TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አውቶብሱ የተገለበጠው የሰሌዳ ቁጥሩ ይፋ ያልተደረገ ኮድ 3 አ/አ መኪና ለመሸሽ ሲሞክር ነው!

እስጢፋኖስ ቤተክርስትያን ጀርባ በሚገኝው ድልድይ ውስጥ የመውደቅ አደጋ የገጠመው የከተማ አውቶብሱ ምክንያት ለጊዜው የሰሌዳ ቁጥር ይፋ ያልተደረገ ኮድ 3 አ.አ መኪና ለመሸሽ ሲል እንደሆነ የእሳት እና ድንገተኛ አደጋዎች የኮምንኬሽን ባለሙያ አቶ ስለሺ ተስፋዬ ለሽገር ራድዮ አስረድተዋል።

አውቶብሱ የተለመደ የመስመር ቁጥር ያልተሰጠው አዲስ ስምሪት እንደሆነም ታውቋል። መነሻውንም ከሽሮሜዳ አድርጎ ወደ ካዛንችስ እየሄደ እንደነበርም ነው ባለሙያው የተናገሩት። አደጋው ያጋጠመው አንበሳ የከተማ አውቶብስ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3- አ/አ 68377 እንደሆነ ታውቋል። በዚሁ አደጋም 31 ሰዎች ብርቱ ጉዳት እንደገጠማቸው ተሰምቷል።

ካሰቡበት ለመድረስ #በአውቶብሱ ተሳፍረው አደጋው ያገኛቸው ኢትዮጵያውያንም ወደ ጥቁር አንበሳ ዘውዲቱ እና አቤት ሆስፒታል መወሰዳቸውን ባለሙያው ተናግረዋል። በደረሰው አደጋ እስካሁን የ2 ሰው ህይወት አልፏል ተብሏል። የሟቾች ቁጥርም ሊጨምር ይችላል ያሉት የኮምንኬሽን ባለሙያው ናቸው።

Via #ShegerFM
@tsegabwolde @tikvahethiopia