TIKVAH-ETHIOPIA
#መገናኛ " የመሬት ውስጥ የእግረኛ መተላለፊያ መስመር ግንባታ ተጀምሯል ፤ ለገንቢው እንዲያጠናቅቅ የተሰጠው 45 ቀናት ነው " - አቶ ጥራቱ በየነ ከፍተኛ መጨናነቅ ባለበት " መገናኛ ' አካባቢ የመሬት ውስጥ የእግረኛ መተላለፊያ መስመር ግንባታ መጀመሩ ተገልጿል። በአዲስ አበባ ከፍተኛ የሆነ የትራፊክ መጨናነቅ ያለበት ፣ መኪና የሚበዛበትና የሚገናኝበት ፣ እጅግ በርካታ እግረኞችም የሚንቀሳቀሱበት…
#እንድታውቁት
በአዲስ አበባ መገናኛ አካባቢ ያለውን ከፍተኛ የትራንስፖርት መጨናነቅ ለመፍታት ያግዛል የተባለው የመሬት ውስጥ የእግረኛ መተላላፊያ መስመር ግንባታ መጀመሩ ይታወቃል።
በመሆኑም በተለይ ከመገናኛ አደባባይ ወደ ቦሌ ፤ ከቦሌ ወደ መገናኛ አደባባይ በሁለቱም አቅጣጫ ለተሽከርካሪ ዝግ መሆኑን ተገልጿል።
እግረኞች በሙሉጌታ ዘለቀ ህንጻ በኩል ማለፍ ስለማይቻል በቦሌ ክ/ ከተማ አስተዳደር ጽ/ቤት ባለው የእግረኛ መንገድ እንዲጓዙ ተጠይቋል።
አሽከርካሪዎች ሌሎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ጥሪ ቀርቧል።
#የአዲስአበባትራፊክማኔጅመንትባለስልጣን
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ መገናኛ አካባቢ ያለውን ከፍተኛ የትራንስፖርት መጨናነቅ ለመፍታት ያግዛል የተባለው የመሬት ውስጥ የእግረኛ መተላላፊያ መስመር ግንባታ መጀመሩ ይታወቃል።
በመሆኑም በተለይ ከመገናኛ አደባባይ ወደ ቦሌ ፤ ከቦሌ ወደ መገናኛ አደባባይ በሁለቱም አቅጣጫ ለተሽከርካሪ ዝግ መሆኑን ተገልጿል።
እግረኞች በሙሉጌታ ዘለቀ ህንጻ በኩል ማለፍ ስለማይቻል በቦሌ ክ/ ከተማ አስተዳደር ጽ/ቤት ባለው የእግረኛ መንገድ እንዲጓዙ ተጠይቋል።
አሽከርካሪዎች ሌሎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ጥሪ ቀርቧል።
#የአዲስአበባትራፊክማኔጅመንትባለስልጣን
@tikvahethiopia