TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59K photos
1.5K videos
211 files
4.07K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ውቕሮ

° " እሁድ ተድራ ሓሙስ በጭካኔ ተግድላለች " - የውቕሮ ከተማ ነዋሪች 

° " ገዳዩ ሙሽራ እጅ ሰጥቷል፤ የድርጊቱ መንስኤ እየተጣራ ነው " - የውቕሮ ከተማ ፓሊስ

ከመቐለ በቅርብ ርቀት የምትገኘው ትንሽዋ እና ደማቅዋ የውቕሮ ከተማ ሓሙስ ጥቅምት 7/2017 ዓ.ም የሃዘን ማቅ ለብሳ ውላለች።

በሃያዎቹ ዕድሜ የምትገኘው ሊድያ በአዲስ አበባ ከተማ በኮንስትራክሽን ሰራዎች የተሰማራች ወጣት ምሁር ነበረች።

ድል ባለ ሰርግ ለማግባትም ወደ ውቕሮ ትግራይ ተጓዘች።

እሁድ ጥቅምት 3/2017 ዓ.ም በውቕሮ ከተማ በደማቅ የሰርግ ስነስርዓት " የወደፊት የትዳር አጋሬ " ያለቸውን ወጣት አገባች።

" የሙሽሪት ሊድያና ባለቤትዋ ሰርግ ደማቅ ነበር " ይላሉ የውቕሮ ከተማ ነዋሪዎች።

ሰኞ ፣ ማክሰኞ ፣ እሮብ ሙሽሪትና ሙሽራ በውቕሮ ከተማ በሚገኘው ባለ ኮኮብ ሆቴል በጫጉላ ሽርሽር  ነበሩ።

ሓሙስ ጥቅምት 7/2017 ዓ.ም ለአራት ቀናት የቆየው ደስታ ወደ ሃዘን ተለወጠ።

ሙሽሪት ሊድያ በባልዋ ተገደለች ፣ መገደልዋ ለፓሊስ የጠቆመው ገዳይ ሙሽራ ነው።

ፓሊስ ግድያ ወደ ተፈፀመበት ቦታ ድረስ በመሄድ ፤ ተጠራጣሪ ሙሽራ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ የቀጠለ ሲሆን ፤ ሙሽራው ሙሽሪትን አንቆ ነው የገደላት ብሏል።

ፓሊስ ጭካኔ የተሞላው የግድያ ተግባሩ መነሻው ምን እንደሆነ በተሟላ መልኩ አጣርቶ ጉዳዩ ለሚመለከተው የህግ አካል ለማቅረብ ተጨማሪ ጊዜ ያስፈልገኛል ማለቱ ተሰምቷል።

ግድያው ቤተሰብ ብቻ ሳይሆን የውቕሮ ነዋሪዎችን ሀዘን ላይ ጥሏል።

ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪዎች " ደስታና ሀዘን ተቀላቀለብን ፤ ሙሽሪት እሁድ ተድራ ሓሙስ በጭካኔ ተግድላለች " ብለዋል።

#TikvahEthiopiaMekelleFamily

@tikvahethiopia