' ስካይ ላይት ሆቴል ' ውስጥ ተሸሽገው ነበር የተባሉ በሙስና ወንጀል የተጠረጠሩ ኃላፊ ዛሬ በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተነገረ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ልደታ ክፍለ ከተማ የመሬት ልማት ጽ/ቤት ተወካይ ሃላፊ የነበሩት አቶ ቴዎድሮስ ፀጋዬ በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ታሰሩ።
ግለሰቡ ሲፈለጉ ቆይተው ዛሬ ' ስካይ ላይት ሆቴል ' ውስጥ ተደብቀው ከነበሩበት መያዛቸውን የከተማ አስተዳደሩ አመልክቷል።
" ተጠርጣሪው በኮሪደር ልማት ስም ከመንግስት አሰራር እና ውሳኔ ውጪ #በመደራደር ባልተገባ መንገድ ለግል ጥቅም ለማግኘት ሲሉ የካሳ ግምት በማናር ውስን የሆነዉን የህዝብ እና የመንግስትን መሬት ከአሰራር ውጪ በማሰተላለፍ ለግለሰቦች አላስፈላጊ ጥቅም በማዋል ተጠርጥረው " መያዛቸው ነው የተገለጸው።
በተጨማሪ በክ/ከተማው ወረዳ 4 ዉስጥ በኮሪደር ልማት ኘላን ልማት ውስጥ የማይካተት ከመመሪያና አሠራር ዉጪ 6 መኖሪያ እና አንድ የንግድ ቤት የሆነውን ከ ' ዋይልድ አፓርትመንት ' የተባለ ህንፃ ባለቤት ጋር ተመሳጥረው ቤቶቹን እንዲፈርሱ በማድረግና ለህንፃው ማስፋፊያ እንዲሆን የሰጡ መሆኑ ተመላክቷል።
የመንግስት ቤት ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ግለሰቦችም የእቃ የማጓጓዥያ ሳይከፈል እንዲነሱ በማድረጉ እንዲሁም " ምትክ ቦታ እስጣቿለው " ፤ " አንደኛ ቦታ አስቀይርላቿለው " እና የተለያዩ የማጭበርበር ወንጀሎችን በማድረግ ህብረተሰቡ ሲያደናግሩ ፤ ያልተገቡ ጥቅሞችን ሲያደርጉ ነበር ተብሏል።
ከተሸሸጉበት ' ስካይ ላይት ሆቴል ' ውስጥ የተያዙት ግለሰቡ " ከሀገር ውጪ ወተዋል " አስብለው እንደነበር ተገልጿል።
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ልደታ ክፍለ ከተማ የመሬት ልማት ጽ/ቤት ተወካይ ሃላፊ የነበሩት አቶ ቴዎድሮስ ፀጋዬ በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ታሰሩ።
ግለሰቡ ሲፈለጉ ቆይተው ዛሬ ' ስካይ ላይት ሆቴል ' ውስጥ ተደብቀው ከነበሩበት መያዛቸውን የከተማ አስተዳደሩ አመልክቷል።
" ተጠርጣሪው በኮሪደር ልማት ስም ከመንግስት አሰራር እና ውሳኔ ውጪ #በመደራደር ባልተገባ መንገድ ለግል ጥቅም ለማግኘት ሲሉ የካሳ ግምት በማናር ውስን የሆነዉን የህዝብ እና የመንግስትን መሬት ከአሰራር ውጪ በማሰተላለፍ ለግለሰቦች አላስፈላጊ ጥቅም በማዋል ተጠርጥረው " መያዛቸው ነው የተገለጸው።
በተጨማሪ በክ/ከተማው ወረዳ 4 ዉስጥ በኮሪደር ልማት ኘላን ልማት ውስጥ የማይካተት ከመመሪያና አሠራር ዉጪ 6 መኖሪያ እና አንድ የንግድ ቤት የሆነውን ከ ' ዋይልድ አፓርትመንት ' የተባለ ህንፃ ባለቤት ጋር ተመሳጥረው ቤቶቹን እንዲፈርሱ በማድረግና ለህንፃው ማስፋፊያ እንዲሆን የሰጡ መሆኑ ተመላክቷል።
የመንግስት ቤት ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ግለሰቦችም የእቃ የማጓጓዥያ ሳይከፈል እንዲነሱ በማድረጉ እንዲሁም " ምትክ ቦታ እስጣቿለው " ፤ " አንደኛ ቦታ አስቀይርላቿለው " እና የተለያዩ የማጭበርበር ወንጀሎችን በማድረግ ህብረተሰቡ ሲያደናግሩ ፤ ያልተገቡ ጥቅሞችን ሲያደርጉ ነበር ተብሏል።
ከተሸሸጉበት ' ስካይ ላይት ሆቴል ' ውስጥ የተያዙት ግለሰቡ " ከሀገር ውጪ ወተዋል " አስብለው እንደነበር ተገልጿል።
@tikvahethiopia