TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.6K videos
216 files
4.35K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
አሜሪካ በቀጥታ ወደ ጦርነቱ ትገባ ይሁን ? እስራኤል በኢራን ላይ እያካሄደችው ባለው ጥቃት ውስጥ አሜሪካ ስለምትሳተፍበት ሁኔታ ለመወያየት ዶናልድ ትራምፕ በዋይት ሐውስ ውስጥ አስቸኳይ ስብሰባ ከከፍተኛ ባለሥልጣኖቻቸው ጋር አድርገዋል። አንድ ሰዓት ከ20 ደቂቃ በቆየው ስብሰባ ላይ ዋነኛ አጀንዳ የነበረው እስራኤል በኢራን የኒውክሌር ማዕከላት ላይ እየፈጸመችው ባለው ጥቃት ውስጥ አሜሪካ መሳትፍ እንዳለባት…
#Update

እስራኤል በኢራን ላይ በፈጸመችው ጥቃት እስከ እሁድ ምሽት ድረስ 224 ሰዎች መገደላቸውን 1 ሺህ 277 መጎዳታቸውን ኢራን አስታውቃለች።

እስራኤል በበኩሏ በኢራን ጥቃት 20 ሰዎች እንደተገደሉባት ገልጻለች።

ተባብሶ በቀጠለው የሁለቱ ሀገራት ጦርነት ምክንያት ነዋሪዎች ከአካባቢያቸው እንዲወጡ በሁለቱም በኩል መልዕክት እየተላለፈ ነው።

ኢራን የእስራኤሏ ሃይፋ ከተማ በተወሰነው ክፍል ያሉ ነዋሪዎች ለህይወታቸው አደጋ ስለሚኖር አካባቢያቸውን ለቀው እንዲወጡ ማስጠንቀቂያ ሰጥታለች።

እስራኤልም ነዋሪዎች ከተለያዩ የቴህራን ክፍሎች ለቀው እንዲወጡ እያስጠነቀቅች ነው። በዚህም ሰዎች በቻሉት አቅም ወደ አጎራባች ከተማ እየወጡ እንዳለ ተነግሯል።

መረጃው ቢቢሲ ነው።

@tikvahethiopia
854😭306🕊169😢46👏33🙏22😡22😱19🤔16💔12🥰5
TIKVAH-ETHIOPIA
" ኃይል ተቋርጧል ! " አዲስ አበባን ጨምሮ በሃገሪቱ አንዳንድ አካባቢዎች የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጧል። በዋናው የኤሌክትሪክ መስመር /ግሪድ/ ባጋጠመ ቴክኒካል ብልሽት ምክንያት አዲስ አበባን ጨምሮ በሃገሪቱ አንዳንድ አካባቢዎች የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጡን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታውቋል። የተቋረጠውን የኃይል አቅርቦት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለመመለስ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ነው…
" በተወሰኑ ቦታዎች ኃይል እየተመለሰ ነው " - የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል

አዲስ አበባን ጨምሮ በኢትዮጵያ በከፊል የተቋረጠው ኃይል በተወሰኑ አካባቢዎች መመለስ እንደጀመረ የኢትዮጵያ ኤሌትክሪክ ኃይል አሳውቋል።

" በተቀሩት አካባቢዎችም በየደረጃው መልሶ ኃይል የማገናኘት ስራ እየተሰራ ነው " ብሏል።

#Update : ሙሉ በሙሉ ኃይል ተመልሷል።

@tikvahethiopia
799👏191😭103😡90🙏66🤔41🥰24🕊24😢22😱14💔13
TIKVAH-ETHIOPIA
" ፍቅረኛዉን በቅናት ተነሳስቶ የገደላት ግለሰብ ማምለጥ እንደማይችል ሲያውቅ እጁን ለፖሊስ ሰጥቷል " - የኮንሶ ዞን ከና ወረዳ ፖሊስ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮንሶ ዞን ከና ወረዳ የገዛ ፍቅረኛዉን በስለት በመዉጋት ሕይወቷ እንዲያልፍ ያደረገው ግለሰብ ከሕግ እንደማያመልጥ ሲገባዉ እጁን ለፖሊስ መስጠቱን የከና ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ምክትል ኢንስፔክተር ገዛኸኝ ካራተ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ። ግለሰቡና…
#Update

" የመምህርት ተዋበች ገዳይ በ25 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጥቷል " - የኮንሶ ዞን ፖሊስ

በኮንሶ ዞን ኬና ወረዳ ፋሻ ቀበሌ ልዩ ስሙ ኮቶላ ወንዝ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከአንድ ወር በፊት የገዛ ፍቅረኛዉን መምህርት ተዋበች ኩሲያን ሌላ " የፍቅር አጋራ ይዘሻል " በሚል ጥርጣሬ በአሰቃቂ ሁኔታ የገደላት ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዉሎ በተመሰረተበት ከባድ የግድያ ወንጀል ጥፋተኛ በመባል የፍርድ ዉሳኔ እንደተላለፈበት የኮንሶ ዞን ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ሰለሞን ካማይታ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ተከሳሹ ወንጀሉን የፈፀመበት ሁኔታ፣ ሰዓት እና የድርጊቱን አሰቃቂነት ዐቃቤ ህግ በሰዉና ኤግዚቢት እንዲሁም የምርመራ ማስረጃ በማቅረቡ የኮንሶ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተከሳሽ ኩሻቦ ኩራዎ ጥፋተኛ በማለት በ25 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም የወንጀል ድርጊቱን በተፈፀመበት ወቅት የኬና ወረዳዉ ፖሊስ ምላሽ አካቶ በጉዳዩ ላይ ዘገባ ማቅረቡ አይዘነጋም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
689😡174😭119👏79💔58🙏35🕊26😢18🥰14🤔13
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

የኢራን መገናኛ ብዙኃን በሰሜናዊ ኢራን ፍንዳታዎች በመሰማታቸው " ተኩስ አቁሙ ተጥሷል " አሉ።

በኢራን እና በእስራኤል መካከል የተኩስ አቁም መደረጉ ቢነገርም በሰሜናዊ ኢራን ማዛንዳራን ግዛት ውስጥ ፍንዳታዎች መሰማታቸውን ነዋሪዎች ተናግረዋል።

ለኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ጓድ ቅርብ የሆነው 'ፋርስ' የተባለው የዜና ወኪል እንዳለው ከዋና ከተማዋ ቴህራን በስተሰሜን ማዛንዳራን ግዛት ውስጥ በምትገኘው ባቦልሳር ከተማ ውስጥ ፍንዳታዎች ተሰምተዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ከፊል መንግሥታዊ የሆኑት 'መህር' እና 'ኢስና' የተባሉት የዜና ወኪሎች በሰሜናዊ ግዛት ውስጥ በሚገኙ የተለያዩ ስፍራዎች ፍንዳታዎች መከሰታቸውን እና የአየር መከላከያ መሳሪያዎች ተኩስ መሳማቱን በመጥቀስ የተኩስ አቁሙ “ተጥሷል” ብለዋል።

በተጨማሪም የኢራን መንግሥት ቴሌቪዥን ፍንዳታዎች መከሰታቸውን እና የግዛቲቱን አስተዳዳሪ ቃል አቀባይ ክስተቱን በተመለከተ ዝርዝር ጉዳዮች ገና አለመታወቃቸውን መናጋራቸው ገልጿል።

በሌላ በኩል ፥ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ " እስራኤል በኢራን ላይ ጥቃት መፈጸም የለባትም " በማለት ማስጠንቀቂያ አስተላልፈዋል።

ፕሬዝዳንቱ  " እስራኤል፤ እነዚያን ቦምቦች አትጣይ። በጥቃቱ የምትቀጥይ ከሆነ ከፍተኛ ጥሰት ነው። የጦር አውሮፕላን አብራሪዎችሽን አሁኑኑ ወደ ቤታቸው መልሺ! " ብለዋል።

ይህ የፕሬዝዳንቱ ማስጠንቀቂያ የመጣው ከዛሬ ጠዋት ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆን የተኩስ አቁም በኢራን እና በእስራኤል መካከል መደረጉን ካስታወቁ በኋላ ነው።

እስራኤል በትራምፕ ሃሳብ መስማማቷን ስታሳውቅ፣ ኢራን ደግሞ ጥቃቱን የምታቆመው እስራኤል ካቆመች ብቻ ነው ብላለች።

ምንጭ ፦ ቢቢሲ

@tikvahethiopia
746🕊79😡34🙏23😭13🤔6👏4💔4😱2😢2🥰1
TIKVAH-ETHIOPIA
" የጉዞ ታሪክ በሌላቸው ሁለት ታዳጊዎች ላይ የMpox ምልክት መታየቱ ስጋት ፈጥሮብናል " - የሰገን ዙሪያ ወረዳ ነዋሪዎች ➡️ " በኮንሶ ዞን የኤም ፖክስ(Mpox) በሽታ ምልክት በሁለት ሰዎች ላይ ታይቶ ናሙና ተወስዶባቸው ዉጤት እየተጠባበቅን ነዉ " - የዞኑ ጤና መምሪያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡ የሰገን ዙሪያ ወረዳ ነዋሪዎች ስለዝንጀሮ ፈንጣጣ (Mpox) በሽታ ምልክቶች በተለያዩ አጋጣሚዎች…
#Update

" በሰገን ዙሪያ ወረዳ በሁለት ሰዎች ላይ የታየዉ ምልክት የMpox በሽታ ስላልሆነ ሕብረተሰቡ ከስጋት ነፃ ሆኖ ጥንቃቄ ማድረግ አለበት " - የኮንሶ ዞን ጤና መምሪያ


ከሰሞኑ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮንሶ ዞን ሰገን ዙሪያ ወረዳ አማራይታ ተብሎ በሚጠራዉ አከባቢ በሁለት እህታማምች ላይ የታየዉን የሰዉነት ላይ ምልክትን ተከትሎ ሕብረተሰቡ " የኤም ፖክስ በሽታ ሊሆን ይችላል " በሚል ስጋት ዉስጥ መግባቱንና የዞኑ ጤና መምሪያ በበኩሉ ከተጠረጠሩት ሁለት የአንድ ቤተሰብ አባላት ላይ ናሙና ወስዶ ለምርመራ መላኩን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳቆ ነበር።

የኮንሶ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ግርማ በሌ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለፁት ከሁሉቱ እህታማሞች የተወሰደዉ ናሙና ዉጤት ከአዲስ አበባ መምጣቱንና በዉጤቱ መሰረት ምልክቱ MPox (የዝንጀሮ ፈንጣጣ) አለመሆኑ ተረጋግጧል ብለዋል።

አቶ ግርማ ሕብረተሰቡ በሽታዉን መጠንቀቁ አግባብ ቢሆንም ልጆቹንና ቤተሰቦቻቸውን ያገለለበት መንገድ ተገቢ አለመሆኑን ገልፀዋል።

ዉጤቱን ተከትሎም ስለ በሽታው የግንዛቤ ማስፋትና የጥንቃቄ ስራዎች እየተሰሩ ያለ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ልጆቹ ከቤተሰቦቻቸው ጋር እንዲቀላቀሉ መደረጉንም አስታውቀዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
378🙏57😭14🤔6😱6🕊5🥰4😢4👏2
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

ከጎንደር መተማ በሚወስደው መንገድ በአንድ ቀን ልዩነት በመንግስት የፀጥታ ሀይሎች ላይና በንፁሀን ላይ " ዘግናኝ " ሲል የጠራው ጭፍጨፋ መፈጸሙን የምዕራብ ጎንደር ዞን አስተዳደር አስታውቋል።

የዞኑ ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ለጥቃቱ " ፅንፈኛው ቅማንት " ሲል የጠራውን ታጣቂ ኃይል ተጠያቂ አድርጓል።

ዞኑ ሰኔ 19 ባወጣው መግለጫ በቀን ሰኔ 16/2017 ዓ.ም 11:00 ገደማ  ከጎንደር ገንዳ ዉሃ በሚወስደው መንገድ " መቃ " በተባለ ቦታ ጥቃቱ መፈጸሙን ገልጿል።

በቀን 16/10/2017 ዓ/ም ከቀኑ11:30 ገደማ ለአርሶ አደሩ እና በአካባቢው በእርሻ ስራ በኢንቨስትመት ለተሰማሩ የሚከፋፈፍል የአፈር ማዳበሪያ የጫኑ ተሽከርካሪ እና ሌሎች የህዝብ መጓጓዣዎችን አጅበው የነበሩ  መከላከያ፣ የፌደራል ፖሊስና የአድማ ብተና ፖሊስ አባላት እንዲሁም አሽከርካሪዎችና ተሳፋሪዎችን " ዘግናኝ በሆነ ጭካኔ ጨፍጭፏቸዋል " ሲል ገልጿል።

" ታጅበዉ እና ማዳበሪያ ጭነዉ ሲመጡ የነበሩ 16 ሹፌሮችን ከመኪና እያስወረደ ዘግናኝ በሆነ ጭካኔ ጨፍጭፏቸዋል። የተወሠኑትንም አግቶ በመውሠድ አድራሻቸውን አጥፍቷል " ሲል መግለጫው ይጠቅሳል።

አክሎሞ " ይህው ታጣቂ ኃይል በቀን 18/10/2017 ዓ/ም ከፍተኛ የመከላከያ ሠራዊታችን አመራሮችና አባላት ላይ አቅዶና ተዘጋጅቶ ድጋሜ በጀግናው የመከላከያ ሠራዊት አባላት ላይ ግጭት አድርጓል " ብሏል።

የዞኑ አስተዳደር " ታቅዶበት የተፈፀመና ዘግናኝ " ብሎ በጠራው በዚህ ጥቃት በመጀመሪያው ቀን የሟቾች ቁጥር 16 ሹፌሮች መሆኑን ሲጠቅስ በሁለተኛው ቀን በተፈፀመው ጥቃት የሟቾችን ቁጥር ከመግለፅ ተቆጥቧል።

በመጀመሪያው ቀን በንፁሃን ላይ ደረሰ ባለው ጥቃት ቁጥራቸውን ያልገለፃቸው ሹፌሮች ታግተው መወሰዳቸውንም አክሏል።

ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስተያየታቸውን የሰጡ የአይን እማኝ ግን  ሰኔ 16፤ 2017 ዓ.ም በተፈፀመው ጥቃት የሟቾችን ቁጥር ከመቶ በላይ እንደሚደርስ ተናግረዋል።

ይህዉ የአይን እማኝ እንደሚለው " በእለቱ ከታጣቂ ሀይሉ ጋር መሬት ላይ ሲጨቃጨቁ የነበሩት አድማ ብተና ፖሊስና በFSR መኪና ተጭነው የነበሩ የፀጥታ ሀይሎችን ከጫካ እየወጡ ነው መኪና ላይ እያሉ የጨፈጨፏቸው " ብሏል።

" እነሱን ሲጨርሱ ደግሞ በየመኪናው ባሉ ሹፌሮችና ተሳፋሪዎች ላይ ጥቃቱን ፈፅመዋል" ሲል ገልጿል።

የዞኑ አስተዳደር " ፅንፈኛ " ሲል የሚጠራውን የቅማንት ታጣቂ ኃይል በአካባቢው ከ2008 ዓ.ም ጀምሮ በንፁሀን ዜጎች ላይ ግድያና እገታ እንደሚፈፅም በመግለጫው አንስቷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ባሕር ዳር
#TikvahEthiopiaFamilyBD

@tikvahethiopia
590😭323😡32💔27🕊21👏12😢10🙏9🤔7😱3🥰2
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

ሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴን ውሳኔ " ተገቢና ህግን ያልተከተለ ውሳኔ " ሲል ተቃወመ።

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፈዴሬሽን የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ ዋንጫ ከሲዳማ ቡና ተነጥቆ ለወላይታ ዲቻ እንዲመለስ ሲል ውሳኔ አሳልፏል።

ይህ ተከትሎ የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ቦርድ ውሳኔውን " ተገቢነት የለሌው ውሳኔ ነው። ውሳኔው እጅግ አሳዝኖናል " ብሏል።

" ብርቅዬ የክለባችን ተጫዋቾች በጨዋታ ሜዳ የገጠሙትን ሁሉንም ከጨዋታ ብልጫ ጋር በማሸነፍ የ2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ ዋንጫ ማሸነፉ የአደባባይ ምስጥር ነዉ " ሲል ገልጿል።

" ይሁን እንጂ ' የሊግ ካምፓኒ ያወጣውን የፋይናንስ ደንብ አላከበራችሁም ' በሚል በክለቡና በተጫዋቾች ላይ ቅጣት ተጥሎባቸዋል ቢባልም ክለቡ  ያነሳዉ ዋንጫ የኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ በ48 ክለቦች መካከል የተደረገው መሆኑ ዕሙን ነው " ብሏል።

" የሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ የታገዱ ተጫዋቾችን አሰልፎ ከሆነ በጥሎ ማለፉ ያሸነፋቸው ክለቦች በሙሉ ፎርፌ አግኝተው ጉዳያቸው እንደገና መታየት አለበት እንደ ማለትም ይሆናል " ብሏል።

" እርስ በርስ የሚጣረሱ ሀሳቦችን በማገናኘት ውጤቱን ለመቀማት መሞከር  ተገቢና ህግን የተከተለ ውሳኔ ነው ብለን አናምንም " ሲል ቦርዱ አሳውቋል።

" ፌዴሬሽኑ ዉሳኔውን ከህግጋቱ ጋር በማገናዘብ እንደገና እንዲያጠነዉ ቅሬታችንን እናሰማለን " ብሏል።

" ህዝባችን በፌደሬሽኑ ውሳኔ የተከፋ ቢሆንም የአፊኒ ባህል ያለው ታላቅ ህዝብ ስለሆነ ክስተቶችን በመረጋጋት መርምሮ በተገቢው እንዲያጠነውና  ሂደቱን  በትዕግሥት እንዲጠባበቅ በአክብሮት እየጠይቃል " ሲል ገልጿል።

" የተነፈግነው ፍትህ እስኪረጋገጥ ድረስ ጉዳዩን እስከ ፊፋ ገላጋይ ፍርድ ቤት ድረስ በይግባኝ ወስደን ለጉዳዩ  ተገቢው እልባት እስኪሰጥ ድረስ የክለቡ ቦርድ ቁርጠኛ መሆኑን እናረጋግጣለን " ሲል አሳውቋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
#TikvahEthiopiaFamily

@tikvahethiopia
1.11K🤔144👏77😭48😡47🙏31🕊23😢10😱8💔7🥰1
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

19 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈርዶበታል !

ታዳጊዋ አያንቱ ቱና ላይ የግበረስጋ ድፍረት የፈጸመው ግለሰብ በ19 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል።

በሲዳማ ክልል ማዕከላዊ ሲዳማ ዞን ሻፋሞ ወረዳ የ13 ዓመቷን ታዲጊ አያንቱ ቱና ላይ የግብረስጋ ድፍረት ወንጀል በመፈጸም የተጠረጠረውና በፖሊስ ተባባሪነት ጭምር አምልጦ ከ1 ዓመት በላይ ተሰዉሮ የነበረዉ ወጣት በቲክቫህ ኢትዮጵያ ላይ መረጃው ከተሰራጨ በኋላ በተደረገ ክትትልና ፍለጋ ተጠርጣሪዉ በቁጥጥር ስር ዉሎ ክስ ተመስርቶበት እንደነበር የአያንቱ ታላቅ ወንድም ወጣት ጴጥሮስ ቱና ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

ይኸው ግለሰብ አርብ ዕለት ፍርድ ቤት ቀርቦ ዉሳኔ እንደተላለፈበት የአያንቱ ወንድም ተናግሯል።

የሻፋሞ ወረዳ ዐቃቤ ሕግ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደምሴ ፉና ስለጉዳዩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሲያስረዱ " የወረዳዉ ፖሊስ እና ዐቃቤ ሕግ በተከሳሹ ላይ ያቀረቡትን ጠንከር ያለ ምርመራ፣ የሰነድ እንዲሁም የሕክምና ማስረጃዎችን የተመለከተዉ የወረዳዉ ፍርድ ቤት ግለሰቡን ጥፋተኛ ነዉ በማለት በ19 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል " ብለዋል።

" ተጠርጣሪዉ በቁጥጥር ስር ከዋለ በኋላ በማቆያ ዉስጥ የምትገኘዉ አያንቱ ደፋሪዋ እንደተያዘ ከተነገራት በኋላ ጥሩ መሻሻል ታይቶባታል " የሚለዉ የታዳጊዋ ወንድም ጴጥሮስ " ከዚህ በኋላ ከማቆያ ወጥታ ወደ ትምህርት ገበታዋ ትመለሳለች " ብሏል

" የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላትን ጨምሮ ለታዳጊዋ ድምፅ ለሆናችሁ ሁሉ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ " ብሏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
1.7K😡1.16K👏344🙏162😭65💔61🕊45😢26🤔16🥰14
TIKVAH-ETHIOPIA
የዘውዱ ሃፍቱ ጉዳይ ከምን ደረሰ ? ከዘውዱ ሃፍቱ የግድያ ወንጀል ጋር በተያያዘ የመጨረሻ ውሳኔ ዛሬ ሰኔ 3/2017 ዓ.ም ሊሰጥ ቀጠሮ ቢያዝለትም ለሰኔ 30/2017 ዓ.ም ተሸጋግሯል። ዛሬ የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል የችሎት ውሎውን ተከታትሏል። የእንስት ዘውዱ ሃፍቱ የግድያ ወንጀል ግንቦት 8/2017 ዓ.ም ለመጨረሻ ውሳኔ ተቀጥሮ ነበር ሆኖም የተከሳሽ ቤተሰቦች በቀሰቀሱት ግርግርና ረብሻ…
#Update

" የዘገየ ፍትህ እንዳልተሰጠ ይቆጠራል ! " - ሂደቱን የሚከታተሉ ታዛቢዎች

አሁንም የእንስት ዘወዱ ሃፍቱ የግድያ ወንጀል የፍርድ ውሳኔ ሌላ ቀጠሮ ተይዞለታል።

የግድያ ወንጀሉ ከተፈፀመ የፊታችን ነሀሴ ወር የሚከበረው የአሸንዳ 2017 ዓ.ም በዓል ሁለት ዓመት ይሞላዋል።

አሰቃቂ የግድያ ወንጀሉ የአሸንዳ በዓል በሚከበርበት ወርሃ ነሀሴ 2015 ዓ.ም ነበር የተፈፀመው።  

የእንስት ዘውዱ ሃፍቱ የግድያ ወንጀል ችሎት የትላንት ውሎ ምን ይመስል ነበር ? 

የእንስት ዘውዱ ሃፍቱ የግድያ ወንጀል በመመልከት ላይ የሚገኘው የመቐለ ማእከላዊ ፍርድ ቤት ግንቦት 8 ቀን 2017 ዓ.ም በተከሳሾች ላይ ያስተላለፈው ውሳኔ ላይ ጥፋተኛ የተባሉት ግለሰቦች የሚያቀርቡት የፍርድ የማቅለያ ለመስማት ነው ለሰኔ 30 ቀን 2017 ዓ.ም የተቀጠረው።

የችሎቱ ዳኞች በያዙት ቀጠሮ ተከሳሾች ለፍርድ ማቅለያ የሚሆናቸውን የህክምናና ሌሎች ሰነድ እንዲያቀርቡ ባዘዙት መሰረት በጠበቃቸው በኩል አቅርበዋል።

አንደኛ ተከሳሽ የልብ ህመም ታማሚና የኪንታሮት ህመምተኛ ፣ ሁለተኛው ተከሳሽ ደግሞ የስኳርና የኪንታሮት ህመምተኛ መሆናቸውን በቃል ቢገልጹም በሃኪሞች ማስረጃ እንዲረጋገጥ ለሀምሌ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷል።

በግድያ ወንጀሉ በመፈፀመ የተጠረጠሩ ሁለቱ ወጣቶች ሀምሌ 3 ቀን 2017 ዓ/ም በሃኪም የተረጋገጠ የፅሁፍ ማስረጃ ያቀርቡ እንደሆነ ያኔ የሚታይ ሆኖ የችሎት ሂደቱን የተከታታሉ የሚድያ ባለሙያዎች ፣ የሴቶች ጥቃት እንዲቆም የሚሰሩ ግለሰቦችና ተቋማት " ይህንን ሁሉ በሽታ ተቋቁመው ይህን መሰል ዘግናኝ ግድያ ለመፈፀም እንዴት ጉልበትና አቅም አገኙ ? " የሚል ጥያቄ ጭረዋል።

የችሎቱ የውሎ መረጃ  በማህበራዊ ሚዲያ የተከታተሉ በርካቶች የፍርድ ሂደቱ ለሁለት አመታት መራዘሙ በመቃወም "  የዘገየ ፍትህ እንዳልተሰጠ ይቆጠራል " ብለዋል።

የአሰቃቂ የግድያ ወንጀሉ የፍርድ ሂደት ሀምሌ 3 ቀን 2017 ዓ.ም መቋጫ ይብጀለት ይሆን ? ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ጉዳዩ ተከታትሎ ያቀርባል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
786😭197😡57🕊23🙏19😢10🥰9💔9😱5👏4
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " የዘገየ ፍትህ እንዳልተሰጠ ይቆጠራል ! " - ሂደቱን የሚከታተሉ ታዛቢዎች አሁንም የእንስት ዘወዱ ሃፍቱ የግድያ ወንጀል የፍርድ ውሳኔ ሌላ ቀጠሮ ተይዞለታል። የግድያ ወንጀሉ ከተፈፀመ የፊታችን ነሀሴ ወር የሚከበረው የአሸንዳ 2017 ዓ.ም በዓል ሁለት ዓመት ይሞላዋል። አሰቃቂ የግድያ ወንጀሉ የአሸንዳ በዓል በሚከበርበት ወርሃ ነሀሴ 2015 ዓ.ም ነበር የተፈፀመው።   የእንስት ዘውዱ…
#Update

የመቐለ ማእከላዊ ፍርድ ቤት በእንስት ዘውዱ ሃፍቱ የግድያ ወንጀል ጉዳይ ላይ የመጨረሻ ያለውን ቀነ ቀጠሮ ሰጠ።

ሰኔ 30 ቀን 2017 ዓ.ም በእስር የሚገኙ ተከሳሽ ተጠርጣሪዎች ለውሳኔ ማቅለያ የሚሆን የህክምና ማስረጃ እናቀርባለን ባሉት መሰረት ለዛሬ ሀምሌ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ቀጠሮ መስጠቱ ይታወሳል።

ይሁን እንጂ ዛሬ ችሎት ላይ የቀረቡት የተከሳሽ ጠበቆች " የመቐለ ዓይደር ሰፔሻላይዝድ ሆስፒታል ነገ አርብ ሀምሌ 4 ቀን 2017 ዓ.ም የህክምና ማስረጃ ለመስጠት ቀጠሮ ሰጥቶናል " ብለዋል።

ፍርድ ቤቱም ይህን አድምጦና ተቀብሎ የመጨረሻ ቀነ ቀጠሮ ለነገ ሰጥቷል።

በእንስት ዘውዱ ሃፍቱ የግድያ ወንጀል ላይ የመጨረሻ ውሳኔ ይሰጣል በሚል ዛሬ በመቐለ ማእከላይ ፍርድ ቤት የተበዳይና ተከሳሽ ቤተሰቦች ፣ በርካታ ሚድያዎች ፣ በሴት ጥቃት መከላከል ዙሪያ የሚሰሩ ስቪክ ማህበራት አመራሮችና አባላት ተገኝተው ነበር ።

ሁለት አመት ያስቆጠረው የእንስት ዘውዱ ሃፍቱ አሰቃቂ የግድያ ወንጀል ነገ ሀምሌ 4 ቀን 2017 ዓ.ም የመጨረሻ መቋጫ የፍርድ ውሳኔ ያገኝ ይሆን ? ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ የችሎቱን ውሳኔ ተከታትሎ ያቀርባል።

ቲክቫህ ኢትጵዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
560😭158🙏35😡30🕊19🤔17😢15💔13🥰6👏6