" ዋና ኃላፊዋ በሀገር ውስጥ የሉም። ነገር ግን ደብዳቤያችን ከደረሳቸው በኃላ ነው የወጡት " - የመንግሥት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ
በዛሬው ዕለት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ወጪ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የ2015 /2016 በጀት አመት የፓስፖርት አገልግሎት አሰጣጥና ውጤታማነትን በተመለከተ የተከናወነ የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት እንዲሁም የ2015 የሂሳብ ኦዲት ሪፖርት ላይ ለመወያየት ስብሰባ ጠርቶ ነበር።
ነገር ግን የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት ስብሰባው ላይ ሳይገኙ መቅረታቸው ቁጣን ፈጥሯል።
የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የሺእመቤት ደምሴ (ዶ/ር) ምን አሉ ?
" በመሰረቱ ምክር ቤቱ ተመርምረው የቀረቡለትን የዋና ኦዲት ሪፖርቶችን ይፋዊ ውይይት የሚያደርግባቸው የመስሪያ ቤቱ የበላይ ኃላፊ ነው።
እኔ የመጣችሁትን የተመርማሪ መ/ቤት ኃላፊዎች ኃላፊነታችሁን አከብራለሁ ነገር ግን ዋና ኃላፊ በኦዲት ሪፖርት ምርመራ ላይ መገኘት ግዴታ ነው።
ዋና ኃላፊዋ በሀገር ውስጥ የሉም። ነገር ግን ደብዳቤያችን ከደረሳቸው በኃላ ነው የወጡት። ይህ ድርጊት ተገቢ አይደለም።
እኛ ከ10 ቀን በፊት ነው የምናሳውቀው ከ10 ቀን በፊት የምናሳውቅበት የራሱ ምክንያት አለው። መገኘት የማይችሉ ከሆነ reschedule መደረግ ካለበት reschedule መደረግ አለበት አለበለዚህ ግን ችግር የለውም ባላቹ ሰዎች መካሄድ ይችላል ተብሎ ወደ ጎን የሚተው ተግባር አይደለም።
ይሄ እኮ የመ/ቤቱ ቁልፍ ተግባር ነው።
ምክር ቤቱ ሃብት ነው የሚሰጠው፣ ይህ ሃብት በአግባቡ፣ በህግ እና በስርዓት መዋሉን ማረጋገጥ መቆጣጠር ይፈልጋል በዛ በሚቆጣጠርበት ሰዓት ኃላፊነት የሰጣቸው አካል አለመገኘት ተገቢ አይደለም።
በርካታ ስራዎች ሊኖሩ ይችላሉ ግን ከበርካታ ስራዎች የቅድሚያ ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር ነው (በኦዲት ምርመራ ሪፖርቱ ላይ መገኘት)።
ይህ የሚያመላክተው ለኦዲቱ የሰጣችሁትን ትኩረት ነው። ትኩረት መስጠታችሁ አንዱ ማሳያ ተገኝቶ ይሄን ተምሪያለሁ፣ ፈጽሚያለሁ፣ ይሄን አልፈጸኩም ብሎ ፊት ለፊት ያልፈጸመበትን ምክንያት ማስረዳት ከአንድ ኃላፊ የሚጠበቅ ነው።
ለወደፊቱ እንዳይደገም አሳስባለሁ " ብለዋል።
ምንም እንኳን ዋና ኃላፊዋ ባይገኙም ስብሰባው ምክትል ዋና ዳይሬክተሮቹ ቢቂላ መዝገቡ እና ጎሳ ደምሴን ጨምሮ ሌሎችም አመራሮች በተገኙበት ተካሂዷል።
ምክትል ዋና ዳይሬክተሮቹ በተፈጠረው ነገር ይቅርታ ጠይቀው " ድጋሚ አይደገምም " ሲሉ ቃል ገብተዋል።
ዋና ኃላፊዋ መገኘት የማይችሉ ከሆነው ቀድመው መናገር ነበረባቸው ተብሏል።
በዚህ አይነት መንገድ (ዋና ኃላፊዋ በሌሉበት) ሰብሰባውን ማድረግ የማይገባ ቢሆንም ከዋና ኦዲተር ጀምሮ፣ ከጠ/ሚ ፅ/ቤት ፣ ከተለያዩ ተቋማትም ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጊዜያቸውን መስዕዋት አድርገው " ዋና ተግባራችን ነው " ብለው ስለተገኙ ብቻ ስብሰባው መደረጉ ተገልጿል።
በዛሬው ስብሰባ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በ2015/2016 በጀት ዓመት የክዋኔ እና ሂሳብ ኦዲት ሲመረመር በርካታ ገድለቶች መገኘታቸው ተገልጿል።
ከሪፖርቱ በመነሳት ቋሚ ኮሚቴው በርካታ ጥያቄዎችን አቅርቧል። በጥያቄዎቹ ላይም የአገልግሎቱ ኃላፊዎች ምላሽ ያሉትን ሰጥተዋል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
በዛሬው ዕለት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ወጪ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የ2015 /2016 በጀት አመት የፓስፖርት አገልግሎት አሰጣጥና ውጤታማነትን በተመለከተ የተከናወነ የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት እንዲሁም የ2015 የሂሳብ ኦዲት ሪፖርት ላይ ለመወያየት ስብሰባ ጠርቶ ነበር።
ነገር ግን የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት ስብሰባው ላይ ሳይገኙ መቅረታቸው ቁጣን ፈጥሯል።
የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የሺእመቤት ደምሴ (ዶ/ር) ምን አሉ ?
" በመሰረቱ ምክር ቤቱ ተመርምረው የቀረቡለትን የዋና ኦዲት ሪፖርቶችን ይፋዊ ውይይት የሚያደርግባቸው የመስሪያ ቤቱ የበላይ ኃላፊ ነው።
እኔ የመጣችሁትን የተመርማሪ መ/ቤት ኃላፊዎች ኃላፊነታችሁን አከብራለሁ ነገር ግን ዋና ኃላፊ በኦዲት ሪፖርት ምርመራ ላይ መገኘት ግዴታ ነው።
ዋና ኃላፊዋ በሀገር ውስጥ የሉም። ነገር ግን ደብዳቤያችን ከደረሳቸው በኃላ ነው የወጡት። ይህ ድርጊት ተገቢ አይደለም።
እኛ ከ10 ቀን በፊት ነው የምናሳውቀው ከ10 ቀን በፊት የምናሳውቅበት የራሱ ምክንያት አለው። መገኘት የማይችሉ ከሆነ reschedule መደረግ ካለበት reschedule መደረግ አለበት አለበለዚህ ግን ችግር የለውም ባላቹ ሰዎች መካሄድ ይችላል ተብሎ ወደ ጎን የሚተው ተግባር አይደለም።
ይሄ እኮ የመ/ቤቱ ቁልፍ ተግባር ነው።
ምክር ቤቱ ሃብት ነው የሚሰጠው፣ ይህ ሃብት በአግባቡ፣ በህግ እና በስርዓት መዋሉን ማረጋገጥ መቆጣጠር ይፈልጋል በዛ በሚቆጣጠርበት ሰዓት ኃላፊነት የሰጣቸው አካል አለመገኘት ተገቢ አይደለም።
በርካታ ስራዎች ሊኖሩ ይችላሉ ግን ከበርካታ ስራዎች የቅድሚያ ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር ነው (በኦዲት ምርመራ ሪፖርቱ ላይ መገኘት)።
ይህ የሚያመላክተው ለኦዲቱ የሰጣችሁትን ትኩረት ነው። ትኩረት መስጠታችሁ አንዱ ማሳያ ተገኝቶ ይሄን ተምሪያለሁ፣ ፈጽሚያለሁ፣ ይሄን አልፈጸኩም ብሎ ፊት ለፊት ያልፈጸመበትን ምክንያት ማስረዳት ከአንድ ኃላፊ የሚጠበቅ ነው።
ለወደፊቱ እንዳይደገም አሳስባለሁ " ብለዋል።
ምንም እንኳን ዋና ኃላፊዋ ባይገኙም ስብሰባው ምክትል ዋና ዳይሬክተሮቹ ቢቂላ መዝገቡ እና ጎሳ ደምሴን ጨምሮ ሌሎችም አመራሮች በተገኙበት ተካሂዷል።
ምክትል ዋና ዳይሬክተሮቹ በተፈጠረው ነገር ይቅርታ ጠይቀው " ድጋሚ አይደገምም " ሲሉ ቃል ገብተዋል።
ዋና ኃላፊዋ መገኘት የማይችሉ ከሆነው ቀድመው መናገር ነበረባቸው ተብሏል።
በዚህ አይነት መንገድ (ዋና ኃላፊዋ በሌሉበት) ሰብሰባውን ማድረግ የማይገባ ቢሆንም ከዋና ኦዲተር ጀምሮ፣ ከጠ/ሚ ፅ/ቤት ፣ ከተለያዩ ተቋማትም ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጊዜያቸውን መስዕዋት አድርገው " ዋና ተግባራችን ነው " ብለው ስለተገኙ ብቻ ስብሰባው መደረጉ ተገልጿል።
በዛሬው ስብሰባ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በ2015/2016 በጀት ዓመት የክዋኔ እና ሂሳብ ኦዲት ሲመረመር በርካታ ገድለቶች መገኘታቸው ተገልጿል።
ከሪፖርቱ በመነሳት ቋሚ ኮሚቴው በርካታ ጥያቄዎችን አቅርቧል። በጥያቄዎቹ ላይም የአገልግሎቱ ኃላፊዎች ምላሽ ያሉትን ሰጥተዋል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ዋና ኃላፊዋ በሀገር ውስጥ የሉም። ነገር ግን ደብዳቤያችን ከደረሳቸው በኃላ ነው የወጡት " - የመንግሥት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በዛሬው ዕለት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ወጪ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የ2015 /2016 በጀት አመት የፓስፖርት አገልግሎት አሰጣጥና ውጤታማነትን በተመለከተ የተከናወነ የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት…
" ዜጎች ምን ያህል እንደሚንገላቱ የአይን ምስክር ነኝ !! " - የሺእመቤት ደምሴ (ዶ/ር)
ዛሬ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት #የፓስፖርት_አገልግሎት አሰጣጥን በተመለከተ በተካሄደው የ2015/2016 የክዋኔ እና ኦዲት ሪፖርት ስብሰባ ላይ በመንግሥት ወጪ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በኩል ስለ ሰራተኞች ስነምግባር ፤ ስለ ዜጎች እንግልት ተነስቷል።
የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የሺእመቤት ደምሴ (ዶ/ር) መ/ቤቱን " ሁላችንም የምንረግጠው በር ነው ያላችሁ " ሲሉ ገልጸዋል።
" ነገር ግን ሁላችንም ተጠቂ / Victim የሆንበት ጉዳይ ነው እውነቱን ለመናገር " ሲሉ ተናግረዋል። ይህንን ያሉት ስለ ሰራተኞች ስነምግባር እና ስለ ተገልጋይ እንግልት ባነሱት ሃሳብ ነው።
በጉዳዩ ላይ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ኃላፊዎች ለምክር ቤቱ " አጃቢዎቻቸው ፣ በቋንቋ ፣ ቦታ ባለማወቅ ... በተለያዩ ምክንያቶች አጅበዋቸው የሚመጡት እንጂ አገልግሎት ፈላጊዎቻችን አይደለም የሚንገላቱት " ብለዋል።
የምክር ቤት አባልና የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዋ ግን " እኔ ምስክር ነኝ እኔ ተንገላትቻለሁ " ሲሉ ተናግረዋል።
" እኔ ተንገላትቻለሁ ፤ እኔ ተገፍቼ ወጥቻለሁ ያውም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መታወቂያ እያሳየሁ ፤ ተጎትቼ ወጥቻለሁ ይህንን ከማንም አይን እማኝ አይደለም እኔ ላይ የደረሰ ነው። እኔ ይሄንን የምለው እኔ ተበድያለሁና እኔ ለምን ተበደልኩ ብዬ አይደለም " ብለዋል።
" እኔ ይህን ሃሳብ እያቀረብኩ ያለሁት ከኃላዬ ያለው ዜጋ ምን ያህል እንደሚንገላታ የአይን ምስክር ነኝ ለማለት ነው " ሲሉ አስረድተዋል።
" ይህንን ፈትሹት ፤ ሩቅ አይደለም የሩቅ ጊዜ ትዝታ አይደለም እየናገርኳችሁ ያለሁት ዛሬ ላይ እየተፈጸመ ያለ ነው " ብለዋል።
" አገልግሎት ፈላጊው ወረቀት ይዞ ፣ የሞላውን ፕሪንት አድርጎ ይዞ በጣም እየተንገላታ ፤ እየተገፋ ያለበት ሰዓት ነው ያ መሆን የለበትም " ሲሉም አሳስበዋል።
አክለው " ለዜጎቻችን መስጠት የምንችለውን አቅማችን የፈቀደውን አገልግሎት በአግባቡና በስርዓት ልንሰጥ ይገባል እንጂ ከዛም አልፎ መንገላታትን ልንጨምርበት አይገባም " ብለዋል።
መ/ቤቱ ያሉትን ቅርንጫፎች አቅም እንዲያጠናክር እና ዜጎችን ከሚያንገላታ አሰራር እንዲታረም በጥብቅ አሳስበዋል።
#TikvahEthiopia
#Passport
@tikvahethiopia
ዛሬ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት #የፓስፖርት_አገልግሎት አሰጣጥን በተመለከተ በተካሄደው የ2015/2016 የክዋኔ እና ኦዲት ሪፖርት ስብሰባ ላይ በመንግሥት ወጪ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በኩል ስለ ሰራተኞች ስነምግባር ፤ ስለ ዜጎች እንግልት ተነስቷል።
የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የሺእመቤት ደምሴ (ዶ/ር) መ/ቤቱን " ሁላችንም የምንረግጠው በር ነው ያላችሁ " ሲሉ ገልጸዋል።
" ነገር ግን ሁላችንም ተጠቂ / Victim የሆንበት ጉዳይ ነው እውነቱን ለመናገር " ሲሉ ተናግረዋል። ይህንን ያሉት ስለ ሰራተኞች ስነምግባር እና ስለ ተገልጋይ እንግልት ባነሱት ሃሳብ ነው።
በጉዳዩ ላይ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ኃላፊዎች ለምክር ቤቱ " አጃቢዎቻቸው ፣ በቋንቋ ፣ ቦታ ባለማወቅ ... በተለያዩ ምክንያቶች አጅበዋቸው የሚመጡት እንጂ አገልግሎት ፈላጊዎቻችን አይደለም የሚንገላቱት " ብለዋል።
የምክር ቤት አባልና የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዋ ግን " እኔ ምስክር ነኝ እኔ ተንገላትቻለሁ " ሲሉ ተናግረዋል።
" እኔ ተንገላትቻለሁ ፤ እኔ ተገፍቼ ወጥቻለሁ ያውም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መታወቂያ እያሳየሁ ፤ ተጎትቼ ወጥቻለሁ ይህንን ከማንም አይን እማኝ አይደለም እኔ ላይ የደረሰ ነው። እኔ ይሄንን የምለው እኔ ተበድያለሁና እኔ ለምን ተበደልኩ ብዬ አይደለም " ብለዋል።
" እኔ ይህን ሃሳብ እያቀረብኩ ያለሁት ከኃላዬ ያለው ዜጋ ምን ያህል እንደሚንገላታ የአይን ምስክር ነኝ ለማለት ነው " ሲሉ አስረድተዋል።
" ይህንን ፈትሹት ፤ ሩቅ አይደለም የሩቅ ጊዜ ትዝታ አይደለም እየናገርኳችሁ ያለሁት ዛሬ ላይ እየተፈጸመ ያለ ነው " ብለዋል።
" አገልግሎት ፈላጊው ወረቀት ይዞ ፣ የሞላውን ፕሪንት አድርጎ ይዞ በጣም እየተንገላታ ፤ እየተገፋ ያለበት ሰዓት ነው ያ መሆን የለበትም " ሲሉም አሳስበዋል።
አክለው " ለዜጎቻችን መስጠት የምንችለውን አቅማችን የፈቀደውን አገልግሎት በአግባቡና በስርዓት ልንሰጥ ይገባል እንጂ ከዛም አልፎ መንገላታትን ልንጨምርበት አይገባም " ብለዋል።
መ/ቤቱ ያሉትን ቅርንጫፎች አቅም እንዲያጠናክር እና ዜጎችን ከሚያንገላታ አሰራር እንዲታረም በጥብቅ አሳስበዋል።
#TikvahEthiopia
#Passport
@tikvahethiopia
#ጥቆማ
እስከ 1 ሚሊዮን ፓውንድ ሽልማት የሚያስገኘውን የ " The Earthshot Prize 2025 " ኢትዮጵያውያን እንዲወዳደሩ ጥሪ ቀረበ።
በእንግሊዝ ልዑል ዊሊያምና ሮያል ፋውንዴሽን በፈረንጆቹ 2020 የተቋቋመውና በዓለም አቀፍ ደረጃ ከአካባቢና አየር ብክለት የፀዳ፣ ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ አስተዋፅኦ የሚያበረክትና ለተፈጥሮ ተስማሚ የሆነ ስራ እየሰሩ ያሉ ተቋማትን ፣ የቢዝነስ ፈጠራ ባለሙያዎችን (ኢንተርፕረነሮችን) ወይም ግለሰቦችን የሚሸልመው " The Earthshot Prize 2025 " የዘንድሮ እጩ ተወዳዳሪዎችን መቀበል ጀምሯል።
በአፍሪካ የውድድሩ ዋና አጋር መልቲቾይስ አፍሪካ ኢትዮጵያውያን ስራ ፈጣሪዎች እንዲወዳደሩ ጥሪ አቅርቧል።
በ5 የተለያዩ ምድቦች የሚካሄደው ይህ ዓመታዊ ሽልማት ላይ በተለይ ለአካባቢ ተስማሚ የሆኑና ተፈጥሮን የማይበክሉ ቢዝነሶችን የሚያንቀሳቅሱ ኢትዮጵያውያን መሳተፍ ይችላኩ።
ውድድሩ እስከ 1 ሚሊዮን ፓውንድ ሽልማት የሚያስገኝ ነው ተብሏል።
ፕሮጀክቶቻቸውን ለማስፋፋትና እየተባባሰ ለመጣው የአየር ንብረት ለውጥ መፍትሄ እንዲያበረክቱም ያግዛል።
መልቲቾይስ አፍሪካ ፤ በደቡብ አፍሪካ በተከናወነው የ2024 ውድድር ከጋና " ግሪን አፍሪካ ዩዝ ኦርጋናዜሽን " እንዲሁም ከኬንያ " ኪፕ ኢት ኩል" የተሰኙ የአረንጓዴ ጉዳይ አቀንቃኞችና የሥራ ፈጣሪዎች አሸናፊ እንደሆኑ አስታውሷል።
ለዚህ ዓመቱ ሽልማት ማመልከት የሚቻለው እስከ ፈረንጆቹ ዲሴምበር 04 / 2024 ሲሆን ኢትዮጵያውያን ስራ ፈጣሪዎች እና ተቋማት በ https://www.multichoice.com/earthshot-nomination.php#prId=324466 እንዲያመለክቱ ጥሪ አቅርቧል።
#TikvahEthiopia
Via @TikvahethMagazine
እስከ 1 ሚሊዮን ፓውንድ ሽልማት የሚያስገኘውን የ " The Earthshot Prize 2025 " ኢትዮጵያውያን እንዲወዳደሩ ጥሪ ቀረበ።
በእንግሊዝ ልዑል ዊሊያምና ሮያል ፋውንዴሽን በፈረንጆቹ 2020 የተቋቋመውና በዓለም አቀፍ ደረጃ ከአካባቢና አየር ብክለት የፀዳ፣ ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ አስተዋፅኦ የሚያበረክትና ለተፈጥሮ ተስማሚ የሆነ ስራ እየሰሩ ያሉ ተቋማትን ፣ የቢዝነስ ፈጠራ ባለሙያዎችን (ኢንተርፕረነሮችን) ወይም ግለሰቦችን የሚሸልመው " The Earthshot Prize 2025 " የዘንድሮ እጩ ተወዳዳሪዎችን መቀበል ጀምሯል።
በአፍሪካ የውድድሩ ዋና አጋር መልቲቾይስ አፍሪካ ኢትዮጵያውያን ስራ ፈጣሪዎች እንዲወዳደሩ ጥሪ አቅርቧል።
በ5 የተለያዩ ምድቦች የሚካሄደው ይህ ዓመታዊ ሽልማት ላይ በተለይ ለአካባቢ ተስማሚ የሆኑና ተፈጥሮን የማይበክሉ ቢዝነሶችን የሚያንቀሳቅሱ ኢትዮጵያውያን መሳተፍ ይችላኩ።
ውድድሩ እስከ 1 ሚሊዮን ፓውንድ ሽልማት የሚያስገኝ ነው ተብሏል።
ፕሮጀክቶቻቸውን ለማስፋፋትና እየተባባሰ ለመጣው የአየር ንብረት ለውጥ መፍትሄ እንዲያበረክቱም ያግዛል።
መልቲቾይስ አፍሪካ ፤ በደቡብ አፍሪካ በተከናወነው የ2024 ውድድር ከጋና " ግሪን አፍሪካ ዩዝ ኦርጋናዜሽን " እንዲሁም ከኬንያ " ኪፕ ኢት ኩል" የተሰኙ የአረንጓዴ ጉዳይ አቀንቃኞችና የሥራ ፈጣሪዎች አሸናፊ እንደሆኑ አስታውሷል።
ለዚህ ዓመቱ ሽልማት ማመልከት የሚቻለው እስከ ፈረንጆቹ ዲሴምበር 04 / 2024 ሲሆን ኢትዮጵያውያን ስራ ፈጣሪዎች እና ተቋማት በ https://www.multichoice.com/earthshot-nomination.php#prId=324466 እንዲያመለክቱ ጥሪ አቅርቧል።
#TikvahEthiopia
Via @TikvahethMagazine
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሽርካ " በየቤቱ ይዘው በማገት ወደ ወንዝ አካባቢ ወስደዋቸው፤ አሰልፈው ነው የገደሏቸው " - ነዋሪዎች በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ሽርካ ወረዳ ትላንት በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች 9 ሰዎችን ከቤታቸው በመውሰድ መግደላቸውን የተጎጂ ቤተሰቦች እና ነዋሪዎችን ዋቢ በማድረግ ቢቢሲ አማርኛ ዘግቧል። ግድያው የተፈጸመው ሐሙስ ኅዳር 19/ 2017 ዓ.ም. ከሌሊቱ 6፡00 አካባቢ መሆኑን ቤተሰቦች ገልጸዋል።…
የሽርካ ወረዳ ነዋሪዎች ምን አሉ ?
" ከዚህ ቀደም ሰዎች ይታገታሉ የሆነ ብር ተከፍሎ ይለቀቁ ነበር። አሁን የተፈጸመው ግን እጅግ አስከፊ ነው " - ነዋሪዎች
የሽርካ ወረዳ፣ ፈረቀሳ ነዋሪዎች ትላንት ለሊት 9 ሰዎች በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ ነዋሪዎች ምን አሉ ?
" በዚህ ሳምንት ሞት አላቋረጠም፤ ቢያንስ ላለፉት ሦስት ቀናት በአከባቢው በተለያዩ ቀበሌያት የሞት አላቋረጠም።
ትላንት ደግሞ በእኛ ቀበሌ ፈረቀሳ የእነዚህ 9 ሰዎች ተገድለዋል። እጅግ አሳዛኝ ነው።
5 ሰዓት ላይ ተኩስ ተጀመረ ግድያው ለሊት 8:00 ገደማ ነው የተፈጸመው።
በየቤታቸው በመሄድ ለቅመው አንድ ላይ ካከማቿቸው በኋላ ነው ጅምላ ጭፍጨፋ ያደረጉባቸው።
ከዚህ ቀደም ሰዎች ይታገታሉ የሆነ ብር ተከፍሎ ይለቀቁ ነበር። አሁን የተፈጸመው ግን እጅግ አስከፊ ነው።
ሰዎቹ ምንም አይነት የሌላ ንክኪ የላቸውም ፤ በሃይማኖት ተለይተው ነው ይህ ጥቃት የተፈጸመባቸው።
ከሞቱት መካከል አባትና ልጅ እንዲሁም ባልና ሚስት ይገኙበታል።
3ቱ አብረው ታግተው ሳለ 9ኙን ሲገድሉ ይኑሩ ይሙቱ አይታወቅም።
ድርጊቱን የፈጸሙት የሸኔ አባላት ናቸው። ሆኖም ግን ምንም እንኳን ስሙ በሸኔ ይነገድ እንጂ በስሩ ሌላ ቡድን የተደራጀ አለ። ሙሉ ለሙሉ ሸኔ ለማለት ያስቸግራል።
በሌላ ቦታ ላይ የሸኔ አድራጎት ሲሰማ ብር ይጠይቃል ሰዎችን ይለቃል ፤ እዚህ ያለው ሃይማኖትን በመቃወም ጥቅም ለማግኘት የሸኔ ስም በመጠቀም የተደራጀ ቡድን አለ ብለን ነው የምናስበው።
የመንግስት አካላት ከዞንም መጥተው ዛሬ ላይ ደርሶ ' አይዟችሁ ነገ ላይ አጸፋውን እንመልሳለን አሳልፋችሁ ከሰጣችሁን ' በሚል የማጽናኛ ተስፋ ሰጥተውናል።
መከላከያውም የመንግስት አመራሩም አለ ገፋ አድርጎ ግን ለህዝብ መፍትሔ የሰጠ የለም።
ጫካውን ደኑን ተገን በማድረግ ግድያ ይፈጸማል።
ባለፈው ዓመት በነሐሴ ወር [2015 ዓ.ም] ነው የተጀመረው አለፍ እያለ እያረሳሱ አሉ የሚባሉ ሰዎች ሽማግሌ አይሉም ወጣት፤ አሉ የተባሉ ሰዎችንዠ ተገድለዋል።
9ኙ የተገደሉት የአንድ ሃይማኖት አባላት ሲሆኑ ቀብራቸውም ዛሬ 9 ሰዓት ነው የተፈጸመው።
ህብረተሰቡ ነግ በኔ ነው እያለ ነው። ከቀብር መልስ የመንግስት አባላት ከዞን መጥተው አጽናንቶ ነው የሄደው።
አዝመራ ልንሰበስብ አንችልም። የቀበሌው አመራር ተደራጅተን አንድ ላይ ሆነን እንሰብስብ እያለን ነው። እንደዚህ በተደራጀ መልኩ የምንቀሳቀስ ከሆነ እንጂ ለዛሬውም አዳር ሰግተን ነው ያለነው።
በተለይ ወጣቱ በአሳዛኝ ሁኔታ ላይ ነው ያለው፤ ይኸው ይሄ ጩኸት 2 ዓመት ያስቆጠረ ነው ምንም የተደረገ ነገር የለም።
ሰርግ ኃዘን አንድ ላይ ነበር ያሳለፍነው [የአከባቢው ማኅበረሰብ] አንድ ቢላ ነበር የሚለየን አሁን ላይ ግን ይሄ ተረስቶ በገቢያም በምንም ያለው ነገር ጎራ መከፈሉን ያሳያል።
በሃይማኖት አባቶች በኩል ህብረተሰቡን ለማቀራረብ ሞክረዋል። በተደጋጋሚ በተደረጉ ስብሰባዎች ግን ስብሰባዎች እየተበተኑ፤ ስብሰባውን ረግጠው እየወጡ ሳይሳካ ቀርቷል።
በድርድሩ ምንም አይነት መፍትሔ የሚመጣ አይመስለኝም የሃይማኖት አባቶች እንዳሉት ከፈጣሪ ከመጠበቅ በቀር ሌላ ምንም ተስፋ የምናደርገው ነገር የለም።
በቀጣይ ቀናትም በተመሳሳይ ጥቃት ይፈጸማል በሚል የአከባቢው ሰው ንብረቱን ትቶ አከባቢውን ለቆ ወደ ቤተክርስቲያንም ወደ ከተማ ቤት ተከራይቶም እየሄደ ነው ያለው።
አሁን ያለው ሁኔታ እንኳን ለወጣቱ ለአዛውንቱም የሚዘገንን ሁኔታ ነው። ምን አይነት ሰዓት ላይ ተፈጠርን በሚል ወጣቱ በኃዘን ተውጦ ነው ያለው።
በአከባቢያችን ካሉ 4 ቀበሌዎች ላይ ካሉ 5 እና 6 ደብሮች አገልግሎት የሚሰጠው አንድ የሚካኤል ደብር ነው። ቀብርም ካለ የሚፈጸመው እዛ ነው። ይህ ከሆነ አንድ አመት አልፎታል።
እንደ ወረዳው ግን ከ35 አብያተ ክርስቲያናት በላይ ተመሳሳይ እጣ ደርሷቸዋል። ሦስት አራት ደብሮች ናቸው አገልግሎት የሚሰጡት። ይህም በጸጥታው ምክንያት ነው።
ከ32 ቀበሌ ከየአቅጣጫው ተመርጦ የሚገደለው ግን የሀገር ሽማግሌ ነው ከዚህ ቀደምም እየተመረጠ አልቋል። ይሄን ያህል ነው ጥቃት የደረሰብን።
የሚመለከተው አካል ከፈጣሪ ጋር የድረሱልን ጥሪ አሰሙልን ወገን ለወገን ደራሽ ነው። "
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
" ከዚህ ቀደም ሰዎች ይታገታሉ የሆነ ብር ተከፍሎ ይለቀቁ ነበር። አሁን የተፈጸመው ግን እጅግ አስከፊ ነው " - ነዋሪዎች
የሽርካ ወረዳ፣ ፈረቀሳ ነዋሪዎች ትላንት ለሊት 9 ሰዎች በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ ነዋሪዎች ምን አሉ ?
" በዚህ ሳምንት ሞት አላቋረጠም፤ ቢያንስ ላለፉት ሦስት ቀናት በአከባቢው በተለያዩ ቀበሌያት የሞት አላቋረጠም።
ትላንት ደግሞ በእኛ ቀበሌ ፈረቀሳ የእነዚህ 9 ሰዎች ተገድለዋል። እጅግ አሳዛኝ ነው።
5 ሰዓት ላይ ተኩስ ተጀመረ ግድያው ለሊት 8:00 ገደማ ነው የተፈጸመው።
በየቤታቸው በመሄድ ለቅመው አንድ ላይ ካከማቿቸው በኋላ ነው ጅምላ ጭፍጨፋ ያደረጉባቸው።
ከዚህ ቀደም ሰዎች ይታገታሉ የሆነ ብር ተከፍሎ ይለቀቁ ነበር። አሁን የተፈጸመው ግን እጅግ አስከፊ ነው።
ሰዎቹ ምንም አይነት የሌላ ንክኪ የላቸውም ፤ በሃይማኖት ተለይተው ነው ይህ ጥቃት የተፈጸመባቸው።
ከሞቱት መካከል አባትና ልጅ እንዲሁም ባልና ሚስት ይገኙበታል።
3ቱ አብረው ታግተው ሳለ 9ኙን ሲገድሉ ይኑሩ ይሙቱ አይታወቅም።
ድርጊቱን የፈጸሙት የሸኔ አባላት ናቸው። ሆኖም ግን ምንም እንኳን ስሙ በሸኔ ይነገድ እንጂ በስሩ ሌላ ቡድን የተደራጀ አለ። ሙሉ ለሙሉ ሸኔ ለማለት ያስቸግራል።
በሌላ ቦታ ላይ የሸኔ አድራጎት ሲሰማ ብር ይጠይቃል ሰዎችን ይለቃል ፤ እዚህ ያለው ሃይማኖትን በመቃወም ጥቅም ለማግኘት የሸኔ ስም በመጠቀም የተደራጀ ቡድን አለ ብለን ነው የምናስበው።
የመንግስት አካላት ከዞንም መጥተው ዛሬ ላይ ደርሶ ' አይዟችሁ ነገ ላይ አጸፋውን እንመልሳለን አሳልፋችሁ ከሰጣችሁን ' በሚል የማጽናኛ ተስፋ ሰጥተውናል።
መከላከያውም የመንግስት አመራሩም አለ ገፋ አድርጎ ግን ለህዝብ መፍትሔ የሰጠ የለም።
ጫካውን ደኑን ተገን በማድረግ ግድያ ይፈጸማል።
ባለፈው ዓመት በነሐሴ ወር [2015 ዓ.ም] ነው የተጀመረው አለፍ እያለ እያረሳሱ አሉ የሚባሉ ሰዎች ሽማግሌ አይሉም ወጣት፤ አሉ የተባሉ ሰዎችንዠ ተገድለዋል።
9ኙ የተገደሉት የአንድ ሃይማኖት አባላት ሲሆኑ ቀብራቸውም ዛሬ 9 ሰዓት ነው የተፈጸመው።
ህብረተሰቡ ነግ በኔ ነው እያለ ነው። ከቀብር መልስ የመንግስት አባላት ከዞን መጥተው አጽናንቶ ነው የሄደው።
አዝመራ ልንሰበስብ አንችልም። የቀበሌው አመራር ተደራጅተን አንድ ላይ ሆነን እንሰብስብ እያለን ነው። እንደዚህ በተደራጀ መልኩ የምንቀሳቀስ ከሆነ እንጂ ለዛሬውም አዳር ሰግተን ነው ያለነው።
በተለይ ወጣቱ በአሳዛኝ ሁኔታ ላይ ነው ያለው፤ ይኸው ይሄ ጩኸት 2 ዓመት ያስቆጠረ ነው ምንም የተደረገ ነገር የለም።
ሰርግ ኃዘን አንድ ላይ ነበር ያሳለፍነው [የአከባቢው ማኅበረሰብ] አንድ ቢላ ነበር የሚለየን አሁን ላይ ግን ይሄ ተረስቶ በገቢያም በምንም ያለው ነገር ጎራ መከፈሉን ያሳያል።
በሃይማኖት አባቶች በኩል ህብረተሰቡን ለማቀራረብ ሞክረዋል። በተደጋጋሚ በተደረጉ ስብሰባዎች ግን ስብሰባዎች እየተበተኑ፤ ስብሰባውን ረግጠው እየወጡ ሳይሳካ ቀርቷል።
በድርድሩ ምንም አይነት መፍትሔ የሚመጣ አይመስለኝም የሃይማኖት አባቶች እንዳሉት ከፈጣሪ ከመጠበቅ በቀር ሌላ ምንም ተስፋ የምናደርገው ነገር የለም።
በቀጣይ ቀናትም በተመሳሳይ ጥቃት ይፈጸማል በሚል የአከባቢው ሰው ንብረቱን ትቶ አከባቢውን ለቆ ወደ ቤተክርስቲያንም ወደ ከተማ ቤት ተከራይቶም እየሄደ ነው ያለው።
አሁን ያለው ሁኔታ እንኳን ለወጣቱ ለአዛውንቱም የሚዘገንን ሁኔታ ነው። ምን አይነት ሰዓት ላይ ተፈጠርን በሚል ወጣቱ በኃዘን ተውጦ ነው ያለው።
በአከባቢያችን ካሉ 4 ቀበሌዎች ላይ ካሉ 5 እና 6 ደብሮች አገልግሎት የሚሰጠው አንድ የሚካኤል ደብር ነው። ቀብርም ካለ የሚፈጸመው እዛ ነው። ይህ ከሆነ አንድ አመት አልፎታል።
እንደ ወረዳው ግን ከ35 አብያተ ክርስቲያናት በላይ ተመሳሳይ እጣ ደርሷቸዋል። ሦስት አራት ደብሮች ናቸው አገልግሎት የሚሰጡት። ይህም በጸጥታው ምክንያት ነው።
ከ32 ቀበሌ ከየአቅጣጫው ተመርጦ የሚገደለው ግን የሀገር ሽማግሌ ነው ከዚህ ቀደምም እየተመረጠ አልቋል። ይሄን ያህል ነው ጥቃት የደረሰብን።
የሚመለከተው አካል ከፈጣሪ ጋር የድረሱልን ጥሪ አሰሙልን ወገን ለወገን ደራሽ ነው። "
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
#Sidama
🔴 " በብልፅግና ፓርቲ መዋጮ ምክንያት አባላትና አመራሮች እየታሰሩብኝ ነው " -የሲዳማ ህዝብ አንድነት ዲሞክራሲያዊ ድርጅት (ሲህአዲድ)
🔵 " በፓለቲካ አቋሙና አመለካከቱ የታሰረ የፖለቲካ ፓርቲ አባልና አመራር የለም " - የሲዳማ ክልል ፖለቲካ ፖርቲ የጋራ ምክር ቤት
🚨" የታሰርነዉ ለሁለት ፖርቲዎች መዋጮ አናዋጣም ስላልን ነው " - የሲህአዲድ አባላትና አመራሮች
የሲዳማ ህዝብ አንድነት ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ሊቀመንበር እና የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባል አቶ ሠለሞን ቡሮዳ የፓርቲያቸው አባላትና አመራሮች " ለብልፅግና ፖርቲ መዋጮ አናዋጣም " በማለታቸዉ እየታሰሩና በሐሰት እየተወነጀሉ ሲሉ ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቀረቡ።
በክልሉ ከጥቅምት ወር መገባደጃ ጀምሮ በሁሉም የክልሉ አከባቢዎች አባላትና አመራሮቻቸው ሰበብ እየተፈለገ ሲታሰሩና ሲፈቱ መቆየታቸውን ገልጸዋል።
አሁን ላይ ደግሞ በአባላቶቻቸው ላይ ሐሰተኛ ክስ እየተፈበረከባቸዉ መሆኑን ጠቁመዋል።
በአንዳንድ ወረዳዎች ማሸማቀቅ ተበራክቷል ሲሉ ቅሬታቸውን አሰምተዋል።
ለአብነትም ፦
- ወንሾ፣
- ጠጥቻ፣
- ጎርቼ፣
- ቦና ዙሪያ፣
- ቡርሳ፣
- ጫቤ ጋምቤልቱ፣
- ሸበዲኖ፣
- ጭሬና በንሳ ወረዳዎች አባላትና አመራሮቻቸው " የብልፅግና ፓርቲ መዋጮ ለምን አታዋጡም " በሚል ለእስር ተዳርገዉ እንደነበር አንስተዋል።
አቶ ሠለሞን ፤ " አሸናፊዉ ፓርቲ ብልፅግና ነዉ፤ ሁሉም ለብልፅግና ፓርቲ የህንፃ ግንባታ መዋጮ የማዋጣት ግዴታ አለበት " የሚል የተሳሳተ ግንዛቤ በአንዳንድ ወረዳዎች በግልፅ እየተስተዋለ ነው ብለዋል።
" በዚህ ሁኔታ የሚደረጉ ኢ-ሕገ መንግስታዊና የሁሉም ፖለቲካ ፓርቲዎች የቃል ኪዳን ሰነድ በሚፃረርር መልኩ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች በአስቸኳይ ሊቆሙ ይገባል " ሲሉ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉዳዩ ላይ የሲዳማ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢና የኢሶዴፖ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልና የደቡባዊ ቀጠና የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ በለጠ ሲጄቦ አነጋግሯል።
ቅሬታ መቅረቡን አልሸሸጉም።
ቅሬታውን ተከትሎ ምክር ቤቱ የታሰሩ ሰዎች እንዲፈቱ በማድረግ ኮሚቴ ተሰይሞ የማጣራት ሥራ መስራቱን ገልጸዋል።
በዚህም የታሰሩት ግለሰቦች በደረቅ ወንጀል የተጠረጠሩ አንጂ በፖለቲካ አቋማቸዉና አመለካከታቸዉ ምክንያት እንዳልሆነ መረጋገጡን አሳውቀዋል።
ከ2013 ዓ/ም ጀምሮ የፓርቲው የወረዳ አባል መሆናቸውን የሚገልጹት የጠጥቻ ወረዳ ነዋሪ አቶ አስራት ወርሶ ግን " ለሁለት ፓርቲ መዋጮ አላዋጣም በማለቴ ታስሬ ነበር " ሲሉ ስለእስራቸው ምክንያት ይገልጻሉ።
ከአንድ ቀን እስር በኋላም የፓርቲው አመራሮች ባቀረቧቸዉ መረጃዎች ምክንያት ከእስር መለለቃቸዉን አስረድተዋል።
የሲዳማ ህዝብ አንድነት ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልና የሁላ ወረዳ ስራ አስፈፃሚ መ/ር ሀንሳሶ በበኩላቸው " እኔም አባላቶቻችን ለምን ታሰሩ " በሚል ልንጠይቃቸዉ በሄድንበት ከሁለት አባላት ጋር ታስረን ነበር ሲሉ " ተጨማሪ ምስክርነት ሰጥተዋል።
አክለውም " ለብልፅግና ፓርቲ የሕንፃ መሰሪያ መዋጮ ካላዋጣችሁ በሚል በአባላትና አመራሮቻቸዉ ላይ በበርካታ ወረዳዎች እየደረሰ ያለዉ ጫና ስጋት ዉስጥ ከቶናል " ሲሉ ገልጸዋል።
የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ እና የገዢዉ ብልፅግና ፓርቲ ሃሳብ ለማካተት ያደረግነዉ ሙከራ ያልተሳካ ሲሆን ኃሳባቸውን እንዳገኘን የምናካትት ይሆናል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
🔴 " በብልፅግና ፓርቲ መዋጮ ምክንያት አባላትና አመራሮች እየታሰሩብኝ ነው " -የሲዳማ ህዝብ አንድነት ዲሞክራሲያዊ ድርጅት (ሲህአዲድ)
🔵 " በፓለቲካ አቋሙና አመለካከቱ የታሰረ የፖለቲካ ፓርቲ አባልና አመራር የለም " - የሲዳማ ክልል ፖለቲካ ፖርቲ የጋራ ምክር ቤት
🚨" የታሰርነዉ ለሁለት ፖርቲዎች መዋጮ አናዋጣም ስላልን ነው " - የሲህአዲድ አባላትና አመራሮች
የሲዳማ ህዝብ አንድነት ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ሊቀመንበር እና የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባል አቶ ሠለሞን ቡሮዳ የፓርቲያቸው አባላትና አመራሮች " ለብልፅግና ፖርቲ መዋጮ አናዋጣም " በማለታቸዉ እየታሰሩና በሐሰት እየተወነጀሉ ሲሉ ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቀረቡ።
በክልሉ ከጥቅምት ወር መገባደጃ ጀምሮ በሁሉም የክልሉ አከባቢዎች አባላትና አመራሮቻቸው ሰበብ እየተፈለገ ሲታሰሩና ሲፈቱ መቆየታቸውን ገልጸዋል።
አሁን ላይ ደግሞ በአባላቶቻቸው ላይ ሐሰተኛ ክስ እየተፈበረከባቸዉ መሆኑን ጠቁመዋል።
በአንዳንድ ወረዳዎች ማሸማቀቅ ተበራክቷል ሲሉ ቅሬታቸውን አሰምተዋል።
ለአብነትም ፦
- ወንሾ፣
- ጠጥቻ፣
- ጎርቼ፣
- ቦና ዙሪያ፣
- ቡርሳ፣
- ጫቤ ጋምቤልቱ፣
- ሸበዲኖ፣
- ጭሬና በንሳ ወረዳዎች አባላትና አመራሮቻቸው " የብልፅግና ፓርቲ መዋጮ ለምን አታዋጡም " በሚል ለእስር ተዳርገዉ እንደነበር አንስተዋል።
አቶ ሠለሞን ፤ " አሸናፊዉ ፓርቲ ብልፅግና ነዉ፤ ሁሉም ለብልፅግና ፓርቲ የህንፃ ግንባታ መዋጮ የማዋጣት ግዴታ አለበት " የሚል የተሳሳተ ግንዛቤ በአንዳንድ ወረዳዎች በግልፅ እየተስተዋለ ነው ብለዋል።
" በዚህ ሁኔታ የሚደረጉ ኢ-ሕገ መንግስታዊና የሁሉም ፖለቲካ ፓርቲዎች የቃል ኪዳን ሰነድ በሚፃረርር መልኩ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች በአስቸኳይ ሊቆሙ ይገባል " ሲሉ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉዳዩ ላይ የሲዳማ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢና የኢሶዴፖ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልና የደቡባዊ ቀጠና የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ በለጠ ሲጄቦ አነጋግሯል።
ቅሬታ መቅረቡን አልሸሸጉም።
ቅሬታውን ተከትሎ ምክር ቤቱ የታሰሩ ሰዎች እንዲፈቱ በማድረግ ኮሚቴ ተሰይሞ የማጣራት ሥራ መስራቱን ገልጸዋል።
በዚህም የታሰሩት ግለሰቦች በደረቅ ወንጀል የተጠረጠሩ አንጂ በፖለቲካ አቋማቸዉና አመለካከታቸዉ ምክንያት እንዳልሆነ መረጋገጡን አሳውቀዋል።
ከ2013 ዓ/ም ጀምሮ የፓርቲው የወረዳ አባል መሆናቸውን የሚገልጹት የጠጥቻ ወረዳ ነዋሪ አቶ አስራት ወርሶ ግን " ለሁለት ፓርቲ መዋጮ አላዋጣም በማለቴ ታስሬ ነበር " ሲሉ ስለእስራቸው ምክንያት ይገልጻሉ።
ከአንድ ቀን እስር በኋላም የፓርቲው አመራሮች ባቀረቧቸዉ መረጃዎች ምክንያት ከእስር መለለቃቸዉን አስረድተዋል።
የሲዳማ ህዝብ አንድነት ዲሞክራሲያዊ ድርጅት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልና የሁላ ወረዳ ስራ አስፈፃሚ መ/ር ሀንሳሶ በበኩላቸው " እኔም አባላቶቻችን ለምን ታሰሩ " በሚል ልንጠይቃቸዉ በሄድንበት ከሁለት አባላት ጋር ታስረን ነበር ሲሉ " ተጨማሪ ምስክርነት ሰጥተዋል።
አክለውም " ለብልፅግና ፓርቲ የሕንፃ መሰሪያ መዋጮ ካላዋጣችሁ በሚል በአባላትና አመራሮቻቸዉ ላይ በበርካታ ወረዳዎች እየደረሰ ያለዉ ጫና ስጋት ዉስጥ ከቶናል " ሲሉ ገልጸዋል።
የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ እና የገዢዉ ብልፅግና ፓርቲ ሃሳብ ለማካተት ያደረግነዉ ሙከራ ያልተሳካ ሲሆን ኃሳባቸውን እንዳገኘን የምናካትት ይሆናል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
" ልመና አልነበረም ማለት አይደለም ፤ አሁን ግን እየተባባሰ ሄዷል ! ... የኑሮ ውድነቱን መቋቋም አቅቶት ህብረተሰቡ መድረሻ እያጣ ነው " - አቶ አበረ አዳሙ
የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ዛሬ 8ኛ መደበኛ ሰብሰባው አድርጎ ነበር።
በዚህም ወቅት ከም/ቤት አባላት ለንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ጥያቄ ቀርቦላቸው ነበር።
ሚኒስትሩም ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባል የሆኑ አቶ አበረ አዳሙ ምን ጠየቁ ?
" 1. በዓለም አቀፍ ተጨባጭ ሁኔታዎች ምክንያት ከውጭ የሚገቡ ሸቀጦች ዋጋ የኑሮ ውድነቱን እያናረው ከመሆኑንም በላይ በተለይ በሀገር ውስጥ ምርቶች ላይ የሚደረገው ምክንያት የለሽ ጭማሪ የህዝቡን ኑሮ እንዲመሰቃቀል አድርጎታል።
ለምሳሌ ፦
- ጤፍ
- ስንዴ
- ምስር ... ሆነ ሌሎች የአትክልት እና ፍራፍሬ ምርቶች በሀገር ውስጥ የሚመረቱ ቢሆኑም በጥራት እና በብዛት ገበያ ላይ አይገኙም ፤ ቢገኙም ዋጋቸው እጅግ የተጋነነ በመሆኑ በቀላሉ የሚቀመስ አይደለም።
የችግሩ ምንጭ ደግሞ ሰው ሰራሽ መሆኑ አይካድም።
ህጋዊ ነጋዴው በኮንትሮባንድ ነጋዴዎች እና ለደላላ እየተጠለፈ መስራት ከማይችልበት ደረጃ ላይ ደርሷል።
በዚህ የተነሳ ' ልጆቼን የማበላቸው አጣሁ ' የሚሉ አዛውንቶች፣ ' ጋሽዬ ቁራሽ የዳቦ መግዣ ስጠኝ ራበኝ ' የሚሉ አንጀት የሚበሉ በርካታ ህጻናትን ማየት በከተማችን እየተለመደ መጥቷል።
ልመና አልነበረም ማለት አይደለም አሁን ግን እጅግ እየተባባሰ ሄዷል።
ደላላው ዋጋ ይተምናል ፤ ደላላው ዋጋ ይሰቅላል ቢፈልግም ያወርዳል ለዚህም አንድ ወቅት የሱዙኪ መኪና ዋጋን ሰማይ አድርሶ መሬት አስልሶት የነበረበትን አጋጣሚ ማስታወስ ይቻላል።
በአጭር አነጋገር ደላላ የንግዱን ስርዓት /ሲስተም እንደ ተባይ ወሮታል። በዚህም የኑሮ ውድነቱን መቋቋም አቅቶት ህብረተሰቡ መድረሻ እያጣ ነው።
ጥቅሙን የሚያገኘው በጋ ከክረምት ደም ታፍቶ ያመረተው አርሶ አደሩ ቢሆን መልካም ነበር።
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶ ህገወጥ ነጋዴዎች እና ደላላዎችን ስርዓት ሊያሲዝ የሚችል ዘላቂነት ያለው ስራ ከመስራት ይልቅ አልፎ አልፎ ወይም የሆነ አጋጣሚ ሲፈጠር ' ይሄን ያህል የንግድ ድርጅቶችን አሽኩ / ልናሽግ ነው ' እያሉ በመገናኛ ብዙሃን ማስታወቂያዎችን ከማስተጋባት የዘለለ ፦
° የንግድ ተቋማቱ በምን ምክንያት እንደታሸጉ
° ምን አይነት ህጋዊ እርምጃ እንደተወሰደባቸው
° የማሸጉ እርምጃ ምን ውጤት እንዳስገኘ
° የንግድ ድርጅቶቹ ከታሸጉ በኃላ የመጣንው ለውጥ ለህዝቡ ሲያሳውቅ አይታይም።
በኑሮ ላይ ጠብ የሚል ለውጥ አይስተዋልም።
ታዲያ የሀገራችንን ገበያ እየመራ ያለው ንግድ ሚኒስቴር ነው ወይስ ደላላና ህገወጥ ነጋዴ ?
2. ለንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ተጠሪ የሆነው የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ከሚቆጣጠራቸው ተቋማት አንዱ መብራት ኃይል ነው። (በየጊዜው የመዋቅር መቀያየር ለውጥ ካለ ይቅርታ ጠይቃለሁ!)
ይሁን እንጂ የመብራት ተደራሽነት እና አግልግሎት አሰጣጥ በእጅጉ የተበላሸ ነው።
👉 ተደራሽነቱ ፍትሃዊነት የጎደለውና ለማዳረስ የተሞከረው ለረጅም አመታት የተተከሉ ፖሎች ሳይቀር ያለ አገልግሎት የቆሙበት፤
👉 ተዳረሰ የተባለውም በኃይል መቆራረጥ ችግር ተጠቃሚውን የሚያሰቃይ፤
👉 አገልግሎቱን ለማግኘት ያለ እፍረት በእጅ መንሻ / ጉባ ካልሆነ በቀር የማይሰራ ሰራተኛ የበዛበት ነው።
የሚያሳዝነው ደግሞ ጉቦ ወንጀል መሆኑ ቀርቶ መብት እስኪመስል ድረስ ዋጋ ተምነው ' ይህን ያህል አምጣ ' የሚሉ ሰራተኞች መብዛታቸው ነው።
በዚህ ከቀጠለ ምናልባትም ፓርላማውን ' የምቀበለው ጉቦ አንሶኛል እና ህግ አውጡልኝ ' ማለት የቀራቸው ይመስላል።
ይህ የእርሶን ተቋም ብቻ የሚመለከት አይደለም በርካታ ተቋማትን የሚያካትት ነው።
ክቡር ሚኒስትር ለመሆኑ ለእርሶ ተጠሪ የሆነው ባለስልጣን መ/ቤት ህዝቡን እያስለቀሰ የሚቀጥለው እስከመቼ ነው ? ይህንን ተቋም መቆጣጠርና ስርዓቱን ማስያዝ ያልተቻለው ለምንድነው ?
3. የኑሮ ውድነቱን ከሚያባብሱ ምክንያቶች አንዱ ነዳጅ ነው።
የዋጋው ማሻቀብ ምክንያቱ የሚታወቅ ቢሆንም ከዋጋው በላይ ሰልፉ ህዝቡን እያማረረ ይገኛል።
ከእጥረቱም በላይ ነዳጅ ለመቅዳት በሚደረግ ረጃጅም ሰልፍ ምክንያት የስራ ሰዓት ያለ አግባብ እየባከነ፣ የትራፊክ ፍሰቱን እያስተጓጎለ፣ እንዲያውም ሲል በህገወጥ መንገድ ነዳጅ ከሀገር እንዲወጣ ሰፊ በር እየከፈተ መሆኑን እማኝ መጥቀስ የሚያስፈልግ አይመስለኝም።
ክቡር ሚኒስትር ይህንን የተበላሸ አሰራር ስርዓት ማስያዝ የማን ኃላፊነት ይመስሎታል ? እባክዎ ለዚህ የተከበረ ም/ቤት እና ለብዙሃኑ የሀገራችን ህዝብ ተገቢውን መልስ ይስጡ። "
ሚኒስትሩ ምን ምላሽ ሰጡ ? ያንብቡ ፦ https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-12-03
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ዛሬ 8ኛ መደበኛ ሰብሰባው አድርጎ ነበር።
በዚህም ወቅት ከም/ቤት አባላት ለንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ጥያቄ ቀርቦላቸው ነበር።
ሚኒስትሩም ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባል የሆኑ አቶ አበረ አዳሙ ምን ጠየቁ ?
" 1. በዓለም አቀፍ ተጨባጭ ሁኔታዎች ምክንያት ከውጭ የሚገቡ ሸቀጦች ዋጋ የኑሮ ውድነቱን እያናረው ከመሆኑንም በላይ በተለይ በሀገር ውስጥ ምርቶች ላይ የሚደረገው ምክንያት የለሽ ጭማሪ የህዝቡን ኑሮ እንዲመሰቃቀል አድርጎታል።
ለምሳሌ ፦
- ጤፍ
- ስንዴ
- ምስር ... ሆነ ሌሎች የአትክልት እና ፍራፍሬ ምርቶች በሀገር ውስጥ የሚመረቱ ቢሆኑም በጥራት እና በብዛት ገበያ ላይ አይገኙም ፤ ቢገኙም ዋጋቸው እጅግ የተጋነነ በመሆኑ በቀላሉ የሚቀመስ አይደለም።
የችግሩ ምንጭ ደግሞ ሰው ሰራሽ መሆኑ አይካድም።
ህጋዊ ነጋዴው በኮንትሮባንድ ነጋዴዎች እና ለደላላ እየተጠለፈ መስራት ከማይችልበት ደረጃ ላይ ደርሷል።
በዚህ የተነሳ ' ልጆቼን የማበላቸው አጣሁ ' የሚሉ አዛውንቶች፣ ' ጋሽዬ ቁራሽ የዳቦ መግዣ ስጠኝ ራበኝ ' የሚሉ አንጀት የሚበሉ በርካታ ህጻናትን ማየት በከተማችን እየተለመደ መጥቷል።
ልመና አልነበረም ማለት አይደለም አሁን ግን እጅግ እየተባባሰ ሄዷል።
ደላላው ዋጋ ይተምናል ፤ ደላላው ዋጋ ይሰቅላል ቢፈልግም ያወርዳል ለዚህም አንድ ወቅት የሱዙኪ መኪና ዋጋን ሰማይ አድርሶ መሬት አስልሶት የነበረበትን አጋጣሚ ማስታወስ ይቻላል።
በአጭር አነጋገር ደላላ የንግዱን ስርዓት /ሲስተም እንደ ተባይ ወሮታል። በዚህም የኑሮ ውድነቱን መቋቋም አቅቶት ህብረተሰቡ መድረሻ እያጣ ነው።
ጥቅሙን የሚያገኘው በጋ ከክረምት ደም ታፍቶ ያመረተው አርሶ አደሩ ቢሆን መልካም ነበር።
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶ ህገወጥ ነጋዴዎች እና ደላላዎችን ስርዓት ሊያሲዝ የሚችል ዘላቂነት ያለው ስራ ከመስራት ይልቅ አልፎ አልፎ ወይም የሆነ አጋጣሚ ሲፈጠር ' ይሄን ያህል የንግድ ድርጅቶችን አሽኩ / ልናሽግ ነው ' እያሉ በመገናኛ ብዙሃን ማስታወቂያዎችን ከማስተጋባት የዘለለ ፦
° የንግድ ተቋማቱ በምን ምክንያት እንደታሸጉ
° ምን አይነት ህጋዊ እርምጃ እንደተወሰደባቸው
° የማሸጉ እርምጃ ምን ውጤት እንዳስገኘ
° የንግድ ድርጅቶቹ ከታሸጉ በኃላ የመጣንው ለውጥ ለህዝቡ ሲያሳውቅ አይታይም።
በኑሮ ላይ ጠብ የሚል ለውጥ አይስተዋልም።
ታዲያ የሀገራችንን ገበያ እየመራ ያለው ንግድ ሚኒስቴር ነው ወይስ ደላላና ህገወጥ ነጋዴ ?
2. ለንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ተጠሪ የሆነው የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ከሚቆጣጠራቸው ተቋማት አንዱ መብራት ኃይል ነው። (በየጊዜው የመዋቅር መቀያየር ለውጥ ካለ ይቅርታ ጠይቃለሁ!)
ይሁን እንጂ የመብራት ተደራሽነት እና አግልግሎት አሰጣጥ በእጅጉ የተበላሸ ነው።
👉 ተደራሽነቱ ፍትሃዊነት የጎደለውና ለማዳረስ የተሞከረው ለረጅም አመታት የተተከሉ ፖሎች ሳይቀር ያለ አገልግሎት የቆሙበት፤
👉 ተዳረሰ የተባለውም በኃይል መቆራረጥ ችግር ተጠቃሚውን የሚያሰቃይ፤
👉 አገልግሎቱን ለማግኘት ያለ እፍረት በእጅ መንሻ / ጉባ ካልሆነ በቀር የማይሰራ ሰራተኛ የበዛበት ነው።
የሚያሳዝነው ደግሞ ጉቦ ወንጀል መሆኑ ቀርቶ መብት እስኪመስል ድረስ ዋጋ ተምነው ' ይህን ያህል አምጣ ' የሚሉ ሰራተኞች መብዛታቸው ነው።
በዚህ ከቀጠለ ምናልባትም ፓርላማውን ' የምቀበለው ጉቦ አንሶኛል እና ህግ አውጡልኝ ' ማለት የቀራቸው ይመስላል።
ይህ የእርሶን ተቋም ብቻ የሚመለከት አይደለም በርካታ ተቋማትን የሚያካትት ነው።
ክቡር ሚኒስትር ለመሆኑ ለእርሶ ተጠሪ የሆነው ባለስልጣን መ/ቤት ህዝቡን እያስለቀሰ የሚቀጥለው እስከመቼ ነው ? ይህንን ተቋም መቆጣጠርና ስርዓቱን ማስያዝ ያልተቻለው ለምንድነው ?
3. የኑሮ ውድነቱን ከሚያባብሱ ምክንያቶች አንዱ ነዳጅ ነው።
የዋጋው ማሻቀብ ምክንያቱ የሚታወቅ ቢሆንም ከዋጋው በላይ ሰልፉ ህዝቡን እያማረረ ይገኛል።
ከእጥረቱም በላይ ነዳጅ ለመቅዳት በሚደረግ ረጃጅም ሰልፍ ምክንያት የስራ ሰዓት ያለ አግባብ እየባከነ፣ የትራፊክ ፍሰቱን እያስተጓጎለ፣ እንዲያውም ሲል በህገወጥ መንገድ ነዳጅ ከሀገር እንዲወጣ ሰፊ በር እየከፈተ መሆኑን እማኝ መጥቀስ የሚያስፈልግ አይመስለኝም።
ክቡር ሚኒስትር ይህንን የተበላሸ አሰራር ስርዓት ማስያዝ የማን ኃላፊነት ይመስሎታል ? እባክዎ ለዚህ የተከበረ ም/ቤት እና ለብዙሃኑ የሀገራችን ህዝብ ተገቢውን መልስ ይስጡ። "
ሚኒስትሩ ምን ምላሽ ሰጡ ? ያንብቡ ፦ https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-12-03
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ኢየሱስ ይወዳችኋል ! " - ማርክ ጉዬ
➡️ የእስልምና እምነት ተከታዩ ሳም ሞርሲም የግብረሰዶማውያንን ምልክት ሳያደርግ ወደ ሜዳ ገብቶ ጨዋታውን አድርጓል !
ማርክ ጉዬ የተባለው እግር ኳስ ተጫዋች በድጋሚ ክንድ ላይ በሚጠለቀው የግብረሰዶማውያን ምልክት ላይ " ኢየሱስ ይወዳችኋል ! " የሚል ፅሁፍ በመፃፍ ወደ ሜዳ በመግባት ጨዋታውን አድርጓል።
ክሪስታል ፓላስ ለተባለው ክለብ የሚጫወተውና የቡድኑ አምበል የሆነው ጉዬ ከቀናት በፊት ኒውካስል ዩናይትድ ከተባለው ቡድን ጋር ሲጫወት ክንዱ ላይ ባጠለቀው የግብረሰዶማውያን ምልክት ላይ " ኢየሱስን እወደዋለሁ " ብሎ ፅፎ በመግባቱ የሊጉን አስተዳዳሪዎች አስቆጥቶ ነበር።
ይኸው ተጫዋች ትላንት ምሽት ቡድኑ ኢፒስዊች ታውን ከተባለው ቡድን ጋር ሲጫወት ክንዱ ላይ ባለው የግብረሰዶማውያን ምልክት ላይ በድጋሚ " ኢየሱስ ይወዳችኋል ! " ብሎ በመፃፍ በመግባት ጨዋታውን አድርጓል።
ባለፈው ቅዳሜ ከፃፈው " ኢየሱስን እወደዋለሁ ! " ከሚለው ፅሁፍ በኃላ ፉትቦል አሶሲዬሽን የተባለው የሊጉ አስተዳዳሪ " ኃይማኖታዊ ምልክቶች የእግር ኳስ ማሊያ እና ሌሎች ቁሳቁሶች ላይ መፃፍ ክልክል ነው " ሲል ለክለቡ እና ለአምበሉ ማስጠንቀቂያ ቢልክም ማስጠንቀቂያው ወዲያ በሉት ብሎ ትላንት ምሽት በድጋሚ " ኢየሱስ ይወዳችኋል ! " ሲል በመፃፍ ገብቶ ተጫውቷል።
የሊጉ አስተዳዳሪ ቅጣት ሊጥልበት ይችላል እየተባለ ነው።
በሌላ በኩል የእስልምና እምነት ተከታይ የሆነው ሳም ሞርሲ የተባለው የኢፒስዊች ታውን ተጫዋች ትላንትም የግብረሰዶማውያንን ምልክት ያለበትን የአምበልነት መለያ ሳያደርግ ነው የገባው።
ተጫዋቹ " ሃይማኖቴ አይፈቅድልኝም " በማለት ባለፈው ቅዳሜም ይህንን የግብረሰዶሞች ምልክት ሳያደርግ መግባቱ የሚዘነጋ አይደለም።
' እኩልነት እና ብዝሃነት ' በሚል ሰብሰብ በዓለም ላይ የግብረሰዶማውያንን እንቅስቃሴ ለማስተዋወቅ እና ሰዎች ጋር ለማድረስ የግብረሰዶማውያን ደጋፊዎች ብዙ አይነት መንገድ ይከተላሉ።
አንዱ ግብረሰዶማውያንን ለማስተዋወቅ የሚጠቀሙት በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ በተለይም ወጣት ተመልካቾች ያሉትን የእግር ኳስ ፍልሚያ ነው።
ከነዚህ የእግር ኳስ ፍልሚያዎች አንዱ ደግሞ በኢትዮጵያ / አፍሪካ ሆነ በዓለም ላይ ብዙ ተመልካች ያለውን እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ነው።
በዚሁ ሊግ የሊጉ አስተዳዳሪ አካላት በ ' እኩልነት እና ብዝሃነት ' ሰበብ የክለብ አምበሎች ክንዳቸው ላይ የግብረሰዶማውያንን ምልክት እንዲያጠልቁ አድርገው ለግብረሰዶማውያን ማስታወቂያ እንዲሰሩ ያደርጋሉ።
ይህንን የሚያደርጉት ደግሞ የሊጉ ፍልሚያ በሚጋጋልበት ወቅት ነው።
ግብረሰዶማውያን እና የነሱ ደጋፊዎች እጅግ በጣም ተወዳጁን የእግር ኳስ ፍልሚያን ተጠቅመው ግብረሰዶምን የሚያስተዋውቁት በልጆች ፣ ታዳጊዎች ፣ ወጣቶች ዘንድ ድርጊቱ ተቀባይነት እንዲያገኝ ለማድረግና እነሱን ለማነሳሳት ነው።
#TikvahEthiopia
#Guehi #Christian #PremierLeague
#SamMorsy #Muslim
@tikvahethiopia
➡️ የእስልምና እምነት ተከታዩ ሳም ሞርሲም የግብረሰዶማውያንን ምልክት ሳያደርግ ወደ ሜዳ ገብቶ ጨዋታውን አድርጓል !
ማርክ ጉዬ የተባለው እግር ኳስ ተጫዋች በድጋሚ ክንድ ላይ በሚጠለቀው የግብረሰዶማውያን ምልክት ላይ " ኢየሱስ ይወዳችኋል ! " የሚል ፅሁፍ በመፃፍ ወደ ሜዳ በመግባት ጨዋታውን አድርጓል።
ክሪስታል ፓላስ ለተባለው ክለብ የሚጫወተውና የቡድኑ አምበል የሆነው ጉዬ ከቀናት በፊት ኒውካስል ዩናይትድ ከተባለው ቡድን ጋር ሲጫወት ክንዱ ላይ ባጠለቀው የግብረሰዶማውያን ምልክት ላይ " ኢየሱስን እወደዋለሁ " ብሎ ፅፎ በመግባቱ የሊጉን አስተዳዳሪዎች አስቆጥቶ ነበር።
ይኸው ተጫዋች ትላንት ምሽት ቡድኑ ኢፒስዊች ታውን ከተባለው ቡድን ጋር ሲጫወት ክንዱ ላይ ባለው የግብረሰዶማውያን ምልክት ላይ በድጋሚ " ኢየሱስ ይወዳችኋል ! " ብሎ በመፃፍ በመግባት ጨዋታውን አድርጓል።
ባለፈው ቅዳሜ ከፃፈው " ኢየሱስን እወደዋለሁ ! " ከሚለው ፅሁፍ በኃላ ፉትቦል አሶሲዬሽን የተባለው የሊጉ አስተዳዳሪ " ኃይማኖታዊ ምልክቶች የእግር ኳስ ማሊያ እና ሌሎች ቁሳቁሶች ላይ መፃፍ ክልክል ነው " ሲል ለክለቡ እና ለአምበሉ ማስጠንቀቂያ ቢልክም ማስጠንቀቂያው ወዲያ በሉት ብሎ ትላንት ምሽት በድጋሚ " ኢየሱስ ይወዳችኋል ! " ሲል በመፃፍ ገብቶ ተጫውቷል።
የሊጉ አስተዳዳሪ ቅጣት ሊጥልበት ይችላል እየተባለ ነው።
በሌላ በኩል የእስልምና እምነት ተከታይ የሆነው ሳም ሞርሲ የተባለው የኢፒስዊች ታውን ተጫዋች ትላንትም የግብረሰዶማውያንን ምልክት ያለበትን የአምበልነት መለያ ሳያደርግ ነው የገባው።
ተጫዋቹ " ሃይማኖቴ አይፈቅድልኝም " በማለት ባለፈው ቅዳሜም ይህንን የግብረሰዶሞች ምልክት ሳያደርግ መግባቱ የሚዘነጋ አይደለም።
' እኩልነት እና ብዝሃነት ' በሚል ሰብሰብ በዓለም ላይ የግብረሰዶማውያንን እንቅስቃሴ ለማስተዋወቅ እና ሰዎች ጋር ለማድረስ የግብረሰዶማውያን ደጋፊዎች ብዙ አይነት መንገድ ይከተላሉ።
አንዱ ግብረሰዶማውያንን ለማስተዋወቅ የሚጠቀሙት በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ በተለይም ወጣት ተመልካቾች ያሉትን የእግር ኳስ ፍልሚያ ነው።
ከነዚህ የእግር ኳስ ፍልሚያዎች አንዱ ደግሞ በኢትዮጵያ / አፍሪካ ሆነ በዓለም ላይ ብዙ ተመልካች ያለውን እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ነው።
በዚሁ ሊግ የሊጉ አስተዳዳሪ አካላት በ ' እኩልነት እና ብዝሃነት ' ሰበብ የክለብ አምበሎች ክንዳቸው ላይ የግብረሰዶማውያንን ምልክት እንዲያጠልቁ አድርገው ለግብረሰዶማውያን ማስታወቂያ እንዲሰሩ ያደርጋሉ።
ይህንን የሚያደርጉት ደግሞ የሊጉ ፍልሚያ በሚጋጋልበት ወቅት ነው።
ግብረሰዶማውያን እና የነሱ ደጋፊዎች እጅግ በጣም ተወዳጁን የእግር ኳስ ፍልሚያን ተጠቅመው ግብረሰዶምን የሚያስተዋውቁት በልጆች ፣ ታዳጊዎች ፣ ወጣቶች ዘንድ ድርጊቱ ተቀባይነት እንዲያገኝ ለማድረግና እነሱን ለማነሳሳት ነው።
#TikvahEthiopia
#Guehi #Christian #PremierLeague
#SamMorsy #Muslim
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሩስያ ከዚህ ቀደም ማንኛውም አይነት #የግብረሰዶም እንቀስቃሴን #ሕገወጥ እና #ጽንፈኛ በማለት ፈርጃ የነበረችው ሩስያ አሁን ደግሞ የግብረሰዶም እንቅስቃሴን #የአክራሪነት እና #የሽብር ድርጊት ዝርዝር ውስጥ አካታዋለች። በዚህም ማንኛውም ዓለም አቀፍ የግብረሰዶም እንቅስቃሴ በሩስያ በአሸባሪነት እና በአክራሪነት ዝርዝር ውስጥ ተካቷል። ውሳኔው የተደረሰው የሩስያ የፍትህ ሚኒስቴር የቀረበለትን አቤቱታ…
#Russia #Putin
ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ ምሽት ላይ የሩስያ ፖሊስ ሞስኮ ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ ባሮችን እና የምሽት መዝናኛ ክለቦችን ሲያስስ ነው ያደረው።
አሰሳው ከግብረሰዶማውያን ፕሮፓጋንዳ ቁጥጥር ጋር የተያያዘ ነው።
በሩስያ ማንኛውም አይነት የግብረሰዶማውያን እንቅስቃሴ ማስተዋወቅ ወይም ፕሮፖጋንዳ መስራት በህገወጥነት መፈረጁ ይታወሳል።
ፖሊስ በቅዳሜ ምሽት አሰሳው በየባሩና በየምሽት ክለቡ እየገባ ጥብቅ ፍተሻ አድርጓል።
በወቅቱም ስማርት ስልኮች፣ ላፕቶፖች፣ የቪድዮ ካሜራዎች ተወርሰዋል።
በየመሸታ ቤቶቹ የተገኙ ሰዎች ዶክመንታቸው በፖሊስ ሲፈተሽ አድሯል።
የሀገር ውስጥ ሚኒስቴር ፤ የታገደውን የግብረሰዶማውያን እንቅስቃሴ ፖሮፖጋንዳ ሲያሰራጭ እንደነበር በተጠረጠረ አንድ በስም ባልገልጸው የምሽት ክለብ ውስጥም አሰሳና ፍተሻ መደረጉን ገልጿል።
ታስ እንደዘገበው ደግሞ " Men Travel " የተባለ የጉዞ ኤጀንሲ ኃላፊ ከፀረ ግብረሰዶማውያን ህግ ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር ውሏል።
ሰውየው በሩስያ አዲስ አመት ወቅት ወደ ግብፅ " መደበኛ ያልሆኑ የወሲብ እሴቶችን " የሚደግፉ ደጋፊዎችን ጉዞ ሊያዘጋጅ እንደሆነ በመጠርጠሩ ነው።
የሩስያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዓለም አቀፍ የግብረሰዶማውያን እንቅስቃሴን " የፅንፈኞች እና አክራሪዎች እንቅስቃሴ " በማለት በህገወጥነት ፈርጆ ካገደ ሰሞኑን አንድ አመት ደፍኗል።
ሩስያ የግብረሰዶም እንቅስቃሴን የአክራሪነት እና የሽብር ድርጊት ዝርዝር ውስጥም ያካተተች ሲሆን የተመሳሳይ ጾታ ጥምረት በሀገሪቱ እውቅና የለውም።
በሌላ በኩል ፥ ባለፈው ቅዳሜ የሩስያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ፤ ጄንደር አፊርሚንግ ኬር (የአንድን ሰው የጾታ ማንነት መደገፍ እና ማረጋገጥ) ወይም ጾታ መቀየር ህጋዊ የሆነባቸው ሀገራት ዜጎች የሩስያ ልጆችን በጉዲፈቻ እንዳይወስዱ የሚያግድ ህግ ላይ ፈርመዋል።
በተጨማሪም ፕሬዝዳንት ፑቲን ሰዎች ልጅ እንዳይወልዱ የሚያበረታታ ማንኛውም አይነት እንቅስቃሴ / ስርጭትን የሚያግድ ህግ አፅድቀዋል።
#TikvahEthiopia
#Russia #TASS
@tikvahethiopia
ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ ምሽት ላይ የሩስያ ፖሊስ ሞስኮ ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ ባሮችን እና የምሽት መዝናኛ ክለቦችን ሲያስስ ነው ያደረው።
አሰሳው ከግብረሰዶማውያን ፕሮፓጋንዳ ቁጥጥር ጋር የተያያዘ ነው።
በሩስያ ማንኛውም አይነት የግብረሰዶማውያን እንቅስቃሴ ማስተዋወቅ ወይም ፕሮፖጋንዳ መስራት በህገወጥነት መፈረጁ ይታወሳል።
ፖሊስ በቅዳሜ ምሽት አሰሳው በየባሩና በየምሽት ክለቡ እየገባ ጥብቅ ፍተሻ አድርጓል።
በወቅቱም ስማርት ስልኮች፣ ላፕቶፖች፣ የቪድዮ ካሜራዎች ተወርሰዋል።
በየመሸታ ቤቶቹ የተገኙ ሰዎች ዶክመንታቸው በፖሊስ ሲፈተሽ አድሯል።
የሀገር ውስጥ ሚኒስቴር ፤ የታገደውን የግብረሰዶማውያን እንቅስቃሴ ፖሮፖጋንዳ ሲያሰራጭ እንደነበር በተጠረጠረ አንድ በስም ባልገልጸው የምሽት ክለብ ውስጥም አሰሳና ፍተሻ መደረጉን ገልጿል።
ታስ እንደዘገበው ደግሞ " Men Travel " የተባለ የጉዞ ኤጀንሲ ኃላፊ ከፀረ ግብረሰዶማውያን ህግ ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር ውሏል።
ሰውየው በሩስያ አዲስ አመት ወቅት ወደ ግብፅ " መደበኛ ያልሆኑ የወሲብ እሴቶችን " የሚደግፉ ደጋፊዎችን ጉዞ ሊያዘጋጅ እንደሆነ በመጠርጠሩ ነው።
የሩስያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዓለም አቀፍ የግብረሰዶማውያን እንቅስቃሴን " የፅንፈኞች እና አክራሪዎች እንቅስቃሴ " በማለት በህገወጥነት ፈርጆ ካገደ ሰሞኑን አንድ አመት ደፍኗል።
ሩስያ የግብረሰዶም እንቅስቃሴን የአክራሪነት እና የሽብር ድርጊት ዝርዝር ውስጥም ያካተተች ሲሆን የተመሳሳይ ጾታ ጥምረት በሀገሪቱ እውቅና የለውም።
በሌላ በኩል ፥ ባለፈው ቅዳሜ የሩስያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ፤ ጄንደር አፊርሚንግ ኬር (የአንድን ሰው የጾታ ማንነት መደገፍ እና ማረጋገጥ) ወይም ጾታ መቀየር ህጋዊ የሆነባቸው ሀገራት ዜጎች የሩስያ ልጆችን በጉዲፈቻ እንዳይወስዱ የሚያግድ ህግ ላይ ፈርመዋል።
በተጨማሪም ፕሬዝዳንት ፑቲን ሰዎች ልጅ እንዳይወልዱ የሚያበረታታ ማንኛውም አይነት እንቅስቃሴ / ስርጭትን የሚያግድ ህግ አፅድቀዋል።
#TikvahEthiopia
#Russia #TASS
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Syria : የ24 ዓመታት የፕሬዜዳንት በሽር አልአሳድን አገዛዝ ያስወገዱት የታጠቁት ተቃዋሚዎች አልአሳድ ሀገር ጥለው መጥፋታቸውን ገልጸዋል። የሶሪያ ተዋጊዎች በደማስቆ የሚገኘውን የአውሮፕላን ማረፊያን ከመቆጣጠራቸው ጥቂት ጊዜ በፊት በሶሪያ አየር ክልል ውስጥ የአንድ አውሮፕላን እንቅስቃሴ ተመዝግቧል። የIL76 አውሮፕላን የበረራ ቁጥሩ ' የሶሪያ አየር 9218 ' ከደማስቆ የተነሳ የመጨረሻ በረራ…
#SYRIA : የ24 ዓመታት የአልአሳድ አገዛዝ እንዴት ተገረሰሰ ?
በፕሬዜዳንት በሽር አላሳድ አገዛዝ ላይ እ.ኤ.አ. በ2011 / ከዛሬ 13 ዓመት በፊት ነው ህዝባዊ አመጽ የተነሳው።
ከዛ ጊዜ አንስቶ ሀገሪቱ መረጋጋት አልቻለችም።
ታጣቂዎች በየቦታው ተነሱ ሀገሪቱ የከፋ የእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ ገባች።
ይኸው 13 ዓመታት በሆነው የማያባራ እልቂት በርካታ ህጻናት፣ እናቶች፣ ወጣቶች ፣ አዛውንቶች ተቀጥፈዋል።
ሀገሪቱ እንዳልነበር ሆና ወድማለች።
ሶሪያ ዳግም ከወደቀችበት አዘቅት ለመውጣት ዘመናት የሚያስፈልጋት ሆናለች።
በዚህ 13 ዓመታትን በቆየው የእርስ በርስ ጦርነት የውጭ ሀይሎች እነ ሩስያ፣ ኢራን፣ አሜሪካ ፣ ቱርክ ... እጃቸው አለበት።
የውጭ ኃይሎቹ እንደግፈዋለን የሚሉትን ኃይል በማገዝ እልቂቱን እንዳያባራ አድርገዋል።
ምንም እንኳን በሀገሪቱ ያሉ የታጠቁ ተቃዋሚዎች የአላሳድን አገዛዝ ለመገርሰስ ሲዋጉ ፣ የተለያዩ ቦታዎችን ሲይዙ ለዓመታት ቢቆዩም የሰሞኑን ከፍተኛ ፍጥነት የታየበት ድንገታዊ ጥቃት ግን " ድራማዊ " ተብሎለታል።
ካለፈው ሳምንት አንስቶ ተጣቂዎቹ በተለያየ የሀገሪቱ አቅጣጫ በከፈቱት መጠነ ሰፊ ጥቃት የሶሪያ ጦር ፈራርሷል።
ወታደሮች ሀገር ጥለው ሸሽተዋል ፤ የአላሳድ መቀመጫ ደማስቆን ጨምሮ ትልልቅ እና ቁልፍ የሚባሉ ከተሞች በፍጥነት በታጠቁት ተቃዋሚዎች እጅ ወድቀዋል።
የአላሳድ ደጋፊ ከሆኑ ሀገራት አንዷ ሩስያ በጦር አውሮፕላኖች ታግዛ ጭምር ለአላሳድ ድጋፍ ብታደርግም ፤ ኢራንም አለሁ " አግዛለሁ " ብትልም አገዛዙን ከውድቀት አልታደጉም።
ተንታኞች የአሳድ ጦር ኃይሎች በዝቅተኛ ደሞዝ እና በመኮንኖች መካከል በተንሰራፋው ሙስና የተነሳ የውግያ ሞራላቸው ተንኮታኩቷል ብለዋል።
ምንም እንኳን በቅርቡ ለሰራዊቱ የ50 በመቶ የደመወዝ ጭማሪ ቢደረግም ይህ ነው የሚባል ለውጥ ሊፈጠር ባለመቻሉ አገዛዙ ፈርሷል።
በአላሳድ ስር ሲዋጉ የነበሩ ወታደሮች ልብሳቸውን እያወለቁ ሲቪል መስለው ሲሸሹ ታይተዋል።
አላሳድም ሀገር ጥለው ጥፍተዋል። የት እንዳሉ አይታወቅም።
ቀጣዩ የሶሪያ ዕጣፋንታ ምንድነው ? ጁላኒ ማናቸው ?
አሁን ወደፊት ወጥተው የሚታዩት የቀድሞ ' አል-ኑስራ ' መሪ አሁን ደግሞ ሃያት ታህሪር አል-ሻም (ኤችቲኤስ) የተባለው የታጠቀ ኃይል መሪ አቡ መሀመድ አል ጁላኒ ናቸው።
በበላይነት የታጣቂዎቹን እንቅስቃሴ እያስትባበሩ ያሉት እሳቸው እንደሆኑ ተነግሯል።
ኑስራን ከመመስረታቸው በፊት ኢራቅ ውስጥ ለ #አልቃይዳ ተዋግተዋል። ወደዛ የሄዱት የአሜሪካን ወራር ተከትሎ ነው።
እኚህ ሰው ለ5 ዓመታት በአሜሪካ እስር ቤት አሳልፈዋል።
የአላሳድን አገዛዝ ለመጣል እንቅስቃሴ ሲጀመር በአልቃይዳው መሪ አቡ ባከር አል ባግዳዲ አማካኝነት የአልቃይዳ ህዋስ እንዲኖር ለማድረግ ታስበው ወደ ሶሪያ ተልከዋል። (IS በኢራቅ በኃላ ISIS የሆነው)
አሜሪካ በ2013 አል-ጁላኒን በአሸባሪነት ፈርጃቸዋለች።
እ.ኤ.አ. 2016 ላይ ከአልቃይዳ መፋታታቸው ከተነገር በኃላ ሃያት ታህሪር አል-ሻም የተሰኘውን ቡድን ይዘው መጥተዋል።
ከአልቃይዳም ሆነ ከሌላ ቡድን መፋታታቸው ተነገረ በኃላ የሶሪያ ኢስላሚክ ሪፐብሊክን የመመስረት ዓላማ አንግበው አላሳድን ሲዋጉ ቆይተዋል።
ይኸው የጁላኒ ቡድን አሁን የአላሳድን አገዛዝ በመጣል ትልቁን ድርሻ እንደያዘ ነው የተነገረው።
አቡ መሀመድ አል ጁላኒ ከአላሳድ መገርሰስ በኃላ በሰጡት ቃል ፤ ሁሉም የመንግስት ተቋማት በይፋ ተላልፈው እስኪሰጡ / ርክክብ እስኪደረግ ድረስ በአላሳድ ጠቅላይ ሚኒስትር ቁጥጥር ስር እንደሚቆዩ ይፋ አድርገዋል።
ጠ/ሚኒስትር መሀመድ ጋዚ አል ጃላሊ በሰጡት መግለጫ ፥ በደማስቆ ቤታቸው እንደሚቆዩ እና የህዝብ ተቋማት ስራቸውን እንዲቀጥሉ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በሽር አላሳድ ማን ናቸው ?
° እድሜያቸው 59 ነው። የተወለዱት ደማስቆ።
° ከህክምና ትምህርት ቤት ተመርቀዋል። ለንደን ውስጥ በኦፕታሞሎጂ ስፔሻላይዝድ አድርገዋል።
° የወንድማቸውን በመኪና አደጋ መሞት ተከትሎ ወደ ሶሪያ መጥተዋል።
° እኤአ 2000 ላይ ነው የአባታቸውን ሃፊዝ አላሳድን መሞት ተከትሎ ወደ አገዛዝ የመጡት። አባታቸው ከ1971 አንስቶ ሀገሪቱን ሲመሩ ነበር።
° ወንድማቸው ባሴል አላሳድ የአባታቸውን ስልጣን ይረከባሉ ተብሎ ቢጠበቅም በመኪና አደጋ በመሞታቸው በሽር አላሳድ ስልጣኑን መያዝ ችለዋል።
° የስልጣን ዘመናቸው ከ2011 በኃላ በጦርነት ተሞላ ነው።
አሁን ከሀገር ፍረጥጠዋል የተባሉት አላሳድ በበርካታ የየሰብዓዊ መብት ጥሰቶች፣ ኬሚካል ጦር መሳሪያ በመጠቀም፣ እና በሌሎችም በርካታ ጉዳዮች ይከሰሳሉ።
🚨በሶሪያ የ13 ዓመታት የእርስ በርስ ጦርነት ከ350 ሺህ በላይ ሰዎች እንደሞቱ ሪፖርቶች ያሳያሉ። ሚሊዮኖች ቤት ንብረታቸውን ጥለው ተሰደዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃዎቹን ከሮይተርስ ፣ አልጀዚራ ፣ ዋሽንግተን ፖስት ፣ከፍራንስ 24 ነው አሰባስቦ ያዘጋጀው።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
በፕሬዜዳንት በሽር አላሳድ አገዛዝ ላይ እ.ኤ.አ. በ2011 / ከዛሬ 13 ዓመት በፊት ነው ህዝባዊ አመጽ የተነሳው።
ከዛ ጊዜ አንስቶ ሀገሪቱ መረጋጋት አልቻለችም።
ታጣቂዎች በየቦታው ተነሱ ሀገሪቱ የከፋ የእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ ገባች።
ይኸው 13 ዓመታት በሆነው የማያባራ እልቂት በርካታ ህጻናት፣ እናቶች፣ ወጣቶች ፣ አዛውንቶች ተቀጥፈዋል።
ሀገሪቱ እንዳልነበር ሆና ወድማለች።
ሶሪያ ዳግም ከወደቀችበት አዘቅት ለመውጣት ዘመናት የሚያስፈልጋት ሆናለች።
በዚህ 13 ዓመታትን በቆየው የእርስ በርስ ጦርነት የውጭ ሀይሎች እነ ሩስያ፣ ኢራን፣ አሜሪካ ፣ ቱርክ ... እጃቸው አለበት።
የውጭ ኃይሎቹ እንደግፈዋለን የሚሉትን ኃይል በማገዝ እልቂቱን እንዳያባራ አድርገዋል።
ምንም እንኳን በሀገሪቱ ያሉ የታጠቁ ተቃዋሚዎች የአላሳድን አገዛዝ ለመገርሰስ ሲዋጉ ፣ የተለያዩ ቦታዎችን ሲይዙ ለዓመታት ቢቆዩም የሰሞኑን ከፍተኛ ፍጥነት የታየበት ድንገታዊ ጥቃት ግን " ድራማዊ " ተብሎለታል።
ካለፈው ሳምንት አንስቶ ተጣቂዎቹ በተለያየ የሀገሪቱ አቅጣጫ በከፈቱት መጠነ ሰፊ ጥቃት የሶሪያ ጦር ፈራርሷል።
ወታደሮች ሀገር ጥለው ሸሽተዋል ፤ የአላሳድ መቀመጫ ደማስቆን ጨምሮ ትልልቅ እና ቁልፍ የሚባሉ ከተሞች በፍጥነት በታጠቁት ተቃዋሚዎች እጅ ወድቀዋል።
የአላሳድ ደጋፊ ከሆኑ ሀገራት አንዷ ሩስያ በጦር አውሮፕላኖች ታግዛ ጭምር ለአላሳድ ድጋፍ ብታደርግም ፤ ኢራንም አለሁ " አግዛለሁ " ብትልም አገዛዙን ከውድቀት አልታደጉም።
ተንታኞች የአሳድ ጦር ኃይሎች በዝቅተኛ ደሞዝ እና በመኮንኖች መካከል በተንሰራፋው ሙስና የተነሳ የውግያ ሞራላቸው ተንኮታኩቷል ብለዋል።
ምንም እንኳን በቅርቡ ለሰራዊቱ የ50 በመቶ የደመወዝ ጭማሪ ቢደረግም ይህ ነው የሚባል ለውጥ ሊፈጠር ባለመቻሉ አገዛዙ ፈርሷል።
በአላሳድ ስር ሲዋጉ የነበሩ ወታደሮች ልብሳቸውን እያወለቁ ሲቪል መስለው ሲሸሹ ታይተዋል።
አላሳድም ሀገር ጥለው ጥፍተዋል። የት እንዳሉ አይታወቅም።
ቀጣዩ የሶሪያ ዕጣፋንታ ምንድነው ? ጁላኒ ማናቸው ?
አሁን ወደፊት ወጥተው የሚታዩት የቀድሞ ' አል-ኑስራ ' መሪ አሁን ደግሞ ሃያት ታህሪር አል-ሻም (ኤችቲኤስ) የተባለው የታጠቀ ኃይል መሪ አቡ መሀመድ አል ጁላኒ ናቸው።
በበላይነት የታጣቂዎቹን እንቅስቃሴ እያስትባበሩ ያሉት እሳቸው እንደሆኑ ተነግሯል።
ኑስራን ከመመስረታቸው በፊት ኢራቅ ውስጥ ለ #አልቃይዳ ተዋግተዋል። ወደዛ የሄዱት የአሜሪካን ወራር ተከትሎ ነው።
እኚህ ሰው ለ5 ዓመታት በአሜሪካ እስር ቤት አሳልፈዋል።
የአላሳድን አገዛዝ ለመጣል እንቅስቃሴ ሲጀመር በአልቃይዳው መሪ አቡ ባከር አል ባግዳዲ አማካኝነት የአልቃይዳ ህዋስ እንዲኖር ለማድረግ ታስበው ወደ ሶሪያ ተልከዋል። (IS በኢራቅ በኃላ ISIS የሆነው)
አሜሪካ በ2013 አል-ጁላኒን በአሸባሪነት ፈርጃቸዋለች።
እ.ኤ.አ. 2016 ላይ ከአልቃይዳ መፋታታቸው ከተነገር በኃላ ሃያት ታህሪር አል-ሻም የተሰኘውን ቡድን ይዘው መጥተዋል።
ከአልቃይዳም ሆነ ከሌላ ቡድን መፋታታቸው ተነገረ በኃላ የሶሪያ ኢስላሚክ ሪፐብሊክን የመመስረት ዓላማ አንግበው አላሳድን ሲዋጉ ቆይተዋል።
ይኸው የጁላኒ ቡድን አሁን የአላሳድን አገዛዝ በመጣል ትልቁን ድርሻ እንደያዘ ነው የተነገረው።
አቡ መሀመድ አል ጁላኒ ከአላሳድ መገርሰስ በኃላ በሰጡት ቃል ፤ ሁሉም የመንግስት ተቋማት በይፋ ተላልፈው እስኪሰጡ / ርክክብ እስኪደረግ ድረስ በአላሳድ ጠቅላይ ሚኒስትር ቁጥጥር ስር እንደሚቆዩ ይፋ አድርገዋል።
ጠ/ሚኒስትር መሀመድ ጋዚ አል ጃላሊ በሰጡት መግለጫ ፥ በደማስቆ ቤታቸው እንደሚቆዩ እና የህዝብ ተቋማት ስራቸውን እንዲቀጥሉ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በሽር አላሳድ ማን ናቸው ?
° እድሜያቸው 59 ነው። የተወለዱት ደማስቆ።
° ከህክምና ትምህርት ቤት ተመርቀዋል። ለንደን ውስጥ በኦፕታሞሎጂ ስፔሻላይዝድ አድርገዋል።
° የወንድማቸውን በመኪና አደጋ መሞት ተከትሎ ወደ ሶሪያ መጥተዋል።
° እኤአ 2000 ላይ ነው የአባታቸውን ሃፊዝ አላሳድን መሞት ተከትሎ ወደ አገዛዝ የመጡት። አባታቸው ከ1971 አንስቶ ሀገሪቱን ሲመሩ ነበር።
° ወንድማቸው ባሴል አላሳድ የአባታቸውን ስልጣን ይረከባሉ ተብሎ ቢጠበቅም በመኪና አደጋ በመሞታቸው በሽር አላሳድ ስልጣኑን መያዝ ችለዋል።
° የስልጣን ዘመናቸው ከ2011 በኃላ በጦርነት ተሞላ ነው።
አሁን ከሀገር ፍረጥጠዋል የተባሉት አላሳድ በበርካታ የየሰብዓዊ መብት ጥሰቶች፣ ኬሚካል ጦር መሳሪያ በመጠቀም፣ እና በሌሎችም በርካታ ጉዳዮች ይከሰሳሉ።
🚨በሶሪያ የ13 ዓመታት የእርስ በርስ ጦርነት ከ350 ሺህ በላይ ሰዎች እንደሞቱ ሪፖርቶች ያሳያሉ። ሚሊዮኖች ቤት ንብረታቸውን ጥለው ተሰደዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃዎቹን ከሮይተርስ ፣ አልጀዚራ ፣ ዋሽንግተን ፖስት ፣ከፍራንስ 24 ነው አሰባስቦ ያዘጋጀው።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
#Democracy👏
" የህዝቤን ውሳኔ አከብራለሁ " - በምርጫ የተሸነፉት ባውሚያ
አፍሪካ ውስጥ የተረጋጋ ምርጫና የስልጣን ሽግግር ከሚደረግባቸው ሀገራት አንዷ ጋና ናት።
ሀገሪቱ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ አካሂዳለች።
ለውድድር የቀረቡትም ተቃዋሚው የናሽናል ዴሞክራቲክ ኮንግረስ ፓርቲው የቀድሞ ፕሬዝዳንት ጆን ድራማኒ ማሃማ እና የአሁን የገዢው ኒው ፓትርዮቲክ ፓርቲ ዕጩና የሀገሪቱ ምክትል ፕሬዝዳንት መሃሙዱ ባውሚያ ናቸው።
ውጤት ?
የቀድሞው ፕሬዝዳንት ጆን ማሃማ የገዢውን ፓርቲና የአሁኑ ምክትል ፕሬዜዳንት ባውሚያን አሸንፈዋቸዋል።
በምርጫው የተሸነፉት የገዢው ፓርቲ ዕጩ ለተፎካካሪያቸው " እንኳን ደስ አልዎት ! " ብለዋቸዋል።
ምርጫውን የተሸነፉት የገዢው ዕጩ ባውሚያ ህዝባቸውን / ጋናውያንን ለለውጥ የሰጡትን ድምጽ እና ውሳኔ እንደሚያከብሩ ተናግረዋል።
" የጋና ፕሬዜዳንት ሆነው ለተመረጡት የተከበሩ ጆን ማሃማ ስልክ ደውዬ እንኳን ደስ አለህ ብዬዋለሁ " ሲሉም ገልጸዋል።
ተመራጩ ፕሬዜዳንት ምርጫውን በማሸነፋቸው ደስታ እንደተሰማቸው ገልጸው በሀገሪቱ ያሉትን ችግሮች ለመፍታት እንደሚሰሩ ቃል ገብተዋል።
ተመራጩ ፕሬዜዳንት ከዚህ ቀደም እ.ኤ አ. ከሃምሌ 2012 እስከ ጥር 2017 ሀገሪቱን መርተዋል።
የምርጫው ውጤት ለሁለት ስልጣን ዘመን የቆየው የፕሬዜዳንት ናና አኩፎ ኦዶ ገዢ ፓርቲ ማብቂያ ሆኗል።
ባለፉት የስልጣን ዘመናት ጋና አይታ የማይታውቀው የኢኮኖሚ ቀውስ እንዳጋጠማት ፣ ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት እንዲሁም ከፍተኛ ዕዳ ጉድለት እንደተመዘገበ ተገልጿል።
ህዝቡም በተለይ ለተሻለ የኢኮኖሚ ለውጥ ፤ ያለው የከፋ የኢኮኖሚ ቀውስ መፍትሄ እንዲያገኝ በማሰብ የገዢውን ፓርቲ ዕጩ በድምጹ በመቅጣት ተቀናቃኙን የቀድሞውን ፕሬዜዳንት ወደ ቢሮ ለመመለስ እንደወሰነ ተመላክቷል።
የሀገሪቱ ምርጫ ትልቁ ማጠንጠኛ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች እንደነበሩ ተሰምቷል።
አጠቃላይ የምርጫው ውጤት ግፋ ቢል ማክሰኞ ይፋ ይደረጋል።
ተሰናባቹ ፕሬዜዳንት ናና አኩፎ ኦዶ ለምን ምርጫ አልተወዳደሩም ?
በጋና የፕሬዜዳንቱ ስልጣን ገደብ አለው።
ሁለት የስልጣን ዘመን አሸንፎ ሀገር ከመራ ለሌላ የስልጣን ዘመን " ልወዳደር " ቢል አይፈቀድለትም።
በዚህም ሀገር ለመምራት የሚፈቀድላቸው የስልጣን ዘመን ገደቡ ላይ ስለደረሰና መወዳደር ስለማይችሉ ምክትል ፕሬዜዳንቱ ነው የተወዳደሩት።
ተሰናባቹ ፕሬዜዳንት ወንበሩን ለሌላ የሀገራቸው ልጅ ያስረክባሉ።
#Ghana
#Democracy #Election
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
" የህዝቤን ውሳኔ አከብራለሁ " - በምርጫ የተሸነፉት ባውሚያ
አፍሪካ ውስጥ የተረጋጋ ምርጫና የስልጣን ሽግግር ከሚደረግባቸው ሀገራት አንዷ ጋና ናት።
ሀገሪቱ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ አካሂዳለች።
ለውድድር የቀረቡትም ተቃዋሚው የናሽናል ዴሞክራቲክ ኮንግረስ ፓርቲው የቀድሞ ፕሬዝዳንት ጆን ድራማኒ ማሃማ እና የአሁን የገዢው ኒው ፓትርዮቲክ ፓርቲ ዕጩና የሀገሪቱ ምክትል ፕሬዝዳንት መሃሙዱ ባውሚያ ናቸው።
ውጤት ?
የቀድሞው ፕሬዝዳንት ጆን ማሃማ የገዢውን ፓርቲና የአሁኑ ምክትል ፕሬዜዳንት ባውሚያን አሸንፈዋቸዋል።
በምርጫው የተሸነፉት የገዢው ፓርቲ ዕጩ ለተፎካካሪያቸው " እንኳን ደስ አልዎት ! " ብለዋቸዋል።
ምርጫውን የተሸነፉት የገዢው ዕጩ ባውሚያ ህዝባቸውን / ጋናውያንን ለለውጥ የሰጡትን ድምጽ እና ውሳኔ እንደሚያከብሩ ተናግረዋል።
" የጋና ፕሬዜዳንት ሆነው ለተመረጡት የተከበሩ ጆን ማሃማ ስልክ ደውዬ እንኳን ደስ አለህ ብዬዋለሁ " ሲሉም ገልጸዋል።
ተመራጩ ፕሬዜዳንት ምርጫውን በማሸነፋቸው ደስታ እንደተሰማቸው ገልጸው በሀገሪቱ ያሉትን ችግሮች ለመፍታት እንደሚሰሩ ቃል ገብተዋል።
ተመራጩ ፕሬዜዳንት ከዚህ ቀደም እ.ኤ አ. ከሃምሌ 2012 እስከ ጥር 2017 ሀገሪቱን መርተዋል።
የምርጫው ውጤት ለሁለት ስልጣን ዘመን የቆየው የፕሬዜዳንት ናና አኩፎ ኦዶ ገዢ ፓርቲ ማብቂያ ሆኗል።
ባለፉት የስልጣን ዘመናት ጋና አይታ የማይታውቀው የኢኮኖሚ ቀውስ እንዳጋጠማት ፣ ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት እንዲሁም ከፍተኛ ዕዳ ጉድለት እንደተመዘገበ ተገልጿል።
ህዝቡም በተለይ ለተሻለ የኢኮኖሚ ለውጥ ፤ ያለው የከፋ የኢኮኖሚ ቀውስ መፍትሄ እንዲያገኝ በማሰብ የገዢውን ፓርቲ ዕጩ በድምጹ በመቅጣት ተቀናቃኙን የቀድሞውን ፕሬዜዳንት ወደ ቢሮ ለመመለስ እንደወሰነ ተመላክቷል።
የሀገሪቱ ምርጫ ትልቁ ማጠንጠኛ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች እንደነበሩ ተሰምቷል።
አጠቃላይ የምርጫው ውጤት ግፋ ቢል ማክሰኞ ይፋ ይደረጋል።
ተሰናባቹ ፕሬዜዳንት ናና አኩፎ ኦዶ ለምን ምርጫ አልተወዳደሩም ?
በጋና የፕሬዜዳንቱ ስልጣን ገደብ አለው።
ሁለት የስልጣን ዘመን አሸንፎ ሀገር ከመራ ለሌላ የስልጣን ዘመን " ልወዳደር " ቢል አይፈቀድለትም።
በዚህም ሀገር ለመምራት የሚፈቀድላቸው የስልጣን ዘመን ገደቡ ላይ ስለደረሰና መወዳደር ስለማይችሉ ምክትል ፕሬዜዳንቱ ነው የተወዳደሩት።
ተሰናባቹ ፕሬዜዳንት ወንበሩን ለሌላ የሀገራቸው ልጅ ያስረክባሉ።
#Ghana
#Democracy #Election
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia