወደ ጨፌ ሜዳ (ፈረሰኛ መብራት )
- ከሞላ ማሩ መስቀለኛ ወደ ጌጃ ሰፈር (ጌጃ ሰፈር መስቀለኛ )
- ከከፍተኛ ፍ/ቤት አደባባይ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ (ከፍተኛ ፍ/ቤት አደባባይ)
- ከሠንጋ ተራ 40/60 ወደ ሠንጋ ተራ መብራት (ሠንጋ ተራ 40/60 መታጠፊያ)
- ከጎማ ቁጠባ መብራት ወደ ብ/ቲያትር (ጎማ ቁጠባ መብራት)
- ከሜትሮሎጂ መታጠፊያ ወደ ፖስታ ቤት መብራት (ሜትሮዎሎጂ መታጠፊያ )
- ከጥቁር አንበሳ ሼል ወደ ኢምግሬሽን (ጥቁር አንበሳ ሼል)
- ከጎላ ሚካኤል መስቀለኛ ወደ ኢምግሬሽን (ጎላ ሚካኤል መስቀለኛ)
- ከቴዎድሮስ አደባባይ ወደ አገር አስተዳደር መብራት (ቴዎድሮስ አደባባይ) ከንጋቱ 11:30 - ሰዓት ጀምሮ ውድድሩ እስከሚጠናቀቅ ይዘጋሉ።
ፖሊስ " ለጋራ ደህንነት ሲባል ፍተሻ ይኖራል " ብሏል።
" ከውድድሩ ዓላማ ውጪ ህገ-ወጥ ተግባራትንና መልእክቶችን ማስተላለፍ የውድድሩን መንፈስ የሚረብሽ ስለሆነ አዘጋጅ ተቋሙ እና ተሳታፊዎች ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው " ሲልም አሳስቧል።
@tikvahethiopia
#InfinixEthiopia
ኢንፊኒክስ ስማርት ስልኮች የሆኑትን ሆት 40 ፣ ኖት 40 ፣ ዜሮ 40 እና የኢንፊኒክስ ስማርት TVን ይግዙ ኩፖን ይወስዱ፡፡ ባሻዎት ስፍራ ፎቶ በመነሳት #InfinixEthiopia የሚለውን ሃሽ ታግ በመጠቀም የማህበራዊ ገጾት ላይ ያጋሩ የዛንዚባር የቢዝነስ ክላስ ደርሶ መልስ የአውሮፕላን ቲኬት እንዲሁም በርካታ የኢንፊኒክስ ምርቶችን ያሸንፉ ይሸለሙ፡፡
መመሪያ
1. የኢንፊኒክስ ኢትዮጵያን ፌስ ቡክ ፣ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ገጾችን ፎሎው ያድርጉ፡፡
2. የተነሱትን ፎቶ በመረጡት ማህበራዊ ሚዲያ ሲለጥፉ የኢንፊኒክስ ኢትዮጵያን ገፅ ከፖስቶት ጋር ታግ ያድርጉ፡፡
3. #InfinixEthiopia የሚለውን ሃሽታግ መጠቀሞን አይርሱ፡፡
Tag ሲያደርጉ ለ Facebook @InfinixMobileEthiopia ፣ ለ Instagram @infinixethiopia ለ TikTok @Infinixet እና ለ Telegram @Infinixeth ሜንሽን ማድረግ እንዳይረሱ።
ኢንፊኒክስ ስማርት ስልኮች የሆኑትን ሆት 40 ፣ ኖት 40 ፣ ዜሮ 40 እና የኢንፊኒክስ ስማርት TVን ይግዙ ኩፖን ይወስዱ፡፡ ባሻዎት ስፍራ ፎቶ በመነሳት #InfinixEthiopia የሚለውን ሃሽ ታግ በመጠቀም የማህበራዊ ገጾት ላይ ያጋሩ የዛንዚባር የቢዝነስ ክላስ ደርሶ መልስ የአውሮፕላን ቲኬት እንዲሁም በርካታ የኢንፊኒክስ ምርቶችን ያሸንፉ ይሸለሙ፡፡
መመሪያ
1. የኢንፊኒክስ ኢትዮጵያን ፌስ ቡክ ፣ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ገጾችን ፎሎው ያድርጉ፡፡
2. የተነሱትን ፎቶ በመረጡት ማህበራዊ ሚዲያ ሲለጥፉ የኢንፊኒክስ ኢትዮጵያን ገፅ ከፖስቶት ጋር ታግ ያድርጉ፡፡
3. #InfinixEthiopia የሚለውን ሃሽታግ መጠቀሞን አይርሱ፡፡
Tag ሲያደርጉ ለ Facebook @InfinixMobileEthiopia ፣ ለ Instagram @infinixethiopia ለ TikTok @Infinixet እና ለ Telegram @Infinixeth ሜንሽን ማድረግ እንዳይረሱ።
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
#DStvEthiopia
⚽️አዲስ ነገር ለኳስ አፍቃሪያን... ፍላጎታችሁን ሰምተናል ! አዲሱን ሜዳ ስፖርት ፓኬጅ በአሪፍ ዋጋ እንኩ ብለናል!
👉 ከሕዳር 16 ጀምሮ ፈጥነው ወደ ሜዳ ስፖርት ፓኬጅ ከፍ ይበሉ! ሁሉንም የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታዎችን፣ የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ፣ ሎችም ዋና ዋና እግር ኳስ እና ምርጥ ምርጥ መዝናኛዎችን ያካተቱ ከ129 በላይ ቻናሎችን በወር በ1699 ብር ብቻ!
ℹ️ ለአዲሱ ፓኬጅ የስትሪም አገልግሎት የሚጀምረው የካቲት 2017 በኋላ ይሆናል። ደንብና ሁኔታዎች ተፈፀሚነት አላቸው! ለበለጠ መረጃ
👇 www.dstv.com/en-et
ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇https://bit.ly/48oVhj8
#ሁሉምያለውእኛጋርነው #MedaSport
⚽️አዲስ ነገር ለኳስ አፍቃሪያን... ፍላጎታችሁን ሰምተናል ! አዲሱን ሜዳ ስፖርት ፓኬጅ በአሪፍ ዋጋ እንኩ ብለናል!
👉 ከሕዳር 16 ጀምሮ ፈጥነው ወደ ሜዳ ስፖርት ፓኬጅ ከፍ ይበሉ! ሁሉንም የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታዎችን፣ የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ፣ ሎችም ዋና ዋና እግር ኳስ እና ምርጥ ምርጥ መዝናኛዎችን ያካተቱ ከ129 በላይ ቻናሎችን በወር በ1699 ብር ብቻ!
ℹ️ ለአዲሱ ፓኬጅ የስትሪም አገልግሎት የሚጀምረው የካቲት 2017 በኋላ ይሆናል። ደንብና ሁኔታዎች ተፈፀሚነት አላቸው! ለበለጠ መረጃ
👇 www.dstv.com/en-et
ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇https://bit.ly/48oVhj8
#ሁሉምያለውእኛጋርነው #MedaSport
TIKVAH-ETHIOPIA
#እንድታውቁት ነገ እሁድ በአዲስ አበባ ከተማ ለ24ኛ ጊዜ የተዘጋጀው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ አዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል። መነሻና መድረሻውን መስቀል አደባባይ ነው። ውድድሩ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ለተሽከርካሪ የሚዘጉት መንገዶች ፦ - ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ (ኦሎምፒያ አደባባይ ) - ከጥላሁን አደባባይ ወደ ሳንጆሴፍ…
#AddisAbaba ዘንድሮ ለ24ኛ ጊዜ የተካሄደው ታላቁ ሩጫ በሰላም መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አሳውቋል።
ፖሊስ " ከአዲስ አበባ እና ከሀገራችን ከተለያዩ አካባቢዎች እንዲሁም የውጭ ሀገር ዜጎች የተሳተፉበት ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በስኬት ተጠናቋል " ብሏል።
@tikvahethiopia
ፖሊስ " ከአዲስ አበባ እና ከሀገራችን ከተለያዩ አካባቢዎች እንዲሁም የውጭ ሀገር ዜጎች የተሳተፉበት ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በስኬት ተጠናቋል " ብሏል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ትግራይ " ህጋዊ ያልሆነ ጉባኤ ያካሄደው ህጋዊ ያልሆነው ቡድን የሚመድባቸው አስተዳዳሪዎች እና የስራ ሃላፊዎች የሚያስተዳድሩት ሃብት የለም " ሲል የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር አስታወቀ። ጊዚያዊ አስተዳደሩ ይህን ያለው በፕሬዜዳንት ፅ/ቤት በኩል ባወጣው መግለጫ ነው። " ህጋዊ ያልሆነው ቡድን " ሲል የገለፀው በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት ግልፅ የመንግስት ግልበጣ አካሂደዋል…
#ትግራይ
የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደተር በ4 ከተሞች የጠራቸው የህዝብ ስብሰባዎች በአንዱ ሲካሄድ በሦስቱ ተስተጓጉሏል።
ለስብሰባዎች መሰተጓጎል የፀጥታ ስጋት እንደ ምክንያት መቀመጡ አንዳንድ የከተሞቹ ነዋሪዎች ይገልፃሉ።
ባለፈው እሮብ ህዳር 4/2017 ዓ.ም የትግራይ ምስራቃዊ ዞን ዋና አስተዳዳሪ በመሆን በፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የተሾሙት ሰለሙን ትኩእ በዓዲግራት ከተማ ከዛላኣንበሳ ከተማ ተፈናቃዮች ለመወያየት እና በህዝብ የተመረጠ አዲስ አስተዳዳሪ ለመሾም የጠሩት ስብሰባ ፈተና የበዛበት ነበር።
ስብሰባ ከተከናወነበት አዳራሽ የወጡ የቪድዮ እና ድምፅ ፋይሎች እንደሚያሳዩት የማይናቅ ቁጥር ያላቸው እናቶች በስድብ ፣ ጩኸት እና ዋይታ ሰብሰባው እንዳይካይሄድ ሲከላከሉ ታይተዋል።
ቢሆንም የእናቶቹ ረብሻ በፀጥታ አካላት እንዲረገብ ሆኖ ወይይቱ ተካሂዶ የዛላምበሳ ከተማ አስተዳዳሪ በህዝብ ድምፅ እንዲመረጥ ሆኗል።
በትግራይ ምስራቃዊ ዞን የጉሎመኸዳ ወረዳ ሦስተኛ ከተማ የሆነችው የዛላኣንበሳ ከተማ እስካሁን በኤርትራ ስራዊት ቁጥጥር ስር እንደምትገኝ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ የወረዳው አስተዳዳሪዎችን ዋቢ በማድረግ በተደጋጋሚ መዘገቡ ይታወሳል።
እሁድ ህዳር 8 /2017 ዓ/ም በትግራይ ምስራቃዊ እና ማእከላዊ ዞኖች በሚገኙ ውቕሮ ፣ ዓብዩ ዓዲ እና አክሱም ከተሞች በጊዚያዊ አስተዳደሩ የተጠሩ ህዝባዊ ስብሰባዎች መሰረዛቸው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ምንጮች ጠቁመዋል።
ስብሰዎቹ ከፀጥታ ስጋት ጋር በተገናኘ የተሰረዙ እንደሆነ የገለጹ አሉ።
ከዚህ ተቃራኒ አስተያያት የሰጡ ደግሞ " በተለይ በዓብዩ ዓዲ እና አክሱም ከተሞች ሊካሄዱ ታቅተደው የተሰተጓጎሉት ህዝባዊ ስብሰባዎች በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት በዞኑ ያካሄደው የአስተዳደር የስልጣን ግልበጣ አካል ናቸው " ብለዋል።
ዛሬ ሊካሄድ የታሰበው ስብሰባ የተሰተጓጎለባቸው የውቕሮ ፣ የተምቤን ዓብዩ ዓዲ እና የአክሱም ከተሞች በአሁኑ ሰዓት ከወትሮ የተለየ የፀጥታ ስጋትና መደፍረስ እንደሌለ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ወደ ከተሞቹ ስልክ በመደወል አረጋግጧል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደተር በ4 ከተሞች የጠራቸው የህዝብ ስብሰባዎች በአንዱ ሲካሄድ በሦስቱ ተስተጓጉሏል።
ለስብሰባዎች መሰተጓጎል የፀጥታ ስጋት እንደ ምክንያት መቀመጡ አንዳንድ የከተሞቹ ነዋሪዎች ይገልፃሉ።
ባለፈው እሮብ ህዳር 4/2017 ዓ.ም የትግራይ ምስራቃዊ ዞን ዋና አስተዳዳሪ በመሆን በፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የተሾሙት ሰለሙን ትኩእ በዓዲግራት ከተማ ከዛላኣንበሳ ከተማ ተፈናቃዮች ለመወያየት እና በህዝብ የተመረጠ አዲስ አስተዳዳሪ ለመሾም የጠሩት ስብሰባ ፈተና የበዛበት ነበር።
ስብሰባ ከተከናወነበት አዳራሽ የወጡ የቪድዮ እና ድምፅ ፋይሎች እንደሚያሳዩት የማይናቅ ቁጥር ያላቸው እናቶች በስድብ ፣ ጩኸት እና ዋይታ ሰብሰባው እንዳይካይሄድ ሲከላከሉ ታይተዋል።
ቢሆንም የእናቶቹ ረብሻ በፀጥታ አካላት እንዲረገብ ሆኖ ወይይቱ ተካሂዶ የዛላምበሳ ከተማ አስተዳዳሪ በህዝብ ድምፅ እንዲመረጥ ሆኗል።
በትግራይ ምስራቃዊ ዞን የጉሎመኸዳ ወረዳ ሦስተኛ ከተማ የሆነችው የዛላኣንበሳ ከተማ እስካሁን በኤርትራ ስራዊት ቁጥጥር ስር እንደምትገኝ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ የወረዳው አስተዳዳሪዎችን ዋቢ በማድረግ በተደጋጋሚ መዘገቡ ይታወሳል።
እሁድ ህዳር 8 /2017 ዓ/ም በትግራይ ምስራቃዊ እና ማእከላዊ ዞኖች በሚገኙ ውቕሮ ፣ ዓብዩ ዓዲ እና አክሱም ከተሞች በጊዚያዊ አስተዳደሩ የተጠሩ ህዝባዊ ስብሰባዎች መሰረዛቸው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ምንጮች ጠቁመዋል።
ስብሰዎቹ ከፀጥታ ስጋት ጋር በተገናኘ የተሰረዙ እንደሆነ የገለጹ አሉ።
ከዚህ ተቃራኒ አስተያያት የሰጡ ደግሞ " በተለይ በዓብዩ ዓዲ እና አክሱም ከተሞች ሊካሄዱ ታቅተደው የተሰተጓጎሉት ህዝባዊ ስብሰባዎች በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት በዞኑ ያካሄደው የአስተዳደር የስልጣን ግልበጣ አካል ናቸው " ብለዋል።
ዛሬ ሊካሄድ የታሰበው ስብሰባ የተሰተጓጎለባቸው የውቕሮ ፣ የተምቤን ዓብዩ ዓዲ እና የአክሱም ከተሞች በአሁኑ ሰዓት ከወትሮ የተለየ የፀጥታ ስጋትና መደፍረስ እንደሌለ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ወደ ከተሞቹ ስልክ በመደወል አረጋግጧል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
#OFC
“ አሁንም ቢሆን ሀገራዊ ምክክሩ በሚሄድበት አቅጣጫ እርካታ የለንም ” - ኦፌኮ
ከዚህ ቀደም በምክክሩ እንደማይሳተው ገልጾ የነበረው የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረንስ (ኦፌኮ) አሁንም እየተሳተፈ እንዳልሆነ፣ ኮሚሽኑ በሚሄድበት አቅጣጫ እርካታ እንደሌለው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጿል።
ፓርቲው ከዚህ ቀደም በሀገራዊ ምክክሩ እንዲሳተፍ ቢጋበዝም በምክክሩ እንዳልተገኘ አስታውሷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በበኩሉ፣ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ሥራውን መቀጠሉን እየገለጸ ነው፤ አሁንስ ፓርቲው ከኮሚሽኑ ጋር ተቀራርቦ ለመስራት አላሰበም ? ከምክክሩ የወጣበት ምክንያትስ ምንድን ነው ? ምላሽስ አላገኘም ? ሲል ጥያቄ አቅቧል።
ፓርቲው ምን ምላሽ ሰጠ ?
“ በእርግጥ ከዚህ ቀደምም ጥሪ ተደርጎልን ነበር። ችግሩ ከዝግጅት ጀምሮ ያለው እንቅስቀሴ አሳታፊ አልነበረም።
ሲጀመር የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ተጠሪነቱ 'ለጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት ይሆናል’ ተባለ፣ ከዚያ ተመልሶ ‘ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይሆናል’ ተባለ።
ይሄ ልዩነቱም አልታየንም። ምክንያቱም የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትም በገዢው ፓርቲ የተሞላ ስለሆነ ገልተኛነቱ ያን ያክል አስተማማኝ እንዳልሆነ ነው የምንረዳው።
ምክንያቱም የሌሎች ተሳትፎ ወይ የለም ወይ በጣም አናሳ ነው፤ ኢንሲግኒፊካንት የሚባል ደረጃ ማለት ነው።
የኛ ሀሳብ ፓለቲካዊ ውይይቶች በፓለቲካ ኃይሎች መካከል መካሄድ ይኖርባቸዋል፣ ሁሉንም ኃይሎች አካታች መሆን አለበት የሚል ነው።
እኛ ሕዝብ ማወያየትን አንጠላም ወይም አናናንቅም ነገር ግን ከሕዝብ ጋር ከመድረሱ በፊት ወይም እየደረሰም እያለ ሌሎች የፓለቲካ ኃይሎች ሊነጋገሩበትና ሊፈቷቸው የሚገቡ ነገሮች አሉ።
ለምሳሌ በተለያዩ አካባቢዎች የኛ ፅሕፈት ቤቶች ተዘግተው ባሉበት፣ አባሎቻችንን ሰብስበን ማነጋገር ባልቻልንበት ሁኔታ፣ ለሀገራዊ ምክክሩ አጀንዳ መፍጠር የሚባለው ነገር ውስጥ መሳተፍ አስፈላጊ አይደለም።
እንደገናም ጦርነት እየተካሄደ ሀገራዊ ምክክር ብሎ ነገር ምንድን ነው? ይሄ እርስ በእርሱ የሚጋጭ ነገር ነው።
ይሄን እርስ በእርስ የሚጋጨውን ነገር የሆነ ጋፕ ስጡት፣ ለመነጋገር፣ ለመወያየት እድል ይሰጠው አገር እየተጠበቀ አገር ቢነጋገርበት ጥሩ ይሆናል በሚል ጥያቄ አቅርበን ነበር።
ይሄን የኛን ሀሳብና ጥያቄ ምንም ከዚህ ግባ አላሉትም። ምናልበት የተሻለ ነገር ቢያመጡ እኛም አጨብጭበን እንቀበላቸዋለንና እንዲሄዱ ነው የተውናቸው።
ኦፌኮ ብቻ ሳይሆን ሌሎች ፓርቲዎች አሉ እንደዚህ ያደረጉ። ጊዜና መነጋገር የሚፈልጉ፣ አንድ ወገንን ብቻ ተጠያቂ ከማድረግ እንድንቆጠብ የሚያደርጉ ነገሮች አሉ።
ስለዚህ ነገሮቹ መፍትሄ ካላገኙና የተወሰነ አቅጣጫ ካልተቀመጠላቸው እንዲያው ለመሳተፍ ተብሎ የምንሳተፍበት ምክንያት አይኖርም።
አሁንም ቢሆን ሀገራዊ ምክክሩ በሚሄድበት አቅጣጫ እርካታ የለንም። እርካታ ቢኖረንና ብንሳተፍበት ጥሩ ነበር ” ብሏል።
ለቀረበበት ትችት ምላሽ እንዲሰጥ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጥያቄ ያቀረበ ሲሆን፣ ኮሚሽኑ ለጊዜው በተደጋጋሚ ስብሰባ ላይ መሆኑን በመግለጹ ምላሹን እንደሰጠ የሚቀርብ ይሆናል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
“ አሁንም ቢሆን ሀገራዊ ምክክሩ በሚሄድበት አቅጣጫ እርካታ የለንም ” - ኦፌኮ
ከዚህ ቀደም በምክክሩ እንደማይሳተው ገልጾ የነበረው የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረንስ (ኦፌኮ) አሁንም እየተሳተፈ እንዳልሆነ፣ ኮሚሽኑ በሚሄድበት አቅጣጫ እርካታ እንደሌለው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጿል።
ፓርቲው ከዚህ ቀደም በሀገራዊ ምክክሩ እንዲሳተፍ ቢጋበዝም በምክክሩ እንዳልተገኘ አስታውሷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በበኩሉ፣ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ሥራውን መቀጠሉን እየገለጸ ነው፤ አሁንስ ፓርቲው ከኮሚሽኑ ጋር ተቀራርቦ ለመስራት አላሰበም ? ከምክክሩ የወጣበት ምክንያትስ ምንድን ነው ? ምላሽስ አላገኘም ? ሲል ጥያቄ አቅቧል።
ፓርቲው ምን ምላሽ ሰጠ ?
“ በእርግጥ ከዚህ ቀደምም ጥሪ ተደርጎልን ነበር። ችግሩ ከዝግጅት ጀምሮ ያለው እንቅስቀሴ አሳታፊ አልነበረም።
ሲጀመር የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ተጠሪነቱ 'ለጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት ይሆናል’ ተባለ፣ ከዚያ ተመልሶ ‘ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይሆናል’ ተባለ።
ይሄ ልዩነቱም አልታየንም። ምክንያቱም የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትም በገዢው ፓርቲ የተሞላ ስለሆነ ገልተኛነቱ ያን ያክል አስተማማኝ እንዳልሆነ ነው የምንረዳው።
ምክንያቱም የሌሎች ተሳትፎ ወይ የለም ወይ በጣም አናሳ ነው፤ ኢንሲግኒፊካንት የሚባል ደረጃ ማለት ነው።
የኛ ሀሳብ ፓለቲካዊ ውይይቶች በፓለቲካ ኃይሎች መካከል መካሄድ ይኖርባቸዋል፣ ሁሉንም ኃይሎች አካታች መሆን አለበት የሚል ነው።
እኛ ሕዝብ ማወያየትን አንጠላም ወይም አናናንቅም ነገር ግን ከሕዝብ ጋር ከመድረሱ በፊት ወይም እየደረሰም እያለ ሌሎች የፓለቲካ ኃይሎች ሊነጋገሩበትና ሊፈቷቸው የሚገቡ ነገሮች አሉ።
ለምሳሌ በተለያዩ አካባቢዎች የኛ ፅሕፈት ቤቶች ተዘግተው ባሉበት፣ አባሎቻችንን ሰብስበን ማነጋገር ባልቻልንበት ሁኔታ፣ ለሀገራዊ ምክክሩ አጀንዳ መፍጠር የሚባለው ነገር ውስጥ መሳተፍ አስፈላጊ አይደለም።
እንደገናም ጦርነት እየተካሄደ ሀገራዊ ምክክር ብሎ ነገር ምንድን ነው? ይሄ እርስ በእርሱ የሚጋጭ ነገር ነው።
ይሄን እርስ በእርስ የሚጋጨውን ነገር የሆነ ጋፕ ስጡት፣ ለመነጋገር፣ ለመወያየት እድል ይሰጠው አገር እየተጠበቀ አገር ቢነጋገርበት ጥሩ ይሆናል በሚል ጥያቄ አቅርበን ነበር።
ይሄን የኛን ሀሳብና ጥያቄ ምንም ከዚህ ግባ አላሉትም። ምናልበት የተሻለ ነገር ቢያመጡ እኛም አጨብጭበን እንቀበላቸዋለንና እንዲሄዱ ነው የተውናቸው።
ኦፌኮ ብቻ ሳይሆን ሌሎች ፓርቲዎች አሉ እንደዚህ ያደረጉ። ጊዜና መነጋገር የሚፈልጉ፣ አንድ ወገንን ብቻ ተጠያቂ ከማድረግ እንድንቆጠብ የሚያደርጉ ነገሮች አሉ።
ስለዚህ ነገሮቹ መፍትሄ ካላገኙና የተወሰነ አቅጣጫ ካልተቀመጠላቸው እንዲያው ለመሳተፍ ተብሎ የምንሳተፍበት ምክንያት አይኖርም።
አሁንም ቢሆን ሀገራዊ ምክክሩ በሚሄድበት አቅጣጫ እርካታ የለንም። እርካታ ቢኖረንና ብንሳተፍበት ጥሩ ነበር ” ብሏል።
ለቀረበበት ትችት ምላሽ እንዲሰጥ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጥያቄ ያቀረበ ሲሆን፣ ኮሚሽኑ ለጊዜው በተደጋጋሚ ስብሰባ ላይ መሆኑን በመግለጹ ምላሹን እንደሰጠ የሚቀርብ ይሆናል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ፎቶ፦ ዛሬ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ መርካቶ ጃቡላኒ ህንፃ በተለምዶ " ድንች በረንዳ " እየተባለ በሚጠራው ቦታ ላይ የእሳት ቃጠሎ አደጋ ተነስቶ ነበር።
እሳቱ ከቀኑ 6:30 ሰዓት ላይ የተነሳ ሲሆን ሳይዛመትና የከፋ ጉዳት ሳያደርስ መቆጣጠር እንደተቻለ የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ገልጿል።
ስለ አደጋው ምክንያት የተባለ ነገር የለም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ እሳቱ በተነሳበት ወቅት የእሳትና ከደጋ ሥራ አመራር ኮሚሽንን ለማነጋገር ሞክሮ ነበር። አንድ የኮሚሽኑ አካል በቦታው ሱቆች እየተቃጠሉ እንደነበር ገልጸዋል።
እኚሁ አካል በሥራ እየተጣደፉ ስለነበር ወደ በኃላ ዝርዝር ሁነቱን እንደሚያሳውቁ ገልጸዋል። በቃላቸው ከተገኙ ቀጣይ ተጨማሪ ማብራሪያ የምናቀርብ ይሆናል።
በቅርቡ መርካቶ " ሸማ ተራ " ከፍተኛ የእሳት አደጋ ደርሶ በርካታ ዜጎች ንብረታቸውን ማጣታቸው የሚዘነጋ አይደለም። የዚሁ የአደጋው ምክንያት እና አጠቃላይ የደረሰው ውድመት " ተመርምሮና ተጣርቶና ለህዝብ ይፋ ይደረጋል " ከተባለ ሳምንታት ቢቆይም እስካሁን በይፋ የተባለ ነገር የለም።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
የፎቶ ባለቤት ፦ የአዲስ አበባ እሳት አደጋና ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን
@tikvahethiopia
እሳቱ ከቀኑ 6:30 ሰዓት ላይ የተነሳ ሲሆን ሳይዛመትና የከፋ ጉዳት ሳያደርስ መቆጣጠር እንደተቻለ የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ገልጿል።
ስለ አደጋው ምክንያት የተባለ ነገር የለም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ እሳቱ በተነሳበት ወቅት የእሳትና ከደጋ ሥራ አመራር ኮሚሽንን ለማነጋገር ሞክሮ ነበር። አንድ የኮሚሽኑ አካል በቦታው ሱቆች እየተቃጠሉ እንደነበር ገልጸዋል።
እኚሁ አካል በሥራ እየተጣደፉ ስለነበር ወደ በኃላ ዝርዝር ሁነቱን እንደሚያሳውቁ ገልጸዋል። በቃላቸው ከተገኙ ቀጣይ ተጨማሪ ማብራሪያ የምናቀርብ ይሆናል።
በቅርቡ መርካቶ " ሸማ ተራ " ከፍተኛ የእሳት አደጋ ደርሶ በርካታ ዜጎች ንብረታቸውን ማጣታቸው የሚዘነጋ አይደለም። የዚሁ የአደጋው ምክንያት እና አጠቃላይ የደረሰው ውድመት " ተመርምሮና ተጣርቶና ለህዝብ ይፋ ይደረጋል " ከተባለ ሳምንታት ቢቆይም እስካሁን በይፋ የተባለ ነገር የለም።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
የፎቶ ባለቤት ፦ የአዲስ አበባ እሳት አደጋና ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን
@tikvahethiopia