#AddisAbaba : የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በተቋሙ ቢሮ አካባቢ በህገ ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ነበሩ ያላቸው 25 ሴቶች የሚገኙባቸው 65 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር እንደዋሉ ገለጸ።
መ/ቤቱ ግለሰቦቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት ከፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን እና ከልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 አስተዳደር ጋር በመቀናጀት እንደሆነ አመልክቷል።
ተጠርጣሪዎች ፦
➡️ በተለያየ የህገ-ወጥ የድለላ ስራዎች ላይ የተሰማሩ፣
➡️ የስራ ከባቢውን በማወክ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ችግር እየፈጠሩ ያሉ፣
➡️ በተለያየ የማጭበርበር እና የማታለል ተግባር ላይ ተሰማርተው የነበሩ
➡️ በህገ-ወጥ መንገድ የኦን ላይን የአስቸኳይ ፓስፖርት የሚሞሉ ናቸው ሲል ገልጿል።
በአጠቃላይ 7 በህገወጥ የንግድ እንቅስቃሴ ላይ የተሰማሩ ቤቶች እንደታሸጉ አመልክቷል።
@tikvahethiopia
መ/ቤቱ ግለሰቦቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት ከፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን እና ከልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 አስተዳደር ጋር በመቀናጀት እንደሆነ አመልክቷል።
ተጠርጣሪዎች ፦
➡️ በተለያየ የህገ-ወጥ የድለላ ስራዎች ላይ የተሰማሩ፣
➡️ የስራ ከባቢውን በማወክ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ችግር እየፈጠሩ ያሉ፣
➡️ በተለያየ የማጭበርበር እና የማታለል ተግባር ላይ ተሰማርተው የነበሩ
➡️ በህገ-ወጥ መንገድ የኦን ላይን የአስቸኳይ ፓስፖርት የሚሞሉ ናቸው ሲል ገልጿል።
በአጠቃላይ 7 በህገወጥ የንግድ እንቅስቃሴ ላይ የተሰማሩ ቤቶች እንደታሸጉ አመልክቷል።
@tikvahethiopia
#AddisAbaba
ነገ የሚዘጉ መንገዶች ይፋ ሆኑ።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ነገ እሁድ ከሚከበረው ከ1446ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል ጋር ተያይዞ የዒድ ሶላት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን ይፋ አድርጓል።
ዝግ የሚሆኑት መንጋዶች የትኞቹ ናቸው ?
➡️ ከመገናኛ በ22 አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ቅዱስ ዑራኤል አደባባይ በተመሳሳይ ከቦሌ አካባቢ በአትላስ መብራት ወደ ቅዱስ ዑራኤል አደባባይ ለሚሄዱ አትላስ መብራት እና ፒኮኪ መብራት ላይ፣
➡️ ከቦሌ ወሎ ሠፈር መታጠፊያ ወደ ኦሎምፒያ አደባባይ ለሚሔዱ አሽከርካሪዎች ኦሎምፒያ አደባባይ ላይ፣
➡️ ከወሎ ሠፈር ጀምሮ እስከ ጋዜቦ አደባባይ ውስጥ ውስጡን ወደ ዋናው መንገድ የሚያስወጡት መንገዶች ዝግ የሚደረጉ ይሆናል፣
➡️ ከአጎና መስቀለኛ ወደ ጥላሁን አደባባይ -ሳንጆሴፍ መብራት አጎና ሲኒማ መስቀለኛ ላይ፣
➡️ ከቡልጋሪያ መብራት ወደ ገነት ሆቴል ሜክሲኮ አደባባይ ለሚሄዱ አሽከርካሪዎች ቡልጋሪያ መብራት ላይ፣
➡️ ከቅድስት ልደታ ፀበል በAU ቅዱስ ሚካኤል መታጠፊያ ወደ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ AU ሚካኤል መታጠፊያ፣
➡️ ከጦር ኃይሎች በከፍተኛ ፍ/ቤት ወደ ሜክሲኮ አደባባይ ለሚሔዱ ከፍተኛ ፍ/ቤት አደባባይ ላይ፣
➡️ ከአብነት አካባቢ በፈረሰኛ ፖሊስ መብራት ወደ ጨፌ ሜዳ መብራት ፈረሰኛ መብራት ላይ፣
➡️ ከሞላ ማሩ መስቀለኛ ወደ ጌጃ ሰፈር መውረጃ ሞላ ማሩ መታጠፊያ ላይ፣
➡️ ከመርካቶ አካባቢ በአቡነ ተክለ ኃይማኖት አደባባይ ወደ ጥቁር አንበሳ ለሚሄዱ አቡነ ተክለ ኃይማኖት አደባባይ ላይ
➡️ ከፒያሳ በባንኮዲሮማ መብራት ወደ ቴዎድሮስ አደባባይ ባንኮዲሮማ መብራት ላይ፣
➡️ ከሲግናል አካባቢ በሴቶች አደባባይ ወደ ካዛንቺስ ለሚሄዱ ተሽከርካሪዎች ሴቶች አደባባይ ላይ ከንጋቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ድረስ መንገዶቹ ዝግ ይሆናሉ።
አሽከርካሪዎች ሌሎች አማራጮችን እንዲጠቀሙ ፖሊስ አሳስቧል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም ዛሬ ከበዓሉ ዋዜማ ምሽት ጀምሮ በተጠቀሱት ቦታዎች ላይ ተሽከርካሪዎችን ለአጭርም ይሁን ለረጅም ሠዓት ማቆም የተከለከለ ነው ተብሏል።
#AddisAbabPolice
@tikvahethiopia
ነገ የሚዘጉ መንገዶች ይፋ ሆኑ።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ነገ እሁድ ከሚከበረው ከ1446ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል ጋር ተያይዞ የዒድ ሶላት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን ይፋ አድርጓል።
ዝግ የሚሆኑት መንጋዶች የትኞቹ ናቸው ?
➡️ ከመገናኛ በ22 አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ቅዱስ ዑራኤል አደባባይ በተመሳሳይ ከቦሌ አካባቢ በአትላስ መብራት ወደ ቅዱስ ዑራኤል አደባባይ ለሚሄዱ አትላስ መብራት እና ፒኮኪ መብራት ላይ፣
➡️ ከቦሌ ወሎ ሠፈር መታጠፊያ ወደ ኦሎምፒያ አደባባይ ለሚሔዱ አሽከርካሪዎች ኦሎምፒያ አደባባይ ላይ፣
➡️ ከወሎ ሠፈር ጀምሮ እስከ ጋዜቦ አደባባይ ውስጥ ውስጡን ወደ ዋናው መንገድ የሚያስወጡት መንገዶች ዝግ የሚደረጉ ይሆናል፣
➡️ ከአጎና መስቀለኛ ወደ ጥላሁን አደባባይ -ሳንጆሴፍ መብራት አጎና ሲኒማ መስቀለኛ ላይ፣
➡️ ከቡልጋሪያ መብራት ወደ ገነት ሆቴል ሜክሲኮ አደባባይ ለሚሄዱ አሽከርካሪዎች ቡልጋሪያ መብራት ላይ፣
➡️ ከቅድስት ልደታ ፀበል በAU ቅዱስ ሚካኤል መታጠፊያ ወደ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ AU ሚካኤል መታጠፊያ፣
➡️ ከጦር ኃይሎች በከፍተኛ ፍ/ቤት ወደ ሜክሲኮ አደባባይ ለሚሔዱ ከፍተኛ ፍ/ቤት አደባባይ ላይ፣
➡️ ከአብነት አካባቢ በፈረሰኛ ፖሊስ መብራት ወደ ጨፌ ሜዳ መብራት ፈረሰኛ መብራት ላይ፣
➡️ ከሞላ ማሩ መስቀለኛ ወደ ጌጃ ሰፈር መውረጃ ሞላ ማሩ መታጠፊያ ላይ፣
➡️ ከመርካቶ አካባቢ በአቡነ ተክለ ኃይማኖት አደባባይ ወደ ጥቁር አንበሳ ለሚሄዱ አቡነ ተክለ ኃይማኖት አደባባይ ላይ
➡️ ከፒያሳ በባንኮዲሮማ መብራት ወደ ቴዎድሮስ አደባባይ ባንኮዲሮማ መብራት ላይ፣
➡️ ከሲግናል አካባቢ በሴቶች አደባባይ ወደ ካዛንቺስ ለሚሄዱ ተሽከርካሪዎች ሴቶች አደባባይ ላይ ከንጋቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ድረስ መንገዶቹ ዝግ ይሆናሉ።
አሽከርካሪዎች ሌሎች አማራጮችን እንዲጠቀሙ ፖሊስ አሳስቧል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም ዛሬ ከበዓሉ ዋዜማ ምሽት ጀምሮ በተጠቀሱት ቦታዎች ላይ ተሽከርካሪዎችን ለአጭርም ይሁን ለረጅም ሠዓት ማቆም የተከለከለ ነው ተብሏል።
#AddisAbabPolice
@tikvahethiopia
#AddisAbaba : የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዛሬ ለህዝብ ትራንስፖርት የሚሰጡ 100 ዘመናዊ የኤሌክትሪክ አውቶቢሶች ወደ ስራ መግባታቸውን አሳውቋል።
አውቶብሶቹ በሁሉም የከተማችን አቅጣጫዎች ለነዋሪዎች ነጻ የትራንስፖርት አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኙ አመልክቷል።
ከተማ አስተዳደሩ በመንግስትና የግል አጋርነት መርሃግብር የመጀመሪያው የትራንስፖርት ኦፕሬተር በመሆን ዛሬ አገልግሎት መስጠት የጀመረውን የበላይነህ ክንዴ ግሩፕ መሆኑ ተመላክቷል።
#MayorOfficeofAA
@tikvahethiopia
አውቶብሶቹ በሁሉም የከተማችን አቅጣጫዎች ለነዋሪዎች ነጻ የትራንስፖርት አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኙ አመልክቷል።
ከተማ አስተዳደሩ በመንግስትና የግል አጋርነት መርሃግብር የመጀመሪያው የትራንስፖርት ኦፕሬተር በመሆን ዛሬ አገልግሎት መስጠት የጀመረውን የበላይነህ ክንዴ ግሩፕ መሆኑ ተመላክቷል።
#MayorOfficeofAA
@tikvahethiopia
#AddisAbaba
" የመንጃ ፈቃድ ዕድሳት አገልግሎት በየአቅራቢያው ማግኘት ይቻለል " - የአሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን
ከመጋቢት 24 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ የመንጃ ፈቃድ ዕድሳት አገልግሎት በየአቅራቢያው በመታወቂያ አድራሻ ሳይገደብ እንዲሰጥ መፈቀዱን የአዲስ አበባ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን አሳውቋል።
ከዚህ ቀደም የአዲስ አበባ መንጃ ፈቃድ ለማሳደስ በመንጃ ፈቃዱ ላይ ወደ ተገለጸው እና ፋይሉ ወዳለበት ክፍለ ከተማ (የመታወቂያ አድራሻ) የሚገኝ የአሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን ቢሮ መሄድ ግድ ይል ነበር።
ከነገ በኃላ ግን በየትኛውም አቅራቢያ በሚገኝ ቦታ በመታወቂያ አድራሻ ሳይገደብ መንጃ ፈቃድ ማሳደስ ይቻላል ተብሏል።
ተገልጋዮች በሚቀርባቸው ቅርንጫፍ ፋይላቸው ያለበት ቅርንጫፍ ሳይጠየቅ የጤና ምርመራ ሰርተፍኬትን በመያዝ የመንጃ ፈቃድ ዕድሳት አገልግሎት እንዲያገኙ መወሰኑን ባለስልጣን መ/ቤቱ አሳውቋል።
@tikvahethiopia
" የመንጃ ፈቃድ ዕድሳት አገልግሎት በየአቅራቢያው ማግኘት ይቻለል " - የአሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን
ከመጋቢት 24 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ የመንጃ ፈቃድ ዕድሳት አገልግሎት በየአቅራቢያው በመታወቂያ አድራሻ ሳይገደብ እንዲሰጥ መፈቀዱን የአዲስ አበባ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን አሳውቋል።
ከዚህ ቀደም የአዲስ አበባ መንጃ ፈቃድ ለማሳደስ በመንጃ ፈቃዱ ላይ ወደ ተገለጸው እና ፋይሉ ወዳለበት ክፍለ ከተማ (የመታወቂያ አድራሻ) የሚገኝ የአሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን ቢሮ መሄድ ግድ ይል ነበር።
ከነገ በኃላ ግን በየትኛውም አቅራቢያ በሚገኝ ቦታ በመታወቂያ አድራሻ ሳይገደብ መንጃ ፈቃድ ማሳደስ ይቻላል ተብሏል።
ተገልጋዮች በሚቀርባቸው ቅርንጫፍ ፋይላቸው ያለበት ቅርንጫፍ ሳይጠየቅ የጤና ምርመራ ሰርተፍኬትን በመያዝ የመንጃ ፈቃድ ዕድሳት አገልግሎት እንዲያገኙ መወሰኑን ባለስልጣን መ/ቤቱ አሳውቋል።
@tikvahethiopia
#AddisAbaba
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር " መደበኛ ያልሆነን የጎዳና ላይ ንግድ ስርዓት ለማስያዝ ይረዳል " ያለውን ደንብ አውጥቷል።
የደንቡን መውጣት ተከትሎ ንግዱ የሚካሄድበት ሰዓት በ5 ፈረቃ ተከፋፍሎ ይፋ ሆኗል።
በዚሁ መሰረት ፦
➡️ ከንጋቱ 11:00 ሰዓት እስከ ንጋቱ 1:00 ሰዓት የአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም የአልባሳት እና መጫሚያዎች ንግድ እንዲካሄድ፤
➡️ ከንጋቱ 1:00 ሰአት እስከ ረፋዱ 3:00 ሰዓት እንደ ብስኩት ፣ ሻይ ፣ ቡና ፣ የታሸገ ውሃ እና ለስላሳ መጠጦች ያሉ እና ለቁርስ የሚሆኑ ቀላል ያሉ ምግቦች ንግድ እንዲካሄድ ፤ የጫማ ፅዳት ወይም ሊስትሮ አገልግሎት በዚሁ ሰዓት እንዲካሄድ፤
➡️ ከረፋዱ 3:00 ሰዓት እስከ ቀኑ 6:00 የመፅሃፍት ፣ መፅሄቶች እና ጋዜጦች ንግድ እንዲካሄድ፤
➡️ ከቀኑ 6:00 ሰዓት እስከ 8:00 ሰዓት ቀላል ምግቦች በመባል የሚታወቁት እንደ ኬክ ፤ ብስኩት ፤ ሻይ ፤ ቡና ፤ የታሸገ ውሃና ለስላሳ መጠጦች ንግድ እንዲካሄድ፤
➡️ ከአመሻሽ 11:00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 3 ሰዓት ተኩል የተጠበሱ ምግቦች ፣ ጁስ ፣ ብስኩት ፣ ኬክ ፣ ሻይ ፣ ቡና ፣ የታሸገ ውሃ እና ለስላሳ መጠጦች እንዲሁም አልባሳት እና መጫሚያዎች ፣ ቀላል የኤሌክትሮኒክስ መገልገያዎች ፣ የውበት መጠበቂያ ኮስሞቲኮስች ንግድ እንዲካሄድ የከተማ አስተዳደሩ መርሃ ግብር አውጥቷል።
ንግዱ የሚካሄድባቸው ቦታዎች #ወደፊት እንደሚለዩና ይፋ እንደሚደረጉ የከተማ አስተዳደሩ አሳውቋል።
መደበኛ ያልሆነ የጎዳና ላይ ንግድ " ኮንትሮባድን ያበረታታል፤ ለትራፊክ መጨናነቅ እና አደጋም መንስኤ ይሆናል እንዲሁም በህጋዊ ንግዱ ላይ ተፅዕኖ ያሳድራል " በሚል በከተማው አስታዳደር ቁጥጥር እንዲደረግበት ሲሞከር እንደነበር ይታወሳል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ነው።
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር " መደበኛ ያልሆነን የጎዳና ላይ ንግድ ስርዓት ለማስያዝ ይረዳል " ያለውን ደንብ አውጥቷል።
የደንቡን መውጣት ተከትሎ ንግዱ የሚካሄድበት ሰዓት በ5 ፈረቃ ተከፋፍሎ ይፋ ሆኗል።
በዚሁ መሰረት ፦
➡️ ከንጋቱ 11:00 ሰዓት እስከ ንጋቱ 1:00 ሰዓት የአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም የአልባሳት እና መጫሚያዎች ንግድ እንዲካሄድ፤
➡️ ከንጋቱ 1:00 ሰአት እስከ ረፋዱ 3:00 ሰዓት እንደ ብስኩት ፣ ሻይ ፣ ቡና ፣ የታሸገ ውሃ እና ለስላሳ መጠጦች ያሉ እና ለቁርስ የሚሆኑ ቀላል ያሉ ምግቦች ንግድ እንዲካሄድ ፤ የጫማ ፅዳት ወይም ሊስትሮ አገልግሎት በዚሁ ሰዓት እንዲካሄድ፤
➡️ ከረፋዱ 3:00 ሰዓት እስከ ቀኑ 6:00 የመፅሃፍት ፣ መፅሄቶች እና ጋዜጦች ንግድ እንዲካሄድ፤
➡️ ከቀኑ 6:00 ሰዓት እስከ 8:00 ሰዓት ቀላል ምግቦች በመባል የሚታወቁት እንደ ኬክ ፤ ብስኩት ፤ ሻይ ፤ ቡና ፤ የታሸገ ውሃና ለስላሳ መጠጦች ንግድ እንዲካሄድ፤
➡️ ከአመሻሽ 11:00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 3 ሰዓት ተኩል የተጠበሱ ምግቦች ፣ ጁስ ፣ ብስኩት ፣ ኬክ ፣ ሻይ ፣ ቡና ፣ የታሸገ ውሃ እና ለስላሳ መጠጦች እንዲሁም አልባሳት እና መጫሚያዎች ፣ ቀላል የኤሌክትሮኒክስ መገልገያዎች ፣ የውበት መጠበቂያ ኮስሞቲኮስች ንግድ እንዲካሄድ የከተማ አስተዳደሩ መርሃ ግብር አውጥቷል።
ንግዱ የሚካሄድባቸው ቦታዎች #ወደፊት እንደሚለዩና ይፋ እንደሚደረጉ የከተማ አስተዳደሩ አሳውቋል።
መደበኛ ያልሆነ የጎዳና ላይ ንግድ " ኮንትሮባድን ያበረታታል፤ ለትራፊክ መጨናነቅ እና አደጋም መንስኤ ይሆናል እንዲሁም በህጋዊ ንግዱ ላይ ተፅዕኖ ያሳድራል " በሚል በከተማው አስታዳደር ቁጥጥር እንዲደረግበት ሲሞከር እንደነበር ይታወሳል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ነው።
@tikvahethiopia
#AddisAbaba
" ከአራት ኪሎ እስከ ሽሮ ሜዳ ያለዉ አካባቢ የዩኒቨርሲቲ መንደር ለማድረግ የቀረበው ጥናት ፀድቋል " - የአዲስ አበባ ካቢኔ
በዛሬዉ እለት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አስተላልፏል።
ከነዚህም አንዱ ፥ በፕላንና ልማት ቢሮ እና በት/ት ሚኒስቴር በጋራ ተጠንቶ የቀረበውን ከአራት ኪሎ እስከ ሽሮ ሜዳ ያለዉ አካባቢ የዩኒቨርሲቲ መንደር የማድረግ ነው።
ካቢኔው " በአካባቢው ያሉትን አገልግሎቶች አካቶ የትምህርት ፣ የምርምር ፣ የእውቀት እና የባህል ልህቀትን በከተማዋ ለማሳደግ በሚያስችል አግባብ የቀረበ በመሆኑ የመንደር ምስረታውን ዉሳኔ ፀድቋል " ሲል አሳውቋል።
ከዚህ ባለፈ ካቢኔው ፦
- የአደጋ ስጋት አመራር ምክር ቤትና ፤የአደጋ ዝግጁነት ፈንድ ማቋቋሚያ ረቂቅ ደንብ ላይ ተወያይቶ ዉሳኔ አሳልፏል።
- በመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ የቀረበዉን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያላቸዉ ፕሮጀክቶች፤ የመሬት ምደባ ጥያቄዎች አስመልክቶም ዉሳኔ አስተላልፏል።
- የምግብ ስርዓትና ኒዉትሪሽን ምክር ቤት ማቋቋሚያ ረቂቅ ደንብ ላይም ተወያይቶ ዉሳኔ አስተላልፏል።
@tikvahethiopia
" ከአራት ኪሎ እስከ ሽሮ ሜዳ ያለዉ አካባቢ የዩኒቨርሲቲ መንደር ለማድረግ የቀረበው ጥናት ፀድቋል " - የአዲስ አበባ ካቢኔ
በዛሬዉ እለት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አስተላልፏል።
ከነዚህም አንዱ ፥ በፕላንና ልማት ቢሮ እና በት/ት ሚኒስቴር በጋራ ተጠንቶ የቀረበውን ከአራት ኪሎ እስከ ሽሮ ሜዳ ያለዉ አካባቢ የዩኒቨርሲቲ መንደር የማድረግ ነው።
ካቢኔው " በአካባቢው ያሉትን አገልግሎቶች አካቶ የትምህርት ፣ የምርምር ፣ የእውቀት እና የባህል ልህቀትን በከተማዋ ለማሳደግ በሚያስችል አግባብ የቀረበ በመሆኑ የመንደር ምስረታውን ዉሳኔ ፀድቋል " ሲል አሳውቋል።
ከዚህ ባለፈ ካቢኔው ፦
- የአደጋ ስጋት አመራር ምክር ቤትና ፤የአደጋ ዝግጁነት ፈንድ ማቋቋሚያ ረቂቅ ደንብ ላይ ተወያይቶ ዉሳኔ አሳልፏል።
- በመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ የቀረበዉን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያላቸዉ ፕሮጀክቶች፤ የመሬት ምደባ ጥያቄዎች አስመልክቶም ዉሳኔ አስተላልፏል።
- የምግብ ስርዓትና ኒዉትሪሽን ምክር ቤት ማቋቋሚያ ረቂቅ ደንብ ላይም ተወያይቶ ዉሳኔ አስተላልፏል።
@tikvahethiopia
#AddisAbaba #EV_Charging
ኢትዮ ቴሌኮም ሁለተኛውን እጅግ ፈጣን የኤሌክትሪክ መኪና ባትሪ መሙያ ጣቢያ አገልግሎት በአዲስ አበባ አስጀምሯል።
ስራ የጀመረው ሁለተኛው ጣቢያ ከመገናኛ ቦሌ መንገድ አንበሳ ጋራጅ ፊት ነው የሚገኘው።
ይህ ጣቢያ የአውሮፓ ስሪት የሆኑ መኪኖችን የኤሌክትሪክ ኃይል መሙላት የሚያስችል እጅግ ፈጣን አቅም ያለው ተብሏል።
የኤሌክትሪክ መኪና መሙያዎቹ በ1 ሰከንድ 1 ኪሎሜትር ለመጓዝ የሚያስችል የኤሌክትሪክ ኃይል በመሙላት በ15 ደቂቃ ውስጥ ሙሉ (100%) የኤሌክትሪክ ኃይል የመሙላት አቅም እንዳላቸው ኩባንያው አሳውቋል።
በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ቴክኖሎጂ የባትሪ መስፈርቶች እና የደንበኛን ትዕዛዝ በመተንተን የባትሪውን ደህንነት እየፈተሸ የተሽከርካሪው ባትሪ በሚችለው ፍጥነት ቻርጅ እንደሚያደርግ ተመላክቷል።
ኩባንያው ቀደም ሲል 16 መኪኖችን ማስተናገድ የሚችል ጣቢያ ወደስራ ያስገባ ሲሆን ከየካቲት 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለ14,280 የኤሌክትሪክ መኪኖች፣ በ376,574.72 ኪሎዋት/ሰዓት ኃይል ቻርጅ ማድረግ እንደቻለ አመልክቷል።
አዲሱ የመሙያ ጣቢያ 4 እጅግ በጣም ፈጣን እና 12 በጣም ፈጣን መሙያዎችን ያካተተ ሲሆን፣ ይህም ያሉንን የኤሌክትሪክ መኪና መሙያ ጣቢያዎች የማስተናገድ አቅም ወደ 32 ለማድረስ አስችሏል፡፡
#EthioTelecom #EcoFriendly #EV_Charging
@tikvahethiopia
ኢትዮ ቴሌኮም ሁለተኛውን እጅግ ፈጣን የኤሌክትሪክ መኪና ባትሪ መሙያ ጣቢያ አገልግሎት በአዲስ አበባ አስጀምሯል።
ስራ የጀመረው ሁለተኛው ጣቢያ ከመገናኛ ቦሌ መንገድ አንበሳ ጋራጅ ፊት ነው የሚገኘው።
ይህ ጣቢያ የአውሮፓ ስሪት የሆኑ መኪኖችን የኤሌክትሪክ ኃይል መሙላት የሚያስችል እጅግ ፈጣን አቅም ያለው ተብሏል።
የኤሌክትሪክ መኪና መሙያዎቹ በ1 ሰከንድ 1 ኪሎሜትር ለመጓዝ የሚያስችል የኤሌክትሪክ ኃይል በመሙላት በ15 ደቂቃ ውስጥ ሙሉ (100%) የኤሌክትሪክ ኃይል የመሙላት አቅም እንዳላቸው ኩባንያው አሳውቋል።
በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ቴክኖሎጂ የባትሪ መስፈርቶች እና የደንበኛን ትዕዛዝ በመተንተን የባትሪውን ደህንነት እየፈተሸ የተሽከርካሪው ባትሪ በሚችለው ፍጥነት ቻርጅ እንደሚያደርግ ተመላክቷል።
ኩባንያው ቀደም ሲል 16 መኪኖችን ማስተናገድ የሚችል ጣቢያ ወደስራ ያስገባ ሲሆን ከየካቲት 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለ14,280 የኤሌክትሪክ መኪኖች፣ በ376,574.72 ኪሎዋት/ሰዓት ኃይል ቻርጅ ማድረግ እንደቻለ አመልክቷል።
አዲሱ የመሙያ ጣቢያ 4 እጅግ በጣም ፈጣን እና 12 በጣም ፈጣን መሙያዎችን ያካተተ ሲሆን፣ ይህም ያሉንን የኤሌክትሪክ መኪና መሙያ ጣቢያዎች የማስተናገድ አቅም ወደ 32 ለማድረስ አስችሏል፡፡
#EthioTelecom #EcoFriendly #EV_Charging
@tikvahethiopia
#AddisAbaba
“ ገንዘብ የማይቀጣ በእስር ይለወጥለታል። በእስር የማይቀጣ ደግሞ አጭር የሆነ የሰውነት ማሟሟቂያ ቅጣቶችንም ይቀጣል ” - ባለስልጣኑ
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2017 ዓ/ም የዘጠኝ ወራት ሪፓርት ግምገማን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥቶ ነበር።
በዚህም፣ “ ከአምናው ዘጠኝ ወር ጋር ሲነጻጸር የዘንድሮው የዘጠኝ ወሩ አፈጻጸማችን 64% የደንብ ጥሰት የቀነሰበት ነው ” ብሏል።
ይህን ያሉት የባለስልጣኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ፣ ከኮሪደር ልማት ጋር በተያያዘ በመንገደኞች ላይ የሚጣለውን ቅጣት ተመጣጣኝ አለመሆን በተመለከተ ስለሚነሳው ቅሬታ ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄም ምላሽ ሰጥተዋል።
ምን መለሱ ?
“ ህጎች፣ ደንቦች የሚወጡበት የህዝቡን ጥቅም ለማስጠበቅ ነው። ሌላ ተልዕኮ የለውም። እንደ ራሳችን ሰውነት፣ ልብስ የምንከባከብበት ቱሩፋታችን ነው ማለት ይቻላል የኮሪደር ልማቱ።
በሳይክል መንገድ የሚሄድ ሰው በሳይክል መንገድ እንዲሄድ ፤ እግረኛውም በእግረኛው መንገድ እንዲሄድ የተደረገበት፣ በሳሮች፣ ፋውንቴሽኖች አካባቢ ቆሻሻ እንዳይጣል የተደረገበት በርካታ ስልጠናዎች ተሰጥዋል።
ቀጥሎ ህግ የማስከበር ሥራ ስራ ነው። ቅጣቱ የዚህን ያህል የጎላምና በጣም የከፋም አይደለም። የቅጣት ደረጃዎች አሉ።
ገንዘብ የሚቀጣ ይቀጣል። ገንዘብ የማይቀጣ በእስር ይለወጥለታል። በእስር የማይቀጣ ደግሞ አጭር የሆነ የሰውነት ማሟሟቂያ ቅጣቶችንም ይቀጣል።
አህያ በኮሪደር ላይ መንዳት (በተለይ በቪአይፒ መንገዶች ከቦሌ እስከ ቤተ መንግስት ሌሎችም አካባቢዎች ላይ) ተቀባይነት የሌለው ነው።
ማህበረሰቡም ሚዲያዎችም እንዲያውቁት የምንፈልገው በከተማችን ውስጥ ምንም አይነት የእንስሳት ዝውውር የማይፈጠርባት ከተማን ከመፍጠር አንፃር አጠንክረን የምንሰራበት ይሆናል።
የቀጣናቸውም ቅጣቶች እንደሚባለው ሳይሆን በሁለት፣ ሦስት (በቦሌ፣ በጊዮርጊስ የፈጸምናቸው) አካባቢዎች አሉ። እሱም ደግሞ የተጋነነ ቅጣት አይደለም ተመጣጣኝ የሆነ ቅጣት ነው። ግን ወደ ፊት አጠናክረን የምንሄድበህ ይሆናል ” ብለዋል።
ከወንዝ ዳር ልማት ጋር በተያያዘ ትላልቅ ተቋማትና ፋብሪካዎች ይቀጣሉ፣ ሁልጊዜ ግንዛቤ እየተፈጠረላቸው ነው ይባላል፤ ግን በመቶ ሺዎች፣ በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ይቀጣሉ ምክንያቱ ምንድን ነው ? የሚል ጥያቄም ቀርቦላቸዋል።
ሻለቃ ዘሪሁን ምን መለሱ?
“ የደንብ ቁጥር 181 የወንዝ ዳርቻ ደንብን በተመለከተ ተቋማችን ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን፣ ከአረንጓዴና ውበት ቢሮና ከመንገዶችና ውሃ ባለስልጣን ጋር በመሆን አብረን ነው እየሰራን ያለነው።
በወንዝ ዳርቻ ላይ በርካታ ግንዛቤዎች ተሰጥተዋል። አንደኛ ጥናቶች ተጠንተዋል። ትላልቅ የሚባሉ ሰባት ወንዞች አሉ። በተለይ ፍሳሾችን ወደ ወንዝ የሚገቡበት ሁኔታ አለ። ያ ተጠንቷል። በተጠናው መሠረት ተጋላጭ ናቸው የተባሉ የመንግስት የግል ተቋማትና የግለሰብም ጭምር ግንዛቤ ተሰጥቷል።
ግንዛቤ የመስጠት ችግር የለም። ሰው ያንን ተቀብሎ የመተግበር ችግር ነው። የምናስተካክለው ህግን በማስከበር ነው ማለት ነው። ስለዚህ ህግን በማስከበር በርካታ ርቀቶች ሂደናል።
በፋብሪካዎች፣ በትላልቅ የመንግስትም ሆነ የግል ሆስፒታሎች የሚወጡ ፍሳሾች አደገኝነታቸው በናሙና ይወሰዳል፣ በላብራቶሪ ተረጋግጦ እንደአደገኝነቱ መጠን በደንቡ ላይ የተቀመጠ የህግ መቀጮ ስላለ በዚያ መሠረት ይቀጣል።
በዚህ ያገኘነው ውጤት፥ ወደ 2,850 በላይ ወደ ወንዙ የሚገቡ ከተለያዩ ተቋማት የሚፈሱ ፍሳሾች ቆመዋል። የራሳቸውን ስፍቲ ታንከር የመስራት ለውጥ አለ ” ነው ያሉት።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
“ ገንዘብ የማይቀጣ በእስር ይለወጥለታል። በእስር የማይቀጣ ደግሞ አጭር የሆነ የሰውነት ማሟሟቂያ ቅጣቶችንም ይቀጣል ” - ባለስልጣኑ
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2017 ዓ/ም የዘጠኝ ወራት ሪፓርት ግምገማን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥቶ ነበር።
በዚህም፣ “ ከአምናው ዘጠኝ ወር ጋር ሲነጻጸር የዘንድሮው የዘጠኝ ወሩ አፈጻጸማችን 64% የደንብ ጥሰት የቀነሰበት ነው ” ብሏል።
ይህን ያሉት የባለስልጣኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ፣ ከኮሪደር ልማት ጋር በተያያዘ በመንገደኞች ላይ የሚጣለውን ቅጣት ተመጣጣኝ አለመሆን በተመለከተ ስለሚነሳው ቅሬታ ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄም ምላሽ ሰጥተዋል።
ምን መለሱ ?
“ ህጎች፣ ደንቦች የሚወጡበት የህዝቡን ጥቅም ለማስጠበቅ ነው። ሌላ ተልዕኮ የለውም። እንደ ራሳችን ሰውነት፣ ልብስ የምንከባከብበት ቱሩፋታችን ነው ማለት ይቻላል የኮሪደር ልማቱ።
በሳይክል መንገድ የሚሄድ ሰው በሳይክል መንገድ እንዲሄድ ፤ እግረኛውም በእግረኛው መንገድ እንዲሄድ የተደረገበት፣ በሳሮች፣ ፋውንቴሽኖች አካባቢ ቆሻሻ እንዳይጣል የተደረገበት በርካታ ስልጠናዎች ተሰጥዋል።
ቀጥሎ ህግ የማስከበር ሥራ ስራ ነው። ቅጣቱ የዚህን ያህል የጎላምና በጣም የከፋም አይደለም። የቅጣት ደረጃዎች አሉ።
ገንዘብ የሚቀጣ ይቀጣል። ገንዘብ የማይቀጣ በእስር ይለወጥለታል። በእስር የማይቀጣ ደግሞ አጭር የሆነ የሰውነት ማሟሟቂያ ቅጣቶችንም ይቀጣል።
አህያ በኮሪደር ላይ መንዳት (በተለይ በቪአይፒ መንገዶች ከቦሌ እስከ ቤተ መንግስት ሌሎችም አካባቢዎች ላይ) ተቀባይነት የሌለው ነው።
ማህበረሰቡም ሚዲያዎችም እንዲያውቁት የምንፈልገው በከተማችን ውስጥ ምንም አይነት የእንስሳት ዝውውር የማይፈጠርባት ከተማን ከመፍጠር አንፃር አጠንክረን የምንሰራበት ይሆናል።
የቀጣናቸውም ቅጣቶች እንደሚባለው ሳይሆን በሁለት፣ ሦስት (በቦሌ፣ በጊዮርጊስ የፈጸምናቸው) አካባቢዎች አሉ። እሱም ደግሞ የተጋነነ ቅጣት አይደለም ተመጣጣኝ የሆነ ቅጣት ነው። ግን ወደ ፊት አጠናክረን የምንሄድበህ ይሆናል ” ብለዋል።
ከወንዝ ዳር ልማት ጋር በተያያዘ ትላልቅ ተቋማትና ፋብሪካዎች ይቀጣሉ፣ ሁልጊዜ ግንዛቤ እየተፈጠረላቸው ነው ይባላል፤ ግን በመቶ ሺዎች፣ በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ይቀጣሉ ምክንያቱ ምንድን ነው ? የሚል ጥያቄም ቀርቦላቸዋል።
ሻለቃ ዘሪሁን ምን መለሱ?
“ የደንብ ቁጥር 181 የወንዝ ዳርቻ ደንብን በተመለከተ ተቋማችን ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን፣ ከአረንጓዴና ውበት ቢሮና ከመንገዶችና ውሃ ባለስልጣን ጋር በመሆን አብረን ነው እየሰራን ያለነው።
በወንዝ ዳርቻ ላይ በርካታ ግንዛቤዎች ተሰጥተዋል። አንደኛ ጥናቶች ተጠንተዋል። ትላልቅ የሚባሉ ሰባት ወንዞች አሉ። በተለይ ፍሳሾችን ወደ ወንዝ የሚገቡበት ሁኔታ አለ። ያ ተጠንቷል። በተጠናው መሠረት ተጋላጭ ናቸው የተባሉ የመንግስት የግል ተቋማትና የግለሰብም ጭምር ግንዛቤ ተሰጥቷል።
ግንዛቤ የመስጠት ችግር የለም። ሰው ያንን ተቀብሎ የመተግበር ችግር ነው። የምናስተካክለው ህግን በማስከበር ነው ማለት ነው። ስለዚህ ህግን በማስከበር በርካታ ርቀቶች ሂደናል።
በፋብሪካዎች፣ በትላልቅ የመንግስትም ሆነ የግል ሆስፒታሎች የሚወጡ ፍሳሾች አደገኝነታቸው በናሙና ይወሰዳል፣ በላብራቶሪ ተረጋግጦ እንደአደገኝነቱ መጠን በደንቡ ላይ የተቀመጠ የህግ መቀጮ ስላለ በዚያ መሠረት ይቀጣል።
በዚህ ያገኘነው ውጤት፥ ወደ 2,850 በላይ ወደ ወንዙ የሚገቡ ከተለያዩ ተቋማት የሚፈሱ ፍሳሾች ቆመዋል። የራሳቸውን ስፍቲ ታንከር የመስራት ለውጥ አለ ” ነው ያሉት።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
#AddisAbaba : በአዲስ አበባ ተቋርጦ የነበረውን የመኖርያ ቤት ህብረት ሥራ አገልግሎት ለማስቀጠል ተጠንቶ የቀረበ ውሳኔ ሃሳብ ላይ ካቢኔው ውሳኔ አሳለፈ።
የከተማው ካቢኔ ዛሬ ባካሄደው 4ተኛ አመት 10ኛ መደበኛ ስብሰባውን የተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ውሳኔ አሳልፏል።
ከነዚህም አንዱ ተቋርጦ የነበረዉ የመኖርያ ቤት ህብረት ሥራ ማህበራት አገልግሎትን የሚመለከት ነበር።
በዚህም አገልግሎቱን ለማስቀጠል ተጠንቶ የቀረበ የውሳኔ ሀሳብ ላይ የመልካም አስተዳደር ጥያቄን ሊፈታ በሚችል አግባብ የውሳኔ ሀሳብ ማሳለፉ ተነግሯል።
ሌላኛው ፦
- የብርሃን አይሰውራን፣
- የመነን
- የገላን ቦርዲንግ ትምህርት ቤቶች ካላቸው ልዩ ስምሪት፣ የጥራት ደረጃ እና ከሚያንቀሳቅሱት ሀብትና ንብረት አስተዳደር አንፃር ህጋዊ ሰውነት ኖሯቸው እንዲተዳደሩ እና ተጠሪነታቸው በቀጥታ ለከተማዉ ትምህርት ቢሮ እንዲሆን የቀረበዉን ደንብ መርምሮ አጽድቋል።
ካቢኔው ሀገራዊ ፋይዳ አላቸው ባላቸው ፕሮጀክቶች የቀረበ የመሬት ማስፋፊያ ጥያቄዎች ላይ ተወያይቶ አጽድቋል።
@tikvahethiopia
የከተማው ካቢኔ ዛሬ ባካሄደው 4ተኛ አመት 10ኛ መደበኛ ስብሰባውን የተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ውሳኔ አሳልፏል።
ከነዚህም አንዱ ተቋርጦ የነበረዉ የመኖርያ ቤት ህብረት ሥራ ማህበራት አገልግሎትን የሚመለከት ነበር።
በዚህም አገልግሎቱን ለማስቀጠል ተጠንቶ የቀረበ የውሳኔ ሀሳብ ላይ የመልካም አስተዳደር ጥያቄን ሊፈታ በሚችል አግባብ የውሳኔ ሀሳብ ማሳለፉ ተነግሯል።
ሌላኛው ፦
- የብርሃን አይሰውራን፣
- የመነን
- የገላን ቦርዲንግ ትምህርት ቤቶች ካላቸው ልዩ ስምሪት፣ የጥራት ደረጃ እና ከሚያንቀሳቅሱት ሀብትና ንብረት አስተዳደር አንፃር ህጋዊ ሰውነት ኖሯቸው እንዲተዳደሩ እና ተጠሪነታቸው በቀጥታ ለከተማዉ ትምህርት ቢሮ እንዲሆን የቀረበዉን ደንብ መርምሮ አጽድቋል።
ካቢኔው ሀገራዊ ፋይዳ አላቸው ባላቸው ፕሮጀክቶች የቀረበ የመሬት ማስፋፊያ ጥያቄዎች ላይ ተወያይቶ አጽድቋል።
@tikvahethiopia
#AddisAbaba
" በ3 ወራት ውስጥ 943 ፍቺዎች እንዲሁም 53 ውሳኔ የተሰጠባቸው ጉዲፈቻዎች ምዝገባ ተከናውኗል !! "
የአዲስ አበባ ከተማ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ከፌደራል የመጀመርያ ፍርድ ቤት ጋር የፍቺ እና ጉዲፈቻ ውሳኔዎችን መዝግቦ በአንድ መስኮት አገልግሎት ለመስጠት የጋራ ስምምነት ፈጽመው እየሰሩ ሲሆን ላለፉት 3 ወራት ውስጥ የተሰሩ ስራዎችን አፈፃፀም በጋራ ገምግመዋል።
በዚህም ወቅት በቀረበ ሰነድ 996 ተገልጋዮች በ3 ወራት የኩነት ምዝገባ አገልግሎቱን በፍርድ ቤቶች በአንድ መስኮት ማግኘታቸው ተመላክቷል።
ከዚህም ውስጥ ውሳኔ ያገኙ 943 #ፍቺዎች እንዲሁም 53 ውሳኔ የተሰጠባቸው #ጉዲፈቻዎች በወቅቱ ምዝገባ በማድረግ በአንድ ማዕከል በፍ/ቤቶች አገልግሎት መሰጠቱ ተመላክቷል።
Via https://t.iss.one/addisvaitalpress/9155
@tikvahethiopia
" በ3 ወራት ውስጥ 943 ፍቺዎች እንዲሁም 53 ውሳኔ የተሰጠባቸው ጉዲፈቻዎች ምዝገባ ተከናውኗል !! "
የአዲስ አበባ ከተማ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ከፌደራል የመጀመርያ ፍርድ ቤት ጋር የፍቺ እና ጉዲፈቻ ውሳኔዎችን መዝግቦ በአንድ መስኮት አገልግሎት ለመስጠት የጋራ ስምምነት ፈጽመው እየሰሩ ሲሆን ላለፉት 3 ወራት ውስጥ የተሰሩ ስራዎችን አፈፃፀም በጋራ ገምግመዋል።
በዚህም ወቅት በቀረበ ሰነድ 996 ተገልጋዮች በ3 ወራት የኩነት ምዝገባ አገልግሎቱን በፍርድ ቤቶች በአንድ መስኮት ማግኘታቸው ተመላክቷል።
ከዚህም ውስጥ ውሳኔ ያገኙ 943 #ፍቺዎች እንዲሁም 53 ውሳኔ የተሰጠባቸው #ጉዲፈቻዎች በወቅቱ ምዝገባ በማድረግ በአንድ ማዕከል በፍ/ቤቶች አገልግሎት መሰጠቱ ተመላክቷል።
Via https://t.iss.one/addisvaitalpress/9155
@tikvahethiopia