#ተመስገን_ደሳለኝ
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ዛሬ ጥር 7 ቀን 2016 ዓ/ም ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰሚ ችሎት በቀረቡበት ወቅት፣ “ትክክለኛ ፍትህ ይሰጣሉ ብዬ ስለማላምን” ያሏቸውን የጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኛ ከችሎት እንዲነሱ ጠይቀዋል።
ጋዜጠኛው ይህን ጥያቄ ያቀረቡት ዛሬ ቀጠሮ ተሰጥቶበት የነበረው ጉዳያቸው ከመታየቱ በፊት የሚያቀርቡት አቤቱታ እንዳላቸው ለዕለቱ ዳኞች ጥያቄ በማቅረብ ነው።
ስለሚያቀርቡት አቤቱታ ችሎቱ ለጋዜጠኛ ተመስገን አቤቱታቸውን እንዲገልጹ ከፈቀደላቸው በኋላ፣ “የግራ ዳኛ የሆኑት ክቡር አቶ አሕመድ መሐመድ ትክክለኛ ፍትህ ይሰጣሉ ብዬ ስለማላምን በዚህ ጉዳይ ከችሎት እንዲነሱልኝ ምክንቻቶቼን አቀርባለሁ” ሲሉ ተደምጠዋል።
ጋዜጠኛ ተመስገን ይህን ከገለጹ በኋላ የቀኝና የመሀል ዳኛ የለሆሳስ ንግግር አድርገው አቤቱታቸውን በፅሑፍ እንዲያቀርቡ ማሳሰቢያ የሰጡ ሲሆን፣ ጋዜጠኛ ተመስገንም ፈቃድ ካገኙ በኋላ፣ “በእዚህ ችሎት በርካታ ጋዜጠኞች ስላሉ አቤቱታዬን በንባብ እንዳሰማ ሊፈቀድልኝ ይገባል” ብለውሸ ሲገልጹ፣ ፅሑፉን ባጭሩ እንዲያቀርቡ ማሳሰቢያ ተሰጥተዋል።
አሳጥረው እንዲያቀርቡ ዳኞች በፈቀዱላቸው መሠረት ያነበቡት ፅሑፉ በዝርዝር ምን ይላል?
“ዐቃቤ ሕግ ጥቅምት 1/2015 ዓ.ም ባቀረበው የይግባኝ ቅሬታ 2ኛ ክስን በሚመለከት 3ኛ እና 4ኛ ፍሬ ነገሮች፤ እንዲሁም 3ኛ ክስን የይግባኝ ቅሬታ ያላቀረበበት መሆኑን ጠቅሶ ወደፊት፦ ፍርድ ከተሰጠ በኋላ ውጤቱን ተመልክቶ የይግባኝ ቅሬታ እንደሚያቀርብበት በይግባኝ ማመልከቻው ላይ በግልጽ አመላክቶ እያለ፣
* ታህሳስ 17/2015 ዓ/ም መልስ ሰጪን ያስቀርባል በሚል ትዕዛዝ ከሰጡት ዳኞች መካከል አቶ መሐመድ አሕመድ የሚገኙበት መሆኑን አረጋግጫለሁ፡፡በችሎቱ የተሰጠው ትዕዛዝም ዐቃቤ ሕግ በ2ኛ ክስ ቅሬታ ያላቀረበባቸውን 3ኛ እና 4ኛ ፍሬ ነገሮችን በመጨመር፤
* እንዲሁም 3ኛ ክስን በማካተት በ1ኛ እና 2ኛ ክሶች መከላከል ሳያስፈልገው በነፃ እንዲሰናበት፣ 3ኛ ክስን በሚመለከት ክስ የቀረበበት ድንጋጌ ወደ ጥላቻ ንግግር ወይም የሀሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከለከል እና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1185/2012 አንቀጽ 4 በመለወጥ እንዲከላከል በአብላጫ ድምጽ የተሰጠውን ብይን፤
*እንዲሁም የተጠቀሰውን አዋጅ ለጉዳዩ ያለውን አግባብነት መጣራት ያለበት መሆኑን ስለታመነበት መልስ ሰጪ ይቅረብ ብለናል በሚል ትዕዛዝ ተሰጥቷል፡፡” የሚል ነው።
ጋዜጠኛ ተመስገን ያነበቡትና ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው ይኼው ሰነድ አክሎም፣ “ይህ ትዕዛዝ ዐቃቢ ህግ በይግባኝ አቤቱታው ከጠየቀው ዳኝነት በማለፍ የተሰጠ ትዕዛዝ መሆኑን መረዳት የሚቻል ከመሆኑም በላይ የመልስ ሰጪን መብት በብርቱ የሚጎዳ አድራጎት ነው” ይላል።
በተጨማሪ ፣ “ከላይ ስማቸውን የጠቀስኩት ዳኛ በዚህ ጉዳይ ከችሎት ሳይነሱ ይቀጥሉ ቢባል ጉዳዩ ፓለቲካዊ ይዘት ያለው እንደመሆኑ መጠን በመዝገቡ ላይ ትክክለኛ ፍትህ ይሰጣሉ ብዬ የማላምንና ወደ ፊትም የሚሰጠው ፍርድ ነጻና ገለልተኛ ይሆናል ብዬ ስለማላምን በአዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 33/1/ሠ መሠረት የግራ ዳኛ የሆኑት ክቡር አቶ መሐመድ አሕመድ በዚህ ጉዳይ ከችሎቱ እንዲነሱልኝ በታላቅ ትህትና እጠይቃለሁ” ሲል ያትታል።
በመጨረሻም፣ የጋዜጠኛውን አቤቱታ ካደመጠ በኋላ ችሎቱ፣ የዳኛውን ከችሎት መነሳትና አለመነሳት ጥያቄን በተመለከተ ለመወሰን፣ እንዲሁም ጋዜጠኛ ተመስገን በዋናው ክሳቸው ይሰጣሉ ተብሎ የሚጠበቀውን መለስ ለመቀበል ለጥር 28 ቀን 2016 ዓ/ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
ዘገባውን የላከው የአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ኢዮብ ትኩዬ ነው።
@tikvahethiopia
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ዛሬ ጥር 7 ቀን 2016 ዓ/ም ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰሚ ችሎት በቀረቡበት ወቅት፣ “ትክክለኛ ፍትህ ይሰጣሉ ብዬ ስለማላምን” ያሏቸውን የጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኛ ከችሎት እንዲነሱ ጠይቀዋል።
ጋዜጠኛው ይህን ጥያቄ ያቀረቡት ዛሬ ቀጠሮ ተሰጥቶበት የነበረው ጉዳያቸው ከመታየቱ በፊት የሚያቀርቡት አቤቱታ እንዳላቸው ለዕለቱ ዳኞች ጥያቄ በማቅረብ ነው።
ስለሚያቀርቡት አቤቱታ ችሎቱ ለጋዜጠኛ ተመስገን አቤቱታቸውን እንዲገልጹ ከፈቀደላቸው በኋላ፣ “የግራ ዳኛ የሆኑት ክቡር አቶ አሕመድ መሐመድ ትክክለኛ ፍትህ ይሰጣሉ ብዬ ስለማላምን በዚህ ጉዳይ ከችሎት እንዲነሱልኝ ምክንቻቶቼን አቀርባለሁ” ሲሉ ተደምጠዋል።
ጋዜጠኛ ተመስገን ይህን ከገለጹ በኋላ የቀኝና የመሀል ዳኛ የለሆሳስ ንግግር አድርገው አቤቱታቸውን በፅሑፍ እንዲያቀርቡ ማሳሰቢያ የሰጡ ሲሆን፣ ጋዜጠኛ ተመስገንም ፈቃድ ካገኙ በኋላ፣ “በእዚህ ችሎት በርካታ ጋዜጠኞች ስላሉ አቤቱታዬን በንባብ እንዳሰማ ሊፈቀድልኝ ይገባል” ብለውሸ ሲገልጹ፣ ፅሑፉን ባጭሩ እንዲያቀርቡ ማሳሰቢያ ተሰጥተዋል።
አሳጥረው እንዲያቀርቡ ዳኞች በፈቀዱላቸው መሠረት ያነበቡት ፅሑፉ በዝርዝር ምን ይላል?
“ዐቃቤ ሕግ ጥቅምት 1/2015 ዓ.ም ባቀረበው የይግባኝ ቅሬታ 2ኛ ክስን በሚመለከት 3ኛ እና 4ኛ ፍሬ ነገሮች፤ እንዲሁም 3ኛ ክስን የይግባኝ ቅሬታ ያላቀረበበት መሆኑን ጠቅሶ ወደፊት፦ ፍርድ ከተሰጠ በኋላ ውጤቱን ተመልክቶ የይግባኝ ቅሬታ እንደሚያቀርብበት በይግባኝ ማመልከቻው ላይ በግልጽ አመላክቶ እያለ፣
* ታህሳስ 17/2015 ዓ/ም መልስ ሰጪን ያስቀርባል በሚል ትዕዛዝ ከሰጡት ዳኞች መካከል አቶ መሐመድ አሕመድ የሚገኙበት መሆኑን አረጋግጫለሁ፡፡በችሎቱ የተሰጠው ትዕዛዝም ዐቃቤ ሕግ በ2ኛ ክስ ቅሬታ ያላቀረበባቸውን 3ኛ እና 4ኛ ፍሬ ነገሮችን በመጨመር፤
* እንዲሁም 3ኛ ክስን በማካተት በ1ኛ እና 2ኛ ክሶች መከላከል ሳያስፈልገው በነፃ እንዲሰናበት፣ 3ኛ ክስን በሚመለከት ክስ የቀረበበት ድንጋጌ ወደ ጥላቻ ንግግር ወይም የሀሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከለከል እና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1185/2012 አንቀጽ 4 በመለወጥ እንዲከላከል በአብላጫ ድምጽ የተሰጠውን ብይን፤
*እንዲሁም የተጠቀሰውን አዋጅ ለጉዳዩ ያለውን አግባብነት መጣራት ያለበት መሆኑን ስለታመነበት መልስ ሰጪ ይቅረብ ብለናል በሚል ትዕዛዝ ተሰጥቷል፡፡” የሚል ነው።
ጋዜጠኛ ተመስገን ያነበቡትና ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው ይኼው ሰነድ አክሎም፣ “ይህ ትዕዛዝ ዐቃቢ ህግ በይግባኝ አቤቱታው ከጠየቀው ዳኝነት በማለፍ የተሰጠ ትዕዛዝ መሆኑን መረዳት የሚቻል ከመሆኑም በላይ የመልስ ሰጪን መብት በብርቱ የሚጎዳ አድራጎት ነው” ይላል።
በተጨማሪ ፣ “ከላይ ስማቸውን የጠቀስኩት ዳኛ በዚህ ጉዳይ ከችሎት ሳይነሱ ይቀጥሉ ቢባል ጉዳዩ ፓለቲካዊ ይዘት ያለው እንደመሆኑ መጠን በመዝገቡ ላይ ትክክለኛ ፍትህ ይሰጣሉ ብዬ የማላምንና ወደ ፊትም የሚሰጠው ፍርድ ነጻና ገለልተኛ ይሆናል ብዬ ስለማላምን በአዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 33/1/ሠ መሠረት የግራ ዳኛ የሆኑት ክቡር አቶ መሐመድ አሕመድ በዚህ ጉዳይ ከችሎቱ እንዲነሱልኝ በታላቅ ትህትና እጠይቃለሁ” ሲል ያትታል።
በመጨረሻም፣ የጋዜጠኛውን አቤቱታ ካደመጠ በኋላ ችሎቱ፣ የዳኛውን ከችሎት መነሳትና አለመነሳት ጥያቄን በተመለከተ ለመወሰን፣ እንዲሁም ጋዜጠኛ ተመስገን በዋናው ክሳቸው ይሰጣሉ ተብሎ የሚጠበቀውን መለስ ለመቀበል ለጥር 28 ቀን 2016 ዓ/ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
ዘገባውን የላከው የአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ኢዮብ ትኩዬ ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ተመስገን_ደሳለኝ
ጋዜጠኛ ተመስገን “ትክክለኛ ፍትሕ ይሰጣሉ ብዬ ስለማላምን ይነሱልኝ” ያሏቸው ዳኛ “ #አልነሳም” አሉ።
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ጥር 7 ቀን 2016 ዓ/ም ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰሚ ችሎት ቀርበው በነበረበት ወቅት፣ “የግራ ዳኛ የሆኑት ክቡር አቶ አሕመድ መሐመድ ትክክለኛ ፍትህ ይሰጣሉ ብዬ ስለማላምን በዚህ ጉዳይ ከችሎት እንዲነሱልኝ ምክንቻቶቼን አቀርባለሁ” ብለው ያዘጋጁትን ምክንያታዊ ፅሑፍ በዝርዝር አቅርበው ነበር።
ችሎቱም የጋዜጠኛውን አቤቱታ ካደመጠ በኋላ፣ የዳኛውን ከችሎት መነሳትና አለመነሳትን ጉዳይ ለመወሰን፣ ጋዜጠኛ ተመስገን በዋናው ክሳቸው ይሰጣሉ ተብሎ የሚጠበቀውን መለስ ለመቀበል ለጥር 28 ቀን 2016 ዓ/ም ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱ አይዘነጋም።
ይሁን እንጂ ለጥር 28 ቀን 2016 ዓ/ም ተሰጥቶ የነበረው ቀጠሮ፣ “አቤቱታ የቀረበባቸው ዳኛ ስልጠና ላይ ስለሆኑ ውሳኔ አልሰጠንም” በሚል ለየካቲት 21 ቀን 2016 ዓ/ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቶበት ተራዝሞ ቆይቷል።
በየካቲት 21 ቀን 2016 ዓ/ምቱ ችሎት ደግሞ፣ ጋዜጠኛው ከችሎቱ እንዲነሱ አቤቱታ ያቀረቡባቸው ዳኛ “አልነሳም” ብለዋል።
ጋዜጠኛው ያቀረቡት የዳኛውን “ከችሎት ይነሱልኝ” አቤቱታ ችሎቱ ወድቅ ያደረገው፣ “እንዲነሱ የተጠየቁት ዳኛ መልካም ስብዕና ያላቸው መሆኑን” በመጥቀስ ነው።
ጋዜጠኛ ተመስገን፣ የተሳሳተ ትዕዛዝ መስጠታቸውን ዋቢ አድርገው በመጥቀስ “ዳኛው ይነሱልኝ” ብለው ባቀረቡት አቤቱታ ሳቢያ የ1,000 (አንድ ሺሕ ብር) ቅጣት ተፈርዶባቸው ክፍያውን ፈጽመዋል።
ጋዜጠኛው ተመስገን፣ ፍርድ ቤቱ ‹ዳኛው ስህተት ሰርተዋል ወይስ አልልሩም?› ወይም ‹ከሳሽ ያለአግባብ ጠቅመዋል ወይስ አልጠቀሙም?› በማለት የቀረበውን ቅሬታ መመርመሩን ወደ ጎን በመተውና የቀድሞ ስብእናቸውን መነሻ በማድረግ ቅሬታዬን ውድቅ ማደረጉ እጅጉን አስደንግጦኛል” ሲሉ ተናግረዋል።
አክለውም፣ “የፍርድ ቤቱ ትእዛዝ እኔን ስጋት ላይ የጣለ ነው” ያሉ ሲሆን፣ ጋዜጠኛው ላይ የቀረበውን የይግባኝ መልስ ለመስማትም ለመጋቢት 16 ቀን 2016 ዓ/ም ቀጠሮ ተስጥቷል።
መረጃውን አዘጋጅዮ የላከው የአ/አ ተክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።
@tikvahethiopia
ጋዜጠኛ ተመስገን “ትክክለኛ ፍትሕ ይሰጣሉ ብዬ ስለማላምን ይነሱልኝ” ያሏቸው ዳኛ “ #አልነሳም” አሉ።
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ጥር 7 ቀን 2016 ዓ/ም ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰሚ ችሎት ቀርበው በነበረበት ወቅት፣ “የግራ ዳኛ የሆኑት ክቡር አቶ አሕመድ መሐመድ ትክክለኛ ፍትህ ይሰጣሉ ብዬ ስለማላምን በዚህ ጉዳይ ከችሎት እንዲነሱልኝ ምክንቻቶቼን አቀርባለሁ” ብለው ያዘጋጁትን ምክንያታዊ ፅሑፍ በዝርዝር አቅርበው ነበር።
ችሎቱም የጋዜጠኛውን አቤቱታ ካደመጠ በኋላ፣ የዳኛውን ከችሎት መነሳትና አለመነሳትን ጉዳይ ለመወሰን፣ ጋዜጠኛ ተመስገን በዋናው ክሳቸው ይሰጣሉ ተብሎ የሚጠበቀውን መለስ ለመቀበል ለጥር 28 ቀን 2016 ዓ/ም ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱ አይዘነጋም።
ይሁን እንጂ ለጥር 28 ቀን 2016 ዓ/ም ተሰጥቶ የነበረው ቀጠሮ፣ “አቤቱታ የቀረበባቸው ዳኛ ስልጠና ላይ ስለሆኑ ውሳኔ አልሰጠንም” በሚል ለየካቲት 21 ቀን 2016 ዓ/ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቶበት ተራዝሞ ቆይቷል።
በየካቲት 21 ቀን 2016 ዓ/ምቱ ችሎት ደግሞ፣ ጋዜጠኛው ከችሎቱ እንዲነሱ አቤቱታ ያቀረቡባቸው ዳኛ “አልነሳም” ብለዋል።
ጋዜጠኛው ያቀረቡት የዳኛውን “ከችሎት ይነሱልኝ” አቤቱታ ችሎቱ ወድቅ ያደረገው፣ “እንዲነሱ የተጠየቁት ዳኛ መልካም ስብዕና ያላቸው መሆኑን” በመጥቀስ ነው።
ጋዜጠኛ ተመስገን፣ የተሳሳተ ትዕዛዝ መስጠታቸውን ዋቢ አድርገው በመጥቀስ “ዳኛው ይነሱልኝ” ብለው ባቀረቡት አቤቱታ ሳቢያ የ1,000 (አንድ ሺሕ ብር) ቅጣት ተፈርዶባቸው ክፍያውን ፈጽመዋል።
ጋዜጠኛው ተመስገን፣ ፍርድ ቤቱ ‹ዳኛው ስህተት ሰርተዋል ወይስ አልልሩም?› ወይም ‹ከሳሽ ያለአግባብ ጠቅመዋል ወይስ አልጠቀሙም?› በማለት የቀረበውን ቅሬታ መመርመሩን ወደ ጎን በመተውና የቀድሞ ስብእናቸውን መነሻ በማድረግ ቅሬታዬን ውድቅ ማደረጉ እጅጉን አስደንግጦኛል” ሲሉ ተናግረዋል።
አክለውም፣ “የፍርድ ቤቱ ትእዛዝ እኔን ስጋት ላይ የጣለ ነው” ያሉ ሲሆን፣ ጋዜጠኛው ላይ የቀረበውን የይግባኝ መልስ ለመስማትም ለመጋቢት 16 ቀን 2016 ዓ/ም ቀጠሮ ተስጥቷል።
መረጃውን አዘጋጅዮ የላከው የአ/አ ተክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።
@tikvahethiopia