TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.61K videos
216 files
4.36K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ተጨማሪ ማዕቀብ እንዲጣል አዘዙ። የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ከትግራይ ክልል ቀውስ ጋር በተገናኘ ተጠያቂ ባደረጓቸው ፦ - የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግስት - የአማራ ክልል ባለስልጣናት - የህወሓት አመራሮች - የኤርትራ መንግስት አመራሮች ላይ ተጨማሪ ማዕቀብ እንዲጣል አዘዙ። ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ዛሬ በፈረሙት የስራ አስፈጻሚ አካል ትዕዛዝ (executive order) የትግራይ…
#US : አሜሪካ የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት ወደተኩስ አቁም ስምምነት የሚመጡ ከሆነ ለመጣል ያቀደችውን ማዕቀብ ልታዘገየው እንደምትችል ገለፀች።

የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት "በመካሔድ ላይ ያለውን ግጭት አቁመው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ በአፋጣኝ ድርድር የሚጀምሩ ከሆነ" ማዕቀቡ ሊዘገይ እንደሚችል የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ዘግይተው በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል።

አንቶኒ ብሊንከን ፥ " ሁለቱ ወገኖች በዚህ ረገድ #አፋጣኝ_እርምጃ የሚወስዱ ከሆነ አሜሪካ ማዕቀቡን ለማዘግየት እና የድርድር ሒደቱን ለመደገፍ ዝግጁ ነች" ማለታቸውን ሮይተርስን ዋቢ በማድርግ የጀርመን ድምፅ ሬድዮ ጣቢያ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
👍3