#ETHIOPIA
ለመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የሚደረግ የበጀት ድጎማ ከመደበኛው ሥራ ይልቅ ከዋናው ተልዕኮ ውጪ ለሆነ #የፖለቲካ_ሥራ እንደሚውል በፌዴራል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን የተጠና ጥናት ላይ መገለፁን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል።
ኮሚሽኑ ጥናቱን ያከናወነው በፌዴራል ደረጃ በሚገኙ የመንግሥትና የግል ዩኒቨርሲቲዎች ሲሆን የጥናቱ ትኩረት ሙስናና ብልሹ አሠራር በትምህርት ዘርፍ ላይ የሚያደርሰውን የሙስና ሥጋት ለመለየት መሆኑ ተጠቁሟል፡፡
ሪፖርተር ጋዜጣ ከምንጮቼ አገኘሁት ያለውና ኮሚሽኑ በተመረጡ 61 ተቋማት ላይ ያደረገው የጥናት ሪፖርት እንደሚያሳየው ፦
- በተቋማቱ፤ ከመምህራን ልማት እና ከአሠልጣኞች ምልመላ ጋር በተገናኘ፣ የዘመድና የፓርቲ አሠራር፣ እንዲሁም አድልኦና ጉቦ የመቀበል አዝማሚያ በስፋት ይስተዋላል።
- በመምህራንና ሠራተኞች አስተዳደር ክፍል ሕገወጥ ቅጥርና ዝውውር መኖር፣ መምህራን ተማሪዎችን ለይቶ ለመጥቀም የሚደረግ ዝንባሌ መኖር፣ ለመምህራን ቅጥር ውድድር ተፈልጎ እኩል ውጤት ሲመጣ፣ አንዱን በትውውቅ ብቻ የመምረጥ አሠራር እንደሚስተዋል ተገልጿል፡፡
- ከሐሰተኛ የትምህርት ሰነድ ጋር በተያያዘ የብቃት ማረጋገጥና ፈቃድ አሰጣጥ ላይ መሥፈርት ሳያሟሉ፣ ለተቋማት ፈቃድ መስጠት እና የፈቃድ ዕድሳት እንደሚከናወን ተግልጿል።
- መምህራንና በትምህርት አስተዳደር አመራር ላይ ያሉ ሠራተኞች ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃዎች እንደተገኘባቸው ፤ ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃዎችን ለማጣራት ሲሞከር ደግሞ ሠራተኞች ከሥራ ቀድመው የመልቀቅ እንቅስቃሴ እንዳለ ተገልጿል።
- በግል ኮሌጆች የሲኦሲ ምዘና ሳያልፉና ትምህርት አጠናቀው ሳይጨርሱ፣ እንዲሁም ፈጽሞ ያልተማሩ ሰዎች የትምህርት ማስረጃ አትሞ መስጠትና በኮሌጆች ሽያጭ የመፈጸም ድርጊት መኖሩን ሪፖርቱ ገልጿል።
- በኮሌጆችና በዩኒቨርሲቲዎች ሬጅስትራሮች ውስጥ የተማሪዎችን ውጤት የማሳሳትና የማጭበርበር ድርጊት እንዳለ ተጠቅሷሳ።
- በግል ትምህርት ተቋማት ውሳኔዎች የሚተላለፉት ለተቋማቸው መልካም ስም ቅድሚያ በመስጠት እንደሆነ፣ በመንግሥት ተቋማት ደግሞ ሰነድ ማዘጋጀት እንጂ ትግበራ ላይ እምብዛም እንደሌሉበት ተገልጿል።
- በተደረገው ጥናት በተቋማቸው ውስጥ የመልካም አስተዳደር ችግሮች አሉ ወይ ተብለው ከተጠየቁት ውስጥ 65 በመቶ የሚሆኑት " አዎ " የሚል መልስ መስጠታቸውን፣ 35 በመቶ የሚሆኑት " የለም " የሚል መልስ ሲሰጡ፣ በተመሳሳይ የሙስና ችግሮች መኖራቸውን 66 በመቶ መናገራቸውና 47 በመቶ ደግሞ ለሚቀርቡ ጥቆማዎች ከተቋማቱ መልስ እንደማይሰጥ ሪፖርቱ ያስረዳል፡፡
- በትምህርት ተቋማቱ የመምህራን በተደጋጋሚ ወደ ክፍል አለመግባት፣ ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ መስጠት፣ በአመራር የሚከናወን ስርቆት፣ ሕገወጥ ዝውውርና የደረጃ ዕድገት፣ ሕግና ደንብን ተከትሎ የማይከናወን ግዥ፣ የመረጃና ማስረጃ ማጭበርበር፣ ግልጽነት የሌለው አሠራር መብዛት፣ በሬጅስትራር የሚፈጸም ብልሹ አሠራር ተቋማቱን ለከባድ ሙስና አደጋ ጥሏቸዋል፡፡
- በግዥ ወቅት ለተቋም የማያስፈልግ ንብረት እንዲገዛ ተጨማሪ በጀት ማስያዝ፣ በጨረታ ወቅት የተወሰኑ ሰዎችን ብቻ እንዲጋብዝ አድርጎ ሰነድ ማዘጋጀት፣ ወቅቱንና ጥራቱን ያልጠበቀ ግንባታ እንዲከናወን ማድረግ፣ በሕንፃ ርክክብ ጥራቱን ያልጠበቀ ሕንፃ እንዲገነባ ማድረግና ያልተጠናቀቀ ሕንፃ መረከብ ተቋማቱን ለከባድ ሙስና እንዳጋለጣቸው ሪፖርቱ ያሳያል።
እንደ ምክንያት የተጠቀሱት ችግሮች ምንድናቸው ?
• የሠራተኞች ዝቅተኛ የደመወዝ ክፍያ ፣
• የተጠናከረ የቁጥጥር ሥርዓት አለመኖር፣
• የሞራል መላሸቅ፣
• የተጠያቂነት ማነስ፣
• የላላ የአመራር ቁጥጥርና ከፍተኛ የሆነ የበጀት ምደባ የሚሉት ይገኙበታል።
ጥናቱ በሚደረግበት ወቅት ምን ችግሮች አጋጠሙ ?
➤ የተቋማት አመራሮች በቦታው ላይ አለመገኘት፣
➤ ተቋማት መረጃ ለመሥጠት ፈቃደኛ አለመሆን፣
➤ የተቋማት አመራሮች እና ሠራተኞች መረጃዎችን በተጨባጭ መረጃ ላይ ተመሥርቶ አለመስጠት ... መሰል ዓይነት ችግሮች ነበሩ።
ሪፖርተር 👇
https://telegra.ph/Reporter-Newspaper-09-25
@tikvahethiopia
ለመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የሚደረግ የበጀት ድጎማ ከመደበኛው ሥራ ይልቅ ከዋናው ተልዕኮ ውጪ ለሆነ #የፖለቲካ_ሥራ እንደሚውል በፌዴራል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን የተጠና ጥናት ላይ መገለፁን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል።
ኮሚሽኑ ጥናቱን ያከናወነው በፌዴራል ደረጃ በሚገኙ የመንግሥትና የግል ዩኒቨርሲቲዎች ሲሆን የጥናቱ ትኩረት ሙስናና ብልሹ አሠራር በትምህርት ዘርፍ ላይ የሚያደርሰውን የሙስና ሥጋት ለመለየት መሆኑ ተጠቁሟል፡፡
ሪፖርተር ጋዜጣ ከምንጮቼ አገኘሁት ያለውና ኮሚሽኑ በተመረጡ 61 ተቋማት ላይ ያደረገው የጥናት ሪፖርት እንደሚያሳየው ፦
- በተቋማቱ፤ ከመምህራን ልማት እና ከአሠልጣኞች ምልመላ ጋር በተገናኘ፣ የዘመድና የፓርቲ አሠራር፣ እንዲሁም አድልኦና ጉቦ የመቀበል አዝማሚያ በስፋት ይስተዋላል።
- በመምህራንና ሠራተኞች አስተዳደር ክፍል ሕገወጥ ቅጥርና ዝውውር መኖር፣ መምህራን ተማሪዎችን ለይቶ ለመጥቀም የሚደረግ ዝንባሌ መኖር፣ ለመምህራን ቅጥር ውድድር ተፈልጎ እኩል ውጤት ሲመጣ፣ አንዱን በትውውቅ ብቻ የመምረጥ አሠራር እንደሚስተዋል ተገልጿል፡፡
- ከሐሰተኛ የትምህርት ሰነድ ጋር በተያያዘ የብቃት ማረጋገጥና ፈቃድ አሰጣጥ ላይ መሥፈርት ሳያሟሉ፣ ለተቋማት ፈቃድ መስጠት እና የፈቃድ ዕድሳት እንደሚከናወን ተግልጿል።
- መምህራንና በትምህርት አስተዳደር አመራር ላይ ያሉ ሠራተኞች ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃዎች እንደተገኘባቸው ፤ ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃዎችን ለማጣራት ሲሞከር ደግሞ ሠራተኞች ከሥራ ቀድመው የመልቀቅ እንቅስቃሴ እንዳለ ተገልጿል።
- በግል ኮሌጆች የሲኦሲ ምዘና ሳያልፉና ትምህርት አጠናቀው ሳይጨርሱ፣ እንዲሁም ፈጽሞ ያልተማሩ ሰዎች የትምህርት ማስረጃ አትሞ መስጠትና በኮሌጆች ሽያጭ የመፈጸም ድርጊት መኖሩን ሪፖርቱ ገልጿል።
- በኮሌጆችና በዩኒቨርሲቲዎች ሬጅስትራሮች ውስጥ የተማሪዎችን ውጤት የማሳሳትና የማጭበርበር ድርጊት እንዳለ ተጠቅሷሳ።
- በግል ትምህርት ተቋማት ውሳኔዎች የሚተላለፉት ለተቋማቸው መልካም ስም ቅድሚያ በመስጠት እንደሆነ፣ በመንግሥት ተቋማት ደግሞ ሰነድ ማዘጋጀት እንጂ ትግበራ ላይ እምብዛም እንደሌሉበት ተገልጿል።
- በተደረገው ጥናት በተቋማቸው ውስጥ የመልካም አስተዳደር ችግሮች አሉ ወይ ተብለው ከተጠየቁት ውስጥ 65 በመቶ የሚሆኑት " አዎ " የሚል መልስ መስጠታቸውን፣ 35 በመቶ የሚሆኑት " የለም " የሚል መልስ ሲሰጡ፣ በተመሳሳይ የሙስና ችግሮች መኖራቸውን 66 በመቶ መናገራቸውና 47 በመቶ ደግሞ ለሚቀርቡ ጥቆማዎች ከተቋማቱ መልስ እንደማይሰጥ ሪፖርቱ ያስረዳል፡፡
- በትምህርት ተቋማቱ የመምህራን በተደጋጋሚ ወደ ክፍል አለመግባት፣ ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ መስጠት፣ በአመራር የሚከናወን ስርቆት፣ ሕገወጥ ዝውውርና የደረጃ ዕድገት፣ ሕግና ደንብን ተከትሎ የማይከናወን ግዥ፣ የመረጃና ማስረጃ ማጭበርበር፣ ግልጽነት የሌለው አሠራር መብዛት፣ በሬጅስትራር የሚፈጸም ብልሹ አሠራር ተቋማቱን ለከባድ ሙስና አደጋ ጥሏቸዋል፡፡
- በግዥ ወቅት ለተቋም የማያስፈልግ ንብረት እንዲገዛ ተጨማሪ በጀት ማስያዝ፣ በጨረታ ወቅት የተወሰኑ ሰዎችን ብቻ እንዲጋብዝ አድርጎ ሰነድ ማዘጋጀት፣ ወቅቱንና ጥራቱን ያልጠበቀ ግንባታ እንዲከናወን ማድረግ፣ በሕንፃ ርክክብ ጥራቱን ያልጠበቀ ሕንፃ እንዲገነባ ማድረግና ያልተጠናቀቀ ሕንፃ መረከብ ተቋማቱን ለከባድ ሙስና እንዳጋለጣቸው ሪፖርቱ ያሳያል።
እንደ ምክንያት የተጠቀሱት ችግሮች ምንድናቸው ?
• የሠራተኞች ዝቅተኛ የደመወዝ ክፍያ ፣
• የተጠናከረ የቁጥጥር ሥርዓት አለመኖር፣
• የሞራል መላሸቅ፣
• የተጠያቂነት ማነስ፣
• የላላ የአመራር ቁጥጥርና ከፍተኛ የሆነ የበጀት ምደባ የሚሉት ይገኙበታል።
ጥናቱ በሚደረግበት ወቅት ምን ችግሮች አጋጠሙ ?
➤ የተቋማት አመራሮች በቦታው ላይ አለመገኘት፣
➤ ተቋማት መረጃ ለመሥጠት ፈቃደኛ አለመሆን፣
➤ የተቋማት አመራሮች እና ሠራተኞች መረጃዎችን በተጨባጭ መረጃ ላይ ተመሥርቶ አለመስጠት ... መሰል ዓይነት ችግሮች ነበሩ።
ሪፖርተር 👇
https://telegra.ph/Reporter-Newspaper-09-25
@tikvahethiopia