TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59K photos
1.5K videos
211 files
4.08K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#KUWAIT

ኩዌት ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ የተገኘባቸውን ሰራተኞች " በህገወጥ መንገድ ያገኙትን ገንዘብ ሁሉ መመለስ አለባቸው " አለች።

" በሕግ ፊት አቆማቸዋለሁ " ብላለች።

ኩዌት፣ ከዚህ ቀደም ባደረገችው ሲቪል ሰራተኞች ያቀረቡትን የትምህርት ሰነድ የማጣራት ስራ የበርካታ ሰራተኞች መረጃ ሀሰተኛ ሆኖ ተገኝቷል።

ይህን ተከትሎ የሀገሪቱ መንግስት ጥፋተኛ ሆነው የተገኙ ሰራተኞች በህገወጥ መንገድ ያገኙትን የመንግስት ገንዘብ ሙሉ በሙሉ እንዲመልሱ ለማዘዝ ማቀዱን የኩዌት ጋዜጣ ዘግቧል።

በዚህም ሀሰተኛ ዲግሪ ፣ ማስተርስ ፣ ዶክትሬት ሆነ ሀሰተኛ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ሰነድ ያለው ሰራተኛ ስራውን ሙሉ በሙሉ መልቀቅና በሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃው በማታለል ከተቀጠረበት ጊዜ ጀምሮ ያገኘውን ገንዘብ ሙሉ በሙሉ መመለስ ይጠበቅበታል ተብሏል።

እነዚህ ሰዎች ገንዘቡን መመለስ ብቻ ሳይሆን ወደ ሕግ ፊት እንዲቀርቡ ተደርጎ በሕግ እንደሚጠየቁ ተነግሯል።

Via @tikvahethmagazine