TIKVAH-ETHIOPIA
#መምህራን " የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ከፌደራል መንግስት በመወያየት የ17 ወራት ውዙፍ ደመወዛችን እንዲከፍለን እንጠይቃለን " - የትግራይ መምህራን ማህበር የትግራይ መምህራን ማህበር የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ከፌደራል መንግስት በመወያየት የመምህራንን የ17 ወራት ውዙፍ ደመወዝ እንዲከፍል ጠየቀ። ማህበሩ ይህን ያለው ታህሳስ 18/2016 ዓ.ም ይፋ ባደረገው ባለ 8 ነጥብ የአቋም መግለጫ ነው።…
“ የ2015 ዓ.ም የ5 ወራት ዉዝፍ ደመወዝ በአጭር ጊዜ እንደሚከፈል መግባባት ላይ ተደርሷል ” - የትግራይ መምህራን ማህበር
የትግራይ መምህራን ማህበር ስራ አስፈፃሚ ከጊዚያዊ አስተዳደሩ ባካሄደው ውይይት ላቀረባቸው ጥያቄዎች የሚጨበጥና ተስፋ ሰጪ መልስ ማግኘቱን ለሁሉም የወረዳ መምህረን ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።
ማህበሩ ምን አለ ?
- የመምህራን መብትና ጥቅም አስመልክቶ ከሚመለከታቸው የመንግስት አካላት በተቀናጀ መልኩ እየጠየቀ መምጣቱን ማህበሩ ገልጿል።
- የመምህራን መብት እንዲጠበቅ በተለይ በጦርነቱ ምክንያት ሳይከፈል የቀረው የ17 ወራት ዉዝፍ ደመወዝ አስመልክቶ ታህሳስ 17 / 2016 ዓ.ም በማህበሩ ማኔጅመንት ደረጃ አስቸኳይ ውይይት በማካሄድ የተለያዩ ውሳኔዎች ማሳለፉን አስታውሷል።
- ከውሳኔዎቹ አንዱ በተለይ የመምህራን ውዝፍ ደመወዝ ጥያቄ እስከ ጥር 15 /2016 ዓ.ም ካልተመለሰ በትግራይ ደረጃ ሰላማዊ ሰልፍ እናካሂዳለን የሚል ነው ፤ ስለዚሁ ጉዳይ የመምህራን ማህበር ስራ አስፈፃሚ ከክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች ባጠረ ጊዜ ውስጥ ውይይት እንዲካሄድ የሚልም የውሳኔ ሃሳብ እንደነበር አመልክቷል።
- በተቀመጠው ውሳኔ መሰረት የትግራይ መምህራን ማህበር ስራ አስፈፃሚ ጥር 4 / 2016 ዓ.ም ከክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕረዚደንት ጌታቸው ረዳና ከትምህርት ቢሮ ሃላፊ ዶክተር ኪሮስ ጉዕሽ ውይይት ማካሄዱን የውይይቱ ዋና ነጥቦችም ፦
➡ የ2015 ዓ.ም የ5 ወራት ዉዝፍ ደመወዝ፣
➡ የ2014 ዓ.ም የ 12 ወራት ዉዝፍ ደመወዝ፣
➡ ከደደቢት ማይክሮፋይናስ ስለተወሰደ የብድር ወለድ ስለሚነሳበት ሁኔታ፣
➡ የመምህራን የትራንስፖርት አገልግሎት ሰርቪስ ስለማግኘት፣ የሚሉ እንደነበሩ አሳውቋል።
- በውይይቱ በተለይ ውዝፍ ደመወዝን በሚመለከት የ2015 ዓ.ም የ5 ወራት በአጭር ጊዜ #እንደሚከፈል ፣ የ2014 ዓ.ም የ12 ወራት ውዝፍ ደመወዝ መከፈል የሚመለከት ጥያቄ ወደ ፌደራል መንግስት መቅረቡ ፣ ከደደቢት ማይክሮፋይናንሰ የተወሰደ የብድር ወለድ ስለሚነሳበት ሁኔታ ቀጣይ ውይይት እንደሚካሄድ ፣ የከተማ የመምህራን ሰርቪስ የሚመለከት ጥያቄ በአጭር ጊዜ እንደሚመለስ መግባባት ላይ ተደርሷል ብሏል።
- በአጠቃላይ ከክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕረዚደንት ጌታቸው ረዳ የተደረገው ግንኙነት ገንቢ እንደነበረ ፣ አቅጣጫ የተቀመጠላቸው ጉዳዮች አፈፃፀማቸው የሚመለከት ቀጣይ ውይይት እንደሚካሄድ መተማመን ላይ መደረሱን ማህበሩ ገልጿል።
መረጃውን ማህበሩ ለሁሉም የትግራይ ወረዳ መምህራን ማህበር ጥር 7 / 2016 ዓ.ም ፅፎ የላከውን ሰርኩላር ደብዳቤ ዋቢ በማድረግ ያደረሰን የመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።
@tikvahethiopia
የትግራይ መምህራን ማህበር ስራ አስፈፃሚ ከጊዚያዊ አስተዳደሩ ባካሄደው ውይይት ላቀረባቸው ጥያቄዎች የሚጨበጥና ተስፋ ሰጪ መልስ ማግኘቱን ለሁሉም የወረዳ መምህረን ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።
ማህበሩ ምን አለ ?
- የመምህራን መብትና ጥቅም አስመልክቶ ከሚመለከታቸው የመንግስት አካላት በተቀናጀ መልኩ እየጠየቀ መምጣቱን ማህበሩ ገልጿል።
- የመምህራን መብት እንዲጠበቅ በተለይ በጦርነቱ ምክንያት ሳይከፈል የቀረው የ17 ወራት ዉዝፍ ደመወዝ አስመልክቶ ታህሳስ 17 / 2016 ዓ.ም በማህበሩ ማኔጅመንት ደረጃ አስቸኳይ ውይይት በማካሄድ የተለያዩ ውሳኔዎች ማሳለፉን አስታውሷል።
- ከውሳኔዎቹ አንዱ በተለይ የመምህራን ውዝፍ ደመወዝ ጥያቄ እስከ ጥር 15 /2016 ዓ.ም ካልተመለሰ በትግራይ ደረጃ ሰላማዊ ሰልፍ እናካሂዳለን የሚል ነው ፤ ስለዚሁ ጉዳይ የመምህራን ማህበር ስራ አስፈፃሚ ከክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች ባጠረ ጊዜ ውስጥ ውይይት እንዲካሄድ የሚልም የውሳኔ ሃሳብ እንደነበር አመልክቷል።
- በተቀመጠው ውሳኔ መሰረት የትግራይ መምህራን ማህበር ስራ አስፈፃሚ ጥር 4 / 2016 ዓ.ም ከክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕረዚደንት ጌታቸው ረዳና ከትምህርት ቢሮ ሃላፊ ዶክተር ኪሮስ ጉዕሽ ውይይት ማካሄዱን የውይይቱ ዋና ነጥቦችም ፦
➡ የ2015 ዓ.ም የ5 ወራት ዉዝፍ ደመወዝ፣
➡ የ2014 ዓ.ም የ 12 ወራት ዉዝፍ ደመወዝ፣
➡ ከደደቢት ማይክሮፋይናስ ስለተወሰደ የብድር ወለድ ስለሚነሳበት ሁኔታ፣
➡ የመምህራን የትራንስፖርት አገልግሎት ሰርቪስ ስለማግኘት፣ የሚሉ እንደነበሩ አሳውቋል።
- በውይይቱ በተለይ ውዝፍ ደመወዝን በሚመለከት የ2015 ዓ.ም የ5 ወራት በአጭር ጊዜ #እንደሚከፈል ፣ የ2014 ዓ.ም የ12 ወራት ውዝፍ ደመወዝ መከፈል የሚመለከት ጥያቄ ወደ ፌደራል መንግስት መቅረቡ ፣ ከደደቢት ማይክሮፋይናንሰ የተወሰደ የብድር ወለድ ስለሚነሳበት ሁኔታ ቀጣይ ውይይት እንደሚካሄድ ፣ የከተማ የመምህራን ሰርቪስ የሚመለከት ጥያቄ በአጭር ጊዜ እንደሚመለስ መግባባት ላይ ተደርሷል ብሏል።
- በአጠቃላይ ከክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕረዚደንት ጌታቸው ረዳ የተደረገው ግንኙነት ገንቢ እንደነበረ ፣ አቅጣጫ የተቀመጠላቸው ጉዳዮች አፈፃፀማቸው የሚመለከት ቀጣይ ውይይት እንደሚካሄድ መተማመን ላይ መደረሱን ማህበሩ ገልጿል።
መረጃውን ማህበሩ ለሁሉም የትግራይ ወረዳ መምህራን ማህበር ጥር 7 / 2016 ዓ.ም ፅፎ የላከውን ሰርኩላር ደብዳቤ ዋቢ በማድረግ ያደረሰን የመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።
@tikvahethiopia