TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Tigray
" ትግራይ ከተደገሰላት የባሰ አዘቅትና አዙሪት የምናድንበት ጊዜ አሁንና አሁን ብቻ ነው " አለ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው የህወሓት ቡድን።
አቶ ጌታቸው የሚመሩት የህወሓት ቡድን ባወጣው መግለጫ "ልዩነቶቻችን በይደር በማቆየት ቂምና ቁርሾ ቀርፈን እኔነትንና ጠቅላይነት አስተሳሰብ ከውስጣችን በማስወገድ ትግራይ እናድናት " ብሏል።
ትግራይ ከገባችበት ቀውስና አጣብቂኝ " ያድናታል ብዬ አምኜበታለሁ " ያለውን የመፍትሄ ሃሳብ ለውይይት ማቅረቡ ያስታወቀው ቡድኑ ከቀረበው የተሻለ ክልሉን ማዳን የሚችል የመፍትሄ ሃሳብ ካለ ለማዳመጥ ዝግጁ መሆኑ ገልጿል።
ደብረፅዮን (ዶ/ር) የሚመሩትን ህወሓት በግልፅና ጠንካራ ቃላት የተቸም ሲሆን ጊዚያዊ አስተዳደሩ ለአንድ ዓመት መራዘሙ በመቀበል የሚከተሉት ሦስት የመፍትሄ ሃሳቦች አቅርበዋል :-
- ጊዚያዊ አስተዳደሩ ሁሉም አመለካከቶች በማቀፍ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ማእከል በማድረግ መዋቅሩ ተጠናክሮ በአስቸኳይ መቋቋም አለበት።
- ዕድሜውን የተራዘመው ጊዚያዊ አስተዳደር ማቋቋም የሚያስችል ሁሉም አመለካከቶችና የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት አፈራራሚዎች ያካተተ ፓለቲካዊ ውይይት ይቅደም።
- የትግራይ ሰራዊት ታጣቂዎች ወደ ማረፍያ ካምፓቸው ተመልሰው የሰላምና የፀጥታ ስራ ሙሉ በሙሉ በህዝባዊ ፓሊስ ይተካ ፤ የጊዚያዊ አስተዳደሩ መዋቅር እስከ ቀበሌ ድረስ ህዝብ ነፃ ሆኖ በመረጣቸው አስተዳዳሪዎች እንዲመራ ፣ ተግባሩ በአንድ ወር ውስጥ እንዲከናወን።
... ብሏል።
ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመሩት የህወሓት ቡድን ከደብረፅዮን (ዶ/ር) ህወሓት ቡድን ጋር ለመወያየት ዝግጁ መሆኑ ባወጣው ወቅታዊ መግለጫ ይፋ አድርጓል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
" ትግራይ ከተደገሰላት የባሰ አዘቅትና አዙሪት የምናድንበት ጊዜ አሁንና አሁን ብቻ ነው " አለ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው የህወሓት ቡድን።
አቶ ጌታቸው የሚመሩት የህወሓት ቡድን ባወጣው መግለጫ "ልዩነቶቻችን በይደር በማቆየት ቂምና ቁርሾ ቀርፈን እኔነትንና ጠቅላይነት አስተሳሰብ ከውስጣችን በማስወገድ ትግራይ እናድናት " ብሏል።
ትግራይ ከገባችበት ቀውስና አጣብቂኝ " ያድናታል ብዬ አምኜበታለሁ " ያለውን የመፍትሄ ሃሳብ ለውይይት ማቅረቡ ያስታወቀው ቡድኑ ከቀረበው የተሻለ ክልሉን ማዳን የሚችል የመፍትሄ ሃሳብ ካለ ለማዳመጥ ዝግጁ መሆኑ ገልጿል።
ደብረፅዮን (ዶ/ር) የሚመሩትን ህወሓት በግልፅና ጠንካራ ቃላት የተቸም ሲሆን ጊዚያዊ አስተዳደሩ ለአንድ ዓመት መራዘሙ በመቀበል የሚከተሉት ሦስት የመፍትሄ ሃሳቦች አቅርበዋል :-
- ጊዚያዊ አስተዳደሩ ሁሉም አመለካከቶች በማቀፍ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ማእከል በማድረግ መዋቅሩ ተጠናክሮ በአስቸኳይ መቋቋም አለበት።
- ዕድሜውን የተራዘመው ጊዚያዊ አስተዳደር ማቋቋም የሚያስችል ሁሉም አመለካከቶችና የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት አፈራራሚዎች ያካተተ ፓለቲካዊ ውይይት ይቅደም።
- የትግራይ ሰራዊት ታጣቂዎች ወደ ማረፍያ ካምፓቸው ተመልሰው የሰላምና የፀጥታ ስራ ሙሉ በሙሉ በህዝባዊ ፓሊስ ይተካ ፤ የጊዚያዊ አስተዳደሩ መዋቅር እስከ ቀበሌ ድረስ ህዝብ ነፃ ሆኖ በመረጣቸው አስተዳዳሪዎች እንዲመራ ፣ ተግባሩ በአንድ ወር ውስጥ እንዲከናወን።
... ብሏል።
ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመሩት የህወሓት ቡድን ከደብረፅዮን (ዶ/ር) ህወሓት ቡድን ጋር ለመወያየት ዝግጁ መሆኑ ባወጣው ወቅታዊ መግለጫ ይፋ አድርጓል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
🕊479❤166👏63😡56🤔25😱17😢14🙏13😭13💔12🥰7
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Tigray
" ሦስት ሳምንት ሳይሞላው የሦስት ወር ደመወዝ በሃሰት ማህተም በመጠቀም ከድርጅቱ የብር ካዝና አለአግባብ መመዝበሩ አረጋግጫለሁ " - ጋዜጠኛ ሓለፎም ንርአ
➡️ " ጉዳዩ በህግ የተያዘ ነው " - አቶ ዘመንፈስቅዱስ ፍስሃ
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ መጋቢት 2/2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:30 አከባቢ በ136ኛው የንጉስ ነገስት ሃፀይ ዮሃንስ መታሰብያ ዝግጅት ተገኝተው መልእክት ካስተላለፉ በኋላ በዚያው ወደ አሉላ አባነጋ የአውሮፕላን ማረፍያ በመሄድ ወደ አዲስ አበባ ከተጓዙ 22 ቀናት ተቆጥረዋል።
አዲስ አበባ ሆነው የፕሬዜዳንትነት መጠሪያቸው ቢጠቀሙም ላለፉት 22 ቀናት መቐለ በሚገኘው ቢሯቸው ገብተው የከወኑት አንዳች የህዝብ አገልግሎት የለም።
ፕሬዜዳንቱ " ለስራ " በሚል ምክንያት ከመቐለ ትግራይ ከወጡ በኋላ በክልሉ ያሉት ሚድያዎች በምን ሁኔታ ላይ ይገኛሉ ?
የዚህ መረጃ ዋና የምልከታና የትኩረት ነጥብ ይኸው ጉዳይ ነው።
ባለፉት ሦስት ሳምንታት በጊዚያዊ አስተዳደሩ ስር ከነበሩት ሦስት ሚድያዎች ፦
- የትግራይ ቴሌቪዥንና ሬድዮ
- የድምፂ ወያነ ቴሌቪዥንናሬድዮ
- 104.4 የመቐለ ኤፍ ኤም ለውጦች ተከስተዋል።
ከለውጦቹ አንዱ የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ወደ አዲስ አበባ በመሄድ ለሚድያዎች የሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዲሁም መጋቢት 22 በግላቸው የማህበራዊ ትስስር ገፅ ያሰራጩት፣ መጋቢት 23/2017 ዓ.ም በእሳቸው ስም የሚመራ ህወሓት ያወጣውን መግለጫ በሦስቱ ሚድያዎች አልተሰናገደም።
በድምፂ ወያነ ፣ ትግራይ ቴሌቪዥንና ሬድዮ በግልፅ የተደረገ የአመራር ለውጥ ባይኖርም የትግራይ ቴሌቪዥን ስራ አስኪያጅ ተሻለ በቀለ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ከመቐለ መወጣታቸውን ተከትለው ወጥተው ዛሬ መጋቢት 24/2017 ዓ.ም ወደ ቢሯቸው መመለሳቸው ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ለማረጋገጥ ችሏል።
ለሦስት ሳምንታት ያህል ከመቐለ የመውጣታቸው ምክንያት በትግራይ ከተፈጠረው ቀውስ ተያይዥነት ይኑረው አይኑረው ቲክቫህ ኢትዮጵያ ማረጋገጥ አልቻለም።
በቀድሞ ኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን የሚድያ ፍቃድ አግኝቶ በመቐለ ከተማ አስተዳደር ስር እንደሚተዳደር የሚነገርለት 104.4 የመቐለ ኤፍ ኤም ደግሞ " እኔ ነኝ ስራ አስኪያጅ " የሚል ክርክር ከተነሳበት መቆየቱ ይታወቃል።
የፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ከመቐለ ከተማ መውጣት ተከትሎ " በመቐለ ከተማ አስተዳደር ተሹሚያለሁ " በሚል የይገባኛል ጥያቄ በሚድያዎች ጭምር በግልፅ ሲያቀርቡ የቆዩት ዘመንፈስ ቅዱስ ፍስሃ የቆዩትን የኤፍ ኤም ጣብያው ስራ አስኪያጅ ሓለፎም ንርአ በመግፋት ጣቢያውን ተቆጣጥረውታል።
" አካሄዱ ህገ-ወጥ ነው " በማለት የታቀወሙትና " አሁንም እኔ ነኝ ህጋዊ ስራ አስኪያጅ " በማለት የሚሞጉቱት ጋዜጠኛ ሓለፎም ንርአ የኤፍ ኤም ጣብያው የባንክ ሂሳብ እንዲዘጋ ለኢትዮጵያ ፌደራል ፓሊስ መስራት ቤት የድርጅቱን ማህተም በመጠቀም ፅፈዋል።
መጋቢት 16/2017 ዓ.ም በፃፉት " የ ይታገድልኝ " ጥያቄ እሳቸው የሬድዮ ጣብያው ህጋዊ ስራ አስኪያጅ መሆናቸው በመጥቀስ የሚድያው ፈራሚዎች እንዳይቀየሩ በማሳሰብ ከእውቅናቸው ውጪ ማንኛውም የገንዘብ እንቅስቃሴ እንዳይኖር ይታገድልኝ ብለዋል።
ስራ አስኪያጁ የእገዳ ደብዳቤ ከመፃፉ በኋላ መጋቢት 23/2017 ዓ.ም በማህበራዊ የትስስር ገፃቸው ባጋሩት ሰፊ ሃተታ ፤ ሬድዮ ጣብያውን " በህገ-ወጥ መንገድ ተቆጣጥሮታል " ሲሉ የከሰሱት ዘመንፈስ ቅዱስ ፍስሃ " ሦስት ሳምንት ሳይሞላው የሦስት ወር ደመወዝ በሃሰት ማህተም በመጠቀም ከድርጅቱ የብር ካዝና አለአግባብ መመዝበሩ አረጋግጫለሁ " ብለዋል። የብር መጠኑ ግን በይፋ አላስቀመጡም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ስለ ቀረበባቸው ክስ ማብራርያ እንዲሰጡ ወደ አቶ ዘመንፈስቅዱስ ፍስሃ በተደጋጋሚ ደውሎ ነበር።
" ጉዳዩ በህግ የተያዘ ነው " ከሚል አጭር ምላሽ ውጪ ዘርዘር ያለ በቂ ማብራርያ ሊሰጡ አልፈገሉም።
በአጠቃላይ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት ከመቐለ ከወጡበት ጊዜ አንስቶ በክልሉ በሚገኙ ሚዲያዎች ግልጽ የሆኑ ለውጦች ታይተዋል።
በፕሪቶሪያ ስምምነት መሰረት ትግራይ ክልልን ለመምራት የተቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር ቆይታው መጋቢት 5/2017 አብቅቷል። ቆይታው ለአንድ አመት እንዲራዘም የሚፈቅድ አዋጅም ፀድቋል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
" ሦስት ሳምንት ሳይሞላው የሦስት ወር ደመወዝ በሃሰት ማህተም በመጠቀም ከድርጅቱ የብር ካዝና አለአግባብ መመዝበሩ አረጋግጫለሁ " - ጋዜጠኛ ሓለፎም ንርአ
➡️ " ጉዳዩ በህግ የተያዘ ነው " - አቶ ዘመንፈስቅዱስ ፍስሃ
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ መጋቢት 2/2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:30 አከባቢ በ136ኛው የንጉስ ነገስት ሃፀይ ዮሃንስ መታሰብያ ዝግጅት ተገኝተው መልእክት ካስተላለፉ በኋላ በዚያው ወደ አሉላ አባነጋ የአውሮፕላን ማረፍያ በመሄድ ወደ አዲስ አበባ ከተጓዙ 22 ቀናት ተቆጥረዋል።
አዲስ አበባ ሆነው የፕሬዜዳንትነት መጠሪያቸው ቢጠቀሙም ላለፉት 22 ቀናት መቐለ በሚገኘው ቢሯቸው ገብተው የከወኑት አንዳች የህዝብ አገልግሎት የለም።
ፕሬዜዳንቱ " ለስራ " በሚል ምክንያት ከመቐለ ትግራይ ከወጡ በኋላ በክልሉ ያሉት ሚድያዎች በምን ሁኔታ ላይ ይገኛሉ ?
የዚህ መረጃ ዋና የምልከታና የትኩረት ነጥብ ይኸው ጉዳይ ነው።
ባለፉት ሦስት ሳምንታት በጊዚያዊ አስተዳደሩ ስር ከነበሩት ሦስት ሚድያዎች ፦
- የትግራይ ቴሌቪዥንና ሬድዮ
- የድምፂ ወያነ ቴሌቪዥንናሬድዮ
- 104.4 የመቐለ ኤፍ ኤም ለውጦች ተከስተዋል።
ከለውጦቹ አንዱ የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ወደ አዲስ አበባ በመሄድ ለሚድያዎች የሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዲሁም መጋቢት 22 በግላቸው የማህበራዊ ትስስር ገፅ ያሰራጩት፣ መጋቢት 23/2017 ዓ.ም በእሳቸው ስም የሚመራ ህወሓት ያወጣውን መግለጫ በሦስቱ ሚድያዎች አልተሰናገደም።
በድምፂ ወያነ ፣ ትግራይ ቴሌቪዥንና ሬድዮ በግልፅ የተደረገ የአመራር ለውጥ ባይኖርም የትግራይ ቴሌቪዥን ስራ አስኪያጅ ተሻለ በቀለ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ከመቐለ መወጣታቸውን ተከትለው ወጥተው ዛሬ መጋቢት 24/2017 ዓ.ም ወደ ቢሯቸው መመለሳቸው ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ለማረጋገጥ ችሏል።
ለሦስት ሳምንታት ያህል ከመቐለ የመውጣታቸው ምክንያት በትግራይ ከተፈጠረው ቀውስ ተያይዥነት ይኑረው አይኑረው ቲክቫህ ኢትዮጵያ ማረጋገጥ አልቻለም።
በቀድሞ ኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን የሚድያ ፍቃድ አግኝቶ በመቐለ ከተማ አስተዳደር ስር እንደሚተዳደር የሚነገርለት 104.4 የመቐለ ኤፍ ኤም ደግሞ " እኔ ነኝ ስራ አስኪያጅ " የሚል ክርክር ከተነሳበት መቆየቱ ይታወቃል።
የፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ከመቐለ ከተማ መውጣት ተከትሎ " በመቐለ ከተማ አስተዳደር ተሹሚያለሁ " በሚል የይገባኛል ጥያቄ በሚድያዎች ጭምር በግልፅ ሲያቀርቡ የቆዩት ዘመንፈስ ቅዱስ ፍስሃ የቆዩትን የኤፍ ኤም ጣብያው ስራ አስኪያጅ ሓለፎም ንርአ በመግፋት ጣቢያውን ተቆጣጥረውታል።
" አካሄዱ ህገ-ወጥ ነው " በማለት የታቀወሙትና " አሁንም እኔ ነኝ ህጋዊ ስራ አስኪያጅ " በማለት የሚሞጉቱት ጋዜጠኛ ሓለፎም ንርአ የኤፍ ኤም ጣብያው የባንክ ሂሳብ እንዲዘጋ ለኢትዮጵያ ፌደራል ፓሊስ መስራት ቤት የድርጅቱን ማህተም በመጠቀም ፅፈዋል።
መጋቢት 16/2017 ዓ.ም በፃፉት " የ ይታገድልኝ " ጥያቄ እሳቸው የሬድዮ ጣብያው ህጋዊ ስራ አስኪያጅ መሆናቸው በመጥቀስ የሚድያው ፈራሚዎች እንዳይቀየሩ በማሳሰብ ከእውቅናቸው ውጪ ማንኛውም የገንዘብ እንቅስቃሴ እንዳይኖር ይታገድልኝ ብለዋል።
ስራ አስኪያጁ የእገዳ ደብዳቤ ከመፃፉ በኋላ መጋቢት 23/2017 ዓ.ም በማህበራዊ የትስስር ገፃቸው ባጋሩት ሰፊ ሃተታ ፤ ሬድዮ ጣብያውን " በህገ-ወጥ መንገድ ተቆጣጥሮታል " ሲሉ የከሰሱት ዘመንፈስ ቅዱስ ፍስሃ " ሦስት ሳምንት ሳይሞላው የሦስት ወር ደመወዝ በሃሰት ማህተም በመጠቀም ከድርጅቱ የብር ካዝና አለአግባብ መመዝበሩ አረጋግጫለሁ " ብለዋል። የብር መጠኑ ግን በይፋ አላስቀመጡም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ስለ ቀረበባቸው ክስ ማብራርያ እንዲሰጡ ወደ አቶ ዘመንፈስቅዱስ ፍስሃ በተደጋጋሚ ደውሎ ነበር።
" ጉዳዩ በህግ የተያዘ ነው " ከሚል አጭር ምላሽ ውጪ ዘርዘር ያለ በቂ ማብራርያ ሊሰጡ አልፈገሉም።
በአጠቃላይ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት ከመቐለ ከወጡበት ጊዜ አንስቶ በክልሉ በሚገኙ ሚዲያዎች ግልጽ የሆኑ ለውጦች ታይተዋል።
በፕሪቶሪያ ስምምነት መሰረት ትግራይ ክልልን ለመምራት የተቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር ቆይታው መጋቢት 5/2017 አብቅቷል። ቆይታው ለአንድ አመት እንዲራዘም የሚፈቅድ አዋጅም ፀድቋል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
❤176🤔58🕊33😭21😱20😢12👏10🙏8🥰7
#Tigray : በሴቶች ላይ የሚፈፀሙ ከባባድ ፆታዊ ጥቃቶችና ሞት የሚፈፅሙ ተከሳሽና ወንጀለኞች ጉዳዮች በሚከታተሉና ህጋዊ ውሳኔ በሚሰጡ ዳኞች ላይ በተለያየ መንገድ የሚገለፅ ጫና እየደረሰ ነው ሲል የትግራይ የዳኞች ማህበር አማረረ።
ማህበሩ ከባባድ ወንጀሎች ለሚከታተሉና ህጋዊ ውሳኔ ለሚሰጡ ዳኞች አስፈላጊውን የደህንነትና የፀጥታ ከለላ እንዲሰጥ አበክሮ ጠይቀዋል።
ማህበሩ በላከው መግለጫ ፤ በሴቶች ላይ የሚፈፀሙ ከባባድ ፆታዊ ጥቃቶችና የሞት ጉዳዮች የሚከታተሉ ውሳኔ የሚሰጡ ዳኞች ስራቸውን ነፃና ገለልተኛ ሆነው ለመከወን እጅግ ተቸግረዋል ብሏል።
" ዳኞቹ ስራቸውን ተረጋግተው በሰከነ የህግ አካሄድ እንዳይመለከቱ በተለያዩ መንገዶች ጫና እየደረሰባቸው ነው ስለሆነም ላለባቸው የደህንነታቸው አደጋ በቂ ከለላ በማጣታቸው ምክንያት ስራውን ከማቆማቸው በፊት የክልሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከሚመለከታቸው የፀጥታ አካላት በመመካከር ችግሩ በአፋጣኝ መፍታት አለበት " ሲል አሳስቧል።
" ከጦርነቱ በኋላ የትግራይ ዳኞቸ በከፍተኛ ፓለቲካዊ ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ቅርቃር ውስጥ ሆነው በማገልገል ላይ ይገኛሉ ጥያቄያቸው ይመለስላቸው " ሲል ጥሪ አቅርቧል።
በፌደራል እና በሌሎች ክልሎች የሚገኙ ዳኞች የሚያገኙት የደመወዝ ጭማሪና ጥቅማ ጥቅም የክልሉ ዳኞች እንደተነፈጉ ገልጾ የክልሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በሌሎች ክልሎች እየተተገበረ ያለውን የጥቅማ ጥቅም አሰራር ለመመለስ " በጥናት ላይ ነኝ " በማለት ከአንድ ዓመት በላይ ማስቆጠሩ ልክ አይደለም ሲል ወቅሷል።
የክልሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የአገሪቱ ህግና የትግራይ ነባራዊ ሁኔታ ከግምት ውስጥ በማስገባት የዳኞች የጥቅማጥቅም ፣ የደመወዝ ፣ የደህንነትና መሰል ጥያቄዎች እንዲመልስ ማህበሩ ጥሪ አቅርቧል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
ማህበሩ ከባባድ ወንጀሎች ለሚከታተሉና ህጋዊ ውሳኔ ለሚሰጡ ዳኞች አስፈላጊውን የደህንነትና የፀጥታ ከለላ እንዲሰጥ አበክሮ ጠይቀዋል።
ማህበሩ በላከው መግለጫ ፤ በሴቶች ላይ የሚፈፀሙ ከባባድ ፆታዊ ጥቃቶችና የሞት ጉዳዮች የሚከታተሉ ውሳኔ የሚሰጡ ዳኞች ስራቸውን ነፃና ገለልተኛ ሆነው ለመከወን እጅግ ተቸግረዋል ብሏል።
" ዳኞቹ ስራቸውን ተረጋግተው በሰከነ የህግ አካሄድ እንዳይመለከቱ በተለያዩ መንገዶች ጫና እየደረሰባቸው ነው ስለሆነም ላለባቸው የደህንነታቸው አደጋ በቂ ከለላ በማጣታቸው ምክንያት ስራውን ከማቆማቸው በፊት የክልሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከሚመለከታቸው የፀጥታ አካላት በመመካከር ችግሩ በአፋጣኝ መፍታት አለበት " ሲል አሳስቧል።
" ከጦርነቱ በኋላ የትግራይ ዳኞቸ በከፍተኛ ፓለቲካዊ ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ቅርቃር ውስጥ ሆነው በማገልገል ላይ ይገኛሉ ጥያቄያቸው ይመለስላቸው " ሲል ጥሪ አቅርቧል።
በፌደራል እና በሌሎች ክልሎች የሚገኙ ዳኞች የሚያገኙት የደመወዝ ጭማሪና ጥቅማ ጥቅም የክልሉ ዳኞች እንደተነፈጉ ገልጾ የክልሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በሌሎች ክልሎች እየተተገበረ ያለውን የጥቅማ ጥቅም አሰራር ለመመለስ " በጥናት ላይ ነኝ " በማለት ከአንድ ዓመት በላይ ማስቆጠሩ ልክ አይደለም ሲል ወቅሷል።
የክልሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የአገሪቱ ህግና የትግራይ ነባራዊ ሁኔታ ከግምት ውስጥ በማስገባት የዳኞች የጥቅማጥቅም ፣ የደመወዝ ፣ የደህንነትና መሰል ጥያቄዎች እንዲመልስ ማህበሩ ጥሪ አቅርቧል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
❤140😭82🤔18🙏15🕊13😡13🥰11👏6😱6😢6
#Tigray
የትግራይ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የመምህራን የ17 ወራት ውዙፍ ደመወዝ እንዲከፈል ወስኗን።
በትግራይ መምህራን ማህበር ጠበቆች የቀረበውና በጦርነቱ ጊዜ ያልተከፈለ የ17 ወራት የመምህራን ደመወዝ ሲመለከት የቆየው ከፍተኛ ፍርድ ቤቱ ዛሬ ሚያዝያ 7/2017 ዓ.ም ባዋለው ችሎት ውሳኔውን ሰጥቷል።
ተከሳሾቹ የትግራይ ትምህርት ቢሮ ፣ የፋይናንስ ቢሮ ፣ የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር እንዲሁም የገንዘብ/ የፋይናንስ ሚንስቴር ሲሆኑ ጉዳያቸው በሌሉበት ሲታይ ቆይቷል።
ፍርድ ቤቱ የቀረበለት ክስ መርምሮ የመምህራኑ የ17 ወራት ውዙፍ ደመወዝ እንዲከፈል ወስኖ ፋይሉ ወደ መዝገብ ቤት መልሶታል።
የፍርድ ቤቱ ውሳኔ እንደሚቀበሉትና እንዳረካቸው የተናገሩት አስተያየት ሰጪ መምህራን ውሳኔው ቶሎ በመተግበር በከፋ ሁኔታ የሚመገኙ መምህራን መታደግ ይገባል ብለዋል።
ተከሳሾቹ ውሳኔው በማስመልከት እስካሁን ያሉት ነገር የለም።
መምህራን ያካተተ የ17 ወራት ያልተከፈለ የመንግስት ሰራተኞች ውዙፍ ደመወዝ የመከፈል ጥያቄ ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ማግስት የጀመረ ነው።
በቀድሞ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ጊዚያዊ አስተዳደር ጉዳዩ በፍርድ ቤት እንዳይታይ የሚከልክል መምሪያ እስከማውጣት ደርሶ ነበር።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
ፎቶ፦ Tigrai TV
@tikvahethiopia
የትግራይ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የመምህራን የ17 ወራት ውዙፍ ደመወዝ እንዲከፈል ወስኗን።
በትግራይ መምህራን ማህበር ጠበቆች የቀረበውና በጦርነቱ ጊዜ ያልተከፈለ የ17 ወራት የመምህራን ደመወዝ ሲመለከት የቆየው ከፍተኛ ፍርድ ቤቱ ዛሬ ሚያዝያ 7/2017 ዓ.ም ባዋለው ችሎት ውሳኔውን ሰጥቷል።
ተከሳሾቹ የትግራይ ትምህርት ቢሮ ፣ የፋይናንስ ቢሮ ፣ የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር እንዲሁም የገንዘብ/ የፋይናንስ ሚንስቴር ሲሆኑ ጉዳያቸው በሌሉበት ሲታይ ቆይቷል።
ፍርድ ቤቱ የቀረበለት ክስ መርምሮ የመምህራኑ የ17 ወራት ውዙፍ ደመወዝ እንዲከፈል ወስኖ ፋይሉ ወደ መዝገብ ቤት መልሶታል።
የፍርድ ቤቱ ውሳኔ እንደሚቀበሉትና እንዳረካቸው የተናገሩት አስተያየት ሰጪ መምህራን ውሳኔው ቶሎ በመተግበር በከፋ ሁኔታ የሚመገኙ መምህራን መታደግ ይገባል ብለዋል።
ተከሳሾቹ ውሳኔው በማስመልከት እስካሁን ያሉት ነገር የለም።
መምህራን ያካተተ የ17 ወራት ያልተከፈለ የመንግስት ሰራተኞች ውዙፍ ደመወዝ የመከፈል ጥያቄ ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ማግስት የጀመረ ነው።
በቀድሞ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ጊዚያዊ አስተዳደር ጉዳዩ በፍርድ ቤት እንዳይታይ የሚከልክል መምሪያ እስከማውጣት ደርሶ ነበር።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
ፎቶ፦ Tigrai TV
@tikvahethiopia
👏929❤123🙏50🕊31😡21😭20🥰15🤔15😱14😢11
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Tigray
በቀድሞ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት በሦስት ጀነራሎች ላይ የተቀመጠው ጊዚያዊ እግድ በአዲሱ ፕሬዜዳንት ተሽሯል።
በአራተኛው ጀነራል የተወሰነው ከሃላፊነት የማንሳት ውሳኔም ተሰርዟል።
የቀድሞ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ፦
- በጀነራል ምግበይ ሃይለ
- በጀነራል ዮውሃንስ ወ/ጊዮርጊስ
- በጀነራል ማሾ በየነ መጋቢት 1/2017 ዓ.ም ጊዚያዊ የእግድ ደብዳቤ መፃፋቸው ይታወሳል።
በተመሳሳይ የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሃላፊ ጀነራል ፍስሃ ኪዳኑ ፈንታ በአቶ ጌታቸው ረዳ በተፃፈ ደብዳቤ ከስራ ገበታቸው እንዲነሱ መወሰኑ ይታወሳል።
በቀድሞ ፕሬዜዳንት የተቀመጠው ጊዚያዊ እግድና ከስራ የማሰናበት ውሳኔ በአዲሱ የጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ሌ/ጀነራል ታደሰ ወረደ ሙሉ በሙሉ ተሰርዟል።
አዲሱ ፕሬዜዳንት ሚያዝያ 9/2017 ዓ.ም በፃፉት ደብዳቤ ጊዚያዊ እግዱና የስራ ስንብቱ ከመሰረዛቸው በተጨማሪ ፤ የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሃላፊው በስራ ገበታቸው እንዲቀጥሉ የሚያፅና የሹመት ደብዳቤ ፅፈዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
በቀድሞ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት በሦስት ጀነራሎች ላይ የተቀመጠው ጊዚያዊ እግድ በአዲሱ ፕሬዜዳንት ተሽሯል።
በአራተኛው ጀነራል የተወሰነው ከሃላፊነት የማንሳት ውሳኔም ተሰርዟል።
የቀድሞ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ፦
- በጀነራል ምግበይ ሃይለ
- በጀነራል ዮውሃንስ ወ/ጊዮርጊስ
- በጀነራል ማሾ በየነ መጋቢት 1/2017 ዓ.ም ጊዚያዊ የእግድ ደብዳቤ መፃፋቸው ይታወሳል።
በተመሳሳይ የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሃላፊ ጀነራል ፍስሃ ኪዳኑ ፈንታ በአቶ ጌታቸው ረዳ በተፃፈ ደብዳቤ ከስራ ገበታቸው እንዲነሱ መወሰኑ ይታወሳል።
በቀድሞ ፕሬዜዳንት የተቀመጠው ጊዚያዊ እግድና ከስራ የማሰናበት ውሳኔ በአዲሱ የጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ሌ/ጀነራል ታደሰ ወረደ ሙሉ በሙሉ ተሰርዟል።
አዲሱ ፕሬዜዳንት ሚያዝያ 9/2017 ዓ.ም በፃፉት ደብዳቤ ጊዚያዊ እግዱና የስራ ስንብቱ ከመሰረዛቸው በተጨማሪ ፤ የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሃላፊው በስራ ገበታቸው እንዲቀጥሉ የሚያፅና የሹመት ደብዳቤ ፅፈዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
🥰214❤111😡90🤔59🕊37🙏28😭20👏10😢9😱7💔1
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray በቀድሞ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት በሦስት ጀነራሎች ላይ የተቀመጠው ጊዚያዊ እግድ በአዲሱ ፕሬዜዳንት ተሽሯል። በአራተኛው ጀነራል የተወሰነው ከሃላፊነት የማንሳት ውሳኔም ተሰርዟል። የቀድሞ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ፦ - በጀነራል ምግበይ ሃይለ - በጀነራል ዮውሃንስ ወ/ጊዮርጊስ - በጀነራል ማሾ በየነ መጋቢት 1/2017 ዓ.ም ጊዚያዊ የእግድ ደብዳቤ መፃፋቸው ይታወሳል።…
#Tigray
በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ እንደ አዲስ የተዋቀረው የጊዚያዊ አስተዳደሩ ካቢኔ ስራ እንደጀመረ ተነግሯል።
በአቶ ጌታቸው ረዳ ሲመራ የነበረውን የካቢኔ ቁጥር ከ27 ወደ 21 ፤ ሁለት ምክትል ፕሬዜዳንት የነበረውን ወደ አንድ እንዲወርድ ያደረጉት ፕሬዜዳንቱ እስካሁን ምክትላቸው ማን እንደሆነ በይፋ አላስታወቁም።
ይሁን እንጂ ከደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የህወሓት ሃይል ሰፊ ቁጥር ያለው የካቢኔ አባል ያካተቱ ስለመሆኑ ተነግሯል።
ምክትላቸው የህግ ምሁርና የህወሓት ምክትል ሊቀመንበር የሆኑት አቶ ኣማኒኤል አሰፋ አደርገው መሾማቸው ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ጨምሮ በርካቶች በመፃፍ ላይ ይገኛሉ።
አንዳንዶች " አዲሱ የጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት የወጣቱ የለውጥ ጥያቄ የሚመልስ አዲስ ካቢኔ አላዋቀሩም " በሚል ነቄፌታ እያቀረቡ ይገኛሉ።
ፕሬዜዳንት ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ አዲሱ ካቢኔ ስራ መጀመሩን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ " ትግራይ በአሸናፊና ተሸናፊ የፓለቲካ ቅኝት ከገባችበት አዘቅት መውጣት አትችልም " ብለዋል።
" ባለፉት ሁለት የጊዚያዊ አስተዳደሩ ዓመታት በርካታ ጥሩና መጥፎ ነገሮች ተፈፅመዋል " ሲሉ ገልጸዋል።
" ጥሩውን ለራስ መጥፎውን ለሌላ መስጠት አይቻልም ድሉም ውድቀቱም የጋራ ነው ከእልህና ህዝብንና አገር ከሚጎዳ ፓለቲካዊ አካሄድ እንውጣ " ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
" የቀድሞ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳና ሌሎች የጊዚያዊ አስተዳደር አመራሮች የሚመሰገኑበት መድረክ ይዘጋጃል " ያሉት ፕሬዜዳንቱ ጥሪውን ተቀብለው እንዲገኙ ከወዲሁ በይፋ የግብዣ ጥሪ አቅርበዋል።
የቀድሞ ፕሬዚዳንትና አመራሮች ይመሰገኑበታል የተባለው የምስጋና ስነስርዓት መቼ እና የት እንደሚዘጋጅ የተባለ ነገር የለም።
በሌላ በኩል ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ ተፈናቃዮች የሚገኙበት ስቃይና ሰቆቃ ባወሳ ንግግራቸው " በዚሁ ዓመት ወደ ቄያቸው የመመለስ ስራ ይሰራል ፤ በማቆያ ጣብያ የሚቆዩት ደግሞ አኗኗራቸው እንዲሻሻል ትኩረት ይደረጋል " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
@tikvahethiopia
በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ እንደ አዲስ የተዋቀረው የጊዚያዊ አስተዳደሩ ካቢኔ ስራ እንደጀመረ ተነግሯል።
በአቶ ጌታቸው ረዳ ሲመራ የነበረውን የካቢኔ ቁጥር ከ27 ወደ 21 ፤ ሁለት ምክትል ፕሬዜዳንት የነበረውን ወደ አንድ እንዲወርድ ያደረጉት ፕሬዜዳንቱ እስካሁን ምክትላቸው ማን እንደሆነ በይፋ አላስታወቁም።
ይሁን እንጂ ከደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የህወሓት ሃይል ሰፊ ቁጥር ያለው የካቢኔ አባል ያካተቱ ስለመሆኑ ተነግሯል።
ምክትላቸው የህግ ምሁርና የህወሓት ምክትል ሊቀመንበር የሆኑት አቶ ኣማኒኤል አሰፋ አደርገው መሾማቸው ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ጨምሮ በርካቶች በመፃፍ ላይ ይገኛሉ።
አንዳንዶች " አዲሱ የጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት የወጣቱ የለውጥ ጥያቄ የሚመልስ አዲስ ካቢኔ አላዋቀሩም " በሚል ነቄፌታ እያቀረቡ ይገኛሉ።
ፕሬዜዳንት ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ አዲሱ ካቢኔ ስራ መጀመሩን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ " ትግራይ በአሸናፊና ተሸናፊ የፓለቲካ ቅኝት ከገባችበት አዘቅት መውጣት አትችልም " ብለዋል።
" ባለፉት ሁለት የጊዚያዊ አስተዳደሩ ዓመታት በርካታ ጥሩና መጥፎ ነገሮች ተፈፅመዋል " ሲሉ ገልጸዋል።
" ጥሩውን ለራስ መጥፎውን ለሌላ መስጠት አይቻልም ድሉም ውድቀቱም የጋራ ነው ከእልህና ህዝብንና አገር ከሚጎዳ ፓለቲካዊ አካሄድ እንውጣ " ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
" የቀድሞ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳና ሌሎች የጊዚያዊ አስተዳደር አመራሮች የሚመሰገኑበት መድረክ ይዘጋጃል " ያሉት ፕሬዜዳንቱ ጥሪውን ተቀብለው እንዲገኙ ከወዲሁ በይፋ የግብዣ ጥሪ አቅርበዋል።
የቀድሞ ፕሬዚዳንትና አመራሮች ይመሰገኑበታል የተባለው የምስጋና ስነስርዓት መቼ እና የት እንደሚዘጋጅ የተባለ ነገር የለም።
በሌላ በኩል ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ ተፈናቃዮች የሚገኙበት ስቃይና ሰቆቃ ባወሳ ንግግራቸው " በዚሁ ዓመት ወደ ቄያቸው የመመለስ ስራ ይሰራል ፤ በማቆያ ጣብያ የሚቆዩት ደግሞ አኗኗራቸው እንዲሻሻል ትኩረት ይደረጋል " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
@tikvahethiopia
❤251😡98🕊53🤔14🙏14🥰11👏7😢7😱6😭6
#Tigray
የካቢኔ አባሉ ለእስር የዳረጋቸው ምንድን ነው ?
በአሁኑ ወቅት በትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ብቸኛ የተቃዋሚው የባይቶና ፓለቲካ ፓርቲ የካቢኔ አባል የሆኑት አቶ ታደለ መንግስቱ በፓሊስ ቁጥጥር ስር ውለው በእስር ወደ ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ መደረጋቸው አነጋጋሪ ሆኖ ውሏል።
የካቢኔ አባሉ አቶ ታደለ የመቐለ ማእከላይ ፍርድ ቤት የሚመሩት የመንግስት መስሪያ ቤት እንዲያስፈፅም የሰጠውን ውሳኔ ባለመተግበራቸው ምክንያት ዛሬ ረቡዕ ለ6 ወራት በእስር እንዲቆዩ ቢወሰነባቸውም ከ1 ቀን እስር በኋላ ተለቀዋል።
በምን ምክንያት ታሰሩ ? እንዴትስ ተለቀቁ ?
ተከሳሹ የትግራይ የትራንስፓርት ቢሮ ሃላፊ አቶ ታደለ መንግስቱ ሲሆኑ ከሳሽ ደግሞ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ነው።
የክሱ ፍሬ ነገር በትግራዩ ጦርነት የተወሰደችበት ላንድ ክሩዘር V8 መኪና እንድትመለስለት የሚጠይቅ ነው።
ባለስልጣኑ ዓይነቷና የሰሌዳ ቁጥሯን ጠቅሶ በቢሮው አስፈፃሚነት እንድትመለስለት የጠየቀባት ላንድ ክሩዘር V8 መኪና የህወሓት ፅህፈት ሃላፊዋ ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገ/ሄር ሲጠቀሙባት ነበር።
የጊዚያዊ አስተዳደሩ የትራንስፓርት ቢሮ V8 መኪናዋ ለባለቤቱ እንድትመለስ እንዲያስፈፅም የቀረበበት ክስ በመቀበል የህወሓት ፓርቲ ሃላፊዋ (ወ/ሮ ፈትለወርቅ) እንዲመለሱ ተጠይቀው አሻፈረኝ በማለታቸው ምክንያት ፍርድ ቤት ጉዳዩን ማስፈፀም ያልቻሉትን የቢሮውን ሃላፊ (አቶ ታደለ) በእስር እንዲቀርቡ ያዛል።
ዛሬ ሚያዝያ 15/2017 ዓ.ም በፓሊስ ተይዘው ፍርድ ቤት የቀረቡት ሃላፊው ጉዳዩ እንዲያስፈፅሙ በተደጋጋሚ የቀረበላቸው ባለመተግበራቸው ምክንያት ለ6 ወር እንዲታሰሩ ይፈርዳል።
ሂደቱ እንዲህ እያለ ወደ ባለቤትዋ እንድትመለስ ጥያቄ የቀረበባት V8 መኪና ሚያዝያ 15/2017 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ በሸኚ ደብዳቤ በኤግዚብትነት ወደ ፓሊስ እጅ በመግባቷ ምክንያት ሃላፊው ከእስር ሊለቀቁ ችለዋል።
ከትግራይ የትራንስፓርት ቢሮ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው በጦርነቱ ምክንያት ከመንግስታዊና ግለሰቦች ተወስደው በማይመለከታቸው አካላት የነበሩት ከ 2800 በላይ ተሽከርካሪዎች ወደ ባለቤቶቹ ተመልሰዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
ፎቶ፦ የLC V8 ምስል ከኢንተርኔት የተወሰደ
@tikvahethiopia
የካቢኔ አባሉ ለእስር የዳረጋቸው ምንድን ነው ?
በአሁኑ ወቅት በትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ብቸኛ የተቃዋሚው የባይቶና ፓለቲካ ፓርቲ የካቢኔ አባል የሆኑት አቶ ታደለ መንግስቱ በፓሊስ ቁጥጥር ስር ውለው በእስር ወደ ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ መደረጋቸው አነጋጋሪ ሆኖ ውሏል።
የካቢኔ አባሉ አቶ ታደለ የመቐለ ማእከላይ ፍርድ ቤት የሚመሩት የመንግስት መስሪያ ቤት እንዲያስፈፅም የሰጠውን ውሳኔ ባለመተግበራቸው ምክንያት ዛሬ ረቡዕ ለ6 ወራት በእስር እንዲቆዩ ቢወሰነባቸውም ከ1 ቀን እስር በኋላ ተለቀዋል።
በምን ምክንያት ታሰሩ ? እንዴትስ ተለቀቁ ?
ተከሳሹ የትግራይ የትራንስፓርት ቢሮ ሃላፊ አቶ ታደለ መንግስቱ ሲሆኑ ከሳሽ ደግሞ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ነው።
የክሱ ፍሬ ነገር በትግራዩ ጦርነት የተወሰደችበት ላንድ ክሩዘር V8 መኪና እንድትመለስለት የሚጠይቅ ነው።
ባለስልጣኑ ዓይነቷና የሰሌዳ ቁጥሯን ጠቅሶ በቢሮው አስፈፃሚነት እንድትመለስለት የጠየቀባት ላንድ ክሩዘር V8 መኪና የህወሓት ፅህፈት ሃላፊዋ ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገ/ሄር ሲጠቀሙባት ነበር።
የጊዚያዊ አስተዳደሩ የትራንስፓርት ቢሮ V8 መኪናዋ ለባለቤቱ እንድትመለስ እንዲያስፈፅም የቀረበበት ክስ በመቀበል የህወሓት ፓርቲ ሃላፊዋ (ወ/ሮ ፈትለወርቅ) እንዲመለሱ ተጠይቀው አሻፈረኝ በማለታቸው ምክንያት ፍርድ ቤት ጉዳዩን ማስፈፀም ያልቻሉትን የቢሮውን ሃላፊ (አቶ ታደለ) በእስር እንዲቀርቡ ያዛል።
ዛሬ ሚያዝያ 15/2017 ዓ.ም በፓሊስ ተይዘው ፍርድ ቤት የቀረቡት ሃላፊው ጉዳዩ እንዲያስፈፅሙ በተደጋጋሚ የቀረበላቸው ባለመተግበራቸው ምክንያት ለ6 ወር እንዲታሰሩ ይፈርዳል።
ሂደቱ እንዲህ እያለ ወደ ባለቤትዋ እንድትመለስ ጥያቄ የቀረበባት V8 መኪና ሚያዝያ 15/2017 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ በሸኚ ደብዳቤ በኤግዚብትነት ወደ ፓሊስ እጅ በመግባቷ ምክንያት ሃላፊው ከእስር ሊለቀቁ ችለዋል።
ከትግራይ የትራንስፓርት ቢሮ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው በጦርነቱ ምክንያት ከመንግስታዊና ግለሰቦች ተወስደው በማይመለከታቸው አካላት የነበሩት ከ 2800 በላይ ተሽከርካሪዎች ወደ ባለቤቶቹ ተመልሰዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
ፎቶ፦ የLC V8 ምስል ከኢንተርኔት የተወሰደ
@tikvahethiopia
❤391🤔108👏69😭48🕊41😡12🥰11😢11🙏8😱4
TIKVAH-ETHIOPIA
" የትግራይ ህዝብ ከሰጠኝ እውቅናና ክብር በላይ የምመኘው የክብርና የምስጋና መድረክ የለም " - አቶ ጌታቸው ረዳ የጠቅላይ ሚንስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር አቶ ጌታቸው ረዳ በአዲሱ የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀነራል) የቀረበላቸው የክብርና የምስጋና የሽኝት መድረክ ውድቅ አደረጉ። አቶ ጌታቸው ረዳ ሚያዝያ 3/2017 ዓ.ም የጠቅላይ ሚንስትሩ የምስራቅ…
" ጌታቸው ላይ መፈንቅለ መንግስት ፈፅሜ ከሆነ በገለልተኛ አካል ይጣራ " - ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ ጀነራል) " አውራ እምባ ታይምስ " ከተባለ ሚድያ ጋር ቃለ መጠይቅ አድርገው ነበር።
በዚህም ወቅት በትግራይ ተካሂደዋል ተብሎ ተደጋግሞ ስለሚነገረው የመፈንቅለ መንግስት ጉዳይ ተጠይቀው መልሰዋል።
በቀድሞ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው የህወሓት ሃይል ባለፈው ባወጣው መግለጫ " በትግራይ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት በማካሄድ ስልጣን ከተያዘ 40 ቀናት ተቆጠረዋል " ብሎ ነበር።
ይኸው ኃይል " የአቶ ጌታቸው አስተዳደር ህገ-ወጥ ተግባሩ ተጋግሎ ወደ ተባባሰ ግጭት እንዳያመራ ስልጣን ጭምር ለሰላም ሲል አሳልፎ ሰጥቷል " የሚል አገላለፅም ተጠቅሞ ነበር።
ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀነራል) ፥ " ጌታቸው ረዳ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት አካል ሆኖ በተቋቋመው ጊዚያዊ አስተዳደር ወደ ኃላፊነት የመጡ ናቸው " ያሉ ሲሆን " ወደ ሃላፊነት መጋቢት 2015 ዓ.ም ነው የመጡት። የጊዚያዊ አስተዳደሩ ቆይታ ሁለት ዓመት መሆኑ ይታወቃል። እንዲያ ሆኖም 6 ወር ሊራዘም ይችላል። ይሁን እንጂ የነበረው ጊዚያዊ አስተዳደር ለ6 ወራት ለማራዘም የሚያስገደድ በቂ ምክንያት አልተገኘም " ብለዋል።
" መጋቢት 2015 ዓ.ም ወደ ሃላፊነት የመጡት አቶ ጌታቸው መጋቢት 2017 ዓ.ም የሁለት ዓመት ቆይታቸውን ጨርሰዋል " ሲሉ አስረድተዋል።
" አሁን የተደረገው በፓርላማ በፀደቀ አዋጅ ጊዚያዊ አስተዳደሩ ለአንድ ዓመት ማራዘም ነው። በተራዘመው የጊዚያዊ አስተዳደሩ ዕድሜ የነበረው ፕሬዜዳንት ሊቀጥል ላይቀጥል ይችላል። አጋጣሚ ሆኖ አቶ ጌታቸው በሃላፊነት አልቀጠለም " ሲሉ ገልጸዋል።
" እኔ እንደ አዲስ በተራዘመው ጊዚያዊ አስተዳደር ወደ ሃላፊነት መጥቻለው። በትግራይ የሃላፊነት ጊዜው ጨርሶ ከሃላፊነት የወረደ እንጂ የተካሄደ መፈንቅለ መንግስት የለም። መፈንቅለ መንግስት አልተካሄደም ብቻ ሳይሆን ወደዛ የሚወሰድ ምክንያትም አልነበረም " ብለዋል።
" ያን ያህል ጉዳዩ አሳሳቢ ሆኖ መፈንቅለ መንግስት ተካሂደዋል ? ወይስ አልተካሂደም የሚል ክርክርና እሰጣ ገባ ካለ ለሦስተኛ ወገን እድል እንስጥ። የሚያጣራ አካል ይኑር። ምናልባት እኔ ይህንን ጉዳይ የሚያጣራ አካል ላቋቁም ብል ተአማኒነትና ተቀባይነት ላይኖረው ስለሚችል ሦስተኛ አካል የሆነ ኮሚቴ ቢያጣራው እላለው " ሲሉ መልሰዋል።
" በጌታቸው ላይ መፈንቅለ መንግስት ፈፅሜ ከሆነ በገለልተኛ አካል ይጣራ " ሲሉም አክለዋል።
#Tigray
@tikvahethiopia
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ ጀነራል) " አውራ እምባ ታይምስ " ከተባለ ሚድያ ጋር ቃለ መጠይቅ አድርገው ነበር።
በዚህም ወቅት በትግራይ ተካሂደዋል ተብሎ ተደጋግሞ ስለሚነገረው የመፈንቅለ መንግስት ጉዳይ ተጠይቀው መልሰዋል።
በቀድሞ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው የህወሓት ሃይል ባለፈው ባወጣው መግለጫ " በትግራይ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት በማካሄድ ስልጣን ከተያዘ 40 ቀናት ተቆጠረዋል " ብሎ ነበር።
ይኸው ኃይል " የአቶ ጌታቸው አስተዳደር ህገ-ወጥ ተግባሩ ተጋግሎ ወደ ተባባሰ ግጭት እንዳያመራ ስልጣን ጭምር ለሰላም ሲል አሳልፎ ሰጥቷል " የሚል አገላለፅም ተጠቅሞ ነበር።
ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀነራል) ፥ " ጌታቸው ረዳ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት አካል ሆኖ በተቋቋመው ጊዚያዊ አስተዳደር ወደ ኃላፊነት የመጡ ናቸው " ያሉ ሲሆን " ወደ ሃላፊነት መጋቢት 2015 ዓ.ም ነው የመጡት። የጊዚያዊ አስተዳደሩ ቆይታ ሁለት ዓመት መሆኑ ይታወቃል። እንዲያ ሆኖም 6 ወር ሊራዘም ይችላል። ይሁን እንጂ የነበረው ጊዚያዊ አስተዳደር ለ6 ወራት ለማራዘም የሚያስገደድ በቂ ምክንያት አልተገኘም " ብለዋል።
" መጋቢት 2015 ዓ.ም ወደ ሃላፊነት የመጡት አቶ ጌታቸው መጋቢት 2017 ዓ.ም የሁለት ዓመት ቆይታቸውን ጨርሰዋል " ሲሉ አስረድተዋል።
" አሁን የተደረገው በፓርላማ በፀደቀ አዋጅ ጊዚያዊ አስተዳደሩ ለአንድ ዓመት ማራዘም ነው። በተራዘመው የጊዚያዊ አስተዳደሩ ዕድሜ የነበረው ፕሬዜዳንት ሊቀጥል ላይቀጥል ይችላል። አጋጣሚ ሆኖ አቶ ጌታቸው በሃላፊነት አልቀጠለም " ሲሉ ገልጸዋል።
" እኔ እንደ አዲስ በተራዘመው ጊዚያዊ አስተዳደር ወደ ሃላፊነት መጥቻለው። በትግራይ የሃላፊነት ጊዜው ጨርሶ ከሃላፊነት የወረደ እንጂ የተካሄደ መፈንቅለ መንግስት የለም። መፈንቅለ መንግስት አልተካሄደም ብቻ ሳይሆን ወደዛ የሚወሰድ ምክንያትም አልነበረም " ብለዋል።
" ያን ያህል ጉዳዩ አሳሳቢ ሆኖ መፈንቅለ መንግስት ተካሂደዋል ? ወይስ አልተካሂደም የሚል ክርክርና እሰጣ ገባ ካለ ለሦስተኛ ወገን እድል እንስጥ። የሚያጣራ አካል ይኑር። ምናልባት እኔ ይህንን ጉዳይ የሚያጣራ አካል ላቋቁም ብል ተአማኒነትና ተቀባይነት ላይኖረው ስለሚችል ሦስተኛ አካል የሆነ ኮሚቴ ቢያጣራው እላለው " ሲሉ መልሰዋል።
" በጌታቸው ላይ መፈንቅለ መንግስት ፈፅሜ ከሆነ በገለልተኛ አካል ይጣራ " ሲሉም አክለዋል።
#Tigray
@tikvahethiopia
🤔186❤92🕊47😡35👏28😭18🙏12🥰6😢6💔5😱3
TIKVAH-ETHIOPIA
" ከብልጽግና ጋር ልክ እንደሌሎቹ በአገር ውስጥ እንደሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች ተባብሮ ለመሥራት ይችላል እንጂ የሚያገናኘው ነገር የለም፤ ገለልተኛ እና ነጻ ፓርቲ ነው " - የቀድሞ የህወሓት አመራር በጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች ሚኒስትር አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ከህወሓት የተከፈለው ቡድን አዲስ የፖለቲካ ፓርቲ ለማቋቋም በሂደት ላይ መሆኑን ከአመራሮቹ መካከል አንዱ ለቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት…
#Tigray
" የትግራይ የፖለቲካ ቀውስ ወደ ባሰ ሁኔታ በማምራት አሸናፊና ተሸናፊ ሳይኖረው ትግራይንና ህዝብዋ ወደ ከፋ ሁኔታ እየመራ ነው " ሲል የትግራይ ስቪል ማህበራት ጥምረት ስጋቱ ገለፀ፡፡
ጥምረቱ ባወጣው መግለጫ " የትግራይ የፖለቲካ ምህዳር በመበላሸቱ ምክንያት በአገር ውስጥና ከአገር ውጭ የሚኖር ትግራዋይ አንደነት ላይ ሳንካ ፈጥሯል " ብሏል።
" በጣም የከፋ ፖለቲካዊና ጠባብ አስተሳሰብ አንሰራፍቷል " በማለት ስጋቱ የገለፀው ጥምረቱ ፣ " አሁንም ሁነኛው መፍትሄ ሁሉን አቀፍ አሳታፊ ውይይት በማካሄድ ልዩነት በሰለጠነ መንገድ መፍታት ነው መፍትሄው " ሲል ገልጿል።
የጋራ መግባባት ላይ እንዲደረስ የሚያግዝና የሚያስችል ብሄራዊ ውይይት በአሰቸኳይ እንዲጀመር " በድጋሜ ጥሪ አቀርባለሁ " ብሏል።
" በአዲሱ ጊዚያዊ አስተዳደር የተቋቋመው ካቢኔ አቃፊና አሳታፊ አይደለም " ሲል የተቸው ጥምረቱ ፣ " አወቃቀሩ ያለውን ፖለቲካዊ ቀውስ የሚያባብስ በመሆኑ ተዋፅኦው ከአሁኑ መታረም አለበት " ሲል አሳስቧል።
" በነባሩ ጊዚያዊ አስተዳደር የተቋቋመው ጊዚያዊ ምክር ቤት አዲሱ ጊዚያዊ አስተዳደር እንዲያስቀጥለውና ፣ የህዝብንና የአገር በጀት በታለመለት ስራ ላይ እንዲውል የመቆጣጠር ስልጣኑ እንዲወጣ ይፈቅድለት " ብሏል።
የትግራይ ሲቪል ማሕበራት ጥምረት ከ120 በላይ በክልሉ የሚንቀሳቀሱ ማህበራት ያቀፈ ፣ የቆይታ ጊዜው ባጠናቀቀው በፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ በተመራው ጊዚያዊ አስተዳደር በተቋቋመው ጊዚያዊ ምክር ቤት ውክልና ያለው መንግስታዊ ያልሆነ ተቋም ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
" የትግራይ የፖለቲካ ቀውስ ወደ ባሰ ሁኔታ በማምራት አሸናፊና ተሸናፊ ሳይኖረው ትግራይንና ህዝብዋ ወደ ከፋ ሁኔታ እየመራ ነው " ሲል የትግራይ ስቪል ማህበራት ጥምረት ስጋቱ ገለፀ፡፡
ጥምረቱ ባወጣው መግለጫ " የትግራይ የፖለቲካ ምህዳር በመበላሸቱ ምክንያት በአገር ውስጥና ከአገር ውጭ የሚኖር ትግራዋይ አንደነት ላይ ሳንካ ፈጥሯል " ብሏል።
" በጣም የከፋ ፖለቲካዊና ጠባብ አስተሳሰብ አንሰራፍቷል " በማለት ስጋቱ የገለፀው ጥምረቱ ፣ " አሁንም ሁነኛው መፍትሄ ሁሉን አቀፍ አሳታፊ ውይይት በማካሄድ ልዩነት በሰለጠነ መንገድ መፍታት ነው መፍትሄው " ሲል ገልጿል።
የጋራ መግባባት ላይ እንዲደረስ የሚያግዝና የሚያስችል ብሄራዊ ውይይት በአሰቸኳይ እንዲጀመር " በድጋሜ ጥሪ አቀርባለሁ " ብሏል።
" በአዲሱ ጊዚያዊ አስተዳደር የተቋቋመው ካቢኔ አቃፊና አሳታፊ አይደለም " ሲል የተቸው ጥምረቱ ፣ " አወቃቀሩ ያለውን ፖለቲካዊ ቀውስ የሚያባብስ በመሆኑ ተዋፅኦው ከአሁኑ መታረም አለበት " ሲል አሳስቧል።
" በነባሩ ጊዚያዊ አስተዳደር የተቋቋመው ጊዚያዊ ምክር ቤት አዲሱ ጊዚያዊ አስተዳደር እንዲያስቀጥለውና ፣ የህዝብንና የአገር በጀት በታለመለት ስራ ላይ እንዲውል የመቆጣጠር ስልጣኑ እንዲወጣ ይፈቅድለት " ብሏል።
የትግራይ ሲቪል ማሕበራት ጥምረት ከ120 በላይ በክልሉ የሚንቀሳቀሱ ማህበራት ያቀፈ ፣ የቆይታ ጊዜው ባጠናቀቀው በፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ በተመራው ጊዚያዊ አስተዳደር በተቋቋመው ጊዚያዊ ምክር ቤት ውክልና ያለው መንግስታዊ ያልሆነ ተቋም ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
❤249😭71🕊57😢29🙏23😡16🤔12🥰9😱9💔3👏1
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray የትግራይ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዜዳንት እና ምክትል ፕሬዜዳንት በጋራ የስራ መልቀቂያ ደብዳቤ አስገቡ። ስራ መልቀቂያውን ያስገቡት ፤ " በፍትህ እና የዳኝነት ሰርዓቱ ለውጥ ለማምጣት ያሰብናቸው ፣ ያቀድናቸው የጀመርናቸው ያስቀመጥናቸው አቅጣጫዎች ለማሳካት የሚያስችል ሁኔታ ማግኘት ስላልቻልን ነው " ብለዋል። ሰኞ ሰኔ 17/2016 ዓ.ም የተፃፈው የስራ መልቀቅያ ደብዳቤ በበርካታ የማህበራዊ…
#Tigray
የከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዜዳንቱና ምክትላቸው ከሃላፊነታቸው ተሰናበቱ።
የትግራይ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዜዳንት ፀጋይ ብርሃነ ገ/ተኽለ እና ምክትላቸው ገብረኣምላኽ የዕብዮ ከስራ ገበታቸው ተሰናብተዋል።
በትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀነራል) ፊርማ ግንቦት 5/2017 ዓ.ም የተፃፈው ደብዳቤ እንደሚያመለክተው ፥ ፕሬዜዳንቱና ምክትላቸው የስራ መልቀቅያ እንዲሰጣቸው በጠየቁትና ባመለከቱት መሰረት ከምስጋና ጭምር ስንብት ተሰጥቶዋቸዋል።
በዚህም ፕሬዜዳንቱና ምክትላቸው ከዛሬ ግንቦት 6/2017 ዓ.ም ጀምሮ ከስራ መሰናበታቸው የተፃፈላቸው ደብዳቤ ያመለክታል።
ፕሬዜዳንቱ እና ምክትላቸው የቀድሞ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ወደ ስልጣን መምጣታቸው ተከትሎ ወደ ሃላፊነት የመጡ ሲሆን ከአንዴም ሁለቴ ጊዜ ስራ ለመልቀቅ ጠይቀው ሳይሳካላቸው ቀርቷል።
የስራ መልቀቅያ እንዲያስገቡ እንደ ምክንያት ከጠቀሱዋቸው ችግሮች የጊዚያዊ አስተዳደሩ ስራ አስፈፃሚ አካላት በህግ ልዕልና የሚያሳዩት ያልተገባ ጣልቃ ገብነት መሆኑን ከዚህ ቀደም መግለጻቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃ ማድረጉ ይታወሳል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
የከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዜዳንቱና ምክትላቸው ከሃላፊነታቸው ተሰናበቱ።
የትግራይ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዜዳንት ፀጋይ ብርሃነ ገ/ተኽለ እና ምክትላቸው ገብረኣምላኽ የዕብዮ ከስራ ገበታቸው ተሰናብተዋል።
በትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀነራል) ፊርማ ግንቦት 5/2017 ዓ.ም የተፃፈው ደብዳቤ እንደሚያመለክተው ፥ ፕሬዜዳንቱና ምክትላቸው የስራ መልቀቅያ እንዲሰጣቸው በጠየቁትና ባመለከቱት መሰረት ከምስጋና ጭምር ስንብት ተሰጥቶዋቸዋል።
በዚህም ፕሬዜዳንቱና ምክትላቸው ከዛሬ ግንቦት 6/2017 ዓ.ም ጀምሮ ከስራ መሰናበታቸው የተፃፈላቸው ደብዳቤ ያመለክታል።
ፕሬዜዳንቱ እና ምክትላቸው የቀድሞ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ወደ ስልጣን መምጣታቸው ተከትሎ ወደ ሃላፊነት የመጡ ሲሆን ከአንዴም ሁለቴ ጊዜ ስራ ለመልቀቅ ጠይቀው ሳይሳካላቸው ቀርቷል።
የስራ መልቀቅያ እንዲያስገቡ እንደ ምክንያት ከጠቀሱዋቸው ችግሮች የጊዚያዊ አስተዳደሩ ስራ አስፈፃሚ አካላት በህግ ልዕልና የሚያሳዩት ያልተገባ ጣልቃ ገብነት መሆኑን ከዚህ ቀደም መግለጻቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃ ማድረጉ ይታወሳል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
❤275🕊73🤔35🙏32😭27👏21🥰7😢6💔6😡5