ኮሎኔል ታደሰ ሙሉነህ አረፉ‼️
ኮ/ል #ታደሰ_ሙሉነህ በኢትዮጵያ አየር ኃይል የ71 ቅጥር አባል ናቸው። በቀደመው አየር ኃይል በሚግ-23 ተዋጊ ስኳድሮን ውስጥ በምሥራቅም ሆነ በሰሜን ግንባር ተሰልፈው ከፍተኛ ተጋድሎ ካደረጉት የአገራችን ኢትዮጵያ ባለውለታ አንዱ ሆነው ይጠቀሳሉ።
በ1991 ኢሕአዴግ ወደ ሥልጣን መምጣትን ተከትሎ በመቃወም ወደ ኤርትራ አቅንተዋል።
የኢትዮጵያ አርበኞች ግንባርን በመምራት በኤርትራና በኢትዮጵያ ሰሜናዊ ምዕራብ በረሃዎች ሳሉ በኤርትራ መንግስት የፀጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ሥር በመዋላቸዉ ለበርካታ አመታት ደብዛቸው፤ አድራሻቸው ጠፍቶ ነበር።
ከወራት በፊት ኮ/ል ታደሰ ከኤርትራ እስር ነፃ ይሁን እንጂ ጤንነታቸው ታውኮ ሰውነታቸው እንደልቡ በማያዝቡት ሁኔታ በመሆኑ በህክምና #በህንድ ሐገር ሲታከሙ ቆይተው ጥር 27 ቀን 2011 ዓም አርፈዋል።
ምንጭ፦ ጋዜጠኛ ጌጡ ተመስገን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኮ/ል #ታደሰ_ሙሉነህ በኢትዮጵያ አየር ኃይል የ71 ቅጥር አባል ናቸው። በቀደመው አየር ኃይል በሚግ-23 ተዋጊ ስኳድሮን ውስጥ በምሥራቅም ሆነ በሰሜን ግንባር ተሰልፈው ከፍተኛ ተጋድሎ ካደረጉት የአገራችን ኢትዮጵያ ባለውለታ አንዱ ሆነው ይጠቀሳሉ።
በ1991 ኢሕአዴግ ወደ ሥልጣን መምጣትን ተከትሎ በመቃወም ወደ ኤርትራ አቅንተዋል።
የኢትዮጵያ አርበኞች ግንባርን በመምራት በኤርትራና በኢትዮጵያ ሰሜናዊ ምዕራብ በረሃዎች ሳሉ በኤርትራ መንግስት የፀጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ሥር በመዋላቸዉ ለበርካታ አመታት ደብዛቸው፤ አድራሻቸው ጠፍቶ ነበር።
ከወራት በፊት ኮ/ል ታደሰ ከኤርትራ እስር ነፃ ይሁን እንጂ ጤንነታቸው ታውኮ ሰውነታቸው እንደልቡ በማያዝቡት ሁኔታ በመሆኑ በህክምና #በህንድ ሐገር ሲታከሙ ቆይተው ጥር 27 ቀን 2011 ዓም አርፈዋል።
ምንጭ፦ ጋዜጠኛ ጌጡ ተመስገን
@tsegabwolde @tikvahethiopia