TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AddisAbaba

የትግርኛ እና የአፋን ኦሮሞ የቋንቋ ትምህርት ሲከታተሉ የነበሩ አመራሮች የማጠቃለያ ፈተና እንደወሰዱ ተነገረ።

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፤ የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ለ5 ተከታታይ ወራት የትግርኛ እና አፋን ኦሮሞ ቋንቋ ትምህርት ሲሰጥ እንደቆየ ተነግሯል።

ትላንትና የማጠቃለያ ፈተና እንደተሰጠ ተገልጿል።

ከክ/ከተማው በተገኘ መረጃ ፥ ከክፍለ ከተማ እስከ ወረዳ የሚገኙ 371 አመራሮች በትግርኛ እና በአፋን ኦሮሞ የቋንቋ ትምህርት ለ5 ወራት ሲከታተሉ ቆይተዋል።

አመራሮቹ ከአፍ መፍቻ ቋንቋቸው ተጨማሪ ቋንቋ ተምረው ትላንት የማጠቃለያ ፈተና መውሰዳቸው ተገልጿል።

የቋንቋ ትምህርቱ ሲሰጥ የነበረው ከጋራ ጉሪ 1ኛ ደረጃ  ትምህርት ቤት ጋር በመቀናጀት እንደነበረ ተነግሯል።

ክ/ከተማው ፤ ብልፅግና ፓርቲ በሀገሪቱ አምስት የስራ ቋንቋዎች እንዲሆኑ ትኩረት በመስጠት እየሰራ ይገኛል ብሏል።

#AddisAbaba
#LamiKuraCommunication

@tikvahethiopia