#HERQA
ከ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ጀምሮ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ከከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ ይሁንታ ሳያገኙ አዲስ ዲፓርትመንት ከፍተው ማስተማር አይችሉም ተባለ።
ኤጀንሲው ከዚህ ቀደም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በርቀት መርሃ ግብር የሚያስተምሯቸውን የትምህርት ክፍሎች ብቻ ይቆጣጠር ነበር።
ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ አዲስ መመሪያ ለመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች መተላለፉን የኤጀንሲው የእውቅና አሰጣጥ ዳይሬክተር አቢይ ደባይ ተናግረዋል።
በዚህም ተቋማቱ የሚከፍቷቸው የትምህርት ክፍሎች መስፈርቶችን ያሟሉ ስለመሆናቸው ኤጀንሲው መመርመር እንደሚጀመር ዳይሬክተሩ ገልፀዋል።
ኤጀንሲው በ2013 ዓ.ም በ1 ሺህ 112 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ ባደረገው ማጣራት፤ 562ቱ ማሟላት የነበረባቸውን ዝቅተኛ መስፈርቶች ሳያሟሉ በመገኘታቸው ውድቅ ተደርገዋል።
ተጠሪነት ለሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሆኖ የቆየውን ኤጀንሲ፤ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ጥራት ኮሚሽን በሚል ስያሜ እንደአዲስ በማቋቋም ተጠሪነቱ ለሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ ውይይት እየተደረገበት ይገኛል።
ምንጭ፦ #ሸገርኤፍኤም
@tikvahuniversity
ከ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ጀምሮ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ከከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ ይሁንታ ሳያገኙ አዲስ ዲፓርትመንት ከፍተው ማስተማር አይችሉም ተባለ።
ኤጀንሲው ከዚህ ቀደም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በርቀት መርሃ ግብር የሚያስተምሯቸውን የትምህርት ክፍሎች ብቻ ይቆጣጠር ነበር።
ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ አዲስ መመሪያ ለመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች መተላለፉን የኤጀንሲው የእውቅና አሰጣጥ ዳይሬክተር አቢይ ደባይ ተናግረዋል።
በዚህም ተቋማቱ የሚከፍቷቸው የትምህርት ክፍሎች መስፈርቶችን ያሟሉ ስለመሆናቸው ኤጀንሲው መመርመር እንደሚጀመር ዳይሬክተሩ ገልፀዋል።
ኤጀንሲው በ2013 ዓ.ም በ1 ሺህ 112 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ ባደረገው ማጣራት፤ 562ቱ ማሟላት የነበረባቸውን ዝቅተኛ መስፈርቶች ሳያሟሉ በመገኘታቸው ውድቅ ተደርገዋል።
ተጠሪነት ለሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሆኖ የቆየውን ኤጀንሲ፤ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ጥራት ኮሚሽን በሚል ስያሜ እንደአዲስ በማቋቋም ተጠሪነቱ ለሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ ውይይት እየተደረገበት ይገኛል።
ምንጭ፦ #ሸገርኤፍኤም
@tikvahuniversity
#MinistryofEducation
ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ተማሪዎች የእንግሊዘኛ ቋንቋ እንዲማሩ ሊደረግ ነው ተባለ፡፡
በ2017 የትምህርት ዘመን በአዲስ አበባ ባሉ የግልም ሆነ የመንግስት ትምህርት ቤቶች ለቅድመ አንደኛ ደረጃ ተማሪዎች የእንግሊዘኛ ትምህርት እንደሚሰጥ ተነግሯል፡፡
በ2015 ዓ.ም ወደ ትግበራ የገባው አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ህፃናት ወይም የቅድመ አንደኛ ደረጃ ተማሪዎች በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው ብቻ እንዲማሩ የሚያዝ መሆኑ ይታወቃል፡፡
አሁን ግን በመጭው የትምህርት ዘመን ህፃናት ተማሪዎች የእንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርት መማር እንደሚጀምሩ የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ተናግረዋል፡፡
ሚኒስትሩ ይህንን ያሉት አዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ባዘጋጀው 31ኛውን ጉባኤ ላይ ነው።
" ተማሪዎች የእንግሊዝኛ ቋንቋ ብቁ እና ተወዳዳሪ ለማድረግ ከቅድመ አንደኛ ደረጃ ጀምሮ ከአፍ መፍቻ ቋንቋቸው በተጨማሪ እንግሊዝኛ ቋንቋ እንዲማሩ እናደርጋለን ያሉት " ሚኒስትሩ ብርሀኑ (ፕ/ር) " ተማሪዎቹ የትምህርት ደረጃቸው ከፍ ሲል የሚማሯቸው ትምህርቶች በእንግሊዘኛ ቋንቋ ስለሚሆኑ ከልጅነታቸው ጀምሮ ቋንቋውን እንዲያውቁት ማድረግ አስፈላጊ ነው " ብለዋል፡፡
አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ወደ ትግበራ ከገባት 2015 ዓ.ም ጀምሮ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ተማሪዎች ሲማሩ የቆዩት በአፍመፍቻ ቋንቋቸው ነው አሁን ደግሞ በመጭው የትምህርት ዘመን የእንግሊዘኛ ቋንቋ ይማራሉ ተብሏል። #ሸገርኤፍኤም
@tikvahethiopia
ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ተማሪዎች የእንግሊዘኛ ቋንቋ እንዲማሩ ሊደረግ ነው ተባለ፡፡
በ2017 የትምህርት ዘመን በአዲስ አበባ ባሉ የግልም ሆነ የመንግስት ትምህርት ቤቶች ለቅድመ አንደኛ ደረጃ ተማሪዎች የእንግሊዘኛ ትምህርት እንደሚሰጥ ተነግሯል፡፡
በ2015 ዓ.ም ወደ ትግበራ የገባው አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ህፃናት ወይም የቅድመ አንደኛ ደረጃ ተማሪዎች በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው ብቻ እንዲማሩ የሚያዝ መሆኑ ይታወቃል፡፡
አሁን ግን በመጭው የትምህርት ዘመን ህፃናት ተማሪዎች የእንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርት መማር እንደሚጀምሩ የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ተናግረዋል፡፡
ሚኒስትሩ ይህንን ያሉት አዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ባዘጋጀው 31ኛውን ጉባኤ ላይ ነው።
" ተማሪዎች የእንግሊዝኛ ቋንቋ ብቁ እና ተወዳዳሪ ለማድረግ ከቅድመ አንደኛ ደረጃ ጀምሮ ከአፍ መፍቻ ቋንቋቸው በተጨማሪ እንግሊዝኛ ቋንቋ እንዲማሩ እናደርጋለን ያሉት " ሚኒስትሩ ብርሀኑ (ፕ/ር) " ተማሪዎቹ የትምህርት ደረጃቸው ከፍ ሲል የሚማሯቸው ትምህርቶች በእንግሊዘኛ ቋንቋ ስለሚሆኑ ከልጅነታቸው ጀምሮ ቋንቋውን እንዲያውቁት ማድረግ አስፈላጊ ነው " ብለዋል፡፡
አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ወደ ትግበራ ከገባት 2015 ዓ.ም ጀምሮ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ተማሪዎች ሲማሩ የቆዩት በአፍመፍቻ ቋንቋቸው ነው አሁን ደግሞ በመጭው የትምህርት ዘመን የእንግሊዘኛ ቋንቋ ይማራሉ ተብሏል። #ሸገርኤፍኤም
@tikvahethiopia
#ደመወዝ
🚨 " የሚከፈለው ክፍያና እንከፍላለን ብለው የሚያሳውቁት በጣም የሚያስቅ ልዩነት ያለው ነው " - ገቢዎች ቢሮ
🔴 " ቢሮው የፈጸመው ህገወጥ ድርጊት ነው " - የህግ ምሁር
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ሆቴሎች እና መጠጥ ቤቶችን ጨምሮ በተመረጡ የንግድ መስኮች የሚሰሩ ሰራተኞችን ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል እና የሰራተኞቻቸውን ብዛት የሚተምን ተመን አውጥቶ ስራ ላይ አውሏል።
ሆቴሎች፣ ስጋ ቤቶች፣ መጠጥ ቤቶች ፣ ምግብ ቤቶች፣ ካፍቴሪያዎችን ጨምሮ ሌሎች የንግድ ዘርፎች ላይ የሰራተኞች ደመወዝን በተመለከተ አሰሪዎች ትክክለኛ መረጃ ስለማይሰጡ ግብር እያጭበረበሩ ነው ብሏል።
ይህንን ተከትሎም ነው ይህን አሰራር መዘርጋቱን ገልጻል።
ስራ ላይ በዋለው ተመን መሰረት ፦
👉 የሆቴሎች ከ32 እስከ 50 ሰራተኞች
👉 ባርና ሬስቶራን ከ20 እስከ 24 ሰራተኞች
👉 ካፍቴሪካ ከ17 እስከ 25 ሰራተኞች
👉 ምግብ ቤት ከ17 እስከ 22 ሰራተኞች
👉 ምግብ፣ መጠጥ እና ስጋ ቤት ከ28 እስከ 48
👉 ስጋ ቤት እና መጠጥ ንግድ ከ20 እስከ 28 ሰራተኞች ይኖራቸዋል ተብሎ ተተምኗል።
በዚህ መሰረት የደመወዝ ግብር በተጠቀሰው የሰራተኛ ቁጥር ልክ ይጠየቃሉ።
ከአስተናጋጅ፣ ጥበቃና የፅዳት ሙያ ውጭ ላሉ ሰራተኞች ትንሹ የሚከፍሉት ደመወዝ 5,000 ብር ሆኖ ተተምኗል።
የወር ደመወዝ ተመኑ ምን ይመስላል ?
➡ ስጋ ቤት እና መጠጥ ንግድ
° የስራ አስኪያጅ /ተቆጣጣሪ/ ከ5,000 እስከ 9,500
° ካሸር 5,000 እስከ 6,000
° ዋናው ሼፍ ከ5,000 እስከ 18,000
° አስተናጋጅ ከ3,000 እስከ 3,500
° ፅዳት ከ2,500 እስከ 3,000
° ጥበቃ ከ2,500 እስከ 3,000
° ዋና ስጋ ቆራጭ ከ5,000 እስከ 7,000
° ረዳት ስጋ ቆራጭ ከ5,000 እስከ 5,500
° ስጋ ጠባሽ ከ6,000 እስከ 9,000
➡ ምግብ፣ መጠጥ እና ስጋ ቤት
° የስራ አስኪያጅ /ተቆጣጣሪ/ ከ8,000 እስከ 13,500
° ካሸር 5,000 እስከ 7,000
° ዋናው ሼፍ ከ6,000 እስከ 18,000
° አስተናጋጅ ከ2,500 እስከ 4,000
° ፅዳት ከ3,000 እስከ 3,500
° ጥበቃ ከ3,500 እስከ 4,000
° ዋና ስጋ ቆራጭ ከ5,000 እስከ 6,000
° ረዳት ስጋ ቆራጭ ከ5,000 እስከ 5,500
° ስጋ ጠባሽ ከ6,000 እስከ 9,000
➡ ምግብ ቤት
° የስራ አስኪያጅ /ተቆጣጣሪ / ከ6,000 እስከ 10,000
° ካሸር 5,000 እስከ 6,000
° ዋናው ሼፍ ከ5,000 እስከ 7,000
° አስተናጋጅ ከ2,000 እስከ 3,000
° ፅዳት ከ2,500 እስከ 3,000
° ጥበቃ ከ2,500 እስከ 3,000
➡ ካፍቴሪያ
° የስራ አስኪያጅ /ተቆጣጣሪ/ ከ6,000 እስከ 7,000
° ካሸር 5,000 እስከ 7,000
° ዋናው ሼፍ ከ5,500 እስከ 7,000
° አስተናጋጅ ከ2,500 እስከ 3,000
° ፅዳት ከ2,500 እስከ 3,000
° ጥበቃ ከ2,500 እስከ 3,000
° ሻይ ቡና / ጁስ አስተናጋጅ ከ5,000 እስከ 8,000
➡ ባርና ሬስቶራንት
° የስራ አስኪያጅ /ተቆጣጣሪ/ ከ7,000 እስከ 10,000
° ካሸር 5,000 እስከ 6,000
° ዋናው ሼፍ ከ5,000 እስከ 7,000
° አስተናጋጅ ከ2,000 እስከ 2,500
° ፅዳት ከ2,500 እስከ 3,000
° ጥበቃ ከ3,000 እስከ 3,500
➡ ሆቴል
° የስራ አስኪያጅ /ተቆጣጣሪ/ ከ8,000 እስከ 13,500
° ካሸር 5,000 እስከ 7,000
° ዋናው ሼፍ ከ6,000 እስከ 18,000
° አስተናጋጅ ከ2,500 እስከ 4,000
° ፅዳት ከ3,000 እስከ 3,500
° ጥበቃ ከ3,500 እስከ 4,000
° ዋና ስጋ ቆራጭ ከ5,000 እስከ 6,000
° ረዳት ስጋ ቆራጭ ከ5,000 እስከ 5,500
ወርሃዊ ደመወዝ ተተምኗል።
ይህ ለአንድ ሰራተኛ ይከፈላል ተብሎ የተተመነ ነው።
በዚህ ተመን ባለቤቶቹ የደመወዝ ግብር ሲከፍሉ ለተጠቀሱት የስራ መደቦች " ከዚህ ያነሰ ነው የምከፍለው " ማለት አይችሉም።
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ምን አሉ ?
ቢሮው ተመን ማውጣቱን አረጋግጠዋል።
ዳይሬክተሩ " በጥናት ላይ ተመስርቶ ነው ውሳኔው የተቀመጠው።
ከደመወዝ ግብር ጋር በተያያዘ የሚከፈለው ክፍያና እንከፍላለን ብለው የሚያሳውቁት በጣም የሚያስቅ ልዩነት ያለው ነው። በጣም ትልቅ ክፍተት ነው ያለው እኛ በከተማችን ያሉ የስራ መደቦችን በዝርዝር ጥናት አድርገን አብዛኛው በትንሹ የሚከፈላቸው ከ5000 ብር በላይ መሆኑ ምንም ጥርጥር የለውም።
ለፅዳት እና የቤት ሰራተኛ እንኳን ስንት እንደሚከፈል ይታወቃል።
እነሱ እንከፍላለን ብለው የሚያቀርቡት ዋጋ በጣም በጣም ዝቅተኛ ነው። ያንን ምንቀበልበት ሁኔታ የለም አሰራሩም አይፈቅድም። ጥናት ላይ ተመስርተን ዝቅተኛውን ተመን አስቀምጠናል " ብለዋል።
ገቢዎች ቢሮ ከተማውን የምታመነጨውን ገቢ አሟጦ ለመሰብሰብ ኃላፊነት እንደተጣለበትና በዚህም ምክንያት ዝቅተኛ የደመወዝ ተመን ስራ ላይ እንዳዋለ አሳውቋል።
ጉዳዩ በሚመለከተው አካል ህግ ሆኖ ሳይወጣ ገቢዎች ቢሮ ዝቅተኛ የደመወዝ መጠን አስቀምጦ ግብር መሰብሰብ ይቻላል ወይ ? የሚለው የህግ ጥያቄ ተነስቶበታል።
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የዓለም አቀፍ ንግድና የኢኮኖሚ ህጎች መምህር አቶ ጌዲዮን ወ/ዮሐንስ ምን ይላሉ ?
" ድርጊቱ ህገወጥ ነው።
እስካሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ በገቢዎች በኩል አነስተኛ ደመወዝን መወሰን ያንን ተከትሎ ግብር መሰስበብ እስካሁን ባለው የህግ ማዕቀፍ ይህንን የሚፈቅድ ነገር ስለሌለ ህጋዊ አይደለም።
በተለይ ከግብር ጋር ተያይዞ ህገመንግስቱ ግብር የሚጣለው በህግ ነው ይላል። በአንድ አስፈጻሚ / በአንድ የስራ ክፍል ኃላፊ ወይም እንደ ገቢዎች ቢሮ አይነት ደብዳቤን መሰረት አድርጎ ደመወዝን መወሰን አይቻልም።
ደመወዝ ግብር የሚከፈልበት አንድ ገቢ ነው። ይሄም ታክስ ቤዝ / ግብር የሚጣልበት አንድ ገቢ እንለዋለን። እሱ በህግ ተወስኗል። ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ከዚህ እስከዚህ ሲሆን ይሄን ያህል ... ከዚህ እስከዚህ ይሄን ያህል ... ብር እየተባለ በግብር አዋጃችን ላይ ተቀምጧል።
በዚህ በገቢ ግብር አዋጅ ላይ በተለያዩ የስራ ክፍሎችና አይነቶች የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ዝቅተኛውን የደመወዝ መጠን ለመወሰን ስልጣን ተሰጥቶታል የሚል ህግ የለም ኢትዮጵያ ላይ።
በህግ ባልተከለከለበት / አይቻልም ባልተባለበት ሁኔታ አንድ ሰው 10,000 ብር ነው ዝቅተኛ መቅጠር የምትችለው ፣ በ8,000 ነው በ18,000 እያሉ ሰንጠረዥ ማውጣት የሰዎችን የመዋዋል ነጻነት ይጎዳል።
ድርጊቱ፦
- የመዋዋል ነጻነትን የሚገድብ
- ህገመንግስታዊ ድንጋጌን የሚጥስ ተግባር ነው።
ቢሮው ' ግብር እየተጭበረበርኩ ነው ' ብሎ ካሰበ የተለያዩ የምርመራ ስራዎችን በመስራት ፣ የስራ ውሉን ከአሰሪዎቹ በመቀበል ይሄም ደግሞ በህግ አነስተኛ ደወመዝን በማውጣትና በመደንገግ ነው። እንጂ የግብር ማጭበርበር ለመከላከል ተብሎ የገቢ ግብርን በዚህ መንገድ ለማስተዳደር መሞከር የታክስ ህግን፣ መርሆችን የሚጥስ ነው። "
NB. በኢትዮጵያ እስካሁን ድረስ መንግሥት ለግሉ ዘርፍ ለተቀጣሪዎች ዝቅተኛ ደመወዝ ወለል አላስቀመጠም። ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል እንዲያስቀምጥ ጥረቶች እየተደረጉ እነደሆነ ይታወቃል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ነው። #ሸገርኤፍኤም
@tikvahethiopia
🚨 " የሚከፈለው ክፍያና እንከፍላለን ብለው የሚያሳውቁት በጣም የሚያስቅ ልዩነት ያለው ነው " - ገቢዎች ቢሮ
🔴 " ቢሮው የፈጸመው ህገወጥ ድርጊት ነው " - የህግ ምሁር
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ሆቴሎች እና መጠጥ ቤቶችን ጨምሮ በተመረጡ የንግድ መስኮች የሚሰሩ ሰራተኞችን ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል እና የሰራተኞቻቸውን ብዛት የሚተምን ተመን አውጥቶ ስራ ላይ አውሏል።
ሆቴሎች፣ ስጋ ቤቶች፣ መጠጥ ቤቶች ፣ ምግብ ቤቶች፣ ካፍቴሪያዎችን ጨምሮ ሌሎች የንግድ ዘርፎች ላይ የሰራተኞች ደመወዝን በተመለከተ አሰሪዎች ትክክለኛ መረጃ ስለማይሰጡ ግብር እያጭበረበሩ ነው ብሏል።
ይህንን ተከትሎም ነው ይህን አሰራር መዘርጋቱን ገልጻል።
ስራ ላይ በዋለው ተመን መሰረት ፦
👉 የሆቴሎች ከ32 እስከ 50 ሰራተኞች
👉 ባርና ሬስቶራን ከ20 እስከ 24 ሰራተኞች
👉 ካፍቴሪካ ከ17 እስከ 25 ሰራተኞች
👉 ምግብ ቤት ከ17 እስከ 22 ሰራተኞች
👉 ምግብ፣ መጠጥ እና ስጋ ቤት ከ28 እስከ 48
👉 ስጋ ቤት እና መጠጥ ንግድ ከ20 እስከ 28 ሰራተኞች ይኖራቸዋል ተብሎ ተተምኗል።
በዚህ መሰረት የደመወዝ ግብር በተጠቀሰው የሰራተኛ ቁጥር ልክ ይጠየቃሉ።
ከአስተናጋጅ፣ ጥበቃና የፅዳት ሙያ ውጭ ላሉ ሰራተኞች ትንሹ የሚከፍሉት ደመወዝ 5,000 ብር ሆኖ ተተምኗል።
የወር ደመወዝ ተመኑ ምን ይመስላል ?
➡ ስጋ ቤት እና መጠጥ ንግድ
° የስራ አስኪያጅ /ተቆጣጣሪ/ ከ5,000 እስከ 9,500
° ካሸር 5,000 እስከ 6,000
° ዋናው ሼፍ ከ5,000 እስከ 18,000
° አስተናጋጅ ከ3,000 እስከ 3,500
° ፅዳት ከ2,500 እስከ 3,000
° ጥበቃ ከ2,500 እስከ 3,000
° ዋና ስጋ ቆራጭ ከ5,000 እስከ 7,000
° ረዳት ስጋ ቆራጭ ከ5,000 እስከ 5,500
° ስጋ ጠባሽ ከ6,000 እስከ 9,000
➡ ምግብ፣ መጠጥ እና ስጋ ቤት
° የስራ አስኪያጅ /ተቆጣጣሪ/ ከ8,000 እስከ 13,500
° ካሸር 5,000 እስከ 7,000
° ዋናው ሼፍ ከ6,000 እስከ 18,000
° አስተናጋጅ ከ2,500 እስከ 4,000
° ፅዳት ከ3,000 እስከ 3,500
° ጥበቃ ከ3,500 እስከ 4,000
° ዋና ስጋ ቆራጭ ከ5,000 እስከ 6,000
° ረዳት ስጋ ቆራጭ ከ5,000 እስከ 5,500
° ስጋ ጠባሽ ከ6,000 እስከ 9,000
➡ ምግብ ቤት
° የስራ አስኪያጅ /ተቆጣጣሪ / ከ6,000 እስከ 10,000
° ካሸር 5,000 እስከ 6,000
° ዋናው ሼፍ ከ5,000 እስከ 7,000
° አስተናጋጅ ከ2,000 እስከ 3,000
° ፅዳት ከ2,500 እስከ 3,000
° ጥበቃ ከ2,500 እስከ 3,000
➡ ካፍቴሪያ
° የስራ አስኪያጅ /ተቆጣጣሪ/ ከ6,000 እስከ 7,000
° ካሸር 5,000 እስከ 7,000
° ዋናው ሼፍ ከ5,500 እስከ 7,000
° አስተናጋጅ ከ2,500 እስከ 3,000
° ፅዳት ከ2,500 እስከ 3,000
° ጥበቃ ከ2,500 እስከ 3,000
° ሻይ ቡና / ጁስ አስተናጋጅ ከ5,000 እስከ 8,000
➡ ባርና ሬስቶራንት
° የስራ አስኪያጅ /ተቆጣጣሪ/ ከ7,000 እስከ 10,000
° ካሸር 5,000 እስከ 6,000
° ዋናው ሼፍ ከ5,000 እስከ 7,000
° አስተናጋጅ ከ2,000 እስከ 2,500
° ፅዳት ከ2,500 እስከ 3,000
° ጥበቃ ከ3,000 እስከ 3,500
➡ ሆቴል
° የስራ አስኪያጅ /ተቆጣጣሪ/ ከ8,000 እስከ 13,500
° ካሸር 5,000 እስከ 7,000
° ዋናው ሼፍ ከ6,000 እስከ 18,000
° አስተናጋጅ ከ2,500 እስከ 4,000
° ፅዳት ከ3,000 እስከ 3,500
° ጥበቃ ከ3,500 እስከ 4,000
° ዋና ስጋ ቆራጭ ከ5,000 እስከ 6,000
° ረዳት ስጋ ቆራጭ ከ5,000 እስከ 5,500
ወርሃዊ ደመወዝ ተተምኗል።
ይህ ለአንድ ሰራተኛ ይከፈላል ተብሎ የተተመነ ነው።
በዚህ ተመን ባለቤቶቹ የደመወዝ ግብር ሲከፍሉ ለተጠቀሱት የስራ መደቦች " ከዚህ ያነሰ ነው የምከፍለው " ማለት አይችሉም።
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ምን አሉ ?
ቢሮው ተመን ማውጣቱን አረጋግጠዋል።
ዳይሬክተሩ " በጥናት ላይ ተመስርቶ ነው ውሳኔው የተቀመጠው።
ከደመወዝ ግብር ጋር በተያያዘ የሚከፈለው ክፍያና እንከፍላለን ብለው የሚያሳውቁት በጣም የሚያስቅ ልዩነት ያለው ነው። በጣም ትልቅ ክፍተት ነው ያለው እኛ በከተማችን ያሉ የስራ መደቦችን በዝርዝር ጥናት አድርገን አብዛኛው በትንሹ የሚከፈላቸው ከ5000 ብር በላይ መሆኑ ምንም ጥርጥር የለውም።
ለፅዳት እና የቤት ሰራተኛ እንኳን ስንት እንደሚከፈል ይታወቃል።
እነሱ እንከፍላለን ብለው የሚያቀርቡት ዋጋ በጣም በጣም ዝቅተኛ ነው። ያንን ምንቀበልበት ሁኔታ የለም አሰራሩም አይፈቅድም። ጥናት ላይ ተመስርተን ዝቅተኛውን ተመን አስቀምጠናል " ብለዋል።
ገቢዎች ቢሮ ከተማውን የምታመነጨውን ገቢ አሟጦ ለመሰብሰብ ኃላፊነት እንደተጣለበትና በዚህም ምክንያት ዝቅተኛ የደመወዝ ተመን ስራ ላይ እንዳዋለ አሳውቋል።
ጉዳዩ በሚመለከተው አካል ህግ ሆኖ ሳይወጣ ገቢዎች ቢሮ ዝቅተኛ የደመወዝ መጠን አስቀምጦ ግብር መሰብሰብ ይቻላል ወይ ? የሚለው የህግ ጥያቄ ተነስቶበታል።
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የዓለም አቀፍ ንግድና የኢኮኖሚ ህጎች መምህር አቶ ጌዲዮን ወ/ዮሐንስ ምን ይላሉ ?
" ድርጊቱ ህገወጥ ነው።
እስካሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ በገቢዎች በኩል አነስተኛ ደመወዝን መወሰን ያንን ተከትሎ ግብር መሰስበብ እስካሁን ባለው የህግ ማዕቀፍ ይህንን የሚፈቅድ ነገር ስለሌለ ህጋዊ አይደለም።
በተለይ ከግብር ጋር ተያይዞ ህገመንግስቱ ግብር የሚጣለው በህግ ነው ይላል። በአንድ አስፈጻሚ / በአንድ የስራ ክፍል ኃላፊ ወይም እንደ ገቢዎች ቢሮ አይነት ደብዳቤን መሰረት አድርጎ ደመወዝን መወሰን አይቻልም።
ደመወዝ ግብር የሚከፈልበት አንድ ገቢ ነው። ይሄም ታክስ ቤዝ / ግብር የሚጣልበት አንድ ገቢ እንለዋለን። እሱ በህግ ተወስኗል። ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ከዚህ እስከዚህ ሲሆን ይሄን ያህል ... ከዚህ እስከዚህ ይሄን ያህል ... ብር እየተባለ በግብር አዋጃችን ላይ ተቀምጧል።
በዚህ በገቢ ግብር አዋጅ ላይ በተለያዩ የስራ ክፍሎችና አይነቶች የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ዝቅተኛውን የደመወዝ መጠን ለመወሰን ስልጣን ተሰጥቶታል የሚል ህግ የለም ኢትዮጵያ ላይ።
በህግ ባልተከለከለበት / አይቻልም ባልተባለበት ሁኔታ አንድ ሰው 10,000 ብር ነው ዝቅተኛ መቅጠር የምትችለው ፣ በ8,000 ነው በ18,000 እያሉ ሰንጠረዥ ማውጣት የሰዎችን የመዋዋል ነጻነት ይጎዳል።
ድርጊቱ፦
- የመዋዋል ነጻነትን የሚገድብ
- ህገመንግስታዊ ድንጋጌን የሚጥስ ተግባር ነው።
ቢሮው ' ግብር እየተጭበረበርኩ ነው ' ብሎ ካሰበ የተለያዩ የምርመራ ስራዎችን በመስራት ፣ የስራ ውሉን ከአሰሪዎቹ በመቀበል ይሄም ደግሞ በህግ አነስተኛ ደወመዝን በማውጣትና በመደንገግ ነው። እንጂ የግብር ማጭበርበር ለመከላከል ተብሎ የገቢ ግብርን በዚህ መንገድ ለማስተዳደር መሞከር የታክስ ህግን፣ መርሆችን የሚጥስ ነው። "
NB. በኢትዮጵያ እስካሁን ድረስ መንግሥት ለግሉ ዘርፍ ለተቀጣሪዎች ዝቅተኛ ደመወዝ ወለል አላስቀመጠም። ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል እንዲያስቀምጥ ጥረቶች እየተደረጉ እነደሆነ ይታወቃል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ነው። #ሸገርኤፍኤም
@tikvahethiopia