TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
214 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Freedom_and_Equality_Party

ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ህዳር 26 እና 27 ቀን 2013 ዓ/ም የሶማሌ ክልል ሸንጎ ምስረታ አካሂዷል።

ከአስራ አንድ ዞኖች ተወክለው ወደ ጅግጅጋ የሄዱ አባላት የመጀመሪያው የክልላዊ ሸንጎ ስብሰባቸውን ማድረጋቸውን ፓርቲው ገልጿል።

የክልሉ ስራ አስፈፃሚ ከሁሉም ዞኖች አንዳንድ ስራ አስፈፃሚ ተካተው እንደገና መዋቀራቸውም ተነገሯል።

ላለፉት 11 ወራት በተለያዩ የሶማሌ ክልል የተከፈቱ ቢሮዎች ስራ እንቅስቃሴ በክልል ደረጃ በጅግጅጋ ዋና መስሪያ ቤት መቀመጫ ላይ ተገምግመዋል።

እስከአሁን በክልሉ በአጠቃላይ 24 የነ.እ.ፓ. ቢሮዎች ተከፍተው ስራ ላይ እንደሚገኙ ፓርቲው ያሳወቀ ሲሆን እነዚህ ቢሮዎች በክልሉ ማዕከልነት በተዋረድ እንዲሰሩ መደረጉን አሳውቋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia