TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Tigray

በትግራይ ክልል የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ዛሬ መሰጠት ተጀምሯል።

ፈተናው በኦንላይን እና በወረቀት እየተሰጠ ነው።

በኢትዮጵያ ለመጀመርያ ጊዜ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና በኦንላይን መስጠት ተግባራዊ ተደርጓል።

በመቐለ ፣ አኽሱም ፣ ዓዲግራት ፣ ራያ ዩኒቨርሲቲዎች የሚሰጠውን ብሔራዊ ፈተና አጠቃላይ ከ54,000 በላይ ተማሪዎች ፈተናውን ይወስዳሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ፈተናው ከሌሎች ክልሎች ለምን ቀድሞ ጀመረ ?

ፈተናውን የሚወስዱት በቀድሞ ስርዓተ ትምህርት የተማሩና በ2013 እና በ2014 የትምህርት ዘመን መፈተን የነበረባቸው ተማሪዎች ናቸው።

በ2012 ዓ/ም የ10ኛ ክፍል የነበሩ (code 01) ብዛታቸው ከ31 ሺህ የሆኑ የማህበራዊ እና የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ከሀምሌ 2 እስከ 5 /2016 ዓ/ም ፈተና ወስደው ሀምሌ 6 እና 7 ወደ ቤታቸው ይመለሳሉ።

ከኮረም ፣ አላማጣ ፣ ዛታ ፣ ኦፍላ ፣ ራያ ጨርጨር ፣ ራያ ዓዘቦ፣ ማይፀብሪ፣ ላዕላይና ታሕታይ ፀለምቲ ሆኖው ትምህርታቸው ሲከታተሉ የነበሩ የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ከሀምሌ 3 አስከ 5 /2016 ዓ/ም ተፈትነው ሀምሌ 6 ና 7 ወደ ቤታቸው ይመለሳሉ። የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ሀምሌ 6 እና 7 ወደ ተመደቡበት ዩኒቨርስቲ ተጉዘው ከሀምሌ 9 እሰከ 11/2016 ዓ/ም ተፈትነው ሀምሌ 12 እና 13 ወደ ቤታቸው ይመለሳሉ።

በ2012 ዓ.ም የ11ኛ ክፍል የነበሩ ( Code 07) የሶሻልና የተፈጥሮ ሳይንስ ብዛታቸው ከ23 ሺህ በላይ የሆኑ ተማሪዎች ሀምሌ 6 እና 7 ወደ ዩኒቨርስቲ ገብተው ከሀምሌ 9 አስከ 12 ቀን 2016 ዓ/ም ፈተና ወስደው ሀምሌ 13 እና 14 ቀን 2016 ዓ/ም ወደ ቤታቸው ይመለሳሉ።

#TikvahEthiopia
#TigrayEducationBureau

@tikvahethiopia