TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.5K photos
1.59K videos
216 files
4.34K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AmahraRegion

አቶ አህመድ አሊ ዛሬ በታጣቂዎች በተተኮሰባቸው ጥይት መገደላቸው ተሰማ።

በአማራ ክልላዊ መንግሥት ፣ የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ አሊ ዛሬ በከሚሴ ከተማ ከሚገኝ መስጅድ ጁምአ ሶላት ሰግደው ወደ ቤታቸው ሲመለሱ በታጣቂዎች በተተኮሰባቸው ጥይት መገደላቸው ተነግሯል።

የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ባወጣው የሀዘን መግለጫ " ግድያው የተፈጸመው በጽንፈኛው የሸኔ ታጣቂ ቡድን ነው " ብሏል።

አቶ አህመድ ከዋና አስተዳዳሪነታቸው በተጨማሪ የአማራ ክልል የብልጽግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል በመሆን ማገልገላቸው ተገልጿል።

#AmharaRegion
#OromooZone

@tikvahethiopia
😭1.74K👏413203😢123🕊104🤔51😱48😡48🙏42🥰34