#HoP
ነገ ማክሰኞ ጥዋት ከ2:00 ሰዓት ጀምሮ የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት መደበኛ ስብሰባውን ያካሂዳል።
ምክር ቤቱ ስብሰባውን የሚያካሂደው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በተገኙበት ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምክር ቤት አባላት ለሚነሱላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ ይሰጣሉ ተብሏል።
@tikvahethiopia
ነገ ማክሰኞ ጥዋት ከ2:00 ሰዓት ጀምሮ የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት መደበኛ ስብሰባውን ያካሂዳል።
ምክር ቤቱ ስብሰባውን የሚያካሂደው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በተገኙበት ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምክር ቤት አባላት ለሚነሱላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ ይሰጣሉ ተብሏል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#HoPR የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ዛሬ እያካሄደው በሚገኘው 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ የ5 ሚኒስትሮችን ሹመት በአብላጫ ድምጽ አጸድቋል። የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለከፍተኛ የመንግሥት ሃላፊነት ቦታዎች ሹመት እንፀድቅላቸው በደብዳቤ ባቀረቡት ጥያቄ መሰረት ነው ሹመቱ በምክር ቤቱ እንዲጸድቅ የተደረገው። ሹመታቸው የፀደቀው ፦ - የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጤሞቲዎስ(ዶ/ር)፣…
#HoP
" የምክር ቤት አባላት ያለመከሰስ መብታችን (immunity) ሳይነሳ እንደ ሽፍታ ተጎትተን ስንታሰርና ለወራት ስንቀመጥ ምን ሰሩ ? " - ደሰለኝ ጫኔ (ዶ/ር)
የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባሉና የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ተመራጩ ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) በቀድሞ የፍትህ ሚኒስትር ጌድዮን ጢሞትዬስ (ዶ/ር) ላይ ከፍተኛ ወቀሳ ሰነዘሩ።
የቀድሞው የፍትህ ሚኒስትር አሁን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው መሾማቸው ላይ ጥያቄ አንስተዋል።
" የፍትህ ዘርፉን ከፍተኛ ችግር ውስጥ የከተቱ ስለሆኑ ትራክሪከርዳቸው የውጭ ጉዳይን ለመምራት ብቁ ሊያደርጋቸው አይገባም " ብለዋል።
ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ፥ ጌዲዮን ጢሞቲዮስ ዶ/ር ወደ ፍትህ ሚኒስቴር ሲመጡ ከፍተኛ ተስፋ አድርገው እንደነበር ጠቁመዋል።
ነገር ግን ከሳቸው በፊት ከነበሩት ሚኒስትሮች ምን የተለየ ነገር አሳኩ ? ሲሉ ጠይቀዋል።
በህግ ከውጭ ዩኒቨርሲቲ ፒኤችዲ ይዘው መምጣታቸውና እዚህም ትልቁ የሀገራችን ተቋም አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ማስተማራቸው ላይ ምን ለውጥ አመጡ የሚለው አልተገመገመም ብለዋል።
በፍትህ ሚኒስትርነት ያላቸው ትራክሪከርድ / የሰሯቸው ስራዎች ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ብቁ ያደርጋቸዋል የሚለውም አልተገመገመም ሲሉ ተናግረዋል።
" እኔ በግሌ ቅሬታ አለኝ " ያሉት ደሳለኝ (ዶ/ር) " በፍትህ ሚኒስትር ዶክተር ጌዲዮን የእውቀት ችግር አለባቸው ብዬ አይደለም ፤ በተለያዩ መድረኮች አይቻቸዋለሁ ሞያቸውን በጣም ጠንቅቀው ያውቃሉ ፤ ነገር ግን አፈጻጸማቸውን ካየነው የኢትዮጵያ ህዝብ ለዘመናት ሲጠይቅ የነበረውን የፍትህ ጥማት ከማስታገስና ያን ከማርካት ይልቅ አሁንም የፍትህ ስርዓቱ የፖለቲካ መሳሪያ እንዲሆን አድርገዋል " የሚል ወቀሳ አቅርበዋል።
" በሀገራችን በተለይ በኢህአዴግ ዘመን የፍትህ ስርዓቱ ተቃዋሚዎችን ማጥቂያ፣ የፖለቲካ መሳሪያ፣ የገዢው ፓርቲ አንድ አርም ተደርጎ ሲሰራ ነበር አሁንም ያ ተቀይሯል ብዬ አላስብም " ብለዋል።
" የምክር ቤት አባላት ያለመከሰስ መብታችን (immunity) ሳይነሳ እንደ ሽፍታ ተጎትተን ስንታሰርና ለወራት ስንቀመጥ ሌሎች የምክር ቤት አባላት የፌዴሬሽን ፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ተገቢ ፍትህ ሳያገኙ ለአመታት ሲንገላቱ የፍትህ ሚኒስትር ምንም የሰራው ነገር የለም። ከሳሹ እራሱ የፍትህ ሚኒስትር ነው። " ሲሉ ተናግረዋል።
ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) " እንደኔ እንደኔ ዶክተር ጌዲዮን የእውቀት ችግር የለባቸው ግን የፍትህ ሚኒስትር ላይ ያላቸው ትራክሪከርድ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ሀገሪቱን ለመምራት የሚያስችላቸው አይደለም። የፍትህ ዘርፉን ከፍተኛ ችግር ውስጥ የከተቱ ስለሆነ ለዛ ቦታ ሊቀርቡ አይገባቸውም " ብለዋል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
" የምክር ቤት አባላት ያለመከሰስ መብታችን (immunity) ሳይነሳ እንደ ሽፍታ ተጎትተን ስንታሰርና ለወራት ስንቀመጥ ምን ሰሩ ? " - ደሰለኝ ጫኔ (ዶ/ር)
የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባሉና የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ተመራጩ ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) በቀድሞ የፍትህ ሚኒስትር ጌድዮን ጢሞትዬስ (ዶ/ር) ላይ ከፍተኛ ወቀሳ ሰነዘሩ።
የቀድሞው የፍትህ ሚኒስትር አሁን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው መሾማቸው ላይ ጥያቄ አንስተዋል።
" የፍትህ ዘርፉን ከፍተኛ ችግር ውስጥ የከተቱ ስለሆኑ ትራክሪከርዳቸው የውጭ ጉዳይን ለመምራት ብቁ ሊያደርጋቸው አይገባም " ብለዋል።
ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ፥ ጌዲዮን ጢሞቲዮስ ዶ/ር ወደ ፍትህ ሚኒስቴር ሲመጡ ከፍተኛ ተስፋ አድርገው እንደነበር ጠቁመዋል።
ነገር ግን ከሳቸው በፊት ከነበሩት ሚኒስትሮች ምን የተለየ ነገር አሳኩ ? ሲሉ ጠይቀዋል።
በህግ ከውጭ ዩኒቨርሲቲ ፒኤችዲ ይዘው መምጣታቸውና እዚህም ትልቁ የሀገራችን ተቋም አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ማስተማራቸው ላይ ምን ለውጥ አመጡ የሚለው አልተገመገመም ብለዋል።
በፍትህ ሚኒስትርነት ያላቸው ትራክሪከርድ / የሰሯቸው ስራዎች ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ብቁ ያደርጋቸዋል የሚለውም አልተገመገመም ሲሉ ተናግረዋል።
" እኔ በግሌ ቅሬታ አለኝ " ያሉት ደሳለኝ (ዶ/ር) " በፍትህ ሚኒስትር ዶክተር ጌዲዮን የእውቀት ችግር አለባቸው ብዬ አይደለም ፤ በተለያዩ መድረኮች አይቻቸዋለሁ ሞያቸውን በጣም ጠንቅቀው ያውቃሉ ፤ ነገር ግን አፈጻጸማቸውን ካየነው የኢትዮጵያ ህዝብ ለዘመናት ሲጠይቅ የነበረውን የፍትህ ጥማት ከማስታገስና ያን ከማርካት ይልቅ አሁንም የፍትህ ስርዓቱ የፖለቲካ መሳሪያ እንዲሆን አድርገዋል " የሚል ወቀሳ አቅርበዋል።
" በሀገራችን በተለይ በኢህአዴግ ዘመን የፍትህ ስርዓቱ ተቃዋሚዎችን ማጥቂያ፣ የፖለቲካ መሳሪያ፣ የገዢው ፓርቲ አንድ አርም ተደርጎ ሲሰራ ነበር አሁንም ያ ተቀይሯል ብዬ አላስብም " ብለዋል።
" የምክር ቤት አባላት ያለመከሰስ መብታችን (immunity) ሳይነሳ እንደ ሽፍታ ተጎትተን ስንታሰርና ለወራት ስንቀመጥ ሌሎች የምክር ቤት አባላት የፌዴሬሽን ፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ተገቢ ፍትህ ሳያገኙ ለአመታት ሲንገላቱ የፍትህ ሚኒስትር ምንም የሰራው ነገር የለም። ከሳሹ እራሱ የፍትህ ሚኒስትር ነው። " ሲሉ ተናግረዋል።
ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) " እንደኔ እንደኔ ዶክተር ጌዲዮን የእውቀት ችግር የለባቸው ግን የፍትህ ሚኒስትር ላይ ያላቸው ትራክሪከርድ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ሀገሪቱን ለመምራት የሚያስችላቸው አይደለም። የፍትህ ዘርፉን ከፍተኛ ችግር ውስጥ የከተቱ ስለሆነ ለዛ ቦታ ሊቀርቡ አይገባቸውም " ብለዋል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia