TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Tigray

ህዝቡ በህብረት ስራ ማህበራት ስም ከሚፈፀሙ #የማደናገር እና #የማጭበርበር ተግባራት ራሱ እንዲጠብቅ ጥሪ ቀረበ።

ይህን የማስጠንቅያ ጥሪ ያቀረቡት የትግራይ ፍትህ ቢሮና የቤቶች ልማትና አስተዳደር ኤጀንሲ በጋራ ሆነው ነው።

መንግስታዊ ተቋማቱ  " አቦ " በሚል ስያሜ በቤቶች ግንባታና ልማት " ተሰማርቻለሁ ... ተመዝገቡ የቤት ባለቤት ሁኑ " በሚል እንቅስቃሴ በማካሄድ የሚገኘው የህብረት ስራ ማህበር እውግዘዋል ፤  እግድም ጥለዋል።

መንግስታዊ ተቋማቱ ባወጡት መግለጫ ፥ " አቦ " በሚል ስም የሚታወቀው የህብረት ስራ ማህበር ፥ " ከደደቢት ማይክሮፋይናንስ በጋራ በትግራይ 5 ከተሞች ቤቶች ገንብቼ አስረክባሎህ " ብሎ ከሰነ 3/2016 ዓ.ም ያስጀመረው የምዝገባ እንቅስቃሴ ህጋዊ አይደለም  ብለዋል።

" አቦ " የተባለ የህብረት ስራ ማህበር በ5 የትግራይ ከተሞች ቤት ገንብቶ ለማስረከብ የተሰጠው መሬት የለም ያለው የትግራይ የቤቶች ልማትና አስተዳደር ኤጀንሲ ድርጅቱ ከድርጊቱ እንዲታቀብ አስጠንቅቋል።

የመኖሪያ የቤቶች ግንባታ በህብረት ስራ ማህበር የማደራጀት ስልጣን የተሰጠው ለፍትህ ቢሮ ነው ያለው የክልሉ ፍትህ ቢሮ ፥ " አቦ የቤቶች ግንባታ ህብረት ስራ ማህበር " በህግ ባልተፈቀደለት የስራ ዘርፍ ሲንቀሳቀስ በመገኘቱ እግድ እንደጣለበት አስገንዝቧል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia            
139😭24🕊10🥰9😢9🙏8😡7🤔4👏3😱2