ለአዲስ አበባ ነዋሪዎች!
በአቃቂ መሿለኪያ ድልድይ የሚያልፍበት ወንዝ ሙላት ምክንያት የሚፈጠሩ እንግልቶችን ለማስቀረት ህብረተሰቡ የተለያዩ የመንገድ #አማራጮችን እንዲጠቀም የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን ያሳስባል፡፡
አማራጮችን ለመጠቆም ያህል፡-
1. ወደ ምስራቅ አዲስ አበባ መሄድ የሚፈልጉ ተሽከርካሪዎች ከደቡብ አፍሪካ ዩኒቨርሲቲ አደባባይ ወደ ቱሉ ዲምቱ ማሳለጫ (ወደ ጎሮ የሚወስደውን ውጫዊ የቀለበት መንገድ) መጠቀም ይችላሉ።
2. ወደ መሃል አዲስ አበባ ለመሄድ የሚፈልጉ ተሸከርካሪዎች ዋናውን አቃቂ ድልድይ መጠቀም ይችላሉ።
3. ወደ ምዕራብ አዲስ አበባ መሄድ የሚፈልጉ ተሸከርካሪዎች ከደቡብ አፍሪካ ዩኒቨርሲቲ አደባባይ በግራ በኩል ወደ ለቡ የሚወስደውን ውጫዊ የቀለበት መንገድ መጠቀም ይችላሉ።
4. ከአዲስ አበባ ወደ ምስራቅ አቅጣጫ የሚጓዙ ተሸከርካሪዎች በላይ አብ ሞተርስ አለፍ ብሎ ወደ ቱሉ ዲምቱ ኮንዶሚኒየም በመታጠፍ መስቀለኛ መንገዱን መጠቀም ይቻላሉ።
እንደሚታወቀው ቃሊቲ ቀለበት መንገድ አደባባይ - ቱሉ ዲምቱ አደባባይ መንገድ ለረጅም ጊዜ የከተማው የምስራቅ መውጫ በር በመሆን በማገልገሉ ምክንያት በመጎዳቱ እና የሚያስተናግደውም የትራፊክ መጠን በከፍተኛ ሁኔታ በማደጉ ወቅቱ የሚጠይቀውን አገልግሎት መስጠት እንዲችል ማስተር ፕላኑን ጠብቆ እንደ አዲስ በመገንባት ደረጃውን የማሻሻል ስራ እየተከናወነ ይገኛል፡፡
በዚህ አጋጣሚ የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን በክረምት ወራት በሚጥለው ከፍተኛ መጠን ያለው ዝናብ በመንገዶች ላይ በሚፈጥረው #የጎርፍ ችግር ምክንያት በነዋሪዎች እንቅስቃሴ ላይ ለሚፈጠረው መስተጓጎል ይቅርታ እየጠየቀ አሽከርካሪዎች ከምን ጊዜውም በላይ ሲያሽከረክሩ ቅድመ ጥንቃቄ በማድረግ እና ሌሎች የመንገድ አማራጮች በመጠቀም ከጎርፍ ስጋትና ከእንግልት እንዲድኑ ይመክራል፡፡
©የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን
@tsegbwolde @tikvahethiopia
በአቃቂ መሿለኪያ ድልድይ የሚያልፍበት ወንዝ ሙላት ምክንያት የሚፈጠሩ እንግልቶችን ለማስቀረት ህብረተሰቡ የተለያዩ የመንገድ #አማራጮችን እንዲጠቀም የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን ያሳስባል፡፡
አማራጮችን ለመጠቆም ያህል፡-
1. ወደ ምስራቅ አዲስ አበባ መሄድ የሚፈልጉ ተሽከርካሪዎች ከደቡብ አፍሪካ ዩኒቨርሲቲ አደባባይ ወደ ቱሉ ዲምቱ ማሳለጫ (ወደ ጎሮ የሚወስደውን ውጫዊ የቀለበት መንገድ) መጠቀም ይችላሉ።
2. ወደ መሃል አዲስ አበባ ለመሄድ የሚፈልጉ ተሸከርካሪዎች ዋናውን አቃቂ ድልድይ መጠቀም ይችላሉ።
3. ወደ ምዕራብ አዲስ አበባ መሄድ የሚፈልጉ ተሸከርካሪዎች ከደቡብ አፍሪካ ዩኒቨርሲቲ አደባባይ በግራ በኩል ወደ ለቡ የሚወስደውን ውጫዊ የቀለበት መንገድ መጠቀም ይችላሉ።
4. ከአዲስ አበባ ወደ ምስራቅ አቅጣጫ የሚጓዙ ተሸከርካሪዎች በላይ አብ ሞተርስ አለፍ ብሎ ወደ ቱሉ ዲምቱ ኮንዶሚኒየም በመታጠፍ መስቀለኛ መንገዱን መጠቀም ይቻላሉ።
እንደሚታወቀው ቃሊቲ ቀለበት መንገድ አደባባይ - ቱሉ ዲምቱ አደባባይ መንገድ ለረጅም ጊዜ የከተማው የምስራቅ መውጫ በር በመሆን በማገልገሉ ምክንያት በመጎዳቱ እና የሚያስተናግደውም የትራፊክ መጠን በከፍተኛ ሁኔታ በማደጉ ወቅቱ የሚጠይቀውን አገልግሎት መስጠት እንዲችል ማስተር ፕላኑን ጠብቆ እንደ አዲስ በመገንባት ደረጃውን የማሻሻል ስራ እየተከናወነ ይገኛል፡፡
በዚህ አጋጣሚ የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን በክረምት ወራት በሚጥለው ከፍተኛ መጠን ያለው ዝናብ በመንገዶች ላይ በሚፈጥረው #የጎርፍ ችግር ምክንያት በነዋሪዎች እንቅስቃሴ ላይ ለሚፈጠረው መስተጓጎል ይቅርታ እየጠየቀ አሽከርካሪዎች ከምን ጊዜውም በላይ ሲያሽከረክሩ ቅድመ ጥንቃቄ በማድረግ እና ሌሎች የመንገድ አማራጮች በመጠቀም ከጎርፍ ስጋትና ከእንግልት እንዲድኑ ይመክራል፡፡
©የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን
@tsegbwolde @tikvahethiopia
👍1