#SouthEthiopia
" በእኛ ደረጃ የደረሰን ኦፊሻል መረጃ የለም። ቅሬታም የለም። ስለዚህ ዞኖቹን አናግራቸዋለሁ " - አቶ ወገኔ ብዙነህ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን ውስጥ በመዋቅር ጥያቄ ምክንያት " ወጣቶች በጅምላ ታስረው ይገኛሉ " ሲሉ የታሳሪ ቤተሰቦች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።
አንድ ለደኅንነታቸው ሲባል ሥማቸው እዳይጠቀስ የጠየቁ ምንጭ፤ በቅርቡ ተዋቀረ ወደተባለው ኮሬ ዞን (የቀድሞው አማሮ ልዩ ወረዳ) የተካለለ ቦታ ወደ ዳኖ ማዕቀፍ እንዲመለስ የሚል ጥያቄ እንደተነሳ፣ በዚህም ማኅበረሰቡ ላይ ቅሬታ በመፈጠሩ ወጣቶች መንገድ ዘግተው ስለነበር የሃይማኖት አባቶች በሰጧቸው ምክር መንገዱ እንደተክፈተ ገልጸዋል።
መንገድ ዘጉ የተባሉትም ለምን እንደዘጉ ከሃይማኖት አባቶች ጥያቄ ሲቀርብላቸው 'እኛ መንገድ ለመዝጋት ፈልገን ሳይሆን ባለሥልጣናት መጥተው እንዲያወያዩን ፈልገን ነው' በማለት መንገዱን እንዲከፈት ተደርጓል ብለዋል።
የሃይማኖት አባቶችም ሕዝቡ እንድታወያዩት ይፈልጋል ብለው ለባለሥልጣናቱ ጥያቄ ማቅረባቸውን አስረድተዋል።
በተያያዘም ጥቅምት 11/2016 ዓ.ም እንደተጻፈ የሚያስረዳው ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው የቅሬታ አቅራቢዎቹ ደብዳቤ፣ ከዳኖ ቀበሌ የወጣው መዋቅር እንዲመለስ በመጠየቃቸው ምክንያት አሉታዊ ተፅዕኖ እየደረሰባቸው መሆኑና ሰዎች በተለይም ወጣቶችን እያሳደዱ የማሰር ተግባር መፈፀሙን ያስረዳል።
የታሳሪ ቤተሰቦች ሕዝቡን #ማወያየት ሲገባ መንገድ ያልዘጉ ወጣቶችን መንገድ ዘግታችኋል ተብለው በጅምላ ታስረዋል ያሉ ሲሆን መንገድ ተዘጋ ቢባል እንኳ አሁን የታሰሩት ሰዎች መንገድ የዘጉ እንዳልሆኑና ያለጥፋታቸው ከአንድ ወር በላይ እንደታሰሩ፣ በቀጠሯቸው ጊዜም ዳኞች እንደማይገኙ አስረድተው፣ የሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ፍትህ እንዲያሰጡ ጠይቀዋል።
ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሁነቱን ያስረዱ ሌላኛው የዓይን እማኝ " ሦስት በአራት የሆነች ክፍል አለች እዚያ ውስጥ አንድ ላይ ነው ታራሚዎች የሚታጎሩት። እስር ቤቱ ውስጥ ላይ ደግሞ አያያዝ በጣም ያስጠላል ትኋን አለ፣ ቁንጫ አለ። በጣም አስቸጋሪ ነው። ይህ ብቻ አይደለም እዚያ ከታሰሩት ሰዎች መካከል ተመርጠው ጥቆማ ለመስጠት የሚቀመጡ አሉ፣ ተንኮል ካሰቡ ሲፈልጉ አሳልፈው ለፖሊስ ይሰጣሉ። የተቀጠረው ተረኛ ፓሊስ በአንድ ግለሰብ ጥቆማ ብቻ መጥቶ ይቀጠቅጣል " ሲሉ አስረድተዋል።
ወጣቶች በጅምላ ታስረዋል መባሉን በተመለከተ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገራቸው አንድ ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ የቀድሞ የአማሮ ልዩ ወረዳ ባለስልጣን ፣ በመዋቅር ጥያቄ ምክንያት ወጣቶች እደታሰሩና በቀጠሮ ቀንም ዳኞች ስለማይገኙ እስካሁን (ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ) ከእስር እንዳልተፈቱ ገልጸዋል።
የኮሬ ዞን አስተዳደር፣ ሰላምና ጸጥታ መምሪያ ባለድርሻ አካላት ስልክ ለማንሳት ፈቃደኛ ባይሆኑም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምላሽ ሰጥቷል።
የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ወገኔ ብዙነህ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፣ " በእኛ ደረጃ የደረሰን ኦፊሻል መረጃ የለም። ቅሬታም የለም። ስለዚህ ዞኖችን አናግራቸዋለሁ " ብለዋል።
አክለውም፣ ቅሬታ በቀረበበት መንገድ የታሰሩበት ሁኔታ በፍጹም ትክክል እንዳልሆነ ገልጸው፣ " እንዲህ አይነት ችግሮችን ቢያንስ የመዋቅር ዞኑ አልፈታ ካለ እኛ ጋ ማድረስ ነበረባቸው አሰራሩም እንደዛ ነው። እኛ ቼክ እናደርጋለን " የሚል ምላሽ ሰጥዋል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በበኩሉ በጉዳዩ ዙሪያ ክትትል እንደተደረገና የእስር ቤት አያያዝ ሁኔታው የሚገለጸው ኮሚሽኑ በሚያወጣው ሪፓርት እንደሆነ አስረድቷል።
@tikvahethiopia
" በእኛ ደረጃ የደረሰን ኦፊሻል መረጃ የለም። ቅሬታም የለም። ስለዚህ ዞኖቹን አናግራቸዋለሁ " - አቶ ወገኔ ብዙነህ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን ውስጥ በመዋቅር ጥያቄ ምክንያት " ወጣቶች በጅምላ ታስረው ይገኛሉ " ሲሉ የታሳሪ ቤተሰቦች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።
አንድ ለደኅንነታቸው ሲባል ሥማቸው እዳይጠቀስ የጠየቁ ምንጭ፤ በቅርቡ ተዋቀረ ወደተባለው ኮሬ ዞን (የቀድሞው አማሮ ልዩ ወረዳ) የተካለለ ቦታ ወደ ዳኖ ማዕቀፍ እንዲመለስ የሚል ጥያቄ እንደተነሳ፣ በዚህም ማኅበረሰቡ ላይ ቅሬታ በመፈጠሩ ወጣቶች መንገድ ዘግተው ስለነበር የሃይማኖት አባቶች በሰጧቸው ምክር መንገዱ እንደተክፈተ ገልጸዋል።
መንገድ ዘጉ የተባሉትም ለምን እንደዘጉ ከሃይማኖት አባቶች ጥያቄ ሲቀርብላቸው 'እኛ መንገድ ለመዝጋት ፈልገን ሳይሆን ባለሥልጣናት መጥተው እንዲያወያዩን ፈልገን ነው' በማለት መንገዱን እንዲከፈት ተደርጓል ብለዋል።
የሃይማኖት አባቶችም ሕዝቡ እንድታወያዩት ይፈልጋል ብለው ለባለሥልጣናቱ ጥያቄ ማቅረባቸውን አስረድተዋል።
በተያያዘም ጥቅምት 11/2016 ዓ.ም እንደተጻፈ የሚያስረዳው ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው የቅሬታ አቅራቢዎቹ ደብዳቤ፣ ከዳኖ ቀበሌ የወጣው መዋቅር እንዲመለስ በመጠየቃቸው ምክንያት አሉታዊ ተፅዕኖ እየደረሰባቸው መሆኑና ሰዎች በተለይም ወጣቶችን እያሳደዱ የማሰር ተግባር መፈፀሙን ያስረዳል።
የታሳሪ ቤተሰቦች ሕዝቡን #ማወያየት ሲገባ መንገድ ያልዘጉ ወጣቶችን መንገድ ዘግታችኋል ተብለው በጅምላ ታስረዋል ያሉ ሲሆን መንገድ ተዘጋ ቢባል እንኳ አሁን የታሰሩት ሰዎች መንገድ የዘጉ እንዳልሆኑና ያለጥፋታቸው ከአንድ ወር በላይ እንደታሰሩ፣ በቀጠሯቸው ጊዜም ዳኞች እንደማይገኙ አስረድተው፣ የሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ፍትህ እንዲያሰጡ ጠይቀዋል።
ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሁነቱን ያስረዱ ሌላኛው የዓይን እማኝ " ሦስት በአራት የሆነች ክፍል አለች እዚያ ውስጥ አንድ ላይ ነው ታራሚዎች የሚታጎሩት። እስር ቤቱ ውስጥ ላይ ደግሞ አያያዝ በጣም ያስጠላል ትኋን አለ፣ ቁንጫ አለ። በጣም አስቸጋሪ ነው። ይህ ብቻ አይደለም እዚያ ከታሰሩት ሰዎች መካከል ተመርጠው ጥቆማ ለመስጠት የሚቀመጡ አሉ፣ ተንኮል ካሰቡ ሲፈልጉ አሳልፈው ለፖሊስ ይሰጣሉ። የተቀጠረው ተረኛ ፓሊስ በአንድ ግለሰብ ጥቆማ ብቻ መጥቶ ይቀጠቅጣል " ሲሉ አስረድተዋል።
ወጣቶች በጅምላ ታስረዋል መባሉን በተመለከተ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገራቸው አንድ ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ የቀድሞ የአማሮ ልዩ ወረዳ ባለስልጣን ፣ በመዋቅር ጥያቄ ምክንያት ወጣቶች እደታሰሩና በቀጠሮ ቀንም ዳኞች ስለማይገኙ እስካሁን (ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ) ከእስር እንዳልተፈቱ ገልጸዋል።
የኮሬ ዞን አስተዳደር፣ ሰላምና ጸጥታ መምሪያ ባለድርሻ አካላት ስልክ ለማንሳት ፈቃደኛ ባይሆኑም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምላሽ ሰጥቷል።
የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ወገኔ ብዙነህ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፣ " በእኛ ደረጃ የደረሰን ኦፊሻል መረጃ የለም። ቅሬታም የለም። ስለዚህ ዞኖችን አናግራቸዋለሁ " ብለዋል።
አክለውም፣ ቅሬታ በቀረበበት መንገድ የታሰሩበት ሁኔታ በፍጹም ትክክል እንዳልሆነ ገልጸው፣ " እንዲህ አይነት ችግሮችን ቢያንስ የመዋቅር ዞኑ አልፈታ ካለ እኛ ጋ ማድረስ ነበረባቸው አሰራሩም እንደዛ ነው። እኛ ቼክ እናደርጋለን " የሚል ምላሽ ሰጥዋል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በበኩሉ በጉዳዩ ዙሪያ ክትትል እንደተደረገና የእስር ቤት አያያዝ ሁኔታው የሚገለጸው ኮሚሽኑ በሚያወጣው ሪፓርት እንደሆነ አስረድቷል።
@tikvahethiopia